“እኛ ጠንካራ ለመሆን የምንችለው በመተባበር ብቻ ነው፤ በተጻራሪው፤ እኛ ደካማ የምንሆነው በመከፋፈል ነው።”                                     ጀሪ ሮሊንግ፤ የቀድሞው የጋና ፕሬዝደንት ዛሬ ግብጾች ስለ ኢትዮጵያ ያወጡትን ዘገባ ስሰማ ከዚህ በፊት ስለ ተሃድሶ ግድብ በተከታታይ ያቀረብኳቸውን ትንተናዎችና […]

(ቁም ነገር መጽሔት፤ 15ኛ ዓመት ቅጽ 15 ቄጥር 264፤ መስከረም 2008 ዓ.ም.) /ተክለ ኪዳን አምባዬ/   መነሻ አንድ በቅርቡ ለአራተኛ ጊዜ የበጎ ሰው ሽልማት መካሔዱ ይታወሳል፡፡ ከሽልማት ሥነ ሥርዓቱ ቀደም ብሎ ስለዝግጅቱ በተጠራ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ፣ ለፕሮግራሙ አዘጋጆች ከጋዜጠኞች የቀረበ አንድ ጥያቄ ነበር፡፡ የበጎ ሰው ሽልማት ከሚሸልምባቸው ዘርፎች መካከል፣ ‹‹የዓመቱ የሰላም ሰው›› የሚል ነበር፤ ነገር …

መጋቤ አእላፍ ቆሞስ አባ ተክለ ሃይማኖት ንጉሤ  ኤጲስ ቆጶስነት ቢሾሙ ምን ሊፈጠር ይችላል? በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤ አሜን፡፡ ይድረስ፡- ለኤጲስ ቆጶሳት አስመራጭ ኮሚቴ፤ የጋምቤላ ክልል፣ ሊቀ ጳጳስ ሳይኖረው መቆየቱ ይታወሳል፡፡ ይኹን እንጂ፣ የጋምቤላና ደቡብ ሱዳን አህጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ የኾኑት፣ መጋቤ አእላፍ ቆሞስ አባ ተክለ ሃይማኖት በኤጲስ ቆጶስነት ሊመረጡ መኾኑን ጭምጭምታ …

የተሐድሶ ኑፋቄ አቀንቃኞችን፣ ለጉባኤ በመጋበዝና በማወደስ ግንባር ቀደም ናቸው ለቅዳሴ የተሠየሙትን ልብሰ ተክህኖ በማስወለቅ ለሥርዓቱ ንቀታቸውን አሳይተዋል በገና እና በሰኔ አጽዋማት ሉካንዳ ያዘወትራሉ፤ በሑዳዴም በጠዋት ገበታ ይሠየማሉ ውዳሴ ማርያም፣ ገድላት፣ ስግደት፣ ጾም፣ ፍትሐት፣ ንስሐ አያስፈልጉም፤ ብለዋል በጸሎተ ቅዳሴ ላይ ሳሉ በሞባይላቸው ፖርኖግራፊ ያያሉ፤ በፌስቡክ ቻት ያደርጋሉ ምንኵስናን “አደንዛዥ ዕፅ” በማለት እንደሕይወት ጥሪ ሳይኾን እንደሸክም ይቆጠራሉ …

• ከስም ማጥፋት ወንጀል በተጨማሪ የ100 ሺሕ ብር የፍትሐ ብሔር ክሥ አቤቱታም ቀርቧል • ግንቦት 17 እና 26 ቀን በፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ቂርቆስ ምድብ ችሎት ይቀርባል • የሕግ አገልግሎት መመሪያው የጉዳዩ አያያዝ እና የክሡ አቀራረብ ጥያቄ አሥነስቷል • ጽሑፉ፡- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ተቋማዊ አሠራር ጥላሸት የሚቀባ እና የቤተ ክርስቲያኒቱን ፓትርያርኩን ስም የሚያጠፋ …

እነሆ በሀገራችን አዲስ ጎሳ መፈጠሩ ተሰማ፡፡ እስከ ዛሬ ድረስ ሰዎች የጎሳ ማንነታቸውን ለማስከበር፣ ባህላቸውንና ታሪካቸውን ለመግለጥ ሲታገሉ ነበር የምናየው፡፡ ታሪክ የማያልቅባት ኢትዮጵያ የነባር ጎሳዎችን መብት ማስከበር ብቻ ሳይሆን አዳዲስ ጎሳዎችንም መመሥረት አለብኝ ብላለች፡፡ በርግጥ በሕገ መንግሥቱ ላይ ነባር ጎሳዎችን በተመለከተ …

‹ፌስዳቢ› – ዳንኤል ክብረት Read more »

ይገርምሃል ወንድሜ በሕይወትህ ድል አድርገህ ዋንጫ ወሰድክ ማለት እዚያው የልዕልና ማማ ላይ እንደተሰቀልክ ትቀራለህ ማለት አይደለም፡፡ አታየውም ቸልሲን መከራውን ሲቀበል፡፡ አምና እርሱ ዋንጫ ሲበላ ያየ ሰው ዘንድሮ መከራውን ይበላል ብሎ ማን ገመተ? ብዙዎችኮ ሲወጡ መውረድን ይረሱታል፡፡ ለሚወጣ ሰው ግን መውረድ …

ሕይወት – ሌስተርና ቼልሲ (ዳንኤል ክብረት) Read more »

ከ500 ዓመታት በፊት የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ዕለተ ስቅለትን እንዴት ታከብር እንደነበር በመጠኑ ሊያሳዩን ከሚችሉ መዛግብት አንዱ ‹ዜና ደብረ ሊባኖስ› የተሰኘው መዝገብ ነው፡፡ ዜና ደብረ ሊባኖስ በ1586 ዓም የተጻፈ መጽሐፍ ነው፡፡ መጽሐፉ አምስት ነገሮችን ይዟል፡፡ የደብረ ሊባኖስን ታሪክ ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት …

ሥርዓተ ዕለተ ስቅለት ዘደብረ ሊባኖስ – ዳንኤል ክብረት Read more »

ማኅደረ ማርያም ሰሞኑን በደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት በፋርጣ ወረዳ፣ ከደብረ ታቦር 28 ኪሎ ሜት ርቀት ላይ፣ በ2450 ሜትር ከፍታ ከባሕር ወለል በላይ፣ በቧኢት ተራራ ላይ ወደተተከለቺው ማኅደረ ማርያም ደብር ተጉዤ ነበር፡፡ የጉዞዬ ዋና ዓላማ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን በተመለከተ ለምሠራው ጥናት …

ማኅደረ ማርያም – ማኅደረ ታሪክ Read more »

ሰሞኑን በአዲስ አበባ አንድ ትልቅ የስብሰባ አዳራሽ ውስጥ የአዲስ አበባ ደረጃ አንድ ሌቦች ስብሰባ አድርገው ነበር፡፡ የስብሰባው መሪ ቃል ‹የሕዝቡን ጥያቄ ለመመለስ ሌቦች ምን ሊያደርጉ ይችላሉ?› የሚል ነው፡፡ ስብሰባው እንደተጀመረ አንደኛው የታወቀ ሌባ እጁን አወጣና ‹መፈክሩ ላይ የተጠቀስንበት ስም ትክክል …

“የሰርቆ አደሮች” ስብሰባ ” – ዲ/ን ዳንኤል ክብረት Read more »

በእንዳለ ጌታ ከበደ የካቲት 2008 ዓም ዋጋ፡- 120 ብር እንዳለ ጌታ ከበደ በዓሉ ግርማን እንደ ጌታ ነፍስ ዘርቶ እንደደአልዓዛር ከሞት አስነሥቶታል፡፡ ከትውልድ ቀየው ጀምሮ ‹እስከ መቃብሩ› ደረስ እየተከተለ፡፡ መዛግብቱን ያገላብጣል፣ እናውቃለን የሚሉትን ይጠይቃል፣ ያውቃሉ ብሎ የገመታቸውን ያናግራል፤ ሄዶበታል፣ ውሎበታል፣ ገብቶበታል፣ …

በዓሉ ግርማ – ሕይወቱና ሥራዎቹ (መጽሃፍ ግምገማ በዳንኤል ክብረት) Read more »

ዛሬ ሚያዚያ 6, 2008ዓ.ም. ዐፄ ቴዎድሮስ የዛሬ 148 ዓመት “ተማርኬ የሐበሻ ንጉሥ ተማረከ! ተብሎ እራሴን ሀገሬንና ሕዝቤን ከማዋርድ ስም ከምሰብር ሞት ይሻለኛል!” ብለው ለሚወዷት ሀገራቸውና ሕዝቧ ክብርና ኩራት ሲሉ ተማርከው በጠላት እጅ ከመውደቅ እራሳቸውን አጥፍተው የጀግና እረፍትን ቢያርፉ መርጠው እራሳቸውን ያጠፉበት የሚታሰብበት ዕለት ነው፡፡ “ዐፄ ቴዎድሮስ ለምን ይተቻሉ! ፈጽሞ መተቸት የለባቸው!” ለማለት አይደለም አነሣሴ፡፡ ነገር […]

የሰው ልጅ አራት የጠባይ እርከኖች አሉት ይላሉ ትውፊታውያን ሊቃውንት፡፡ በነባሩ የኢትዮጵያ ትምህርት መሠረት ጠባይና ባሕርይ ይለያያሉ፡፡ ‹ባሕርይ› ማንነት ነው፡፡ በፍጥረትህ ታገኘዋለህ፡፡ ይዘህው ትኖራለህ፡፡ አትለውጠውም፤ አታሻሽለውም፡፡ ለምሳሌ ሰውነት ባሕርይ ነው፡፡ ሰው መሆንን፣ እንስሳ ወይም ዛፍ ወይም ውኃ በመሆን አትለውጠውም፡፡ ‹ጠባይ› ደግሞ …

አራቱ የጠባይ እርከኖች – ዳንኤል ክብረት Read more »

ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገርሙኝ ዘፈኖች አንዱ ‹ሀገር ማለት ሰው ነው› የሚለው ነው፡፡ እሥራኤላዊና ጂፕሲ ይህንን ቢሰሙ ምን ይሉ ይሆን? እላለሁ፡፡ አይሁድ በመላው ዓለም ለ1900 ዓመታት ያህል ተበታትነው ሲኖሩ በየአካባቢው ሰው ነበራቸው፤ያውም እንደ ብረት የጠነከረ ማኅበረሰብ፤ ሀገር ግን አልነበራቸውም፡፡ ሀገር ማለት ሰው …

‹ሀገር ማለት ሰው ነው›፤ እስኪ ሙት በለኝ! – ዳንኤል ክብረት Read more »

ሰሞኑን ሻለቃ ኃይሌ ገ/ሥላሴ ለአንድ የውጪ ጋዜጠኛ “ዲሞክራሲ (መስፍነ ሕዝብ) ለአፍሪካ አያስፈልጋትም! ለአፍሪካ የሚያስፈልጋት መልካም አሥተዳደር ነው!” ብሎ መናገሩን ሰምተናል፡፡ እንደሰማንም በእጅጉ አፍረናል ተሸማቀናልም፡፡ እኔ በበኩሌ “እንዲያው ይሄ ሰውየ እያሰበና ነገሮችን በቅጡ ተረድቶ ተገንዝቦ ገብቶት መናገር የማይችል ከሆነ ምናለ ዝም ቢል ባይናገርስ!” ብያለሁ፡፡ ይሄንን ንግግሩን “አይ እሱ ለማለት የፈለገው…” ብለን ልንለው የምንችለው ምንም ሌላ ነገር […]

ዐፄ ቴዎድሮስ በበጌምድር ማንም ለሞተ ዘመዱ እንዳያለቅስ የሚል ዐዋጅ ዐውጀው ‹ሰው ሁሉ ዕንባውን ያጠጣ ነበር፡፡› በዚህ መካከል ደጃች ውቤ ሞቱና ለእቴጌ ጥሩ ወርቅ ወደ መቅደላ መርዶ ተላከ፡፡ ዐፄ ቴዎድሮስም ሕዝቡን ‹ለደጃች ውቤ አልቅሱልኝ› ብለው አዘዙ፡፡ ሰውም ሁሉ ዘመዱ ሲሞት የቀረበት …

የደጃች ውቤ ልቅሶ – ዳንኤል ክብረት Read more »

ወያኔና ሌሎች የጥፋት ኃይሎች አማራን የማጥፋት የቆረጠ የጥፋት ዓላማና ድርጊት ይዘው መምጣታቸውና ሀገሪቱን ከመቆጣጠራቸው የወሰዱት የተቀናጀ ዘግናኝ የዘር ማጥፋት ጥቃት መፈጸማቸው የአማራ ልኂቃንን አስጨንቆ ሕዝቡን ከወያኔና መሰሎቹ የዘር ማጥፋት ጥቃት የታደጉ፣ የሠወሩ፣ ያዳኑ፣ የከለሉ፣ የተከላከሉ መስሏቸው ሁለት የተለያዩ አቋሞችን ለማራመድ ሲያስገድድ ከአማራው ሕዝብም ቀላል ቁጥር ያልያዘውን ምናልባትም አሁን የአማራ ሕዝብ ተብሎ ከሚገለጸው የሚበዛውን በተለይ በወያኔ […]

በገድለ ወለተ ጴጥሮስ ላይ እንዲህ የሚል ታሪክ አለ፡፡ እምነ ወለተ ጴጥሮስ ወደ ዋልድባ ገዳም በገባች ጊዜ ለአንዲት እናት ረድእ ሆነች፡፡ እኒህ እናት ፈጽሞ ጠባይ የሚባል ያልፈጠረባቸው ነበሩ፡፡ አሁን የተናገሩትን አሁን ይሽሩታል፣ በሆነው ባልሆነው ይቆጣሉ፤ ከእርጅናቸው ብዛት የተነሣ ይነጫነጫሉ፤ ትእዛዛቸው ሁሉ ውኃ ቀጠነ ነው፡፡ በዚህ ዐመላቸው የተነሣ ማንም ከእርሳቸው ጋር ለመኖር ፈቃደኛ አልነበረም፡፡ ከእርሳቸው ጋር ለመኖር ፈቃደኛ ሆና ለረዥም ጊዜ ያገለገለቻቸው ወለተ ጴጥሮስ ነበረች፡፡
አንድ ቀን መነከሳዪያቱ ተሰባስበው ‹እንዴት ከእኒህ እማሆይ ጋር ለዚህን ያህል ዘመን አብረሽ ለመኖር ቻልሽ? እንዴትስ ታገሥሻቸው? እንዴትስ መሮሽ ጥለሽ አልወጣሽም? ሲሉ ጠየቋት፡፡ ወለተ ጴጥሮስም ‹ንብ ታውቃላችሁ? እኒህ እናት ንብ ናቸው፡፡ ከእርሳቸው የሚገኝ ብዙ ዕውቀት፣ ብዙ ጥበብ፣ ብዙ ልምድ፣ ብዙ ታሪክ፣ ብዙም ጸጋ አለ፡፡ ነገር ግን እናንተ መናደፋቸውን ብቻ ነው የምታዩት፤ ስለዚህም ማሩን ከእርሳቸው ልትቆርጡ አልቻላችሁም፡፡ ንብ ትናደፋለች፣ ነገር ግን ማር የሚገኘው ከምትናደፈው ንብ ነው፡፡ የማትናደፈው ዝንብ ቆሻሻ እንጂ ማር የላትም፡፡ እኔ ግን ከንብ ጋር እንዴት እንደሚኖር ዐውቃለሁ፤ ከንብ ጋር እየኖርኩም ማሩን እቆርጣለሁ› አለቻቸው ይባላል፡፡

ትዳር ማለትም እንዲሁ ነው፡፡
‹አበባው አበበ ንቡም ገባልሽ
እንግዲህ አልማዜ ማር ትበያለሽ›
የሚለው የሠርግ ዘፈን ከዚህ ጋር ይስማማል፡፡ አፍንጅም ከጋብቻ በኋላ ያለውን ጫጉላ ‹ማር ጨረቃ› ሲለው ይኼ ታይቶት እንደሆነ እንጃ፡፡ አንዳንዶቹ የትዳር ንድፊያው ብቻ ስለሚታያቸው ወይ ትዳር ሳይመሠርቱ ወይም የመሠረቱትን ትዳር ሲፈቱ ይታያሉ፡፡ ሌሎቹ ደግሞ የትዳር በጎነቱን ብቻ ስለሚያውቁት እስኪገቡበት ሲጓጉ፣ ከገቡበት በኋላ ደግሞ
ስሳል እንዳልኖርኩኝ አስንቺን እስካገኝ
ካገኘሁሽ ወዲያ እላለሁ አውጣኝ
እያሉ ያንጎራጉራሉ፡፡
ምናልባትም ደግሞ በሠርግ ላይ የሚዘፈነው
ማን ፈርሚ አለሽ፣ ማን ፈርሚ አለሽ
በተወለወለው በአለንጋው ጣትሽ
የሚለው ዜማ ‹ትንቢት ይቀድሞ ለነገር› ዓይነት ሳይሆን አይቀርም፡፡
ትዳር ግን ሁለቱም ብቻ አይደለም፡፡ ትዳር ከንብ ጋር መኖር ነው፡፡ ንብ ሁለት ጠባይ አላት፡፡ አንዱ ያስደስታል፤ ሌላኛው ያስከፋል፡፡ አንዱ ጤና ይሆናል፣ ሌላኛው ግን ያማል፡፡ አንዱ ይጣፍጣል፤ ሌላው ግን ይመራል፡፡ አንዱን ይቆርጡታል፣ ሌላውን ግን ይከላከሉታል፡፡
ትዳርም እንዲሁ ነው፡፡ ሁለት ጠባይ አለው፡፡ አንደኛው ያስቃል አንዱ ያሰቅቃል፤ አንዱ ያስደስታል፣ ሌላው ያሳዝናል፡፡ አንዱ ግቡ ግቡ ሌላው ውጡ ውጡ ያሰኛል፡፡ አንዱ ይናደፋል፣ አንዱ ይጣፍጣል፤ አንዱ ጤና ሌላው ሕመም ይሰጣል፡፡ አንደኛው ግን ያለ ሌላው አይገኝም፡፡
ይኼን ለመድኃኒት፣ ለብርዝ፣ ለጠጅ፣ የምናደርገውን ማር የምትሰጠው ንብ ናት የምትናደፈው፡፡ ያቺ ስትናደፍ ፊት የምታሳብጠው፣ ውስጥን የምትመርዘው፣ የምትጠዘጥዘው፣ ንብ ናት ማሩን የምትሰጠው፡፡ በትዳርም ውስጥ ሁለቱም አሉ፡፡ ጭቅጭቁ፣ ንዝንዙ፣ ጠቡ፣ ኩርፊያው፣ አንዱ ለሌላው የግድ መታዘዙ፣ አንዱ የሌላው አገልጋይ መሆኑ፣ አንዱ ያለ ሌላው ለመወሰን አለመቻሉ፤ የሌላውን ጠባይ፣ የሌላውን ዐመል የግድ መታገሡ፤ ከሚታገሡት ሰው ጋር አብሮ መኖሩ፤ ይኼ ነው የንቧ ንድፊያ፡፡
ሰው የወለደውን አያገባም፡፡ ያሳደገውን አያገባም፣ የተዛመደውን አያገባም፡፡ የቤቱን ሰው አያገባም፡፡ ሰው ደግሞ በዐመልም፣ በፍላጎትም፣ በአመለካከትም ይበልጥ የሚቀራረበው አብሮት ከኖረና ካደገ ሰው ጋር ነበር፡፡ እምነቱና ባሕሉ ግን ጋብቻን እስከ ሰባት ቤት አርቆ ለባዕድ ይሰጠዋል፡፡ አብረነው ላልኖርነው፣ አብረን ላላደግነው አብረን ላልተወለድነው፣ ላልተዛመድነው ሰው፡፡ ከሌላ ተወልዶ፣ ሃያ ሠላሳ ዓመት ሌላ ቦታ ኖሮ፣ ከሌላ ጋር አድጎ፣ ሌላ ጠባይ ነሥቶ፣ በሌላ መንገድ መጥቶ ያገኘነውን ሰው ነው የምናገባው፡፡ ይኼንን ሰው ወይም ይህችን ሴትዮ በዕውቅ አላሠራናትም፣ አላሠራነውም፡፡ ዐመሉ እንዲህ፣ ሐሳቡ እንዲያ፣ መንገዱ እንዲህ፣ እምነቱ እንዲያ፣ ዕውቀቱ እንዲህ፣ ምግባሩ እንዲያ ብለን ዝርዝር ሰጥተን አላስመረትነውም፡፡ ‹ሬድ ሜድ› ነው ያገኘነው፡፡ ዓይተን እንመርጣለን እንጂ፣ መርጠን አናሠራም፡፡
ንብን እኛ ብናሠራት ኖሮ የርሷን መናደፍ ለዝንብ ሰጥተን የዝንብን ጠባይ ለንብ በመለስንላት ነበር፡፡ ግን ንብን እንዲሁ ሆና አገኘናት፣ አላመድናት፣ ወደ ቀፏችን አስገባናት እንጂ አንድም አልፈጠርናት፣ አንድም አላስፈጠርናት፡፡ ንቧን ማርና ንድፊያ እንደያዘች ነው ያገኘናት፡፡ ሰው በውስጡ ማርና ንድፊያ አለው፡፡ የተገዛ የሱፐር ማርኬት ማር የሚበላ ልጅ ንብ የምትባለውን የሚያውቃት በጣሳው ላይ ባለው ሥዕል ነው፡፡ መልኳን እንጂ ንድፊያዋን አያውቀውም፡፡ እርሱ እድሜ ልን በንብ እየተነደፈ ለጌቶቹ ማር ቆርጦ የሚሰጥ ገባርም ንብ እንደምትናደፍ እንጂ ማር እንደምትሰጥ አያውቅም፡፡ ‹ጌቶች ምን ምን ቢላቸው ነው ይህን የቀፎ እንጀራ የሚያስገፈግፉኝ› አለ የሚባለውም ለዚህ ነው፡፡
አንዳንዶች በሠርግ ዘፈን፣ በተረት፣ በሠርግ ሥነ ሥርዓት፣ በስብከት፣ በድራማና በፊልም ትዳርን ሲያዩ ምናልባት ማሩ ይሆናል የሚታያቸው፡፡ ያገኛቸውም ሰው ሁሉ ‹ምነው አንተ አታገባም እንዴ› ይላቸዋል እንጂ ተገብቶ ምን እንዳለ አይነግራቸውም፡፡ ‹የዛሬ ዓመት፣ የዛሬ ዓመት፣
የእንትናዬ አባት
ሲወለድ ማሞ፣ ሲወለድ ማሞ
እንመጣለን ደግሞ፤
ያሉት ሰዎች ደግመው ላይመጡ ይችላሉ፡፡ አንዳንዶችም ማሞ ሲወለድ እንደማይመጡ እያወቁት የሚዘፍኑት ዘፈን ነው፡፡ ‹የዛሬ ዓመት የእንትናዬ አባት› መሆን ለሁሉ ያልተሰጠ መሆኑን የሚናገርም የለም፡፡ ይኼ ያልተነገራቸው የዋሐንም ናቸው ልጅ የለም ብለው የሚፋቱት፡፡
ሌሎች ደግሞ ትዳር ሲባል የንቧ ንድፊያ ነው ትዝ የሚላቸው፡፡
‹ታሠረች አሉ በትዳር፣
ከንግዲህ ቀረ መሽርቀር› የሚለው ዘፈንም ውስጠ ዘ አለበት፡፡
ትዳር ምን ዕዳ ነው ትዳር ምን ዕዳ ነው
ጉልቻው ስሙኒ ምጣዱ ብር ነው
የሚለው ባሕላዊ ዜማ የምጣዱና የጉልቻው ዋጋ ዛሬ ሰማይ በነካበት ጊዜ ቀርቶ ትናንትም በርካሹ ዘመን ትዳርን ‹ዕዳ› ነው እያለ የንቧን መናደፍ እየነገረን ነው፡፡
ትዳር ግን ሁለቱም ብቻ አይደለም፡፡ ትዳር ከንብ ጋር መኖር ነው፡፡ ለማሩ ስንል ንድፊያውን መታገሥ፡፡ ቆይተህ ደግሞ ንድፊያውን መልመድ፡፡ ገበሬ ቀፎ ሰቅሎ ንብ ሲያንብ ንብ እንደምትናደፍ ሳያውቅ ቀርቶ አይደለም፡፡ የማትናደፍ ንብ ከፈለገ በየደጁ ቆሻሻ ፍለጋ የምትጓዘው ዝንብ ነበረችለት፡፡ ዝንብ ምን ጠባይዋ ሸጋ ቢሆን፤ ጠብ የሚላት ግን ሌላ ነገር ነው፡፡ ይህን ያውቃል ገበሬው፡፡ እያወቀም ንብ ያንባል፡፡ ማነብ ብቻ ሳይሆን ከንብ ጋር እንዴት መኖር እንደሚቻልም ያውቃል፡፡ ንብ ትናደፋለች፤ ግን እንዳትናደፍ ማድረግም ይችላል፡፡ የምትወደውና የማትወደው ሽታ አለ፡፡ ስትቀርብህ ምን ማድረግ እና ምን አለማድረግ እንዳለብህ ገበሬው ያውቃል፡፡ በሀገራችን ንብ አትገደልም፡፡ ነውር ነው፡፡ ብትነድፍም አትገደልም፡፡ የንቧን ማር ለመውሰድም ንቧን ገድሎ፣ አጥፍቶ፣ ጎድቶ ወይም አሰቃይቶ ሳይሆን በጭስ ራሱን እየተከላከለ፣ ፊቱን በጨርቅ ሸፍኖ፣ ወደ ንቧ ቀፎ ገብቶ ነው ማሩን የሚቆርጠው፡፡ ንቧም ሳትጎዳ፣ ማሩም ሳይጠፋ፣ እርሷም ሳትናደፍ፡፡
ትዳርም እንዲህ ነው፡፡ አኗኗሩን ነው ማወቅ፡፤ የንቧን ንድፊያ የመቀነሻውን መንገድ ነው ማወቅ፣ የማሩን አቆራረጥ መንገድ ነው ማወቅ፡፡ ደግሞምኮ አስገራሚው ገበሬው የሚከባከበው ይህቺኑ የምትናደፈውን ንብ መሆኑ ነው፡፡ የምትቀስመው አበባ ትፈልጋለች፣ ንጹሕ አካባቢ ትፈልጋለች፣ ከጉንዳንና ከአውሬ ነጻ የሆነ ቀፎ ትፈልጋለች፡፡ ግን ትናደፋለች፡፡ ደግሞም ማር ትሰጣለች፡፡ ትዳር አስደሳች ነገር ብቻ ሳይሆን አስመራሪ፣ አንገብጋቢ፣ አስጠሊታ፣ ጨጓራ አንዳጅ፣ አንጀት ቆራጭ፣ ልብ አቃጣይም ክፍል አለው፡፡ ይናደፋል፡፡ ግን ደግሞ ክብካቤም ይፈልጋል፡፡ ንጹሕ ልብ፣ ታማኝ ኅሊና፣ ቻይ አንጀት፣ ታጋሽ ሆድ፣ ጠቢብ አእምሮ፣ አሳላፊ ልቡና ይፈልጋል፡፡ ለምን ቢሉ? ማር ይሰጣልና፡፡
አንዳንዶች ቤት ካለችው ወይም ካለው ንብ ይልቅ ውጭ ያቺውን ወይም ያለው ዝንብ ሲያደንቁ ይሰማል፡፡ መቼም ከቀፎ ውጭ ምን እንደሚኖር የታወቀ ነው፡፡ ንብ ትናደፋለች ብሎ ንብ የማያነባ ገበሬ ስንፍናውን እንጂ የንቢቱን ክፋት ማንም አይረዳለትም፡፡ ጥበብ አልባ መሆኑን፣ ትዕግሥት አልባ መሆኑን፣ ተሸናፊነቱን እየተናገረ እንጂ የንቧን ጠባይ እየተናገረ አለመሆኑን ሁሉም ያውቅለታል፡፡ የትዳርን ችግር ብቻ የሚያወራ፣ በትዳር ተመርሮ ከቀፎው ውጭ የሚሄድም ስንፍናውንና ዐቅመ ቢስነቱን እንጂ የቀፎውን ችግር እየተናገረ አይምሰለው፡፡ ቀፈ ውስጥ ማር የምትሠራው ን እንዳለች ሁሉም ያውቃልና፡፡ ሌላው ቀርቶ ውጭ ያለቺው ዝንብም ይኼንን ታውቃለች፡፡   
አንዳንዶች ከንብ ጋር የመኖር ጥበብ ሲያንሳቸው የማትናደፍ ንብ ፍለጋ ይኳትናሉ፡፡ የማትናደፍ ንብ መፈለግ ከመረቁ አወጡልኝ ከሥጋው ጦመኛ ነኝ እንደማለት ነው፡፡ ወይም የማትዞር መሬት እንደመፈለግ፡፡ የመትናደፍ ንብ ከፈለግክ ከዝንብ ጋር ተጋባ፡፡ 
ይህ ጽሑፍ በአዲስ አድማስ ጋዜጣ የወጣ ነው፡፡

ፖሊስ አምስት ተጠርጣሪዎችን ይዞ ምርመራ እያካሔደ ነው ከደረጃቸው ዝቅ የተደረጉት የሀገረ ስብከቱ ሓላፊ ይገኙበታል አማሳኞች፣ ጠንቋይ አስጠንቋዮችና መናፍቃን ፈተና ኾነዋል (ሰንደቅ፤ ረቡዕ፤ ጥር ፲፩ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም.) በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ በብፁዕ አቡነ ኤፍሬም የደብረ ብርሃን መኖርያ ቤታቸው፣ ታኅሣሥ 26 ቀን 2008 ዓ.ም. ምሽት ቦምብ መፈንዳቱ ተገለጸ፡፡ በመንበረ …

  ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው እንደሚታወቀው በተማሪዎች የተጀመረው ተቃውሞ ሌላው የኅብረተሰብ ክፍልም ተቀላቅሎት ሲደረግ የቆየው ሕዝባዊ ተቃውሞ እነሆ ሁለት ወራት እየሆነው ነው፡፡ እያየነው እንዳለነው እስከአሁን ተቃውሞው ያመጣው ውጤት ወይም ለውጥ የለም፡፡ ወደፊትም ሕዝቡ በዓመፁ የመቀጠል ብርታት የሚኖረው ከሆነ “በእኔ ግምት ይኖረዋል ብየ ስላልገመትኩ ነው ምክንያቶች አሉኝ” እንዲያው ከሆነ ግን ወያኔ ሁሉንም ለቃቅሞ እስኪፈጅ ድረስ ሳይሰለች […]

ሰሞኑን በኦሮሚያ እና በሰሜን ጎንደር የተከሰተው የተቃውሞ ንቅናቄ ሀገሪቱን ውጥረት ውስጥ ከትቷታል፡፡ አመጹ እየተጋጋለ መሄድ እንጂ የመቀዛቀዝ ባህሪ አላሳይ ብሏል፡፡ አሁንም በልዩ ልዩ አካባቢዎች ቀጥሏል፡፡ በአራቱም አቅጣጫዎች ውጥረት ሰፍኗል፡፡ በህይወት ዘመኔ ይህንን ያህል ዘላቂ ሆኖ የቆየ አመጽ አይቼ አላውቅም፡፡ በዚህ አመጽ ለጠፋው ህይወትና ንብረት እናዝናለን፡፡ በየትኛውም ወገን ሆኖ በትርኢቱ ውስጥ የተሳተፈው የኛው ዜጋ በመሆኑ ነፍሱና […]

ከፍተኛ አካላዊ ድካም እና የሰውነት መዛል ታይቶባቸዋል የበዓታ ለማርያምን በዓል በዲሲ መድኃኔዓለም ያከብራሉ (ሰንደቅ፤ ረቡዕ፤ ኅዳር ፳፱ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም.) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፣ ለከፍተኛ ሕክምና ወደ አሜሪካ ማምራታቸውን የመንበረ ፓትርያርኩ ምንጮች ገለጹ። ከትላንት በስቲያ፣ ሰኞ ማምሻውን ከምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ እና ሌላ ረዳታቸው ጋር …

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ኒው ዮርክ ከተማ (የተራድኦ ድግስ ምሽት፥ ኅዳር ፬ ቀን ፳፻፯ ዓ. ም. – November 14, 2015) [ ጌታቸው ኃይሌ ] ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን እንድታገለግሉ የተመረጣችሁ የተከበራችሁ ካህናትና ዲያቆኖት፥ የመድኃኔ ዓለም አባላት እንድትሆኑ የሐዋርያትን …

“በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የጽሑፍ ቅርስ ላይ ከአለኝ ትዝብት” (ዳንኤል ክብረት) Read more »

ፈረንጅ ሆይ ናና ፈረንጅ ሆይ ናና አንተ ስትናገር ይታመናልና ፈረንጅ ሆይ ናና ፈረንጅ ሆይ ናና አንተ ስትናገር ትሰማለህና ፈረንጅ ሆይ፤ አንተ ገድላቱንና ድርሳናቱን፣ ዜና መዋዕሎችንና ታሪከ ነገሥቱን፣ የፍልስፍናውንና የጥበቡን፣ የመድኃኒቱንና የጠልሰሙን ነገር ከግእዝ ወደ እንግሊዝኛ ስትተረጉመው ሁሉም ያደንቅሃል፣ ያነብሃል፡፡ ይጠቅስሃል፡፡ …

ፈረንጅ ሆይ ናና – ዳንኤል ክብረት Read more »

የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ በዋና ሥራ አስኪያጅነት በመቀጠሉ “የምስጋና ሰርፕራይዝ” ነው ያልታቀደው ወጪ፣ የፓትርያኩን የመኖርያ ቤት ዕቃዎች ለመቀየር መዋሉ ተነግሯል ጽርሐ መንበረ ፓትርያርኩን የማስተዳደር ሓላፊነት ያለው ጠቅላይ ጽ/ቤቱ አያውቀውም የሀ/ስብከቱ ሒሳብ፣ ያለተቆጣጣሪና ያለዕቅድ በየማነ ዓምባገነንነት እንዲባክን ተፈርዶበታል በወሬ እና በይስሙላ አካሔዶች የተሳሳተ ምስል እየፈጠረ ራሱን እንደ ለውጥ አራማጅ እና መሪ በመስበክ የሥልጣን ወራቱን እያራዘመ የሚገኘው የአዲስ …

“ክ/ከተማው ቦታው አይነካባችኹም ብሎ አዘናግቶናል፤ ለሌላ ዓላማ መዋሉ አሳዝኖናል” /ምእመናን/ “ለሌላ ዓላማ ሳይውል አጥቢያዎቹ በዕቅዳቸው እንዲያለሙት አመራር ይሰጥላቸው” /ቅ/ሲኖዶስ/ “ልማቱ በዓለ ጥምቀቱን ታሳቢ ያደረገ ነው፤ ቦታው በታቦት ማደርያነቱ ይቀጥላል” /ክ/ከተማው/ (አዲስ አድማስ፤ ናፍቆት ዮሴፍ፤ ቅዳሜ ጥቅምት ፳፯ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም.) ላለፉት 52 ዓመታት በበዓለ ጥምቀት ማክበርያነት እና በታቦት ማደርያነት ሲያገለግል የነበረው የባሕረ ጥምቀት ቦታ ለሌላ …

ለመሪ ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ከአምስት ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቧል የቤተ ክርስቲያንን ኹለንተናዊ ችግር የሚያጠና ዐቢይ ኮሚቴ አቋቁሟል የሙስና እና የመልካም አስተዳደር ዕጦት በኮሚቴው ጥናት ተካተዋል የጥናቱ ግኝትና መፍትሔ ተቋማዊ ህልውናዋንና አቅጣጫዋን ይወስናል

የሳተላይት ሥርጭቱ መካከለኛው ምሥራቅን፣ ደቡብ አውሮፓንና ሰሜን አፍሪቃን ያካልላል (አዲስ አድማስ፤ ቅጽ ፲፮ ቁጥር ፰፻፳፬፤ ጥቅምት ፳ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም.) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ በሀገር ውስጥና በዓለም ዙሪያ ለሚገኙ አገልጋዮችዋ እና ምእመናንዋ ድምፅዋን የምታሰማበትና መረጃ የምትሰጥበት የ24 ሰዓት የቴሌቪዥን አገልግሎት እንድትጀምር ቅዱስ ሲኖዶስ ወሰነ፡፡ ከጥቅምት 12 ጀምሮ የዓመቱን የመጀመሪያ የምልአተ ጉባኤ መደበኛ ስብሰባ በማካሔድ …

አሜሪካ ስመጣ ሦስት ቦታ ያለው የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ይማርከኛል፡፡ ላስቬጋስ  ኪዳነ ምሕረትና ቅዱስ ሚካኤል፣ ዴንቨር መድኃኔዓለምና ሚነሶታ ቅድስት ሥላሴ፡፡ ሃይማኖታቸውን የተረዱ፣ ለአገልግሎት የተጉና ምራቃቸውን የዋጡ ክርስቲያኖች ያሉበት ቦታ፡፡ ወደነዚህ ቦታዎች ስመጣ ከማስተምረው የምማረው ይበልጣል፡፡ በአስቸጋሪው የአሜሪካ ኑሮና ፈተና ውስጥ የቤተ …

ላስቬጋስ – ጎንደር (ዳንኤል ክብረት) Read more »

የአቅም ግንባታ ፕሮጀክቱ፣ በአህጉረ ስብከት እና በአጥቢያ ሠራተኞች ሥልጠና ይቀጥላል “ለቤተ ክርስቲያን መልካምነትም ኾነ ውድቀት መሪዎች ትልቁን ድርሻን ይወስዳሉ፡፡” /ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል/ በመንፈሳዊ አመራር እና በዘመናዊ የሙዓለ ንዋይ አስተዳደር፣ የቤተ ክርስቲያን መሪዎችን አቅም በማጎልበት ክሂሎታቸውን ለማዳበር ያስችላል የተባለ የከፍተኛ ሓላፊዎች ሥልጠና በልማት እና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን ተሰጠ፡፡ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት እና በመላው አህጉረ …

የመቅደላው ጀግና ዐፄ ቴዎድሮስ በመጨረሻዋ ሰዓት ለጄኔራል ናፒየሪ በጻፉት ደብዳቤ አበክረው የጠየቁት ነገር ከሁለት ቀናት በፊት በተደረገው ውጊያ የወደቀውን የወዳጃቸውንና የጦር መሪያቸውን የፊታውራሪ ገብርዬን አስከሬን ለመቅበር እንዲፈቀድላቸው ነበር፡፡ ‹‹ፊታውራ ገብርዬን የኔን ወዳጅ ሳላነሣው ያደርኩ ከሞትኩኝ ሁሉንም አብረው ይቅበሩኝ ብየ ነበር፡፡ …

የወታደሮቻችን ነገር (ዳንኤል ክብረት) Read more »

በቤተ ክርስቲያን ስም በሚዲያዎች ስለሚተላለፉ ‘ትምህርቶች’ ይወስናል የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አስተዳደር ጉዳይ ከመነጋገርያ አጀንዳዎቹ ተካቷል እነየማነ ዘመንፈስ ቅዱስ፣ በአዳራሹ መግቢያና በአባቶች ቤት ደጅ እየጠኑ ነው በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቁጥር 164 ድንጋጌ መሠረት፣ ትላንት ጥቅምት 12 ቀን በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የመክፈቻ ንግግር የተጀመረው የቅዱስ ሲኖዶስ ዓመታዊ መደበኛ ስብሰባ፤ ዘመኑን የዋጁ እና ወቅቱን የተመለከቱ የመነጋገርያ …

መሠረታዊ ችግር ሊኾን የሚችለው ክፍተት ለምን ተፈጠረ የሚለው ሳይኾን ክፍተት መኖሩ እየታወቀ ዝም ብሎ መኖሩ ነው ሕዝበ ክርስቲያኑ ቤተ ክርስቲያኑን ለመደገፍና ለማልማት የሚያደርገው ቀና ትብብር ከመቼውም ጊዜ የበለጠ ተሰፋ ሰጪ ኾኖ ይታያል ሐዋርያዊ ተልእኮን ለማስፋፋት በተደረገው እንቅስቃሴ ከምዕራብ አሜሪካ እስከ ጃፓን፤ ከአየርላንድ እስከ አውስትራልያ ቤተ ክርስቲያናችን ክንፎቿዋን የዘረጋችበት ኹኔታ በመፈጠሩ ዓለም አቀፋዊት ወደ መኾን አድጋለች …

ሲኖዶስ ማለት፡- ሲኖዶስ፣ ቃሉም ሥራውም የምሥራቃውያን ነው ቃሉ ግሪክኛ ኾኖ የአንድነት ስብሰባ ማለት ነው የእኛ ቤተ ክርስቲያን ከምሥራቃውያን አንዷ ነች ቤተ ክርስቲያናችን ሐዋርያዊትና ሲኖዶሳዊት ነች የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ፡- የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ እንደ ማንኛውም ጉባኤ አይደለም፤ የቤተ ክርስቲያን የበላይ መሪዎች ስብሰባ ነው፤ በመንፈስ ቅዱስ ስለሚመራ ቅዱስ ሲኖዶስ ተብሎ ነው የሚጠራው፤ ሰዎች የሰውን ልጅ ማን ይሉታል እንደተባለው፤ …

በጠቅላይ ጽ/ቤቱ ትግበራው የተጀመረው ዘመናዊው የኹለትዮሽ ሒሳብ አሠራር፣ በሥልጠና ተደግፎ ግልጽና ተጠያቂ በኾነ መንገድ እስከ አጥቢያ መዋቅር እንዲተገበር የጋራ አቋም ተይዟል ካለፈው ሰኞ ጀምሮ ላለፉት አራት ቀናት ሲካሔድ የቆየው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ 34ኛ ዓመታዊ መደበኛ ስብሰባ፣ ዛሬ ቀትር ላይ ተጠናቋል፡፡ የሀገር ውስጥ ኃምሳ አህጉረ ስብከት እና የውጭ ስምንት አህጉረ ስብከት የሥራ ክንውን …

በሀ/ስብከቱ÷ 55 ከእስልምና 115 ከሌሎች እምነቶች በጥምቀተ ክርስትና ተመልሰዋል   በመካከለኛው ምሥራቅ(በሊባኖስ እና የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ) ሀገረ ስብከት፣ በዱባይ ከተማ ቤሪያ በተባለ አካባቢ፣ በቤተ ክርስቲያን ስም የሚነግዱ የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ምንደኞች ከቅዱስ ሲኖዶስ ዕውቅና ውጭ ስለከፈቱት ኮሌጅ ውሳኔ እንዲሰጥ ሀገረ ስብከቱ ጠየቀ፡፡ ሀገረ ስብከቱ፣ ዛሬ ሦስተኛ ቀኑን በያዘው የመንበረ ፓትርያርክ የሰበካ አስተዳደር አጠቃላይ ጉባኤ 34ኛ ዓመታዊ …

“ሦስተኛ ሲኖዶስ አቋቁመዋል” በሚል ብፁዕ ሊቀ ጳጳሱን ለመክሠሥ ተዘጋጅተው ነበር “ቤተ ክርስቲያን ለ30 ዓመት በሰላም ኖራ እየተናወጠች ትገኛለች”/ሊቀ ካህናት መርዓዊ ተበጀ/ “መጥነው እንዲያወሩ ዕድል ቢሰጣቸው ተዋረዱ፤ የእግዚአብሔር ሥራ ነው”/ብፁዕነታቸው/   ከሦስት ዐሥርት ዓመታት በላይ በጀርመን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሓላፊነት ሲያገለግሉ የቆዩትና ከደቡብ ምሥራቅ እና ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት ጋር ውዝግብ ውስጥ የገቡት፣ ሊቀ …

 

ሰሞኑን የቀድሞው የደርግ ከፍተኛ ባለሥልጣን ሌ/ኮሎኔል ፍሥሐ ደስታ የጻፉትንና ‹አብዮቱና ትዝታዬ› የተሰኘውን መጽሐፍ ሳነብብ ስለ አቡነ ቴዎፍሎስ አሟሟት የጻፉትን አገኘሁ፡፡ ሌ/ኮሎኔል ፍሥሐ ደስታ እስካሁን ከጻፉት የቀድሞ ባለሥልጣናት በሁለት ነገር ተለይተውብኛል፡፡ የመጀመሪያው በቡድንና በጋራ ለሠሯቸው ስሕተቶች ይቅርታ መጠየቃቸው ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በሁሉም ወገኖች የተፈጠሩትን ያለፉትን ስሕተቶች ለማረም ያስችላል ያሉትን የጋራ መድረክ ሐሳብ ማቅረባቸው ነው፡፡
ምንም እንኳን በዘመነ ደርግ የተፈጠሩት ስሕተቶችና ጥፋቶች ደርግ ብቻውን ያደረጋቸው ባይሆኑም አንዱና ዋነኛው ተዋናይ ደርግ ነበርና ለተሠሩት ጥፋቶች ይቅርታ መጠየቃቸው ለሌሎች አካላትም አርአያነት ያለው ነው፡፡ ዋናው የደርጉ መሪ ያ ሁሉ ጥፋት ሲሠራ ‹እኔ አላውቅም ነበር›› ብለው በካዱበት ሁኔታ ሌ/ኮሎኔል ፍሥሐ ደስታ የራሳቸውን ይቅርታ መጠየቃቸው ለሰማዩም ለምድሩም ጉዟቸው ምትክ አልባ ተግባር የሚሆን ነው፡፡ ክብር ይስጥልን፡፡

ያ ዘመን በተሻለ እንመራለን ብለው የተነሡ ፖለቲካዊ ኃይሎች እንደየዐቅማቸው ስሕተቶችን የሠሩበትና ጥፋቶችን ያጠፉበት ዘመን ነው፡፡ ሁሉንም ጥፋት ለደርግ በመስጠት እጅን መታጠብ አይቻልም፡፡ እርሳቸው እንዳሉትም የደርግን ባለ ሥልጣናት ብቻ ወደ ፍርድ ከማቅረብ ይልቅ የነበረው ጥፋት ከየአቅጣጫው የሚፈተሽበትና ሁሉም እንደ ጥፋቱ የሚከሰስበት ወይም የሚወቀስበት አለበለዚያም ደግሞ ይቅርታ የሚጠይቅበት መንገድ ቢመቻች መልካም ነበር፡፡ ችግሩንም በተቻለ መንገድ ሊፈታው የሚችለው ሁሉን አቀፍ የሆነው አካሄድ ነበር፡፡ አሁንም መሪ ተዋናዮቹ ከማለፋቸው በፊት ሁሉም እንደየድርሻው ኃላፊነቱን የሚወስድበትና ይቅርታ የሚጠይቅበት ሥርዓት ቢመቻች መልካም ነበር፡፡
ያ ካልሆነ ግን ሥርዓት በተቀየረና ሕጎች በተሻሻሉ ቁጥር ተከድነው የሚንተከተኩ ነገሮች እንደገና የመውጣታቸውና በመድረቅ ላይ ያሉ ቁስሎችን የማመርቀዝ ዕድላቸው ሰፊ ነው፡፡ ፕላስተር የተለጠፈበት ቁስል ሁሉ አይድንምና፡፡
ሌ/ኮሎኔል ፍሥሐ ደስታ በጻፉት መጽሐፍ ላይ ግን ጥያቄ እንዳነሣ ያደረገኝ አንድ ጉዳይ አለ፡፡ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስን የተመለከተ፡፡ በመጽሐፉ ላይ የሚከተሉት ነገሮች ከብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ መገደል ጋር ተያይዘው ቀርበዋል፡፡
1.      1. ቤተ ክህነት መሬቷ ስለተነጠቀ አብዮቱን እንደተቃወመች

እግዚአብሔር የለም ብሎ የሚክደው ኮሚንስታዊ መንግሥት ሲመጣ ቤተ ክህነት ባትቃወም ነበር የሚገርመው፡፡ በተለይም የመሬት ለአራሹ አዋጅ የጭሰኛውን የዘመናት ጥያቄ የመለሰ ቢሆንም የፈጠራቸውም ጥያቄዎች ነበሩ፡፡ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የተመሠረተው በመሬት ላይ በመሆኑ አብያተ ክርስቲያናትና ገዳማትም የመተዳደሪያ መሬት ነበራቸው፡፡ ልክ ዛሬ የመተዳደሪያ ሕንጻና ገንዘብ እንዳላቸው ሁሉ፡፡ ነገሥታቱና መኳንንቱ አብዛኞቹ ክርስቲያኖች ስለነበሩም ለቤተ ክርስቲያን የመሬት ስጦታ ሰጥተዋል፡፡ የመሬት ላራሹ ዐዋጅ ሲታወጅ ግን የካህናትንና የገዳማውያን ሁኔታ ግምት ውስጥ ሊያስገባ አልቻለም፡፡ እንደ አንድ በመሬት የሚተዳደር ኢትዮጵያዊ ዜጋ ካህናቱና መነኮሳቱ ለአንድ ገበሬ የተመደበውን መሬት እንዲያገኙ እንኳን አልተደረገም፡፡ በቤተ ክርስቲያን ስም መኳንንቱ ይዘውት የነበረው  መሬት ከግምት ውስጥ አልገባም፡፡ ቢያንስ በቶፍነት ሥርዓት ውስጥ የነበሩትን ካህናት እንኳን አብዮቱ ሊያያቸው አልፈቀደም፡፡ ሲሆን ቅርስና ባሕል ጠባቂ እንደመሆናቸው በተለይ ገዳማቱ ተጨማሪ የጋራ መሬት ያስፈልጋቸው ነበር፡፡ የወቅቱ የደርግ ባለሥልጣናት ግን ቤተ ክርስቲያኒቱን ከመጀመሪያው በጠላትነት ስለፈረጁ የድርሻዋን እንኳን ለመስጠት አልቻሉም፡፡ በምዕራብ ሸዋ የነበረው ደብረ ጽሙና ገዳም መሬቱን ሙሉ በሙሉ አጥቶ ሊፈርስ ሲል ኮሎኔል ደበላ ዴንሳ በሰጡት መመሪያ ጥቂት መሬት አግኝቶ መትረፉን አረጋውያኑ ዛሬም ከምስጋና ጋር ያስታውሱታል፡፡
ገዳማትና አድባራቱ ከልክ በላይ የያዟቸው መሬቶች ከነበሩ መጠኑን መቀነስና በቂ ነው የተባለውን ያህል መስጠት እንጂ ያላቸውን በሙሉ ነጥቆ በድህነት እንዲማቅቁ ማድረግ በምንም መልኩ ፍትሐዊ ሊሆን የማይችል ነው፡፡ ‹‹ኮሚኒዝም ማለት ድህነትን እኩል ማካፈል ነው – an even distribution of poverty›› የተባለው ነው የተፈጸመው፡፡ ፍትሐዊነት ያላገኘውን አካል እንዲያገኝ አድርጎ እኩል ማድረግ እንጂ ያገኘውን እንዲያጣ አድርጎ በድህነት ማስተካከል አይደለም፡፡ ይኼንን የወቅቱ ቤተ ክህነት ብትቃወመውና ከአብዮቱ ጋር ለመጓዝ ቢቸግራት ተገቢ ነው፡፡ ያውም በበቂ ሁኔታ አልሄደችበትም፡፡ አቡነ ቴዎፍሎስ በ1967 ዓም ለዘመን መለወጫ ባስተላለፉት መልእክት ‹‹በጦር ኃይሉና በሕዝቡ የተጀመረው የተቀደሰ እንቅስቃሴ መልካም ውጤት እንዲያስገኝ ፈጣሪያችን ይርዳን›› ነበር ያሉት፡፡(ሐዲስ ሕይወት፣ ግንቦት 1፣ 1967 ዓም፣ ገጽ 17)፣ የዕድገት በኅብረት ዘመቻንም ፓትርያርኩ በበጎ ነበር ያዩት፤ ይህም ጥቅምት 3 ቀን 1967 ዓም በሰጡት መግለጫ ላይ ተመልክቷል፡፡(ገጽ 17)
ይኼ ጉዳይ በከተማ ቦታና ትርፍ ቤት ዐዋጁም ጊዜ ተከሥቷል፡፡ ብዙ ምእመናን ብጽዐት ገብተው እየሠሩ፣ ሲሞቱም እያወረሱ ለአድባራትና ገዳማት የሰጧቸው ቤቶች ነበሩ፡፡ እነዚህ ቤቶች በሀገር ቤት ብቻ ሳይሆን በኢየሩሳሌም ከተማ ሳይቀር ይገኙ ነበር፡፡ የከተማ ቦታና ትርፍ ቤት ዐዋጅ ሲታወጅ ግን ለአንድ ሰው የሚኖርበት የ500 ካሬ ሜትር ቦታና አንድ ቤት ሲፈቅድ ለአድባራትና ገዳማት ግን ምን አልተፈቀደም፡፡ በሙሉ ነው የተወረሰው፡፡ ራሳቸው ፍሥሐ ደስታ እንደመሰከሩት ዐዋጁ ጠላ ሽጣ፣ ማገዶ ቸርችራ ድኻዋ የሠራቺውን፣ ኮርያና ኮንጎ ዘምተው ባገኙት የደም ዋጋ መለዮ ለባሾች የገነቡትን ሁሉ ሀብት ከተትረፈረፋቸው ጋር እኩል በመውረሱ ‹‹ብዙዎች አብዮቱን የደገፉ ጭቁኖች ከበዝባዦች ጋር አብዮቱን ያጥላሉ ጀመር››(ገጽ 160)፡፡
ከነዚህ በዐዋጁ ከተጎዱት መካከል አብያተ ክርስቲያናቱ አንዱ ናቸው፡፡ ቢያንስ የተወሰነውን ቤት እንዲያገኙ መደረግ ነበረባቸው፡፡ ነገር ግን ቤተ ክርስቲያኒቱን ደርግ የተመለከተበት መነጽር ችግሩን እንዳያይ የሚጋርደው ነበር፡፡ ለዚህም ነው ቤተ ክህነት ለውጡን በበጎ ልታየው ያልቻለቺው፡፡ በርግጥ መንግሥት 4 ሚሊዮን ብር ምትክ ካሣ ሰጥቻለሁ ብሎ ነበር፡፡ በጎላ ወስዶ በጭልፋ መመለስ ማለት እንዲህ ነው፡፡ ያውም አራት ሚሊዮን ብሩ ሳይጨመር ሳይቀነስ በደርግ ዘመን ሁሉ የኖረ ነው፡፡
አቡነ ቴዎፍሎስ በ60ው ባለ ሥልጣናት የግፍ ግድያና በንጉሠ ነገሥቱ ሞት በእጅጉ አዝነው ነበር፡፡ የንጉሠ ነገሥቱን አስከሬን ወስደው በክብር ለመቅበር በነሐሴ 1967 ዓም ደርግን ጠይቀው አልተፈቀደላቸውም፡፡ ከዚህም አልፎ ለንጉሠ ነገሥቱ በይፋ የፍትሐት ጸሎት እንዳያደርጉም ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው(ፍሥሐ ደስታና ሌሎችም ቢዘሉትም)፡፡ አቡነ ቴዎፍሎስ ከዚህ በኋላ ነው ለውጡን በሥጋት ማየት የጀመሩት፡፡
2     2. አቡነ ቴዎፍሎስ የራሳቸውን ወገኖች በመሾም በአብዮቱ ላይ ውስጥ ውስጡን ሤራ እንደሠሩ
አቡነ ቴዎፍሎስ የራሳቸውን ሰዎች ሾሙ ያሰኛቸው ሦስት አባቶችን በጵጵስና መሾማቸው ነው፡፡ ደርግ መንግሥትና ቤተ ክርስቲያን ተለያይተዋል፤ እንዱ በሌላው ጣልቃ አይገባም ብሎ ዐወጀ፡፡ ፓትርያርኩ ይህንን ተከትለው ደርግን ሳይጠይቁ ሦስት አባቶችን ሾሙ፡፡ አቡነ ጳውሎስን፣ አቡነ ባስልዮስና አቡነ ጴጥሮስን፡፡ ሦስቱም አባቶች በነበራቸው ዕውቀት የተሾሙ እንጂ ለአቡነ ቴዎፍሎስ በነበራቸው ዝምድና አልነበረም፡፡ በሀገር ልጅነትም ሆነ በዝምድና አይገናኟቸውም ነበር፡፡ ደርግን ተደፈርኩ አስብሎ ፓትርያርኩን እንዲያሥር ያደረገው ይኼ የፓትርያርኩ ሳያስፈቅዱ መሾማቸው ነው፡፡ ያሠረውም ፓትርያርኩንና አዲስ የተሾሙትን ኤጲስ ቆጶሳትን ነው፡፡  
3  3. አቡነ ቴዎፍሎስን በተመለከተ የቤተ ክህነት ሰዎች ለመንግሥት አቤቱታ አቅርበው ነበረ ፡፡
  በሌ/ኮሎኔል ፍሥሐ ደስታ መጽሐፍ ላይ የቤተ ክህነት ሰዎች አቡነ ቴዎፍሎስን በተመለከተ ያቀረቧቸው ክሶችና አቀራረቡን ገልጠውታል፡፡ የመጀመሪያው ክስ አቡነ ቴዎፍሎስ አባ መልእክቱ ተብለው መነኩሴ እያሉ በአቡነ ጴጥሮስ ግድያ ላይ እጃቸው አለበት የሚለው ነው፡፡ አቡነ ቴዎፍሎስ ወደ አዲስ አበባ ከቤተሰቦቻቸው ጠፍተው የመጡት በ1920 ዓም ነው፡፡ የሄዱትም በአዲስ ዓለም ማርያም ወደነበሩት ሐዲስ ተክሌ ዘንድ ነው፡፡ ሐዲስ ተክሌ በቀለም አያያዛቸው ስለወደዷቸው አቀረቧቸው፡፡ አባ መልእክቱ ከአዲስ ዓለም ወደ ደብረ ሊባኖስ ሄደው በ1930 መነኮሱ፡፡ ጣልያን ሀገሪቱን ሲወር እርሳቸው የመምህራቸው የሐዲስ ተክሌ ደቀ መዝሙር ሆነው በአዲስ አበባ ነበሩ፡፡
በወቅቱ የነበሩት አባቶች የጣልያን ወረራን በተመለከተ ሁለት ዓይነት ሐሳብ ነበራቸው፡፡ እንደ ሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስና አቡነ ሚካኤል ያሉት ከዐርበኞች ጋር ሆነው ጣልያንን ለመፋለምና ሀገሪቱን ነጻ ለማውጣት ወሰኑ፡፡ ሌሎች አባቶች ደግሞ ሕዝቡ ያለ እረኛ መቅረት የለበትም የሚለውን ሐሳብ ደግፈው የሊቃውንት ጉባኤ በማቋቋም ወደ ሀገራቸው የሄዱትን  ግብጻዊውን አቡነ ቄርሎስን ተክተው መሥራት ጀመሩ፡፡
አቡነ ቴዎፍሎስ የአቡነ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር እንደመሆናቸው መምህራቸውን ተከትለው ከማገልገል ያለፈ በአቡነ ጴጥሮስ ላይ በተፈጸመው ግፍ እጃቸው ነበረበት የሚል ምንም ዓይነት ማስረጃ እስካሁን አልቀረበም፡፡ ደግሞም በዚያ ጊዜ በነበራቸው ሁኔታ ይህንን ለመፈጸም የሚበቃ ሥልጣን አልነበራቸውም፡፡ የጠሉትን ሰይጣን፣ የወደዱትን መልአክ ማለት ልማድ ሆኖ ጠላቶቻቸው ለውጡን ተጠቅመው ለጥብስ አቀረቧቸው እንጂ ማስረጃ ሊያቀርቡበት የሚችሉበት ነገር አልነበረም፡፡ ደርግም ማስረጃ አልጠየቀም፤ ለማጣራትም አልሞከረም፡፡ ሌ/ ኮሎኔል ፍሥሐም አገላለጣቸው ‹ቤተ ክህነቱ ስለከሰሳቸው አሠርናቸው እንጂ ነገሩ ከኛ አልመጣም› ዓይነት ነው፡፡ የአቡነ ቴዎፍሎስን ሕይወት የቀጠፈው ግን ክሱ ሳይሆን ‹ከፍርድ በፊት ወንጀለኛ የሚያደርገው› የደርግ አሠራር ነበር፡፡ በዚያ ላይም ሳያስፈቅዱኝ ሾሙ ብሎ ደርግ ምክንያት ፍለጋ ላይ ነበር፡፡
ሁለተኛው ክስ ‹በቤተ ክህነት ሤራና አሻጥር ይሠራሉ› የሚለው ነው፡፡ ምን ዓይነት ሤራና አሻጥር እንደሆነ አልተገለጠም፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ ለውጥ በመጣ ቁጥር ሰውን የመክሰሻ ቀላሉ መንገድ ‹ለውጡን ይቃወማል፣ ያለፈውን ሥርዓት ይደግፋል፣ ውስጥ ውስጡን አድማ ይመታል› የሚሉት አቤቱታዎች ናቸው፡፡ ምግቡን ለበዪው እንዲስማማ አድርጎ ማቅረብ፡፡ ይህንን እንድገምት ያደረገኝ ክሱን ያቀረቡትን አካላት በተመለከተ ኮሎኔሉ የሰጡን መረጃ ነው፡፡ ‹ዘጠና በመቶ የሚሆኑት ገዳማት ፈርመውበት ነበር›(ገጽ 199) ይላል፡፡
እጅግ አስገራሚ መረጃ ነው፡፡ ሳይበጠር ይከካ፣ ሳይለቀም ይፈጭ እንደነበር የሚያሳይ፡፡ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በ1972 ዓም ባካሄደው የሰበካ ጉባኤ ቆጠራ የኢትዮጵያ ገዳማት ቁጥር 1000 እንደነበረ ያመለክታል፡፡(ከ1966-1972 ባለው ጊዜ እንኳን አዲስ የሚቋቋምበት ያሉትም በፕሮፓጋንዳውና በለውጡ እየተንገዳገዱ ነበር) ያ ዘመን እንዳሁኑ መንገድ ያልተስፋፋበት፣ ሞባይል ስልክ የሌለበት ጊዜ ነው፡፡ ወቅቱም የግርግር በመሆኑ ገዳማውያን ከበኣታቸው እንዲወጡ የሚያበረታታ አይደለም፡፡ በዚህ ላይ ራሳቸው ፍሥሐ ደስታ እንደነገሩን ገዳማቱ ሁሉ መሬታቸውን ተወርሰዋል፡፡ እንዴት ሆነው ነው በአብዮቱ ቅር የተሰኙ 900 ገዳማት ተገናኝተው በአቡነ ቴዎፍሎስ ላይ ሊፈራረሙ የሚችሉት? በየቦታቸው ሆነው ፈረሙ ቢባል እንኳን ማነው በዚያ ዘመን ከዋልድባ እስከ ማንዳባ፣ ከደብረ ዳሞ እስከ ደብረ ወገግ፣ ከማኅበረ ሥላሴ እስከ ዝቋላ፣ ከደብረ ቢዘን እስከ ደብረ ሊባኖስ ተዘዋውሮ ገዳማቱን ሊያስፈርም የሚችለው(ያውም ያኔ የኤርትራንም ገዳማት ይጨምራል)፡፡ ገዳማቱ ያሉበት አስቸጋሪ አካባቢ፣ የገዳማቱ ብዛትና የወቅቱ ሁኔታ ተደምሮ 10 በመቶ ገዳማት እንኳን ሊፈርሙ አይችሉም፡፡ አብያተ ክርስቲያናቱ ናቸው የፈረሙት እንዳንል እንኳን እነርሱም ቁጥራቸው በ1972 ዓም ከ25 ሺ በላይ ነበሩ፡፡ ፈጽሞ ሊሆን የማይችል ነው፡፡
የአቡነ ቴዎፍሎስ ሞትና አሟማት አሁንም ያልተፈታ ጉዳይ ነው፡፡ በሞታቸውና አሟሟታቸው ሦስት አካላት የነበራቸው ሚና አሁንም በሚገባ መፈተሽ አለበት፡፡ ቤት ክህነት(ከጳጳሳት ጀምሮ)፣ ደርግና ሌሎች አካላት(ለምሳሌ አስያዛቸው የሚባለው ሰው እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ጎፋ አካባቢ ነበረ)፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቱ የእኒህን አባት ሁኔታ በሚገባ ማጣራት ይኖርባታል፡፡ አንድም ዋና ተዋንያን የነበሩት የቤተ ክህነትና የቤተ መንግሥት ሰዎች መረጃውን ይዘውት ጨርሰው ከማለፋቸው በፊት፤ ሁለት ቤተ ክህነቱንም ሆነ ደርግን የሚያስወቅስ ያልተሰማ መረጃ ነገ ከመውጣቱና ማጣፊያው ከማጠሩ በፊት፡፡ ቤተ ክህነት አንድ አጣሪ አካል አቋቁማ ታሪኩ የተጣራ እንዲሆን ማድረግ አለባት፡፡ የአብዮቱን ዘመን ታሪክ የምትነግሩን አካላትም መጻፋችሁ የሚያስመሰግናችሁ ቢሆንም የምትሰጡን መረጃ ግን እውነትና ሊታመን የሚችል ቢሆን በታሪክ ውስጥ የሚኖራችሁን ሥፍራ ምቾት የሚሰጠው ይሆናል፡፡
የአቡነ ቴዎፍሎስን አሟሟት በተመለከተ ሻለቃ ፍቅረ ሥላሴ ወግደረስም ሆኑ ሌ/ኮሎኔል ፍሥሐ ደስታ በሁለተኛው እትሞቻቸው የሚያብራሩት ነገር ሊኖር ይገባል፡፡ አዲስ እየጻፋችሁ ያላችሁም አስቡበት፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ፡- ቤተ ክርስቲያናችንን ከሌሎች አብያተ ክርስቲያናት በቊጥር እጅግ የላቀ የውሉደ ክህነት ብዝኅነት ያላት ስትኾን ስብከተ ወንጌልን ለውሉደ ሰብእ በማዳረስ ረገድ ያለን ውጤት ግን አናሳ ነው ማለት ይቻላል ባሕርን አቋርጦ፣ ድንበርን ተሻግሮ እስከ ጽንፈ ምድር ተጉዞ፣ አስተምሮና ያላመነውን አሳምኖ የቤተ ክርስቲያን ልጅ ማድረጉ ይቅርና በሀገር ውስጥ ያሉትን ወገኖች በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አሰባስቦ ምእመናንን ማብዛት …

የሥርዐት ለውጡ÷ ጽ/ቤቱ፣ ከሐምሌ 2002 – ሰኔ 2005 ዓ.ም. ያለውን የሒሳብ አሠራሩን በውጭ ኦዲተሮች ካስመረመረ በኋላ የተሰጠውን አስተያየት ተከትሎ የተካሔደ ነው የፋይናንስ ፖሊሲው እና ማኑዋሉ፣ የቤተ ክርስቲያንን የምጣኔ ሀብት እና የሙዓለ ንዋይ አስተዳደር መመሪያዎች በሚያወጣው በቅዱስ ሲኖዶስ ተመርምሮ የተወሰነ ነው ከኹለትዮሽ የአመዘጋገብ ሥርዐት ጋር ጽ/ቤቱ በተከተለው ማእከላዊ የበጀት አሠራር (budget centralization)፤ ወጪ ቆጣቢ፣ ውጤታማ እና …

የቤተ ክርስቲያን ተረካቢ የሰንበት ት/ቤቶች ወጣቶች÷ በአህጉረ ስብከትና በሀገር አቀፍ ደረጃ የአንድነት መድረክ በመፍጠር፣ በፀረ ፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ኑፋቄና በፀረ ሙስና ንቅናቄ፣ ለዕቅበተ እምነትና ለመልካም አስተዳደር መስፈን በየአጥቢያቸው ተጋድሏቸውን በአቀጣጠሉበት በአሁኑ ወቅት፤ ራሱን ከአማሳኞችና ከአፅራረ ቤተ ክርስቲያን ምንደኞች ጎራ በገሃድ አሰልፎ በሥልጣን ለመሰንበትና ምዝበራውን ለማጧጧፍ ለሚወራጨው የየማነ ዘመንፈስ ቅዱስ የሀገረ ስብከት አስተዳደር፣ ወጣቶቹን በማሳደድና በመበተን እኩይ …

እስከ 360 ሺሕ ብር ከፍተኛ ውዝፍ ያለባቸው ተከራዮች እንደሚገኙበት ታውቋል በቤተ ዘመድ የተሸፋፈነው የክፍያው አሰባሰብ የአስተዳደር ጉባኤ አባላቱን አወቃቅሷል በፍሳሽ እና በቃጠሎ አደጋ የተጎዳው ሕንጻ ከዕድሳት ዕጦት ደኅንነቱ ለአደጋ ተጋልጧል *          *          * ሓላፊው፣ በደንቡ መሠረት ለአስተዳደር ጉባኤው የሒሳብ ሪፖርት አቅርበው አያውቁም የበጀት ዓመቱ የኻያ በመቶ የፈሰስ …

(አዲስ አድማስ፤ ቅጽ 16 ቁጥር 821፤ ቅዳሜ መስከረም 29 ቀን 2008 ዓ.ም.) የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ሰርቪስ(ኢቢኤስ)፤ በሳምንት አንድ ቀን በጣቢያው መንፈሳዊ ዝግጅት የሚያስተላልፉ ሃይማኖታዊ ፕሮግራሞች፣ የታደሰ የፈቃድ ማስረጃዎቻቸውን እንዲያስገቡ አስቸኳይ ትእዛዝ ሰጠ፡፡ የቴሌቪዥኑ ፕሮግራሚንግ ኮሚቴ መስከረም 21 ቀን 2008 ዓ.ም. ለአራት የሃይማኖታዊ ፕሮግራም ክፍሎች በጻፈው ደብዳቤ፤ ከጣቢያው ጋር በገቡት ውል መሠረት ለሚወክሉት የሃይማኖት ተቋም ወይም የሃይማኖት …

ገዳሟን ለችግር የዳረጉት ጥበቃና ክብካቤ እየተደረገላቸው፣ ሰበካ ጉባኤው እንዳይሠራ ተደርጓል ለጠቅላላ ጉባኤው ሪፖርት ለማቅረብ ጽ/ቤቱ ቢጠየቅም ሌላ የሰበካ ጉባኤ ምርጫ ተካሒዷል የገዳሟ ሒሳብ በውጭ ኦዲተር እንዲጣራ በፓትርያርኩ የተሰጠው ትእዛዝ ተግባራዊ አልኾነም ፓትርያርኩ፣ ወደ ተግባራዊ የፀረ ሙስና እና የመልካም አስተዳደር ርምጃ እንዲገቡ ተጠይቋል *          *          * በ7 ወራት ሒሳብ የቅድመ ኦዲት ዳሰሳ ብቻ ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ …

አንጋፋው ጋዜጠኛና ደራሲ ሙሉጌታ ሉሌ በድንገት ከዚህ አለም በሞት ተለየ። በትላንትናው እለት ከቀትር በኋላ እኔ ጋዜጠኛ ተስፋዬ ተሰማና ጋሽ ሙሉጌታ በሲልቨር ስፕሪግ ምሳ በልተን፣ ስለመፅሀፍ እያወራን ከዋልን በኋላ በሰላም ነበር የተለያየነው። በዛሬው እለት ግን ቨርጂኒያ በሚገኘው መኖሪያ ቤቱ በተኛበት ህይወቱ …

ጋዜጠኛ ሙሉጌታ ሉሌ ከዚህ አለም በሞት ተለየ Read more »

የአ/አበባ ጎልማሶችና ወጣቶች ማኅበራት ኅብረት ተቃውሞውን ያስተባብራል ለተቃውሞው፣ በሰባት ቀናት ከ100 ሺሕ በላይ የድጋፍ ፊርማዎች ተሰባሰቡ የጥቅምቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ እንዲወስንበት ለማድረግ ታቅዷል “በማስረጃ ተደግፎ የሚቀርብ ነገር ካለም እርምት እንወስዳለን” /የጣቢያው ሓላፊ/ (ምንጭ: አዲስ አድማስ፤ ቅጽ ፲፮ ቁጥር ፰፻፳፤ ቅዳሜ መስከረም ፳፪ ቀን ፳፻፰) በኢትዮጵያን ብሮድካስቲንግ ሰርቪስ (EBS) ቴሌቪዥን በሚተላለፉት “ታዖሎጐስ” እና “ቃለ ዐዋዲ” …


(ክፍል ሁለት)
1.   ተአምራት ማድረግ የምን ውጤት ነው? ተአምራት ማድረግ ከሁለት ነገሮች ሊመጣ ይችላል፡፡ ከመንፈሳዊ ብቃትና ከሰይጣን አሠራር፡፡ በክርስትና ሕይወቱ የበረታ ሰው መንፈሳዊ ብቃቱ በሕይወቱ በሚገለጡ ተአምራት ሊታወቅ ይችላል፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን የምናገኛቸው ቅዱሳን በገድል ተቀጥቅጠው፣ ሰማዕትነት ከፍለው፣ በመንፈሳዊ ሕይወታቸው በሚገባ ተጉዘው ዲያብሎስን ድል ሲነሡት በሕይወታቸው ውስጥ ተአምራት ይገለጣሉ፡፡ ይህም ማለት ተአምራት የመንፈሳዊ ብቃት መገለጫ ነው ማለት ነው፡፡ የተአምራት ስጦታ እንዲሁ በድንገት አይገለጥም፡፡ በዚያ ክርስቲያን ሕይወት ውስጥ እያደገ፣ እየተገለጠና እየተመሰከረለት በሚመጣ መንፈሳዊ ዕድገት ምክንያት እንጂ፡፡ ለዚህ ሁለት ምሳሌዎች እናንሣ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስና አቡነ ተክለ ሃይማኖት፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ በሐዋርያት ሥራ ውስጥ አራት ምዕራፍ ያለው መንፈሳዊ ዕድገቱ በየዘመናቱ ተገልጦልናል፡፡ በፍኖተ ደማስቆ መመለሱ(የሐዋ8)፤ በአንጾኪያ በሱባኤ መኖሩ(የሐዋ13)፣ ለአገልግሎት ተጠርቶ ከበርናባስ ጋር መውጣቱ እና ከአረማውያን፣ ከአይሁድና ከመናፍቃን ጋር ባደረገው ተጋድሎ የምናገኘው በትምህርትና በተአምራት የተገለጠ ሕይወቱ ናቸው፡፡ የቅዱስ ጳውሎስ ሕይወት ቀስ በቀስ እያደገ (ወየሐውር እም ኃይል ውስተ ኃይል እንዲል) የመጣ ነው፡፡

የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ሕይወት በመንፈሳዊ ትምህርት፣ በአካባቢያዊ ተጋድሎ፣ ገዳማትን በመሳለምና በመማር፣ ወንጌልን ለአረማውያን በማስተማር እየተገለጠ የመጣ የማያቋርጥ መንፈሳዊ ዕድገት የነበረው ነው፡፡ ክርስትና ደንገቴ ሊሆን አይችልም፡፡(ለ&