#‎Ethiopia‬ : እሳት ላይ ሕዝብን ጥዶ እያመሱ የሚደረግ የትግል ሽሚያ ይቁም!!!የእርስ በእርስ መነካከሱ አንድም የወያኔን እድሜ ማስረዘም ሲልም የሕዝብን ስቃይ ከማባባስ አያልፍም:: ‪ Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) በኢትዮጵያ ያለው የወያኔ አገዛዝ በሕዝቦች ላይ የሚያደርሰው በደል እጅግ ብዙና ተነግሮ የሚያልቅ አይደለም …

እሳት ላይ ሕዝብን ጥዶ እያመሱ የሚደረግ የትግል ሽሚያ ይቁም!!! የእርስ በእርስ መነካከሱ አንድም የወያኔን እድሜ ማስረዘም ሲልም የሕዝብን ስቃይ ከማባባስ አያልፍም:: ‪ Read more »

የጋምቤላን ሕዝብ በደቡብ ሱዳን ኑኤር ቅጥረኞች ማስጨፍጨፍ ለምን ኣስፈለገ !? ጋምቤላ እንዲህ ነች !!! ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎Gambella‬ ‪#‎MinilikSalsawi‬ ‪#‎EPRDF‬ ‪#‎SouthSudan‬ ‪#‎Freedom‬ Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – በኣሁን ወቅት በጋምቤላ ክልል የክልሉ መስተዳደር ስልጣን የሌለው ሲሆን የክልሉ ፖሊስ ሙሉ በሙሉ ማት ይቻላል …

የጋምቤላን ሕዝብ በደቡብ ሱዳን ኑኤር ቅጥረኞች ማስጨፍጨፍ ለምን ኣስፈለገ !? ጋምቤላ እንዲህ ነች !!! (ምንሊክ ሳልሳዊ) Read more »

ግርማ ካሳ

Tesfaye Gebreab, ተስፋዬ ገብረአብ

አቶ ተስፋዬ ገብረአብ በአንድ ወቅት የኢሕአዴግ ባለሥልጣን የነበሩ ሰው ናቸው። ጥሩ ፀሐፊ ናቸው። ከኦሮሞ ብሔረተኞች ጋር የቅርብ ግንኙነት አላቸው። አንድ ወቅት እንደውም የኦሮሞ ተማሪዎች ማኅህበር ላይ የክብር እንግዳ ሆኖ ቀርበው ነበር። በዚያን ወቅት “በሞጋሳ እኔም ኦሮሞ ነኝ” ብለው ነበር። ሞጋሳ አንድ ሰው “ኦሮሞ” ባይሆንም የኦሮሞን ባህልንና ቋንቋን ከተቀበለ፣ በኦሮሞ “ሽማግሌዎች” ፍቃድ “ኦሮሞ” የሚሆንብት ሥርዓት ነው (naturalized ኦሮሞነት)።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ የተቃውሞ ፖለቲካ ጎራውን በመምራት ላለፉት 25 ዓመታት በአገሪቱ የፖለቲካ መድረክ ከፍተኛ የሆነ ሚና የተጫወቱ ፖለቲከኛ ናቸው፡፡ ከሽግግር መንግሥቱ ምሥረታ ጀምሮ የተለያዩ ኅብረቶችንና የፓርቲዎችን ስብስብ በመምራት የሚታወቁ ፖለቲከኛም ናቸው፡፡ በአሁኑ ወቅትም የአራት ፓርቲዎች ስብስብ የሆነው የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ አንድነት …

‹‹የኢሕአዴግ ፀባይ እኛን መተንበይ የማንችል መሪዎች አድርጎ ነው ያስቀመጠን›› = ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ፣ የመድረክ ፕሬዚዳንት Read more »

‹‹አገሪቱ እየተዘረፈች ነው›› ዋና ኦዲተር አቶ ገመቹ ዱቢሶ ‹‹የማዕድን ዘርፉን እየመራችሁ ስለመሆኑ ሥጋት አለን›› የፓርላማው አባላት በፓርላማው የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴና የፌዴራል ዋና ኦዲተር የማዕድን፣ ፔትሮሊየምና የተፈጥሮ ጋዝ ሚኒስቴር የሥራ ኃላፊዎችን ክፉኛ ወቀሱ፡፡ የሚኒስቴሩ የሥራ ኃላፊዎች ባለፈው …

‹‹አገሪቱ እየተዘረፈች ነው›› : ዋና ኦዲተሩ – የማዕድን ሚኒስቴር ኃላፊዎች ላይ ከፍተኛ ወቀሳ ሰነዘሩ Read more »

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ላዕላይ ምክር ቤት ሰኞ ጥር 16 ቀን 2008 ዓ.ም. ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ፣ የፓርቲውን ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሐሪን አገደ፡፡ ቀጣዩ ጠቅላላ ጉባዔ እስከሚካሄድ ድረስም ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ እንድርያስ ኤሮ ፓርቲውን እንዲመሩ ወስኗል፡፡ ‹‹ፕሬዚዳንቱ ስብሰባ እንዲጠሩንና …

የመኢአድ ላዕላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንቱን አገደ Read more »

የጋምቤላው ግጭት ተባብሶ መቀጠሉ ታውቋል። ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎Gambella‬ ‪#‎MinilikSalsawi‬ በቅርቡ የብሄር ብሄረሰብ ቀን የተከበረባትና የብሄሮች መቻቻል ኣንድነት እና ፍቅር ተምሳሌት ተደርጋ በወያኔ ኣገዛዝ የተንቆለጳጰሰችው ጋምቤላ በጎሳ ጦርነት እየተናጠች ነው ። አዲስ ስታንዳርድ የተባለው እንግሊዘኛ ድህረገጽ ባወጣው ሰበር ዜና መሰረት በጋምቤላ ክልል …

የጋምቤላው ግጭት ተባብሶ መቀጠሉ ታውቋል። (VIDEO) Read more »

የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች በመኪና አደጋ ህይወታቸው አለፈ:: ሶስት ህፃናት ሃዋሣ ዩኒቨርሲቲ ጉድጓድ ውስጥ ገብተው ሞቱ :: አምስት በሃዋሣ ከተማ ውስጥ በሚገኘው የሃዋሣ ዩኒቨርሲቲ ፍሳሽ ማጠራቀሚያ ገንዳ ውስጥ የገቡ 3 ህፃናት ህይወታቸው አለፈ፡፡ ዕድሜያቸው 8‚ 12‚ እና 14 የሚሆናቸው ህፃናት፤ በሽቦ አጥር …

ሶስት ህፃናት ሃዋሣ ዩኒቨርሲቲ ጉድጓድ ውስጥ ገብተው ሞቱ Read more »

ረሃቡ እና ድርቁ አስጨናቂና አሳሳቢ ሆኗል:: ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎Ethiopiafamine‬ ‪#‎FAO‬ ‪#‎MinilikSalsawi‬ • በድርቁ አካባቢዎች 350ሺ ተጨማሪ ህፃናት ይወለዳሉ:: — • የነፍሰ ጡር እናቶች ቁጥር እየጨመረ ነው • የእርዳታ እህል በፍጥነት እንዲጓጓዝ ተጠየቀ:: — በድርቅ በተጐዱ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በሚቀጥሉት 6 ወራት ውስጥ …

ረሃቡ እና ድርቁ አስጨናቂና አሳሳቢ ሆኗል:: Read more »

• ዩኒቨርሲቲው ለ15 ቀን ተዘግቶ ተማሪዎች ተሰናብተዋል • የመሬት መንቀጥቀጡ ትናንት ለ5 ተከታታይ ጊዜያት ተከስቷል • የኮንዶሚኒየም ነዋሪዎች ከቤት ወጥተው በድንኳን ውስጥ ናቸው • የርዕደ መሬቱን መጠን የሚለካ መሳሪያ ነገ ይተከላል • መንቀጥቀጡ ለቀጣዮቹ ዘጠኝ ቀናት ይቀጥላል በሃዋሣ ከተማና በዙሪያዋ …

ሃዋሳ አሁንም በሥጋት ተወጥራለች :: የመሬት መንቀጥቀጡ ለ5 ተከታታይ ጊዜያት ተከስቷል:: Read more »

ጥር 7፣ 2008 ዓ.ም | በወንድወሰን ጥበቡ ክርስቲያኖ ሮናልዶ እንግሊዝ እና ፖርቱጋል ለዩሮ 2016 ለሚያደርገት የአቋም መፈተሻ ጨዋታ ወደኦልትራፎርድ ሊመለስ ይችላል። የእንግሊዝ እግር ኳስ ማህበር ሁለቱ ሃገራት ስለሚያደርጉት የወዳጅነት ጨዋታ ከፖርቱጋል አቻው ጋር ንግግር እያደረገም ይገኛል። በአሁኑ ጊዜ ክርስቲያኖ ሮናልዶ በዝውውር ወደእንግሊዝ እንደሚመጣ ማረፊያውም ኤልራፎርድ ሊሆን እንደሚችል በሰፊው እየተወራ ይገኛል። የፖርቱጋል እግር ኳስ ማህበር ምንጭ … Continue reading “ክርስቲያኖ ሮናልዶ ወደኦልትራፎርድ ዳግም ሊመለስ ነው”

ወያኔና ሌሎች የጥፋት ኃይሎች አማራን የማጥፋት የቆረጠ የጥፋት ዓላማና ድርጊት ይዘው መምጣታቸውና ሀገሪቱን ከመቆጣጠራቸው የወሰዱት የተቀናጀ ዘግናኝ የዘር ማጥፋት ጥቃት መፈጸማቸው የአማራ ልኂቃንን አስጨንቆ ሕዝቡን ከወያኔና መሰሎቹ የዘር ማጥፋት ጥቃት የታደጉ፣ የሠወሩ፣ ያዳኑ፣ የከለሉ፣ የተከላከሉ መስሏቸው ሁለት የተለያዩ አቋሞችን ለማራመድ ሲያስገድድ ከአማራው ሕዝብም ቀላል ቁጥር ያልያዘውን ምናልባትም አሁን የአማራ ሕዝብ ተብሎ ከሚገለጸው የሚበዛውን በተለይ በወያኔ […]

ጥር ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የሰርቫይቫል ኢንተርናሽናል ዳይሬክተር አቶ ኒካው ኦቻላ ለኢሳት እንደገለጹት የንዌር ተወላጆች የጋምቤላ እስር ቤትን ሰብረው በመግባት 7 የአኝዋክ ተወላጆችን ሲገድሉ፣ 7ቱን ደግሞ አቁስለዋል። 4 የሌሎች ብሄረሰቦች አባላት መቁሰላቸውምን ዳይሬክትሩ ገልጸዋል። በሁለቱ ብሄረሰቦች መካካል እንዲህ አይነት ደም የሚያፋሰስ የመረረ ግጭት ተቀስቅሶ እንደማያውቅ የገለጹት አቶ ኒካው፣ ለአሁኑ ግጭት መባባስ …

የአዲስ አበባ ህዝብ ለምን ተቃውሞ አላሰማም ይህ ጥያቄ ሰሞኑን በተደጋጋሚ እዚህ ፌስቡክ ላይ ሲመላለስ እያየሁ ነው የአዲስ አበባ ልጅ እንደመሆኔ ጉዳዩ ስቦኝ የተወሰኑትን ፅሁፎች አነበብኩኝ አንዳንዶቹ በጭፍን የአዲስ አበባን ህዝብ ሲያጥላሉ የተወሰኑት ደግሞ የአዲስ አበባ ህዝብ ለምን አልተነሳም ሲሉ ይጠይቃሉ …

የአዲስ አበባ ህዝብ ለምን ተቃውሞ አላሰማም (ኤርሚያስ ቶኩማ‬) Read more »

በኦሮሚያ ክልል የተማሪዎች ተቃውሞ ዛሬም ቀጥሏል። ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎Oromoprotests‬ ‪#‎OPDO‬ ‪#‎Miniliksalsawi‬ Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – በወለጋ ዩንቨርስቲ የፌዴራል ፖሊስ በመግባት ተማሪዎች ላይ ኣስለቃሽ ጭስ በመተኮስ ላይ ሲገኝ መብራቱን በማጥፋት ጨለማን ተገን በማድረግ ወደ ሴቶች መኝታ ክፍል ገብቶ ሴቶችን ክፉኛ እየደበደበ …

በኦሮሚያ ክልል የተማሪዎች ተቃውሞ ዛሬም ቀጥሏል። Read more »

አዲስ አበባ ለምን ዝም አለች ~~~~~~~~~~ <<ቅድስት ብዙ ግዜ እያመሸች ትሰራልች። አንድ ቀን ለአይን ያዝ ማድረግ ሲጀምር ከስራ ወጥታ ወደምትኖርበት የጨረቃ ቤቶች ወደሚበዙበት መንደር ታዘግማለች። ጓደኛዋ ጋር ደውላ ስራ በማምሸቷ ምክንያት ልታገኘው እንዳልቻለች በማውራት ላይ ሳለች ሁለት ጎረምሶች ስልኳን በጉልበት …

አዲስ አበባ ለምን ዝም አለች (Eyasped Tesfaye) Read more »

ሕዝቡ ለደርጅቶች የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ መስጠት አለበት- ግርማ ካሳ ======================================== በሚቅጥሉት ሁለት፣ ሶስት ሳምንታት የተለያዩ የፖለቲካ ስብሰባዎች ይደረጋሉ። የፊታችን እሁድ ጥር 22፣ የግንቦት ሰባት አርበኞች ንቅናቄ፣ ሊቀመንበሩ ዶር ብርሃኑ ነጋ ባሉበት በዲሲ ስብሰባ ያደርጋል። “ታላቅ ሕዝባዊ ስብሰባ” ብለዉታል። http://ecadforum.com/…/grand-public-meeting-with-professor…/ በሳምንቱ ጥር …

ሕዝቡ ለደርጅቶች የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ መስጠት አለበት- ግርማ ካሳ Read more »

ከጧት ጀምሮ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የፌደራል ፖሊስ በከተማዋ ፈሷል፡፡ በትላንትናው ዕለት በአኙዋክና በኑዌር ብሔረሰቦች መካከል በተቀሰቀሰው ግጭት ቁጥሩ በውል ያልታወቀ በርካታ ሰው መሞቱ የሚታወስ ነው፡፡ ከሟቾቹ መካከል የቀድሞ የክልሉ የፋይናንስ ቢሮ ሐላፊ ከቅርብ ጊዜ ጀምረው ደግሞ የክልሉ የገጠር መንገድ ስራዎች …

ጋምቤላ ከፍተኛ ውጥረት ላይ ነች፡፡ Read more »

የቃሊቲ ማረሚያ ቤት አስተዳደር ጀግኖቻችን ላይ እያደረገ ያለውን ወከባ ሊያቆም ይገባል! እስረኞችን ማንገላታት ይቁም! አርብ ጥር 20/2008 የቃሊቲ ማረሚያ ቤት አስተዳደር ጀግኖች ታሳሪዎቻችንን አላግባብ እያንገላታ ይገኛል፡፡ በትናንትናው እለት በማረሚያ ቤቱ ከተነሳ ጸብ እና ወከባ ጋር በተያያዘ ‹‹እናንተ ናችሁ ያስበጠበጣችሁት›› በሚል …

የቃሊቲ ማረሚያ ቤት አስተዳደር ጀግኖቻችን ላይ እያደረገ ያለውን ወከባ ሊያቆም ይገባል! እስረኞችን ማንገላታት ይቁም! Read more »

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን አሳፍራ ወደ አዲስ አበባ ስትጓዝ በነበረች ተሽከርካሪ ላይ የከፋ የትራፊክ አደጋ ደርሶ የአምስት ሰዎች ህይወት አለፈ።ተሽከርካሪዋ ከአዲስ አበባ ወደ ሀዋሳ ሲጓዝ ከነበረ ኤፍ ኤስ አር አይሱዙ የጭነት መኪና ጋር በመጋጨቷ ነው አደጋው የደረሰው። ዛሬ ሰባት ሰዓት ላይ …

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን አሳፍራ ስትጓዝ በነበረች ተሽከርካሪ ላይ የከፋ የትራፊክ አደጋ ደረሰ Read more »

ተስፋዬ ገብረአብ (Gadaa)

Abay Tsehaye. አባይ ፀሐዬ

ከኦሮሚያ አመጽ ጋር በተያያዘ አባይ ፀሐዬ ስሙ በተደጋጋሚ ይነሳል። አንዳንድ ደንፊ ንግግሮች መናገሩንም ስናነብ ሰነባብተናል። ምን እንደነካው እንጃ እንጂ ጠባዩ እንኳ እንዲያ አልነበረም። አባይ በጠባዩ ድመት መሆኑ ነበር የሚታወቀው። ሊያጠቃ ሲፈልግ እንደ ፈረስ ጋማህን እያሻሸ እንጂ እንደ ቋረኛው ካሳ ጎራዴ አያወዛውዝም። ከታላቁ የኦሮሚያ አመጽ ጋር በተያያዘ “በሚናገራቸው ንግግሮች” ግን ስሜቱን መቆጣጠር የተቸገረ ይመስላል። ዞረም ቀረ አባይ ፀሐዬ እና ጓደኞቹ የገጠማቸውን ጦርነት በአሸናፊነት ለመወጣት መጣራቸውን ቀጥለዋል። ይሳካላቸው ይሆን?

ሙሉውን አስነብበኝ …

ጥር ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የሃዋሳ ዩንቨርሲቲ ተማሪዎች ለአስራ አምስት ቀናት ትምህርት መቋረጡን የዩንቨርሲቲው አስተዳደር መግለጹን ተከትሎ ግቢውን ለቀው ወጥተዋል። በአንድ ተሽከርካሪ ላይ ተጭነው ከግቢው በመውጣት ወደ ወላጆቻቸው በመሄድ ላይ ከነበሩት ተማሪዎች ውስጥ ወደ በመቂ እና ሞጆ ከተሞች መዳረሻ አካባቢ የመኪና አደጋ ደርሶባቸዋል። የአደጋው መንስኤ የሚጓዙበት ተሽከርካሪ ከአዲስ አበባ ወደ ሀዋሳ …

መረጃ ሙሉ ያደርጋል ለዚህ ደግሞ የኢትዮጵያ ወጣቶች ድምፅ ሳምንታዊ ዜናዎችን News Ethiopia Wetatoch Dimts Jan 28.2016 እንዲሁም መጣጥፎችን ለስለስ ካሉ ሙዚቃዎች ጋር ይዘንላችሁ ቀርበናል አብራችሁን ሁኑ ። [youtube http://www.youtube.com/watch?v=xInOp43hhqY]  

ኢሳት (ጥር 19 ፥ 2008) የኦሮሞ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦህዴድ) ማዕከላዊ ኮሚቴ በስራ አስፈጻሚ ደረጃ አስቸኳይ ስብሰባ መቀመጡ ታወቀ። የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚደንት አቶ ሙክታር ከድር እየተገመገሙ እንደሆነና ስልጣናቸውን ሊለቁ እንደሚችሉ ለኢሳት የደረሰው መረጃ ያመለክታል። ከጨፌ ኦሮሚያ የውስጥ ምንጮች ለኢሳት የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ ኦህዴድ በመላው የኦሮሚያ አካባቢ የተቀጣጠለውን ህዝባዊ እምቢተኝነት ቁልፍ አመራር እየገመገመ መሆኑ ታውቋል። የድርጅቱ …

በኦሮሚያ ክልል ተቃውሞው ተጠናክሮ ቀጥሏል።በዶዶላ ደህንነቶች ስልጤ የኦሮሞ ጠላት ነው የሚል ወረቀት መበተናቸው ታወቀ:: ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎Oromoprotests‬ ‪#‎Gambella‬ ‪#‎MinilikSalsawi‬ ‪#‎Dodola‬ Minilik Salsawi – Ethiopian DJ – በጉጂ በደብረጽጌ በገብረጉራቻ በሜታ በሜኢሶ እና ኣሰቦት የኦሮሞ ተማሪዎች አና የኣከባቢው ነዋሪዎች በኦሮሞ ሕዝብ ላይ …

በኦሮሚያ ክልል ተቃውሞው ተጠናክሮ ቀጥሏል።በዶዶላ ደህንነቶች ስልጤ የኦሮሞ ጠላት ነው የሚል ወረቀት መበተናቸው ታወቀ:: Read more »

By Eyob Dadi |ጥር 19 ፣ 2008 ዓ. ም ስዋሬዝ እንግሊዝ ደርሷል።የህክምና ምርመራውን ዛሬ ሀሙስ አመሻሹ ላይ እንደሚያደርግ ተረጋግጧል። የፊዮረንቲና አማካይ የሆነው ስፔናዊው ማሪዮ ስዋሬዝ ከስፔኑ አትሌቲኮ ማድሪድ ከተዛወረ በኋላ በጣሊያን ሴሪ ኣ ተጽእኖ መፍጠር አቅቶታል። ተጨዋቹ በፊዮረንቲና 5 ጨዋታ ብቻ የተጫወተ ሲሆን ወደ እንግሊዙ ዋትፎርድ ለመዘዋወር ዛሬ ሀሙስ በምሳ ሰአት ላይ እንግሊዝ እንደደረሰ ታውቋል። … Continue reading “ስዋሬዝ ወደ እንግሊዝ ፕሪምየርሊግ ሊዛወር ነው።የህክምና ምርመራ ለማድረግ እንግሊዝ ደርሷል”

ሕዝቡን በሕቡእ በተገኘበት ማደራጀት እና እንዲደራጅ ማድረግ የወቅቱ ግዴታ ነው:: ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎EthiopianOppositionparties‬ ‪#‎OrganizeStruggle‬ ‪#‎MinilikSalsawi‬ Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) በሕቡእ መደራጀት ከቻልን ራሳችንን ከወያኔ ጥቃቶች መከላከል እንችላለን:: በሕቡእ መደራጀት ከቻልን አስፈላጊ በሆነ ሰአት አድፍጠን በወያኔ እና ጭፍሮቹ ላይ አስደንጋጭ አደጋ ልናደርስ …

ሕዝቡን በሕቡእ በተገኘበት ማደራጀት እና እንዲደራጅ ማድረግ የወቅቱ ግዴታ ነው:: Read more »

[ክቡር ሚኒስትሩ አንድ ትልቅ ሆቴል ውስጥ የቀጠሩት ደላላ ስላረፈደባቸው ደወሉለት] –    ሄሎ ክቡር ሚኒስትር፡፡ –    የት ደርሰሃል? –    ኧረ ክቡር ሚኒስትር ታስሬያለሁ፡፡ –    ማን አሰረህ? –    ማለቴ መንገዱ ተዘጋግቶ አንድ ቦታ ታስሬያለሁ፡፡ –    ለምንድን ነው መንገድ የተዘጋው? –    ስብሰባ አለ …

የቢዝነስ ስልኮች ፦ክቡር ሚኒስትሩ አንድ ትልቅ ሆቴል ውስጥ የቀጠሩት ደላላ አረፈደባቸው:: Read more »

በዓለም ዙሪያ የሚሰማው የምጣኔ ኃብት ድቀት እና የማኅበራዊ ነውጥ ፍራቻ አምባገነን መንግሥታት በአውሮፓ አቆጣጠር ባለፈው 2015 ዓ.ም ይበልጥ አፋኝና ጨቋኝ እንዲሆኑ ሰበብ ሳይሰጣቸው እንዳልቀረ ዛሬ የወጣ የዓለም የነፃነት ሁኔታ ሪፖርት አስታውቋል፡፡

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) በሃገሪቱ መጭውን ጊዜ ኣስመልክቶ የሕወሓት ወታደራዊ ባለስልጣናት ስብሰባ በመቀመጥ የተወያዩ ቢሆንም በሰራዊቱ ላይ ያለውን መተማመን አጅግ የወደቀ አና ለውጊያ ሞራል የለውም የሚል መደምደሚያ ላይ መድረሳቸው ታውቃል። ከዚህ ቀደም እንደተባለው የትግራይ ሚሊሻዎችን በወታደራዊ መልኩ ማደራጀት የትግራይ ወጣት …

ሰራዊቱ ለውጊያ የሚሆን ሞራል የለውም ሲል የሕወሓት ወታደራዊ ሹማምንት ስብሰባ ጠቆመ። Read more »

By Eyob Dadi የቀድሞ ኮከብ ሮናልዲንሆ ጎቾ የሴይንት ናግጄ የእግርኳስ ውድድር ለመክፈት በህንድ ይገኛል። ሮናልዲንሆ በህንድ ቆይታው ከሞት መትረፉን ነው ጎል ስፓርት የዘገበው። ሮናልዲንሆ በአድናቂዎቹ ፉጨት እና ጩኸት ታግዞ በሚጓዝበት ወቅት ግዙፍ የሆነ የዛገ የትራፊክ መብራት ፓል ከመኪናው በቅርብ ርቀት ላይ ከፊትለፊቱ ተሰብሮ ወድቆ መኪናውን ሳያገኘው ቀርቷል። ፓሉ ሲወድቅ አድናቂዎቹ በድንጋጤ ጸጥ እንዳሉ ሲታወቅ ወዲያው … Continue reading “ሮናልዲንሆ ከሞት ተረፈ”

#Ethiopia  #‎ShareEthioHarmony‬ ‪#‎EBCDocumentary‬ ‪#‎1460DaysOfPeacefulStruggle‬ ‪#‎EthioMuslims‬ #MinilikSalsawi ‹‹ማህበራዊ መስተጋብራችንን እንካፈል!›› መንግስት በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች እና በሌሎች ወገኖቻቸው መካከል ለማ facebook.com/hashtag/shareethioharmony ንደድ የሚሞክረውን እሳት በጋራ የማጥፋት ጥሪ! ከረቡእ ጥር 18 እስከ እሁድ ጥር 22/2008 የሚቆይ የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ረቡእ ጥር 18/2008 መንግስት በኢትዮጵያውያን …

በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች እና በሌሎች ወገኖቻቸው መካከል ለማንደድ የሚሞክረውን እሳት በጋራ የማጥፋት ጥሪ! Read more »

የአዲስ አበባንና የፊንፊኔ ዙሪያ ዞኖችን የከተሞች ማስፊፊያ እቅድ ተንተርሶከተቀሰቀሰውና በኦሮምያ ክልል የተለያዩ ከተሞች የሚገኙ ትምሕርት ቤቶችተማሪዎች ሲያካሂዱ የቆዩት የተቃውሞ እንቅስቃሴ የክልሉ መንግስት እቅዱንመተዉን ካስታወቀም በኋላ በአንዳንድ አካባቢዎች አሁንም መቀጠሉ እየተዘገበ ነው።

ሰሞኑን በምዕራብ ወለጋ ጊዳ ወረዳ፤ ጉደቱ አርጆ ከተማ በተከናወነ የሰርግ ሥነ ሥርዓትላይ በጭፈራው መሃል የተቃውሞ ድምጽ …

በሬክተር የምድር ንዝር መለኪያ 4.3 ያስቆጠረ የመሬት ነዉጥ ባለፈዉ እሁድ ምሽትና ሰኞ ጥዋት በሃዋሳ ከተማ መሰማቱ ተዘገበ።

የምድር ነዉጡ በሰዉ ሆነ በንብረት ላይ ጉዳት አላደረሰም ተብሏል። ለኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮሮሬሽን ትንታኔ የሰጡ የአድስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከርሰ-ምድር ጥናት ምሁርን መግለጫ ተንተርሶ እስክንድር ፍሬዉ ዘግቧል።

የድምጽ ፋይሉን በመጫን ያድምጡ።

 

ይገረም አለሙ

Dr. Merera Gudan and Girma Seifu. ዶ/ር መረራ ጉዲና (በግራ) እና አቶ ግርማ ሰይፉ (በቀኝ)

ለዚህች ጽሑፍ መነሻ ምክንያት የሆነኝ አቶ ግርማ ሰይፉ “የዶ/ር መረራ የቡዳ ፖለቲካ እና መቀበል ያቃተው መራራ እውነት”በሚል ርዕስ ያስነበቡን ጽሑፍ ሲሆን፤ ርሳቸው ለጽሑፋቸው ምክንያት የሆናቸው ደግሞ “የኢትዮጵያ የታሪክ ፈተናዎች እና የሚጋጩ ሕልሞች” የሚለው የዶ/ር መረራ መጽሐፍ እንደሆነ ገልጸዋል። የቡዳ ፖለቲካ የሚለው ቃልም ከዚሁ መጽሐፍ የተገኘ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ጥር ፲፯ (አሥራ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በምእራብ ጎጃም ዞን የየስማላ ከተማ ነዋሪዎች መብራት ከተቋረጠባቸው 5 አመታትን ማሳለፋቸውን፣ በሰሜን ጎንደር ሃሙሲት ከተማ ደግሞ የከተማው ነዋሪዎች የቧንቧ ውሃ ከተቋረጠባቸው 5 አመታትን ማሳለፋቸውን ዘጋቢያችን ነዋሪዎችን አነጋግሮ የላከው ዘገባ ያሳያል። ነዋሪዎቹ ችግሮቻቸው እንዲፈቱላቸው በተደጋጋሚ ጥያቄ ቢያቀርቡም ሰሚ አካል አላገኙም። በሞጣ ከተማ ደግሞ መብራት ከተቋረጠ 2 ወር …

Ethiopia Oromo students protest addis ababa plan. የኦሮሞ ተማሪዎች በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ላይ ያሰሙት ተቃውሞይገረም አለሙ

በሀገር ውስጥም በውጪም ቁጥራው እጅግ የበዛ ተግባራቸው ግን ብዙም የማይታይ ፓርቲዎች አሉ። እነዚህ የሚችሉት ተዋህደው አንድ በመሆን፤ የማይችሉት ተባብረው ትብብርም ይሁን ግንባር በመፍጠር የነጻነት ቀናችንን ለማፋጠን የሚያስችል ትግል ያደርጉ ዘንድ ስንመኝ፣ ስንጠይቅ፣ ስንማጸን፣ ይህን ባለማድረጋቸውም ስንኮንን ወዘተ ዓመታት ተቆጥረዋል። እነርሱ ግን መተባበሩ ቀርቶ መከባበሩ አልሆን ብሎአቸው፣ ተደጋግፎ መቆሙ ቢቀር አንዱ ለአንዱ እንቅፋት ከመሆን መቆጠብ ተስኖአቸው ወያኔ ያሻውን እንዳሻውና ባሰኘው መንገድና ግዜ እየፈጸመ ከዚህ እንዲደርስ አድርገውታል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

በወያኔው ፍርድ ቤት የቀረበው የሰማያዊ ፓርቲው ዮናታን ተስፋዬ ድጋሚ በቀጠሮ ወደ እስር ቤት ተመልሷል። ፍ/ቤቱ ለ2ኛ ጊዜ 28 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ሰጠ *‹‹ነጻነት ይሰማኛል›› ዮናታን ተስፋየ በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር በሽብር ወንጀል ተጠርጥሮ በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ማዕከል በእስር ላይ የሚገኘው የቀድሞው …

በወያኔው ፍርድ ቤት የቀረበው የሰማያዊ ፓርቲው ዮናታን ተስፋዬ ድጋሚ በቀጠሮ ወደ እስር ቤት ተመልሷል። Read more »

በትናንትናው ዕለት በእስራኤል ሃገር ከአሜሪካ ኤምባሲ ፌት ለፊት የተደረገው ሰላማዊ ሰልፍ በተሳካ ሁኔታ እንደተካሄደና በተለያዩ ፍከራዎች ደምቆ ውሏል ከተሰሙት መፈክሮችም መካከል ” ኢትዮጵያ አትቆረስም ” አሜሪካ እርዳታሽን ለወያኔ መንግስት አቁሚ” የኦሮሞ ተማሪዎች ላይ የሚደርሰው ግፍ ይቁም” ወያኔ ገዳይ መንግስት ነው …

በእስራኤል ሃገር ከአሜሪካ ኤምባሲ ፌት ለፊት የተደረገው ሰላማዊ ሰልፍ በተሳካ ሁኔታ እንደተካሄደና በተለያዩ ፍከራዎች ደምቆ ውሏል Read more »

የኢትዮጵያ ሙስሊም ፈተና በ224 ደቂቃዎች (በዘላለም ክብረት) ክፍሉ ከኮሪደሩ ላይ ከተንጠለጠለ አምፖል በሚመጣ ብርሃን ፈገግ ብሏል፡፡ እኔም ከምሽቱ አራት ሰዓት ላይ ወደክፍሉ ስገባ ከክፍሉ አንደኛው ጫፍ ላይ አንድ ቀጠን ያለ ሰው ድምፁን በትንሹ ከፍ አድርጎ ቁርዓን ‹እየቀራ› ነበር፡፡በክፍሉ ሌላኛው ጫፍ …

የኢትዮጵያ ሙስሊም ፈተና በ224 ደቂቃዎች (በዘላለም ክብረት) Read more »

ክፍል አንድ ‪#‎እውነቱን_ማወቅ_ለሚፈልግ‬ ከቀናት በፊት በፓርቲያችን ውስጣዊ ጉዳይ ለመነጋገር ከኢ/ር ይልቃል ጋር ከቢሮ ውጪ ተገናኝተን ለመነጋገር ችለናል፡፡በዚህ አጋጣሚ እየሆነ ያለወ ነገር ዳር ቆሞ ከመመልከት ይልቅ በመነጋገር መፍትሔ ማምጣት ይቻላል የሚል ጽኑ እምነት ያለው፣በኢትዮጵያ የፖለቲካ ተሳትፎ እረጅም እድሜ የስቆጠረው ምርጥ ጓዳችን …

እውነቱን ማወቅ ለሚፈልግ‬ – Yidnekachew Kebede – ሰማያዊ ፓርቲ Read more »

በኢትዮጵያ፥ በኦሮሞ ተቃዋሚዎችና በመንግሥቱ የፀጥታ ኃይሎች መካከል ለሁለት ወራት ግድም ግጭቶች ከተካሄዱ በኋላ፥ ባለሥልጣናቱ የአዲስ አበባን ግዛት ለማስፋት የኦሮሞ ገበሬዎችን ያፈናቅላል የተባለውን ማስተር ፕላን መሠረዛቸውን አስታውቀዋል።

ታዛቢዎች ግን፥ የመንግሥቱ ባለሥልጣናት የማስተር ፕላኑን ለመሰረዝ በወሰዱት እርምጃ ላይ ጥርጣሬ አላቸው።

እርምጃው በእርግጥ የፖሊሲ ለውጥ መደረጉን ያመለክታል? ወይስ ለቀረቡበት ተቃውሞዎች ማስታገሻ  ነው? ሲሉ ይጠይቃሉ።

ባልደረባችን ሳሌም ሰለሞን ያጠናቀረችው ዘገባ አለ። ሰሎሞን ክፍሌ አቅርቦታል።

ከዚህ በታች ካለው የድምጽ ፋይሉ ያድምጡ።

 

ከይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ኣሰጣጥ ጋር በተያያዘ በኣዲስ ኣበባ ከፍተኛ ተቃውሞ ይነሳል የሚል ስጋት ኣይሏል። የኦሮሞ ገበሬዎችን ለማፈናቀል ሲነሳ በተቃውሞ ምክንያት መግቢያ መውጫ ያጣው የሕወሓት ኣገዛዝ ፊቱን በማዞር የኣዲስ ኣበባ ነባር ነዋሪዎችን ኣፈናቅሎ በምትካቸው በሕወሓት ስር ያሉትን የኣንድ ብሄር ትግሬ ካድሬዎችና …

ከይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ኣሰጣጥ ጋር በተያያዘ በኣዲስ ኣበባ ከፍተኛ ተቃውሞ ይነሳል የሚል ስጋት ኣይሏል። Read more »

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ቡድን ከቻን አፍሪካ ዋንጫ ውድድር ተሰናበተ! ዘገባ፡- በናታ በሩዋንዳ አስተናጋጅነት ሲካሄድ በነበረው ፕሮፌሽናል ተጫዋቾችን በማያካትተው የቻን አፍሪካ ዋንጫ ዋሊያዎቹ ከምድባቸው ማለፍ ሳይችሉ ቀርተዋል። ጠባብ የማለፍ እድል ይዘው ወደ ሶስተኛው የምድብ ጫወታ ቢያቀኑም ከምድቡ ደካማ በሆነችው አንጎላ 2-1 ተረተዋል። ወደ ጫወታው ስናመራ በማግባት ቅድሚያውን የወሰዱት አንጎላዎች ሲሆኑ በ54 ኛው ደቂቃ ላይ የመሃል ሜድ … Continue reading “የኢትዮጵያ እግር ኳስ ቡድን ከቻን አፍሪካ ዋንጫ ውድድር ተሰናበተ!”

የነገረ ኢትዮጵያ ጋዜጣ ምክትል ኣዘጋጅ ታሰረ ፤ ኣዘጋጁን ማእከላዊ ማሰቃያ እንዳለ ይታወቃል።(ምንሊክ ሳልሳዊ) በላይ ማናየ የሰማያዊ ፓርቲ ልሳን የነገረ ኢትዮጵያ ምክትል አዘጋጅ ከአራዳ ፍርድ ቤት ወደ ማዕከላዊ መወሰዱን ማረጋገጥ ተችሏል።በላይ ማናዬ የታሰሩ የሰማያዊ ኣባላትን ጉዳይ ተከታትሎ ለመዘገብ ፍርድ ቤት በተገኘበት …

የነገረ ኢትዮጵያ ጋዜጣ ምክትል ኣዘጋጅ ታሰረ ፤ ኣዘጋጁም ማእከላዊ ማሰቃያ እንዳለ ይታወቃል።(ምንሊክ ሳልሳዊ) Read more »

አዲስ መረጃ የቴዲ አፍሮን አዲስ አልበም በተመለከተ:- የመጨረሻውን አልበም ካወጣ አራት አመት የሆነው ዝነኛው ቴዲ አፍሮ ቀጣዩን አልበም ኒዮርክ ስትዲዮ ለመስራት ዝግጅቱን ማጠናቀቁ ታወቀ። ቴዲ ከአዲሱ አልበም ውስጥ አምስት ዘፈኖቹን የሚያቀናብርለት ታዋቂውና የሶስት ግራሚ ተሸላሚ የሆነው ዝነኛው አሜሪካዊ አቀናባሪ ጎርደን …

የቴዲ አፍሮን አዲስ አልበም የሚያቀናብርለት የ3 ግራሚ ተሸላሚ የሆነው ዝነኛው አሜሪካዊ አቀናባሪ ጎርደን ዊሊያምስ ነው። Read more »

በገድለ ወለተ ጴጥሮስ ላይ እንዲህ የሚል ታሪክ አለ፡፡ እምነ ወለተ ጴጥሮስ ወደ ዋልድባ ገዳም በገባች ጊዜ ለአንዲት እናት ረድእ ሆነች፡፡ እኒህ እናት ፈጽሞ ጠባይ የሚባል ያልፈጠረባቸው ነበሩ፡፡ አሁን የተናገሩትን አሁን ይሽሩታል፣ በሆነው ባልሆነው ይቆጣሉ፤ ከእርጅናቸው ብዛት የተነሣ ይነጫነጫሉ፤ ትእዛዛቸው ሁሉ ውኃ ቀጠነ ነው፡፡ በዚህ ዐመላቸው የተነሣ ማንም ከእርሳቸው ጋር ለመኖር ፈቃደኛ አልነበረም፡፡ ከእርሳቸው ጋር ለመኖር ፈቃደኛ ሆና ለረዥም ጊዜ ያገለገለቻቸው ወለተ ጴጥሮስ ነበረች፡፡
አንድ ቀን መነከሳዪያቱ ተሰባስበው ‹እንዴት ከእኒህ እማሆይ ጋር ለዚህን ያህል ዘመን አብረሽ ለመኖር ቻልሽ? እንዴትስ ታገሥሻቸው? እንዴትስ መሮሽ ጥለሽ አልወጣሽም? ሲሉ ጠየቋት፡፡ ወለተ ጴጥሮስም ‹ንብ ታውቃላችሁ? እኒህ እናት ንብ ናቸው፡፡ ከእርሳቸው የሚገኝ ብዙ ዕውቀት፣ ብዙ ጥበብ፣ ብዙ ልምድ፣ ብዙ ታሪክ፣ ብዙም ጸጋ አለ፡፡ ነገር ግን እናንተ መናደፋቸውን ብቻ ነው የምታዩት፤ ስለዚህም ማሩን ከእርሳቸው ልትቆርጡ አልቻላችሁም፡፡ ንብ ትናደፋለች፣ ነገር ግን ማር የሚገኘው ከምትናደፈው ንብ ነው፡፡ የማትናደፈው ዝንብ ቆሻሻ እንጂ ማር የላትም፡፡ እኔ ግን ከንብ ጋር እንዴት እንደሚኖር ዐውቃለሁ፤ ከንብ ጋር እየኖርኩም ማሩን እቆርጣለሁ› አለቻቸው ይባላል፡፡

ትዳር ማለትም እንዲሁ ነው፡፡
‹አበባው አበበ ንቡም ገባልሽ
እንግዲህ አልማዜ ማር ትበያለሽ›
የሚለው የሠርግ ዘፈን ከዚህ ጋር ይስማማል፡፡ አፍንጅም ከጋብቻ በኋላ ያለውን ጫጉላ ‹ማር ጨረቃ› ሲለው ይኼ ታይቶት እንደሆነ እንጃ፡፡ አንዳንዶቹ የትዳር ንድፊያው ብቻ ስለሚታያቸው ወይ ትዳር ሳይመሠርቱ ወይም የመሠረቱትን ትዳር ሲፈቱ ይታያሉ፡፡ ሌሎቹ ደግሞ የትዳር በጎነቱን ብቻ ስለሚያውቁት እስኪገቡበት ሲጓጉ፣ ከገቡበት በኋላ ደግሞ
ስሳል እንዳልኖርኩኝ አስንቺን እስካገኝ
ካገኘሁሽ ወዲያ እላለሁ አውጣኝ
እያሉ ያንጎራጉራሉ፡፡
ምናልባትም ደግሞ በሠርግ ላይ የሚዘፈነው
ማን ፈርሚ አለሽ፣ ማን ፈርሚ አለሽ
በተወለወለው በአለንጋው ጣትሽ
የሚለው ዜማ ‹ትንቢት ይቀድሞ ለነገር› ዓይነት ሳይሆን አይቀርም፡፡
ትዳር ግን ሁለቱም ብቻ አይደለም፡፡ ትዳር ከንብ ጋር መኖር ነው፡፡ ንብ ሁለት ጠባይ አላት፡፡ አንዱ ያስደስታል፤ ሌላኛው ያስከፋል፡፡ አንዱ ጤና ይሆናል፣ ሌላኛው ግን ያማል፡፡ አንዱ ይጣፍጣል፤ ሌላው ግን ይመራል፡፡ አንዱን ይቆርጡታል፣ ሌላውን ግን ይከላከሉታል፡፡
ትዳርም እንዲሁ ነው፡፡ ሁለት ጠባይ አለው፡፡ አንደኛው ያስቃል አንዱ ያሰቅቃል፤ አንዱ ያስደስታል፣ ሌላው ያሳዝናል፡፡ አንዱ ግቡ ግቡ ሌላው ውጡ ውጡ ያሰኛል፡፡ አንዱ ይናደፋል፣ አንዱ ይጣፍጣል፤ አንዱ ጤና ሌላው ሕመም ይሰጣል፡፡ አንደኛው ግን ያለ ሌላው አይገኝም፡፡
ይኼን ለመድኃኒት፣ ለብርዝ፣ ለጠጅ፣ የምናደርገውን ማር የምትሰጠው ንብ ናት የምትናደፈው፡፡ ያቺ ስትናደፍ ፊት የምታሳብጠው፣ ውስጥን የምትመርዘው፣ የምትጠዘጥዘው፣ ንብ ናት ማሩን የምትሰጠው፡፡ በትዳርም ውስጥ ሁለቱም አሉ፡፡ ጭቅጭቁ፣ ንዝንዙ፣ ጠቡ፣ ኩርፊያው፣ አንዱ ለሌላው የግድ መታዘዙ፣ አንዱ የሌላው አገልጋይ መሆኑ፣ አንዱ ያለ ሌላው ለመወሰን አለመቻሉ፤ የሌላውን ጠባይ፣ የሌላውን ዐመል የግድ መታገሡ፤ ከሚታገሡት ሰው ጋር አብሮ መኖሩ፤ ይኼ ነው የንቧ ንድፊያ፡፡
ሰው የወለደውን አያገባም፡፡ ያሳደገውን አያገባም፣ የተዛመደውን አያገባም፡፡ የቤቱን ሰው አያገባም፡፡ ሰው ደግሞ በዐመልም፣ በፍላጎትም፣ በአመለካከትም ይበልጥ የሚቀራረበው አብሮት ከኖረና ካደገ ሰው ጋር ነበር፡፡ እምነቱና ባሕሉ ግን ጋብቻን እስከ ሰባት ቤት አርቆ ለባዕድ ይሰጠዋል፡፡ አብረነው ላልኖርነው፣ አብረን ላላደግነው አብረን ላልተወለድነው፣ ላልተዛመድነው ሰው፡፡ ከሌላ ተወልዶ፣ ሃያ ሠላሳ ዓመት ሌላ ቦታ ኖሮ፣ ከሌላ ጋር አድጎ፣ ሌላ ጠባይ ነሥቶ፣ በሌላ መንገድ መጥቶ ያገኘነውን ሰው ነው የምናገባው፡፡ ይኼንን ሰው ወይም ይህችን ሴትዮ በዕውቅ አላሠራናትም፣ አላሠራነውም፡፡ ዐመሉ እንዲህ፣ ሐሳቡ እንዲያ፣ መንገዱ እንዲህ፣ እምነቱ እንዲያ፣ ዕውቀቱ እንዲህ፣ ምግባሩ እንዲያ ብለን ዝርዝር ሰጥተን አላስመረትነውም፡፡ ‹ሬድ ሜድ› ነው ያገኘነው፡፡ ዓይተን እንመርጣለን እንጂ፣ መርጠን አናሠራም፡፡
ንብን እኛ ብናሠራት ኖሮ የርሷን መናደፍ ለዝንብ ሰጥተን የዝንብን ጠባይ ለንብ በመለስንላት ነበር፡፡ ግን ንብን እንዲሁ ሆና አገኘናት፣ አላመድናት፣ ወደ ቀፏችን አስገባናት እንጂ አንድም አልፈጠርናት፣ አንድም አላስፈጠርናት፡፡ ንቧን ማርና ንድፊያ እንደያዘች ነው ያገኘናት፡፡ ሰው በውስጡ ማርና ንድፊያ አለው፡፡ የተገዛ የሱፐር ማርኬት ማር የሚበላ ልጅ ንብ የምትባለውን የሚያውቃት በጣሳው ላይ ባለው ሥዕል ነው፡፡ መልኳን እንጂ ንድፊያዋን አያውቀውም፡፡ እርሱ እድሜ ልን በንብ እየተነደፈ ለጌቶቹ ማር ቆርጦ የሚሰጥ ገባርም ንብ እንደምትናደፍ እንጂ ማር እንደምትሰጥ አያውቅም፡፡ ‹ጌቶች ምን ምን ቢላቸው ነው ይህን የቀፎ እንጀራ የሚያስገፈግፉኝ› አለ የሚባለውም ለዚህ ነው፡፡
አንዳንዶች በሠርግ ዘፈን፣ በተረት፣ በሠርግ ሥነ ሥርዓት፣ በስብከት፣ በድራማና በፊልም ትዳርን ሲያዩ ምናልባት ማሩ ይሆናል የሚታያቸው፡፡ ያገኛቸውም ሰው ሁሉ ‹ምነው አንተ አታገባም እንዴ› ይላቸዋል እንጂ ተገብቶ ምን እንዳለ አይነግራቸውም፡፡ ‹የዛሬ ዓመት፣ የዛሬ ዓመት፣
የእንትናዬ አባት
ሲወለድ ማሞ፣ ሲወለድ ማሞ
እንመጣለን ደግሞ፤
ያሉት ሰዎች ደግመው ላይመጡ ይችላሉ፡፡ አንዳንዶችም ማሞ ሲወለድ እንደማይመጡ እያወቁት የሚዘፍኑት ዘፈን ነው፡፡ ‹የዛሬ ዓመት የእንትናዬ አባት› መሆን ለሁሉ ያልተሰጠ መሆኑን የሚናገርም የለም፡፡ ይኼ ያልተነገራቸው የዋሐንም ናቸው ልጅ የለም ብለው የሚፋቱት፡፡
ሌሎች ደግሞ ትዳር ሲባል የንቧ ንድፊያ ነው ትዝ የሚላቸው፡፡
‹ታሠረች አሉ በትዳር፣
ከንግዲህ ቀረ መሽርቀር› የሚለው ዘፈንም ውስጠ ዘ አለበት፡፡
ትዳር ምን ዕዳ ነው ትዳር ምን ዕዳ ነው
ጉልቻው ስሙኒ ምጣዱ ብር ነው
የሚለው ባሕላዊ ዜማ የምጣዱና የጉልቻው ዋጋ ዛሬ ሰማይ በነካበት ጊዜ ቀርቶ ትናንትም በርካሹ ዘመን ትዳርን ‹ዕዳ› ነው እያለ የንቧን መናደፍ እየነገረን ነው፡፡
ትዳር ግን ሁለቱም ብቻ አይደለም፡፡ ትዳር ከንብ ጋር መኖር ነው፡፡ ለማሩ ስንል ንድፊያውን መታገሥ፡፡ ቆይተህ ደግሞ ንድፊያውን መልመድ፡፡ ገበሬ ቀፎ ሰቅሎ ንብ ሲያንብ ንብ እንደምትናደፍ ሳያውቅ ቀርቶ አይደለም፡፡ የማትናደፍ ንብ ከፈለገ በየደጁ ቆሻሻ ፍለጋ የምትጓዘው ዝንብ ነበረችለት፡፡ ዝንብ ምን ጠባይዋ ሸጋ ቢሆን፤ ጠብ የሚላት ግን ሌላ ነገር ነው፡፡ ይህን ያውቃል ገበሬው፡፡ እያወቀም ንብ ያንባል፡፡ ማነብ ብቻ ሳይሆን ከንብ ጋር እንዴት መኖር እንደሚቻልም ያውቃል፡፡ ንብ ትናደፋለች፤ ግን እንዳትናደፍ ማድረግም ይችላል፡፡ የምትወደውና የማትወደው ሽታ አለ፡፡ ስትቀርብህ ምን ማድረግ እና ምን አለማድረግ እንዳለብህ ገበሬው ያውቃል፡፡ በሀገራችን ንብ አትገደልም፡፡ ነውር ነው፡፡ ብትነድፍም አትገደልም፡፡ የንቧን ማር ለመውሰድም ንቧን ገድሎ፣ አጥፍቶ፣ ጎድቶ ወይም አሰቃይቶ ሳይሆን በጭስ ራሱን እየተከላከለ፣ ፊቱን በጨርቅ ሸፍኖ፣ ወደ ንቧ ቀፎ ገብቶ ነው ማሩን የሚቆርጠው፡፡ ንቧም ሳትጎዳ፣ ማሩም ሳይጠፋ፣ እርሷም ሳትናደፍ፡፡
ትዳርም እንዲህ ነው፡፡ አኗኗሩን ነው ማወቅ፡፤ የንቧን ንድፊያ የመቀነሻውን መንገድ ነው ማወቅ፣ የማሩን አቆራረጥ መንገድ ነው ማወቅ፡፡ ደግሞምኮ አስገራሚው ገበሬው የሚከባከበው ይህቺኑ የምትናደፈውን ንብ መሆኑ ነው፡፡ የምትቀስመው አበባ ትፈልጋለች፣ ንጹሕ አካባቢ ትፈልጋለች፣ ከጉንዳንና ከአውሬ ነጻ የሆነ ቀፎ ትፈልጋለች፡፡ ግን ትናደፋለች፡፡ ደግሞም ማር ትሰጣለች፡፡ ትዳር አስደሳች ነገር ብቻ ሳይሆን አስመራሪ፣ አንገብጋቢ፣ አስጠሊታ፣ ጨጓራ አንዳጅ፣ አንጀት ቆራጭ፣ ልብ አቃጣይም ክፍል አለው፡፡ ይናደፋል፡፡ ግን ደግሞ ክብካቤም ይፈልጋል፡፡ ንጹሕ ልብ፣ ታማኝ ኅሊና፣ ቻይ አንጀት፣ ታጋሽ ሆድ፣ ጠቢብ አእምሮ፣ አሳላፊ ልቡና ይፈልጋል፡፡ ለምን ቢሉ? ማር ይሰጣልና፡፡
አንዳንዶች ቤት ካለችው ወይም ካለው ንብ ይልቅ ውጭ ያቺውን ወይም ያለው ዝንብ ሲያደንቁ ይሰማል፡፡ መቼም ከቀፎ ውጭ ምን እንደሚኖር የታወቀ ነው፡፡ ንብ ትናደፋለች ብሎ ንብ የማያነባ ገበሬ ስንፍናውን እንጂ የንቢቱን ክፋት ማንም አይረዳለትም፡፡ ጥበብ አልባ መሆኑን፣ ትዕግሥት አልባ መሆኑን፣ ተሸናፊነቱን እየተናገረ እንጂ የንቧን ጠባይ እየተናገረ አለመሆኑን ሁሉም ያውቅለታል፡፡ የትዳርን ችግር ብቻ የሚያወራ፣ በትዳር ተመርሮ ከቀፎው ውጭ የሚሄድም ስንፍናውንና ዐቅመ ቢስነቱን እንጂ የቀፎውን ችግር እየተናገረ አይምሰለው፡፡ ቀፈ ውስጥ ማር የምትሠራው ን እንዳለች ሁሉም ያውቃልና፡፡ ሌላው ቀርቶ ውጭ ያለቺው ዝንብም ይኼንን ታውቃለች፡፡   
አንዳንዶች ከንብ ጋር የመኖር ጥበብ ሲያንሳቸው የማትናደፍ ንብ ፍለጋ ይኳትናሉ፡፡ የማትናደፍ ንብ መፈለግ ከመረቁ አወጡልኝ ከሥጋው ጦመኛ ነኝ እንደማለት ነው፡፡ ወይም የማትዞር መሬት እንደመፈለግ፡፡ የመትናደፍ ንብ ከፈለግክ ከዝንብ ጋር ተጋባ፡፡ 
ይህ ጽሑፍ በአዲስ አድማስ ጋዜጣ የወጣ ነው፡፡

በአዲስ አበባ : የተለያዩ አካባቢዎች በግራቪቲ ፅሁፎች አሸብርቀው አደሩ ! ምሽቱን ተፅፈው ካደሩ ፅሁፎች መካከል ድምፃችን ይሰማ ! ግድያው ይቁም በቃ ! አምባገነናዊ ፍርድ አንቀበልም ! ብሔራዊ ጭቆናው ይብቃ ! የታሰሩት ይፈቱ ፣ ዋ ዋ ዋ ፣ ና ሌሎች መፈክሮች …

በአዲስ አበባ : የተለያዩ አካባቢዎች በግራቪቲ ፅሁፎች አሸብርቀው አደሩ ! Read more »

ሕወሓት በፈጠራና በቆሸሸ ታሪክ ውስጥ የሚርመሰመሱ ሰዎችን በመጠቀም በጎሳ ፖለቲካ ኣጀንዳውን ለማስፈጸም አየሮጠ ነው። ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎Oromoprotests‬ ‪#‎EPRDF‬ ‪#‎MinilikSalsawi‬ ‪#‎Ethiopianism‬ Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – በኦሮሚያ ክልል የተነሳው ንቅናቄ ተከትሎ የሚራገቡ የዘረኝነት ኣጀንዳዎች እየበረቱ ነው፤በስሜት የሚነዱ ጥቂቶች ፣የሕወሓትን መሰረታዊ የዘረኝነት ኣጀንዳ …

ሕወሓት በፈጠራና በቆሸሸ ታሪክ ውስጥ የሚርመሰመሱ ሰዎችን በመጠቀም በጎሳ ፖለቲካ ኣጀንዳውን ለማስፈጸም አየሮጠ ነው። Read more »