ሰሞኑን ደግሞ ፀጥታ አስከባሪዎች ጥያቄ ያቀረበዉን ሕዝብ አስተባብረዋል ባሏቸዉ ሰዎች ላይ እርምጃ በመዉሰዳቸዉ ግጭት ተከስቷል።በግጭቱ በርካታ ሰዎች መገደላቸዉን፤ ቤትና ንብረት መጥፋቱን የአይን ምስክሮችና ፖለቲከኞች አስታዉቀዋል

ዘንድሮ በተለያዩ ውድድሮች ስኬታማ ውጤቶችን ያስመዘገበችው የ5000 እና 10,000 ሜትር ሩጫ ብርቱ ተፎካካሪዋ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት አልማዝ አያና ከሪዮ ኦሎምፒክ ድሏም በኋላ ተጨማሪ ድል አስመዝግባለች።

ኢትዮጵያ ዉስጥ እየተካሄደ ያለዉ ግድያና የሰብዓዊ መብት ጥሰት እስርና እንግልት ይቁም፤ የመንግስት የፀጥታ ኃይላት በሰላማዊ ሰዎች ላይ የሚወስዱትን የኃይል እርምጃ ያቁሙ፤ የታሰሩ ፖለቲከኞች የሐይማኖት መሪዎችና ጋዜጠኞች ይፈቱ፤ የዘር መድሎ ይቁም ሲሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዉያን ዛሬ ጀርመን መዲና በርሊን ላይ የተቃዉሞ ሰልፍ አካሄዱ።

ብሪታንያ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ለንደን በሚገኘዉ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፊት ለፊት ተሰልፈዉ የኢትዮጵያ መንግሥት እየፈፀመ ያለዉ ግፍ ይብቃ ሲሉ የተቃዉሞ ሰልፍ ማድረጋቸዉ ተመልክቶአል ።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቤቶችና የከተማ ልማት ሚኒስቴር የሥራ አፈፃፀም ዝርዝር ዘገባ ባደመጠበት ወቅት ጠፉ እየተባለ ስለሚነገርላቸዉ የኮንደሚኒየም ቤቶች የሚኒስቴር መሥርያ ቤቱ አጣርቶ እንዲያቀርብ መጠየቁ ተሰምቷል። ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ታቅደዉ ያልተሠሩ መኖራቸዉን ለምክር ቤቱ ቢጠቁምም፤ ጠፋ የተባሎት የኮንደሚኒየም ቤቶች ጉዳይ …

ኮንደሚኒየሞቹ የት ተሰወሩ? – ዶይቸ ቬለ Read more »

ነገረ ኢትዮጵያ የተሰኘዉ ጋዜጣ አዘጋጅ ጌታቸዉ ሽፈራዉ ክስ ሳይመሰረትበት ከአራት ወራት በላይ መታሠሩን ጠበቃዉ አስታወቁ። ጠበቃ አመሐ መኮንንን ዛሬ እንዳስታወቁት የሐገሪቱ የፀረ-ሽብር አዋጅ በሚያዘዉ መሠረት ፖሊስ በደንበኛቸዉ ላይ በአራት ወራት ዉስጥ ክስ መመሥረት አለያም እስረኛዉን መልቀቅ ነበረበት። ፖሊስ በተደጋጋሚ የጊዜ …

ያለፍርድ የታሠረዉ ጋዜጠኛ – ዶይቸ ቬለ Read more »

በጥቂት ቀናት ልዩነቶች ውስጥ የደረሱትን እነዚህን ጥቃቶች መንግሥት ፈጥኖ መከላከል አለመቻሉ ደግሞ እያስወቀሰው ነው ። ከግጭቱ በኋላም ስለተወሰዱ እርምጃዎች ግልፅ መረጃ ባለመስጠትም እየተተቸ ነው ።

ገጣሚ ናቸዉ። ፀሐፌ ተዉነትም። ከብዙ የግጥምና የተዉኔት ድርሰቶቻቸዉ መሐል ጣልቃ የገባች አንዲት የታሪክ መፅሐፍ አለቻቸዉ። መፅሐፏ በ19ኛዉ መቶ ክፍለ-ዘመን በሥነ-ፅሑፉ መድረክ ዓለም አቀፍ ክብርና ሞገሥ ያተረፈዉ የሩሲያዊዉ ባለቅኔ የአሌክሳንደር ሰርግዬቪች ፑሽኪን ታሪክን ነዉ የምትወሳዉ። በእሳቸዉ አገላለፅ «ሕዝባዊ» የሚሉት ለገበሬዉና ለዝቅተኛዉ …

ባለቅኔ እና ፀሐፌ-ተዉኔት አያልነህ ሙላቱ – ዶይቸ ቬለ Read more »

የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ የወንጀል ችሎት በሽብር ተግባር በተከሰሱ ሰባት ተከሳሾች ላይ ዛሬ ከሰባት እስከ ዘጠኝ ዓመት ፅኑ የእስራት ቅጣት በየነ። በብይኑ መሰረት፣ የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ፕሬዚደንት አቶ ኦኬሎ ኦኳይ

ባለፈዉ ሐሙስ በጋምቤላ ክልል በጄዊ የስድተኞች መጠለያ ካምፕ አከባቢ ንብረትነቱ /ACF/ የተባለ ግብረ ሰናይ ድርጅት የሆነ አንድ ተሽከርካሪ ባደረሰው አደጋ ሁለት የስደተኞች ልጆች ከሞቱ በኋላ ስደተኞቹ 21 የአካባቢውን ነዋሪዎች ሲገድሉ፣ ከ10 በላይ መቁሰለቸዉን ዘገባዎች ያሳያሉ።

«የሽምብራው ጥርጥር የዛፎቹ ፍሬ የትም የትም ዞሬ ትዝ አለኝ ሀገሬ» የዛሬ ሳምንት ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩን «የመሰንቆው ሊቅ» ጌታመሳይ አበበ ዘመን ተሻጋሪ ከሆኑ የባህል ሙዚቃ ጨዋታዎች በግንባር ቀደምትነቱ የሚታወቀዉ ነዉ። ሁለ ገቡ ከያኒ ጌታመሳይ አበበ «የጥበብ ገበሪም » በመባል ይታወቃሉ። …

«የመሰንቆው ሊቅ» ጌታመሳይ አበበ – ዶይቸ ቬለ Read more »


ጥር 9/2008 ዓ.ም. ማለዳ ከአዲስ አበባ ወደ አዳማ አዲስ በተገነባው የፍጥነት መንገድ ላይ ይጓዝ የነበረ አሽከርካሪ መኪናውን መቆጣጠር ተስኖታል። የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪው በከፍተኛ ፍጥነት እየተጓዘ ነው። ከተቃራኒ አቅጣጫ አንድ መለስተኛ አዉቶቡስ አስራ ስድስት ሰዎች ጭኖ ከአዳማ ወደ አዲስ አበባ እየተጓዘ ነው። የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪው የሚጓዝበትን መንገድ ስቶ

የዓለም የጤና ድርጅት ሰነድ እንደሚለዉ በአሁኑ ወቅት የዓለማችን 37 ሚሊየን ሕዝብ HIV ተሐዋሲ በደሙ ዉስጥ ይገኛል። ባለፈዉ ጎርጎሪዮሳዊ ዓመት 2015 ላይ 16 ሚሊየኑ ፀረ ኤች አይቪ መድኃኒት እንደሚወስዱ ተመዝግቧል። በሽታዉ እስካሁን ከ34 ሚሊየን በላይ ሰዎችን ሕይወት ቀጥፏል። የመድኃኒቱ ስርጭት እና …

የፀረ ኤች አይቪ መድኃኒቶች – ዶይቸ ቬለ Read more »

በተለያዩ ምክንያቶች ከአፍንጫ ደም ሊፈስ ይችላል። ነስር የምንለዉ ማለት ነዉ። ብዙዎች መንስኤዉ ምንድነዉ ብለዉ ይጨነቃሉ። ነስር ድንገተኛ እና አስደንጋጭ የመሆኑን ያህል አብዛኛዉን ጊዜ ቤት ዉስጥ ሊቆጣጠሩት የሚቻል እንደሆነ አንዳንድ የህክምና ጽሑፎች ይጠቁማሉ። ሆኖም አልፎ አልፎ ደግሞ ብዙ ደም የሚፈስበት ከባድ …

የአፍንጫ መድማት ወይም ነስር – ዶይቸ ቬለ Read more »

በምዕራብ ኢትዮጵያ ከደቡብ ሱዳን ድንበር የተሻገሩ ታጣቂዎች በዕለተ አርብ ማለዳ በፈጸሙት ጥቃት ህጻናት መታገታቸውን የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል-አቀባይ ተናገሩ። ቃል-አቀባዩ አቶ ተወልደ ሙሉጌታ በጥቃቱ ምን ያኽል ሰዎች ታግተው እንደተወሰዱ አለመናገራቸውን የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘግቧል።

ጋምቤላ ኢትዮጵያ ውስጥ ከ140 በላይ ሰዎች ዐርብ ሚያዝያ 7 ቀን፣ 2008 ዓ.ም. ማንነታቸው ባልታወቀ ታጣቂዎች ተገደሉ። የኑዌር ጎሳ አባላት የመኖሪያ መንደሮች ላይ ባነጣጠረው ጥቃት የተገደሉት ሰዎች ቁጥር ከ221 በላይ መሆኑን ሱዳን ትሪቡዩን ዘግቧል።

ጫት ለኢትዮጵያ የሚሰጠው ጥቅምና በጤና ላይ የሚያስከትለው ጉዳት በቅጡ እንዲጤን ስለ ጫት ጥናታዊ ጽሁፎች ያቀረቡ ምሁራን አሳሰቡ ። «ፎረም ፎር ሶሻል ስተዲስ» የተባለው መንግሥታዊ ያልሆነው ድርጅት ባዘጋጀው አዲስ አበባ ውስጥ ለሁለት ቀናት በተካሄደው ዐውደ ጥናት ላይ የጫት ኤኮኖሚያዊ እና ባህላዊ …

የጫት ጉዳትና ጥቅሞች በኢትዮጵያ – ዶይቸ ቬለ Read more »

ሰሞኑን የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ለከፍተኛ የዉኃ እጥረት ተዳርገዋል። የአፍሪቃ ኅብረት ርዕሰ መዲና አዲስ አበባ በርካታ ዲፕሎማቶችን የምታስተናግድ ብትሆንም የመብራት ኃይልን ጨምሮ የዉኃ አቅርቦት እጥረት ችግር ላይ መዉደቅዋን አስመልክቶ የተለያዩ ዘገባዎች እየወጡ ነዉ።

ዓለም አቀፍ አዉቅና ያተረፉት እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ ያረፉት ከዓራት ዓመት በፊት ነበር።አዲስ አበባ ዉስጥ በመንበረ ፅባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቅፅር ግቢ የቆመዉን ሐዉልት ያስቀረፀዉ የኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለሥልጣን ነዉ

ከጅቡቲ ወደ ኢትዮጵያ የሚጓጓዘው የእርዳታ እህል እና ማዳበሪያ ጭነት መብዛት በአገሪቱ የትራንስፖርት ዋጋ ንረት ፈጥሯል። የኢትዮጵያ መንግስት ጅቡቲ ወደብ ላይ የተፈጠረውን መጨናነቅ ለመቀነስ የበርበራ ወደብን ለመጠቀም ስምምነት ፈርሟል። ለመሆኑ የሶማሌላንድ የበርበራ ወደብ ምን ያክል ለአጠቃቀም ምቹ ነው?

የኢትዮጵያ ትልቁ የኢንተርኔት አገልግሎት ሰጭ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ ሰሞኑን በቫይበር፣ በዋትስ አፕና መሰል የድምፅ ጥሪ አገልግሎቶች መስጫዎች ላይ ክፍያ ለመጠየቅ እንዳቀደ የኩባንያዉ የሥራ አመራር ለተለያዩ ሚዲያዎች መናገራቸዉ ይታወቃል።

የኢትዮጵያ መንግስት ለመሰረተ-ልማት ግንባታዎች ከቻይና ብቻ 17.6 ቢሊዮን ዶላር ተበድሯል። የኢትዮጵያ መንግስት ለሰፋፊ የመሰረተ-ልማት ግንባታዎች እና የማምረቻ ዘርፉን ለማሳደግ ከውጭ አገራት የሚበደረው ገንዘብ መጠን ያሰጋቸው ባለሙያዎች ግን ከአመት አመት በሚጨምረው ብድር ምክንያት አገሪቱ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ያሰጋታል እያሉ ነው።

አዋሳኝ ድንበራቸዉም የጦር ሐይል ፍጥጫ፤ ጠብ እና ቁርቁስ ተለይቶት አያዉቅም።አሁን በሰዎች መታገት በተለይ የኢትዮጵያን የምጣኔ ሐብት እና የሰዉ ሐይል ዋና ዋና ማዕከል ኦሮሚያን በሚንጠዉ ተቃዉሞና አመፅ ሰበብ እንዳዲስ መቀጣጠሉ «የከፋ ይከተላል» የሚል ሥጋት ማጫሩ አልቀረም-እንደ ሮንግ።

በኦሮሚያ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሐላፊ እንደሚሉት ዕቅዱን ሕዝቡ፤ በእሳቸዉ አገላለጥ «ከጫፍ እስከ ጫፍ» ተቃዉሞታል።በማስተር ፕላኑ ሰበብ በተነሳው ተቃውሞ በሁለት ወራት ጊዜ ዉስጥ ወደ 140 ሰዎች እንደተገደሉ ና በርካቶች እንደቆሰሉ የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ በምህፃሩ ኦፌኮ አስታውቋል

ሱዳን፣ ግብፅ እና ኢትዮጲያ ለብዙ ግዜ እየተንከባለለ ከመጣ ድርድር በኋላ በጎርጎሮሳዊው አቆጣጠር ታህሳስ 29 2015 ካርቱም ሱዳን ሊይ Declaration of Prinicples ወይም የመሰረታዊ መ መርሆዎች ሰነድ ተብሎ የምጠራዉን ሰነድ መፈራረማቸዉ ተዘግቧል ።

የኢትዮጵያ የምግብ የመድኃኒት ጤና ክብካቤ አስተዳደር እና ቁጥጥር ባለስልጣን ወደሀገር ዉስጥ በሕጋዊ መንገድ የሚገቡትንም ሆነ እዚያዉ የሚመረቱትን መድኃኒቶች የጥራት ደረጃ ይከታተላል።

ተቃዉሞ-ግጭቱ ቆመም-ተዳፈነ እስካሁን በነበረዉ ግጭት ከ100 በላይ ሰዎች ተገድለዋል። የተገደሉት ሰዎች ቁጥር የታሠሩና ብዛት፤ የጠፋዉ ሐብትና ንብረት መጠን ብዙ እንዳከራከረ ነዉ። መንግሥት ግጭቱ በተቀሰቀሰ ሰሞን አምስት ሰዎች መገደላቸዉን ከማሳወቁ ባለፍ በሰዉ ሕይወት፤ አካልና ንብረት ላይ ሥለደረሰዉ ጥፋት እስካሁን ይፋ ያደረገዉ ነገር የለም

ባለፉት ሁለት ወራት በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ ከተሞች በተፈጠረው የተማሪዎች ተቃውሞ 140 ሰዎች ሳይገደሉ እንዳልቀረ መቀመጫውን በኒውዮርክ ከተማ ያደረገው የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት Human Rights Watch ገልጿል።

በውጭ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ወደ አገር ቤት የሚልኩት የገንዘብ መጠን መጨመሩን የዓለም ባንክ በቅርቡ ባወጣው ዘገባ አስታውቋል። በውጭ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ግን ሁልጊዜም ገንዘብ የሚልኩት በህጋዊ መንገዶች አይደለም።

በሰሜን አሜሪካ በዋሽንግተን ዲሲና በምኒያፖሊስ ምኒሶታ ነዋሪ የሆኑ የክልሉ ተወላጆችም ለኦሮሞ ተማሪዎች ያላቸውን አጋርነት በሰላማዊ ሰልፍ፣በሻማ ማብራትና በተለያዩ የውይይት መድረኮች በመግለፅ ላይ ናቸው።

አኩሪ አተርን በተለያየ መንገድ ለምግብነት በርካቶች ይጠቀሙበታል። ከምሥራቅ እስያ አካባቢ መገኘቱ የሚገርለት ይህ የእህል ዘር በፕሮቲን የበለፀገ በመሆኑ ለተለያዩ የተመጣጠኑ ምግቦች ዝግጅት ሲዉል ዓመታት ተቆጥረዋል።

የዛሬው የወጣቶች ዓለም እንግዳችን ብዙ ፈተናዎችን ያሳለፈች ወጣት ናት። ከልጅነቷ አንስቶ የቤት ሰራተኛ ሆና አገልግላለች ፤ኃላም የጎዳና ተዳዳሪ ነበረች። እዛው ጎዳና ላይም ነፍሰ ጡር እና እመጫት ሊስትሮም ሆና ሰርታለች።

የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ሒውማን ራይትስ ዎች ትናንት ባወጣው መግለጫ በኢትዮጵያ የኦሮሚያ ክልል በተቀሰቀሰውና ሣምንታትን ባስቆጠረው ተቃውሞ ቢያንስ 75 ሰዎች መገደላቸውን እና በርካቶች መቁሰላቸውን አስታወቀ።

የሳውዲ አረብያ የተፈጥሮ ሃብት፣ ሃገሪቱን ባለፀጋ እና ተሰሚነት ያላት አገር እንድትሆን አድርጓል ። ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ግን የሳውዲ የሃብት ምንጭ የሆነው የነዳጅ ዘይት ዋጋ መውረዱና የየመኑ ጦርነት እንዲሁም በአካባቢው ከኢራን ጋር የሚካሄደው ሽኩቻ እስካሁን በገንዘብ አቅም የያዘችውን ቦታ ሳያሳጣት አይቀርም ።