ታኀሳስ ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከክረምቱ መግባት ጀምሮ በከተማዋ በተደጋጋሚ የሚታየው የመብራት መቆራረጥ ነዋሪውን ያስመረረ ሲሆን፣ በአስቸኳይ ጥገና መስክ የተሰማሩት ሰራተኞች የሚጠቀሙበት መኪና ከአስርት አመታት በፊት የነበረ አሮጌ ከመሆኑም በላይ በቁጥርም አንድ ብቻ መሆኑ ስራውን እንዳወሳሰበው ባለሙያዎቹ ተናግረዋል፡፡ የደንበኞች ቁጥር እየበዛ በሄደ ቁጥር ያሉት ገመዶች የኤሌክትሪክ ኃይሉን መሸከም ባለመቻላቸው መቀየር ሲገባቸው …

በሰሜን አሜሪካ በዋሽንግተን ዲሲና በምኒያፖሊስ ምኒሶታ ነዋሪ የሆኑ የክልሉ ተወላጆችም ለኦሮሞ ተማሪዎች ያላቸውን አጋርነት በሰላማዊ ሰልፍ፣በሻማ ማብራትና በተለያዩ የውይይት መድረኮች በመግለፅ ላይ ናቸው።

Finote Democracy Voice of #Ethiopia n Unity Satellite Radio News ታኅሣሥ 12 ቀን 2008 ዓ.ም. (December 22, 2015) – የወያኔ ቁንጮዎች በሕዝብ ላይ ተመጣጣኝ ያልሆነ እርምጃ የወሰዱትና ያስወሰዱት የኦህዴድ አመራሮች ናቸው በማለት ከሰሱ – የኦህዴድ አመራሮች የተሰነዘረባቸውን ክስና ውንጀላ በግልጽ …

የወያኔ ቁንጮዎች በሕዝብ ላይ ተመጣጣኝ ያልሆነ እርምጃ የወሰዱትና ያስወሰዱት የኦህዴድ አመራሮች ናቸው በማለት ከሰሱ – የኦህዴድ አመራሮች መቃወምና መከራከር ጀምረዋል Read more »

ኢትዮጵያዊው ሙስሊም የፍርሀት ድባቡን አሸንፎ ለአራት ዓመታት በትግል ጎዳና ላይ ፀንቷል! ረቡእ ታህሳስ 13/2008 አምባገነን ስርዐቶች የህዝቦችን መብት በማክበር፣ ነፃነታቸውን በመጠበቅ፣ ለጥያቄዎቻቸው ምላሽ፣ለችግሮቻቸው መፍትሄ በመስጠት ህዝብን ከጎናቸው ከማድረግ ይልቅ የፍርሀትን ድባብ በመፍጠር ህዝብ አንገቱን ደፍቶና ተሸማቆ በፍርሀት ታፍኖ እንዲኖር ማድረግን …

ኢትዮጵያዊው ሙስሊም የፍርሀት ድባቡን አሸንፎ ለአራት ዓመታት በትግል ጎዳና ላይ ፀንቷል! (ድምፃችን ይሰማ) Read more »

በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ትራንስፖርት መስመር ዝርጋታ በመሬት ውስጥ ለማከናወን፣ ሲባል ከነባር ስፍራው ተነሥቶ የነበረው የሰማዕቱ ቅዱስ አቡነ ጴጥሮስ ሐውልትን ከነበረበት ቦታ መልሶ ለመትከል የመሠረት ግንባታ ተጀመረ፡፡ የሐውልቱን መሠረት ግንባታ የሚያካሂደው አሰር ኮንስትራክሽን መሆኑን የተናገሩት የአዲስ አበባ መንገዶች ባለሥልጣን ዋና …

የሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስ ሐውልትን መልሶ ለማቆም የመሠረት ግንባታ ተጀመረ Read more »

Habtamu ayalew . abrha desta .yeshiwas . daniel shibeshi in Ethiopian Prison

የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት ነሐሴ 14 ቀን 2007 ዓ.ም. በሰጠው ውሳኔ፣ ከተጠረጠሩበት የሽብር ወንጀል መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነፃ እንዲሰናበቱ የተደረጉት፣ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ አመራሮች አቶ ሐብታሙ አያሌውና አቶ ዳንኤል ሺበሺ፣ የአረና ፓርቲ አመራር የነበሩት አቶ …

የሰማያዊና አንድነት ፓርቲዎች አመራሮች የነበሩ ተከሳሾች ሰብሳቢ ዳኛው እንዲነሱ ጠየቁ Read more »

ሰመጉ ይህን ያስታወቀው ‹‹ከአዲስ አበባና ከኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ ማስተር ፕላን ተቃውሞ እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ የሚፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በአስቸኳይ ይቁሙ›› በሚል ርዕስ ታኅሳስ 11 ቀን 2008 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ አማካይነት ነው፡፡ ሰመጉ በመግለጫው የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ለተቃውሞ በወጡ ዜጎች …

በኦሮሚያ ክልል የደረሰውን ጉዳት የሚያጣራ ገለልተኛ አካል እንዲቋቋም ሰመጉ ጠየቀ Read more »

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) እና ሰማያዊ ፓርቲ የፊታችን እሑድ ታኅሳስ 17 ቀን 2008 ዓ.ም. ለማድረግ ያሰቡት ሰላማዊ ሠልፍ እንደማይካሄድ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ድሕፈት ቤት አስታውቋል፡፡ በመድረክ አማካይነት የዕውቅና ጥያቄ የቀረበለት ሰላማዊ ሠልፍ፣ ሰሞኑን በኦሮሚያ ክልል ውስጥ …

መድረክ እና ሰማያዊ ያሰቡት ሰላማዊ ሠልፍ ዕውቅና መስጠት መቸገሩን የአዲስ አበባ ከንቲባ ድ/ቤት አስታውቋል፡፡ Read more »

በኦሮሚያ ክልል የተፈጠረው ግጭት ጉዳቱ ከባድ መሆኑ ተጠቆመሆኖም ግጭቱን ሙሉ በሙሉ ለማስወገድና ኦሮሚያን ወደ ነበረችበት የመመለስ ሥራ በመካሄድ ላይ እንደሆነ ታውቋል፡፡ በግጭቱ ምክንያት ከባድ ጉዳት መድረሱ እየተነገረ ነው፡፡ የደረሰውን የጉዳት መጠን አስመልክቶ ከመንግሥት እስካሁን ይፋዊ መግለጫ ባይሰጥም፣ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች …

በኦሮሚያ ክልል የተፈጠረው ግጭት ጉዳቱ ከባድ መሆኑ ተጠቆመ Read more »

የኢትዮጵያ ብሄራዊ አንድነት ፓርቲ ፕሬዝደንት አቶ ዘሪሁን ገ/እግዚያብሄር የህክምና አገልግሎት እንዳያገኝ መደረጉን ቤተሰቦቹ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡ አቶ ዘሪሁን ገ/እግዚያብሄር በማዕከላዊ በደረሰበት ድብደባ እጁ፣ እግሩና ጆሮው ላይ ጉዳት የደረሰበት ቢሆንም ህክምና እንዳያገኝ መደረጉን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡ አቶ ዘሪሁን በማዕከላዊ እጁን ታስሮና …

የፀረ ሽብር አዋጁ በወጣ በወራት ውስጥ ከታሰሩት ፖለቲከኞች አንዱ ዘሪሁን ገ/እግዚያብሄር ህክምና እንዳያገኝ መደረጉ ተገለፀ Read more »

የህንዱ ካሩቱሪ ግሎባል ሊሚትድ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተበደረውን 55.8 ሚሊዮን ብር አልከፍልም ስላለ የወሰደውን 100 ሺሕ ሔክታር፣ መጋዘን፣ የሠራተኞች ተገጣጣሚ ቤትን ለጨረታ ቢያቀርብም እስካሁን በሃራጅ ተሽጦ ባንኩ ሊያገኘው የቻለው 2.6 ሚሊዮን ብር ብቻ ነው። የካሩቱሪ ዳይሬክተር ራማክሪሽና ካሩቱሪ ለ100 ሺህ ሔክታር ሊዝ መሬት አንድ ጊዜ የሚከፈል 5.6 ሚሊዮን ዶላር በባንክ እንዳይከፍል ታዞ በጥሬ ገንዘብ ጉዳዩ […]

በኦሮሚያ ክልል አሰላ ከተማ፣ በጉጂ ዞን፣ በሃርቀሎ ወረዳና በሆሮ ጉዱሩ፤ በወለጋ ኢበንቱ ወረዳ ተማሪዎችና ነዋሪዎች ድብደባ እየተፈፀመባቸውና በመከላከያ አባላት እየታሠሩ መሆናቸውን እየተናገሩ ነው፡፡

ታኀሳስ ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከአሁን በፊት የባህርዳር ነዋሪዎች ባህርዳር ላይ የሚገኘው የአባይ ድልድይ ችግር አጋጥሞታል በማለት በልዩ ልዩ ስብሰባዎች ቢያሳስቡም የገዢው መንግስት አመራሮች በቅርቡ ተለዋጭ ይሰራል በማለት ሲሸነግሉ ቆይተዋል። ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ጀምሮ የድልድዩ ወደ ሰሜን መውጫ ክፍል ላይ ያለው ንጣፍ ዝቅ እያለ በመሄዱ ከቅዳሜ ጠዋት ጀምሮ በቦታው የፌደራልና …

አኩሪ አተርን በተለያየ መንገድ ለምግብነት በርካቶች ይጠቀሙበታል። ከምሥራቅ እስያ አካባቢ መገኘቱ የሚገርለት ይህ የእህል ዘር በፕሮቲን የበለፀገ በመሆኑ ለተለያዩ የተመጣጠኑ ምግቦች ዝግጅት ሲዉል ዓመታት ተቆጥረዋል።

በሰሜን ጎንደር የጭልጋ የቋራ እና የመተማ ሕዝብ እርቀ ሰላም ባለው ወያኔ ላይ ተቃውሞውን ቀጥሏል:: ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎Gonder‬ ‪#‎Ethiopiaprotests‬ ‪#‎MinilikSalsawi‬ ‪#‎EPRDF‬ Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – ወያኔ በሚከተለው የጎሳ ፖለቲካ በሕዝቦች መሃል ግጭትን እየፈጠረ እንደሆነ እና ታሪካዊ የኢትዮጵያ መሬቶች ለሱዳን ለመስጠት መስማማቱን …

በሰሜን ጎንደር የጭልጋ የቋራ እና የመተማ ሕዝብ እርቀ ሰላም ባለው ወያኔ ላይ ተቃውሞውን ቀጥሏል:: Read more »

ለነጻነታቸው በሚያደርጉት ትግል፣ ኢትዮጵያ እንደ እናት ሆና የረዳቻቸዉ ፣ እንደ ጋና፣ ታንዛኒያና ሴኔጋል ያሉ የአፍሪካ አገሮች እንኩዋን ሳይቀሩ የትናየት በደረሱበት ዘመን፣ እንደ ደርግ ዘመን አሁንም በኢትዮጵያ፣ ረሃብና ችጋር የሚገድለን አልበቃ ብሎ፣ ኢትዮጵያዉያን በኢትዮጵያዉያን እጅ እየተገደሉ ነው። በቅርቡ በጎንደር እና በኦሮሚያ የተለያዩ ቦታዎቸ እንዳየነው፣ በዜጎች ላይ የደረሰው ግድያ፣ ድብደባና ግፍ እጅግ በጣም ልቤን እንዳደማው መግለጽ እወዳለሁ። […]

The post ግፍ ሲፈጸም ዝምታን ከመረጥን እንደ አገር እንጠፋለን -ሃብታሙ አያሌው appeared first on ሳተናው .

የጂቡቲ የጸጥታ ሃይሎች ዛሬ በአንድ ሀይማኖታዊ ኩነት ላይ በከፈቱት ተኩስ በርካታ ሰዎች ሞተዋል ሲሉ እማኞች ለአሜሪካ ድምጽ ሬድዮ የሶማልኛ አገልግሎት ተናግረዋል።

የጸጥታ ሃይሎቹ ሃይማኖታዊው ኩነት እንዳይካሄድ ያስጠነቀቁ ቢሆንም አዘጋጆቹ ችላ እንዳሉትና ሟቹ ሃይማኖታዊ መሪ ሼኽ ዮኒስ ሙሴን ለማሰብ እንደተሰባሰቡ ምንጮች ጠቁመዋል።

የጸጥታ ሃይሎቹ የተሰባሰቡትን ሰዎች ለመበተን ሞክረው እንደነበር ጂቡቲ ያሉት ጋዜጠኞችና እማኞች ተናግረዋል። በሀገሪቱ ያለ የአሜሪካ ድምጽ ሬድዮ ዘጋቢ ቢያንስ ሁለት ሰዎች እንደተገድሉ ዘግቧል። ሌሎች ምንጮች ደግሞ ከዛ የበዛ ነው ይላሉ።

የዜና ዘገባውን ለማዳመጥ የድምጽ ፋይሉን ይጫኑ።

 

የአዲስ አበባ ከተማና የኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ የጋራ ማስተር ፕላንን ተቃውመው ሰላማዊ ሰልፍ የወጡ ተማሪዎች በኦሮሚያ ክልል በርካታ ወረዳዎችና ከተሞች  እያቀረቡት ያለው ሠላማዊ ጥያቄ በሰከነ መንገድ መልስ ለመስጠት ከመሞከር ይልቅ ተመጣጣኝ ያልሆነ ሀይል በመጠቀም ጥያቄውን ለማፈን እየተሞከረ ነው፡፡ በዚህ ሂደትም ብዙዎች ህይወታቸውን አጥተዋል፣ ለቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል፣ እስካሁን ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ዜጎችም ለእስር ተዳርገዋል፡፡ ሰሞኑን ከሚወጡት መግለጫዎችና የመንግስት ባለስልጣናት ቃለመጠይቆች እንደተረዳነው  ጥያቄዎቻቸውን በሃይል ለመመከት ከመዛትና ዜጎችን ከሰው በታች አውርዶ ቁጣን በሚጋብዝ መልኩ ከመጥራት በዘለለ ሀላፊነት እንደሚሰማው አካል ለችግሩ መፍትሔ  ለመፈለግ ዝግጁነት እንደሌለ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ሁሌም እንዲከበር የምንጠይቀውን የሀገሪቱ ሕጎች ሁሉ የበላይ የሆነውን ሕገ-መንግስት የሚጻረር ነው፡፡

በዚህ ሂደት በጥቂቱ ከዚህ በታች የተዘረዘሩት የሕገ-መንግስቱ አንቀጾች ተጥሰዋል

1.    የሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 15 የሕይወት መብት

‹‹ማንኛውም ሰውበሕይወት የመኖር መብት አለው፡፡ማንኛውም ሰው በሕግ በተደነገገከባድ የወንጀል ቅጣት ካልሆነበስተቀር ሕይወቱን አያጣም፡፡›› ቢልም ከሰላማዊ ሰልፉ ጋር በተያያዘ ከ8 ዓመት ልጅ አንስቶ እስከ የ80 ዓመት አዛውንት ድረስ ሕይወት እየተቀጠፈ ነው፤ እስከዛሬ የሞቱት ሰዎች ቁጥር በሶስተኛ ወገን ማረጋገጥ ባይቻልም ጉዳዬን  በቅርበት የሚከታሉ ሰዎች እንደዘግቡት ወደ መቶ እየተጠጋ ይገኛል፡፡

2.   የሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 15 የአካል ደኅንነት መብት

‹‹ማንኛውም ሰውበአካሉ ላይ ጉዳት እንዳይደርስየመጠበቅ መብት አለው፡፡ ›› አሁንም ከሰላማዊ ሰልፉ ጋር በተያያዘ በጥይት የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ዜጎች ቁጥራቸው በርካታ ነው፡፡ ድብደባ እና አላግባብ አንግልት የደረሰባቸውንም ቤት ይቁጠራቸው፡፡

3.   አንቀጽ 24.1 የክብርና የመልካም ስም መብት

‹‹ማንኛውም ሰው ሰብዓዊ ክብሩና መልካም ስሙ የመከበር መብት አለው፡፡ ›› እየሆነ ያለው ዜጎችን አጋንንት እያሉ መጥራት፣ ጥፋተኛ ተብለው በሕግ ያልተፈረደባቸውን አሸባሪ እያሉ ክብራቸውን በሚዲያ መግፈፍ ነው፡፡

4.   አንቀጽ 30.1 የመሰብሰብ፤ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ነጻነትና አቤቱታ የማቅረብ መብት

‹‹ማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋር በመሆን መሣሪያ ሳይዝ በሰላም የመሰብሰብ፣ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ነጻነትና፣ አቤቱታ የማቅረብ መብት አለው፡፡ ከቤት ውጭ የሚደረጉ ስብሰባዎችና ሰላማዊ ሰልፎች በሚንቀሳቀሱባቸው ቦታዎች በሕዝብ እንቅስቃሴ ላይ ችግር እንዳይፈጥሩ ለማድረግ ወይም በመካሔድ ላይ ያለ ስብሰባ ወይም ሰላማዊ ሰልፍ ሰላምን፣ ዴሞክራሲያዊ መብቶችንና የሕዝብን የሞራል ሁኔታ እንዳይጥሱ ለማስጠበቅ አግባብ ያላቸው ሥርዓቶች ሊደነገጉ ይችላሉ፡፡ ››  ቢልም መንግስት ይህን የህገ መንግሰቱን አንቀጽ በመጣስ ብዙ ሰብዓዊ ጉዳቶችን አድርሷል፡፡

ዜጎች ለመረጃ ቅርብ በሆኑበት በዚህ ጊዜ መንግስት እያደረጋቸው ያሉትን ተግባራት መካድ፣ እንዲሁም እንደሌሉ አደርጎ ለማስተባበል መሞከር ብዙ ኃላፊነት የሚጠበቅበት መንግስት የሚያሰገምትና ትዝብት ላይ የሚጥል ነው፡፡ ይህ የመንግስት ግዴለሽነት ብዙኃን ዜጎችን እየገፋ ከመስመር እያስወጣ ነው፡፡ ሰላማዊውን የሕዝብ እንቅስቃሴ ወደ አመጽ እና ወደአልተፈለገ ዕልቂት ከመግፋት ይልቅ የተቀናጀ የጋር ማስተር ፕላኑን  መሰረዝ፣ በዚህ ሒደት ጥፋት የፈጸሙ በየደረጃው የሚገኙ የመንግስት አስፈጻሚ አካላትን ለፍርድ ማቅረብ፣ የግል ተበዳዮችን  መካስና ሌሎች አስፈላጊ የመፍትሔ እርምጃዎችን ሁሉ መውሰድ ይጠበቅበታል፡፡  ሁልጊዜም እንደምንለው በሰላማዊ መንገድ የመብት ጥያቄ ማቅረብ ወንጀል አይደለም፡፡  መንግሰት በሰላማዊ መንገድ መብታቸውን ከሚጠይቁ ዜጎች ጋር እልህ አይጋባ ፣ ህገ መንግስታዊ መብቶቻቸው ይከበሩ ፣ የመብት ጥሰት ድብደባ እና ግድያው ይቁም፡፡  ሕገ-መንግስታዊነት የታሰርንለት፣ ከሀገር የተሰደድንለት፣ ብዙ ዋጋ የከፈልንበትና አሁንም እየከፈልንበት ያለ ዐሳብ ነውና  በሀገሪቱ ህጋዊነት እንዲሰፍን ህይወታቸውን እስከመስጠት ድረስ ዋጋ ለከፈሉ ዜጎች ክብር እንሰጣለን፡፡ ለሕገ መንግስታዊ ስርዓት መስፈን ዜጎች የከፈሉት ዋጋ እጅግ ብዙ እና ከበቂ በላይ ነውና ተጨማሪ ሰብዓዊ ዋጋ መክፈል ሳያፈልገን ሕገ መንግስቱ እንዲከበር አንጠይቃለን፡፡


ሕገ-መንግስቱ ይከበር!  

በኢትዮጵያ ሱዳን የድንበር መካለል ላይ በሃገር መሸጥ የተሳተፈ ይሁን የደገፈ ከተጠያቂነት አያመልጥም:: ‪ Minilik Salsawi – ለሕዝብ እልቂት የመሪነት ሚና የሚጫወተው ሕወሓት ሸምጥጦ ቢክድም የወያኔው አሻንጉሊት ጠቅላይ ሚኒስትር የሆነው ሃይለማርያም ደሳለኝ የኢትዮጵያ እና የሱዳን የድንበር ማካለል ከሱዳኑ መሪ በሽር ጋር …

በኢትዮጵያ ሱዳን የድንበር መካለል ላይ በሃገር መሸጥ የተሳተፈ ይሁን የደገፈ ከተጠያቂነት አያመልጥም:: ‪ Read more »

በጎጃም ማንኩሳ መሬታችንን አንለቅም ያሉ ግለሰቦችን ንብረት በእሳት አነደደው።በቃጠሎው ከፍተኛ ንብረት የወደመ ሲሆን የአካባቢውን ማህበረሰብ በእጅጉ አስቆጥቶ ለአመፅ አስነስቷቸሗል።ይህንን ቃጠሎ የወያኔ አሽከር በመሆን በዋናነት የፈፀሙት ኮማንደር ሽታሁን እና ደሳለኝ በእውቀት የተባሉ የወያኔ አመራሮች መሆናቸው ታውቋል። እንደሚታወቀው ወያኔ በትላልቅ ከተሞች የሚፈልገውን …

የወያኔ ቡድን የማንኩሳ ነዋሪዎችን ንብረት በእሳት አነደደ። Read more »

ከረዥም ጊዜ ጀምሮ በብዙ አፍሪካ አገሮች የሚታየው የአስተዳደር ብልሹነት፣ የህዝቦች ኑሮ መዘበራረቅና ዓላማ-ቢስ መሆን፣ እንዲያም ሲል በአንድ አገር ውስጥ የሚኖር ህዝብ በሃይማኖትና በጎሳ አሳቦ ርስ በርሱ እንዲጠላላ ማድረግና፣ የመጨረሻ መጨረሻም ወደ ርስ በርስ መተላለቅ እንዲያመራ መንገዱን ማዘጋጀት፣ በተራ አነጋገር ከመልካም …

ፍልስፍና አልባ የሆነ አገዛዝና የፖለቲካ ትግል ዘዴ የአንድን ህብረተሰብ አስተሳሰብ ያዘበራርቃል- የመጨረሻ መጨረሻም አገርን ያወድማል! በፈቃዱ በቀለ፣ ዶ/ር Read more »

ከአዲስ አበባው ማስተር ፕላን ጋር በተያያዘ መንግስት የወሰደውን እርምጃ በመቃወም የኢትዮዺያ ሙስሊሞች አንድነት ማህበር መግለጫ አወጣ ። በሳዑዲ አረቢያ ሪያድ ከተማ መቀመጫውን ያደረገው የኢትዮዺያ ሙስሊሞች አንድነት ማህበር ከአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጋር በተያያዘ የኢህአዴግ መንግስት በዜጎች ላይ እየወሰደ ያለውን የኃይል …

ከአዲስ አበባው ማስተር ፕላን ጋር በተያያዘ መንግስት የወሰደውን እርምጃ በመቃወም የኢትዮዺያ ሙስሊሞች አንድነት ማህበር መግለጫ አወጣ ። Read more »

በደቡብ ኦሮሚያ ክልል በቦረና ዞን በሞያሌ ፣ ቡሌ ሆራ፣ ደሬ ፣ ያቤሎ ፣ ዱግደዳዋ ፣ ተልተሌ ፣ አሬሮና በሌሎችም ወረዳዎችና ቀበሌዎች የሚገኙ መምህራን ፣ ተማሪዎች፣ ገበሬዎችና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ትግሉ የሚፈልገውን አስፈላጊውን መሰዋዕትነት በመክፈል እስከ መጨረሻው ለመጓዝ መቁረጣቸውንና እንቅስቃሴ መጀመራቸውን …

በኦሮሚያ ክልል በቦረና ዞን ህዝቡ ትግሉን አፋፍሞ ለመቀጠል እየተንቀሳቀሰ መሆኑ ታወቀ ። Read more »

ታኀሳስ ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአጋዚ ጦር በህዝቡ ላይ የወሰደውን እርምጃ በጽኑ አውግዘዋል። የኦሮሞ ህዝብ በአጋንንት ተመስሎ ተሰድቧልና ተሳዳቢው ባለስልጣን ይቅርታ ይጠይቅ ብለዋል። መንግስት ለሞቱት ዜጎች ሃላፊነቱን እንዲወስድና ለህዝብ ጥያቄ መልስ እንዲሰጥ አሳስበዋል።በአዲስ አበባ የሚገነቡት ፎቆች የማን ናቸው? ሲሉም ጠይቀዋል።አርጅተናል አልቻልንም ስልጣናችንን እናስረክብ ያሉ አመራሮችም አሉ። ሰፊ ሰአት በሚሸፍነው ስብሰባ …

የሰማያዊ ፓርቲ እና የአራት ደርጅቶች ስብስበ የሆነው መድረክ በጋራ ሰላማዊ ሰልፍ ጠርተዋል። ቀደም ሲል ኦፌኮ በአዳማና ለሌች የኦሮሚያ ቦታዎች ሰልፍ ጠርቶ እንደነበረና በባላስልጣናት ሕግ ወጥ በሆነ መንገድ እውቅና እንደተነፈገ ይታወቃል። ይህ የአሁኑ ሰልፍ ፣ በመድረክ ያሉትን እና ሰማያዊን ጨመሮ አምስት ደርጅቶች በጋራ የጠሩት ሰልፍ ሲሆን፣ የሚደረገዉን በአዲስ አበባ ነው። ኦፈኮ የጠራው ሰልፍ ማስተር ፕላኑን በመቃወም […]

The post ለታህሳስ 17 ቀን በአዲስ አበባ ሰልፍ ተጠርቱዋል – የሚሊዮኖች ድምጽ appeared first on ሳተናው .

#‎Ethiopia‬ ‪#‎Oromoprotests‬ የሕወሓት የደህንነት ቢሮ ሪፖርት ለኦሕዲድ ሹሞች ከነአጋሮቻቸው እስር ሲያቅድ ብቻችንን ቀርተናል በማለት መንግስት መነቃነቁን አምኗል:: ‪#‎MinilikSalsawi‬ Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – ዛሬ ከከሰአት በኋላ ጀምሮ በአዲስ አበባ የደህንነት ቢሮ ውስጥ የሕወሓት ማፊያዎች ተሰብስበዋል::ስብሰባው ያተኮረው ባለፉት ሳምንታቶች ተከስቶ ስለነበረው …

የሕወሓት የደህንነት ቢሮ ሪፖርት ለኦሕዲድ ሹሞች ከነአጋሮቻቸው እስር ሲያቅድ ብቻችንን ቀርተናል በማለት መንግስት መነቃነቁን አምኗል:: Read more »

ባህርዳር ከተማ ማረሚያ ቤት የሚገኙ እስረኞች የሚደርስባቸውን በደል በመቃወም ከትናንት ታህሳስ 9/2008 ዓ.ም ጀምሮ በእስር ቤቱ የሚዘጋጀውን ምግብ እንደማይበሉ ማሳወቃቸውንና ጩኸት በማሰማት ተቃውሟቸውን መግለፃቸውን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገልፀዋል፡፡ በትናንትናው ዕለት በማረሚያ ቤቱ የሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ያመልጣሉ በሚል በእግር ብረት ታስረው እንደሚገኙ መዘገባችን የሚታወስ ሲሆን እስረኞቹ በርካታ በደሎች እየደረሰባቸው እንደሚገኝ ምንጮቻችን ገልፀዋል፡፡ በተለይ በሽብር […]

The post ባህርዳር ላይ እስረኞች ተቃውሞ አሰሙ appeared first on ሳተናው .

የወያኔ ሰርጎ ገብ ካድሬዎች የኦሮሞ ተማሪዎችን ተቃውሞ ተገን አድርገው በአመያ የአማሮችን ቤት አቃጥለዋል:: ማንምም ለወገኑ የሚቆረቆር ሊያረጋግጠዉ የሚችል ሃቅ:: በአመያ ወረዳ በሮሙረያ ቀበሌ ቤታቸው ከተቃጠለባቸው አማራዎች መካከል 1 አባበይ ታዬ 2 ጌታቸው ክር 3 አስጨናቂ ታዬ 4 ጌታቸው መንግስት 5 …

የወያኔ ሰርጎ ገብ ካድሬዎች የኦሮሞ ተማሪዎችን ተቃውሞ ተገን አድርገው በአመያ የአማሮችን ቤት አቃጥለዋል:: Read more »

ሰማያዊ ፓርቲ እና የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) አዲስ አበባ ላይ በጋራ ሰላማዊ ሰልፍ መጥራታቸውን የሰማያዊ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ነገሰ ተፋረደኝ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ እና መድረክ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት መስማማታቸው የሚታወስ ሲሆን እሁድ ታህሳስ …

ሰማያዊ ፓርቲ እና መድረክ ማስተር ፕላኑ እና ለሱዳን አሳልፎ ለመስጠት ያቀደውን መሬቱ እንዳይሰጥ ለመቃወም በጋራ ሰላማዊ ሰልፍ ጠሩ:: Read more »

ታኀሳስ ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በሃረር ከተማ ህዝቡ የመንግስትን እርምጃ ሙሉ በሙሉ አውግዟል። በሌላ በኩል መድረክና ሰማያዊ ፓርቲ በአዲስ አበባ የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል። ሰማያዊ ፓርቲ እና መድረክ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት መስማማታቸው ተከትሎ እሁድ ታህሳስ 17/2008 ዓ.ም በጋራ ሰልፍ ጠርተዋል። የሰልፉ አላማ በዋነኛነት ከማስተር ፕላኑ ጋር በተያያዘ መንግስት …

ሕጋዊው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ወቅታዊ የአገራችንን ሁኔታ አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል።  ሲኖዶሱ በዚህ መግለጫው  አምባገነኑ የወያኔ አገዛዝ መብታቸውን በህጋዊ መንገድ የጠየቁ የኦሮሞ ኢትዮጵያውያን ላይ እያደረሰ ያለውን ጭፍጨፋ በጥብቅ አውግዟል። ከዚህም በተጨማሪ ሲኖዶሱ ወያኔ የአገራችንን መሬት ለባዕዳን አሳልፎ መስጠቱንና …

ወቅታዊ የአገራችንን ሁኔታ አስመልክቶ ከሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ Read more »

የሚደርስባቸውን በደል በመቃወም ባህርዳር ላይ እስረኞች ተቃውሞ አሰሙ ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎BahrDar‬ ‪#‎Ethiopiaprotests‬ ‪#‎NegereEthiopia‬ ‪#‎MinilikSalsawi‬ ባህርዳር ከተማ ማረሚያ ቤት የሚገኙ እስረኞች የሚደርስባቸውን በደል በመቃወም ከትናንት ታህሳስ 9/2008 ዓ.ም ጀምሮ በእስር ቤቱ የሚዘጋጀውን ምግብ እንደማይበሉ ማሳወቃቸውንና ጩኸት በማሰማት ተቃውሟቸውን መግለፃቸውን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች …

ባህርዳር ከተማ ማረሚያ ቤት የሚገኙ እስረኞች የሚደርስባቸውን በደል በመቃወም ተቃውሞ አሰሙ Read more »

የኦሮሞ ህዝብ ጥያቄ ከዚህች ከኣዲስ ኣበባዋ የመሬት ነጠቃ ጥያቄ በጅጉ ገዝፎ የሄደ ነው። ከፍተኛው ጥያቄ የመልካም ኣስተዳደር ጥያቄ ነው። በመጀመሪያ ህወሃት ይህን ዘረኛ ፖለቲካውን ተሸክሞ ኣዲስ ኣበባ ከገባ በሁዋላ በተለይ ኦሮሞንና ኣማራን ጸጥ ኣድርጎ ለመግዛት የተጠቀመው ዘዴ በነዚህ ክልሎች ውስጥ ከታች እስከ ላይ ያሉትን ባለ ስልጣናት በኣልተማሩና የማስተዳደር ችሎታ በሌላቸው ነገር ግን ታዛዥ ብቻ በሆኑ […]

የዛሬው የወጣቶች ዓለም እንግዳችን ብዙ ፈተናዎችን ያሳለፈች ወጣት ናት። ከልጅነቷ አንስቶ የቤት ሰራተኛ ሆና አገልግላለች ፤ኃላም የጎዳና ተዳዳሪ ነበረች። እዛው ጎዳና ላይም ነፍሰ ጡር እና እመጫት ሊስትሮም ሆና ሰርታለች።

ሰላማዊ ተቃውሞ፣ ከፖሊስ ጋር ግጭት፣ ከዚያ ረብሻና እስር፣ ቃጠሎና ግድያ… ከዚህ አሳዛኝ የጥፋት ሰንሰለት መላቀቅ ያቃተን፤ መውጫ የሌለው አዙሪት የሆነብን ለምንድነው? እንዲህ አይነት ቀውስ በተፈጠረ ቁጥር፤ መንግስት እየደጋገመ የሚናገረው ነገር አለ። ቅሬታዎችን ማቅረብ፣ ተቃውሞን በሰላም መግለፅ፣ ተፈጥሯዊ መብት ነው ይላል …

“የተረገመ አዙሪት” – አገሬውን በአፈናና በጉልበት ዝም ለማሰኘት መሯሯጥ Read more »

የትግራይ ህዝብ ውርደት = Amdom Gebreslasie ************ በኣሁኑ ሰዓት በድርቅ ምክንያት 1.2 ሚልዮን ህዝብ ኣስቸኳይ እርዳታ የሚጠባበቅ ሲሆን 1.5 ደግሞ በሴፍትኔት እርዳታ( ሰርቶ ለምግብ) በድምሩ 2.7 ሚልዮን ህዝብ ጥገኛ ሆኖ እንደሚገኝ የትግራይ ክልል ኣደጋ መከላከልና ዝግጁነት ፅህፈት ቤት ሰነዶች ይገልፃሉ። …

የትግራይ ህዝብ ውርደት :- 1.2 ሚ. ህዝብ ኣስቸኳይ እርዳታ የሚጠበቅ -1.5ሚ. ሰርቶ ለምግብ በድምሩ 2.7 ሚልዮን ህዝብ ጥገኛ Read more »

    ባለፈው መስከረም ወር መጨረሻ ላይ ታመው ተክለሃይማኖት ጠቅላላ ሆስፒታል ከገቡትና ለ10 ቀናት በህክምና ላይ ቆይተው ጥቅምት 6 ቀን ህይወታቸው ካለፈው ወይዘሮ አየለች ደግፌ ጆሮ ላይ የጠፋው 5 ግራም የጆሮ ወርቅ፤ ሆስፒታሉንና የሟች ቤተሰብን እያወዛገበ ነው፡፡ የሆስፒታሉ የፅኑ ህሙማን ክፍል ኃላፊ ሲስተር አስናቀች ተጠይቀው ሲመልሱ፤ “ወርቁ ከአስከሬኑ ጋር አብሮ የተገነዘ በመሆኑ መቃብሩ ይቆፈርልኝ” ማለታቸውን የሟች ልጅ አቶ ሰለሞን ጌታቸው ለአዲስ አድማስ ገልጿል፡፡
እናቴን “ለመጨረሻ ጊዜ ፅኑ ህሙማን ክፍል ገብተን ስናያት ወርቁ ጆሮዋ ላይ መሆኑን ተመልክቻለሁ” ያለው አቶ ሰለሞን፤ “ከሞተች በኋላ ወርቁን ስጠይቅ ከአስከሬኑ ጋር ተገንዟል ተባልኩኝ፤ እውነቱ እንዲወጣ ስለምፈልግ መቃብሩ እንዲቆፈር ብፈቅድም እስካሁን ምንም ምላሽ አላገኘሁም” ብሏል፡፡
“ዛሬ ነገ እያሉኝ በመመላለስ ብዙ ተንከራተትኩ፤ እኔ ጉዳዬ ከወርቁ አይደለም፤ ነገር ግን መቃብሩ ተቆፍሮ እውነቱ እንዲወጣና ለሌሎችም ትምህርት እንዲሆን እፈልጋለሁ” ይላል አቶ ሰለሞን፡፡ ሆኖም ሥራዬንና ጊዜዬን ከማባከን በቀር እስካሁን አጥጋቢ ምላሽ ማግኘት አልቻልኩም ሲል አማርሯል የሟች ልጅ፡፡
የሆስፒታሉን ሥራ አስኪያጅ አቶ ጌታሁን ስዩምን አነጋግሬ ነበር ያለው አቶ ሰለሞን፤ “ኃላፊዋ ወርቁን እንድትከፍል ወስነው ነበር፤ ነርሷ ዋጋውን ከጠየቀችኝና ከነገርኳት በኋላ ነው መቃብሩ ይቆፈር ያለችኝ” ብሏል፡፡ እኔ ከራሴ ጋር እየታገልኩም ቢሆን እውነት እንዲወጣ፣  ወጪውን ሸፍና ቁፋሮውን እንድታካሂድ ብፈቅድም ኃላፊዋ የተለያዩ ምክንያቶች እየፈጠረች ጊዜዬን እያባከነች ነው ያለው አቶ ሰለሞን፤ ሆስፒታሉ ለጉዳዩ እልባት የማይሰጠኝ ከሆነ ማስረጃዎቼን ይዤ ወደ ፍርድ ቤት አመራለሁ ብሏል፡፡
አንድ ህመምተኛ ወደ ፅኑ ህሙማን ክፍል (ICU) ሲገባ ስላለው አጠቃላይ ሁኔታ የጠይቀናቸው የህክምና ባለሙያ እንደነገሩን፤ ህመምተኛው “እንኳን ጌጣጌጥ ከቤቱ ያመጣውን ፒጃማ እንኳን መልበስ አይችልም፤ ብዙ ጊዜ ፅኑ ህሙማን በማሽን ስለሚተነፍሱና የልብ ምታቸው በየጊዜው ስለሚታይ በአብዛኛው ደረታቸው ክፍት መሆን አለበት፤ ስለዚህ በአንሶላና በብርድልብስ ብቻ ይሸፈናሉ” ከዚህ አንፃር ህመምተኞች ወደ ፅኑ ህሙማን ክፍል ሊገቡ ሲዘጋጁ ማናቸውም ጌጣጌጥና ብራስሌት ወላልቆ ለቅርብ ቤተሰባቸው እንደሚሰጥ የጠቆሙት ባለሙያዋ፤ ይህም የፅኑ ህሙማን ክፍል ኃላፊዎች ሥራ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡  
“የጆሮ ጌጡ ከአስከሬኑ ጋር ተገንዞ ቢሆን እንኳን የፅኑ ህመምተኛ ክፍል ኃላፊዋ ስራቸውን በአግባቡ ባለመወጣታቸው ከተጠያቂነት አያመልጡም” ብለዋል – ባለሙያዋ፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ አቶ ጌታሁን ስዩም ምላሽ እንዲሰጡን ጥረት ብናደርግም ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል፡፡

የሕዝብን ተቃውሞ ማፈን ቀውስን አያስወግድም !!! ( የኢሕአፓ መግለጫ ) ባለፉት ጥቂት ቀናት የወያኔን የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ሲቃወሙ የነበሩ በርካታ ዜጎችን ወያኔ በግፍ ጨፍጭፏል።ኢሕአፓ አምባገነኑ የወያኔ ቡድን በዜጎች ላይ ያካሄደውን አረመኔያዊ ድርጊት እየኮነነና እያወገዘ ይህን አጥፊ ቡድን ለማስወገድ የሚካሄደው …

የሕዝብን ተቃውሞ ማፈን ቀውስን አያስወግድም !!! ( የኢሕአፓ መግለጫ ) Read more »

የጥርስ መቦርቦር — (በዶክተር ሆነሊያት ኤፍሬም ቱፈር) ==== የጥርስ መቦርቦር የሚከሰተው በአፋችን ውስጥ የሚገኙ ጀርሞች (ባክቴሪያ) ጥርሳችንን የሚያበሰብሱ አሲዶችን በሚያመነጩበት ጊዜ ነው፣ ይህም በጥርሳችን ላይ የተቦረቦሩ ቀዳዳዎችን (Cavities) እንዲፈጠሩ ያደርጋል። የተቦረቦሩ ጥርሶች ህመም ከማስከተል ባለፈ ለኢንፌክሽን ያጋልጣሉ። ✔ የጥርስ መቦርቦር …

የጥርስ መቦርቦር (በዶክተር ሆነሊያት ኤፍሬም ቱፈር) Read more »

ላለፉት ሦስት ሳምንታት የኦሮሞ ብሔረሰብ አባላት ተማሪዎች የአዲስ አበባ እና የፊንፊኔ ዙሪያ የኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ ማስተር ፕላን ተግባራዊ ይደረጋል መባሉን ሲቃወሙ ሰንብተዋል። የተቃውሞን ጅምር የሚያትተውን የማርታ ፋን ደር ቮልፍ የአዲስ አበባ ዘገባ ጨምራ፤ ጽዮን ግርማ የዛሬውን የተቃውሞ ሰልፍ ውሎ የተመለከት ርእሶችን ይዛለች፡፡

የደንነት መስሪያ ቤቱ በሚንስትሮች ምክር ቤት በኩል ለጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያ የሰባት ቀን የጌዜ ገደብ የተሰጠው ማስጠንቀቂያ ማስተላለፉ ታውቆአል። የደህንነት መስሪያ ቤቱ በሀገሪቱ ውስጥ ሳይታሰብ የፈነዳውን አመፅ ለመቆጣጠር ምን አይነት እርምጃ መወሰድ እንዳለበት ሙሉ ስምምነት ላይ መድረስ አልችል ብሎ ሲወዛገብ መሰንበቱ ሲታወቅ ዛሪ ከጥዋት ጁምሮ ሲአካሂድ በዋለው ውይይት ላይ ግን ማንኛውንም አይነት ሀይል ተጠቅሞ አመፁን ለመቆጣጠር […]

መንግሥት ሁከት በሚፈጥሩት ላይ የማያዳግም እርምጃ እወስዳለሁ ብሏል

   በጎንደር ጭልጋ አካባቢ ቅማንትና አማራ በሚል በተደራጁ ቡድኖች መካከል በተፈጠረ ግጭት በርካቶች ለሞት መዳረጋቸው የተገለፀ ሲሆን ነዋሪዎች በስጋት ከቤታቸው ሳይወጡ እንደሰነበቱ ምንጮች ገለፁ፡፡
ግጭቱ ስር የሰደደ እንደነበር የጠቆሙት የአካባቢው ምንጮቻችን፤ ከመስከረም ጀምሮ ተማሪዎች ትምህርታቸውን መከታተል እንዳልቻሉ፣ ከሳምንት በላይ ባስቆጠረው አደገኛ ግጭትም ኢትዮጵያን ከሱዳን የሚያገናኘው መንገድ ሙሉ በሙሉ ተዘግቶ መቆየቱን ገልፀዋል፡፡
ቅማንት በሚል የተደራጀው ቡድን፣ “የቅማንት ጥያቄ እስኪመለስ ትምህርት የለም፤ እናንተም አትማሩም” በሚል ት/ቤቶች ላይ ጥቃት ሲፈፅሙ እንደነበር የጠቀሱት ምንጮች፤ በዚህም የተነሳ የአካባቢው ልጆች ከትምህርት ገበታቸው ተፈናቅለዋል ይላሉ፡፡ የቅማንቶች የማንነት ጥያቄ ምላሽ ካገኘ በኋላ ከሰሞኑ ለተፈጠረው ግጭት መነሻ የሆነው “ዞን ይዋቀርልን፣ ድንበር ይከለልልን” በሚል በተነሳ ጥያቄ ነው ተብሏል፡፡
ቅማንቶች የማንነት ጥያቄ ማቅረብ ከጀመሩበት ከ3 ዓመት በፊት አካባቢው ውጥረትና ግጭት ተለይቶት እንደማያውቅ የሚጠቅሱት ነዋሪዎች፤ ከሁለት አመት በፊት ሚያዚያ ወር ላይ በአይከል ከተማ ከፍተኛ ረብሻ ተነስቶ ሰዎች መጎዳታቸውንና በርካታ ሱቆችና መኖሪያ ቤቶች መቃጠላቸውን ያስታውሳሉ፡፡
ባሳለፍነው ሐሙስ ህዳር 30 ቀን 2008 ዓ.ም ግጭቱ በከፍተኛ ደረጃ መቀስቀሱን የጠቀሱት ምንጮቻችን፤ በእለቱ አንድ የቅማንት ወጣት መገደሉን ተከትሎ ቅማንት በሚል የተደራጁ ቡድኖች፤ ዳቦ ቤት ማቃጠላቸውንና ሱቅ ማውደማቸውን ይጠቅሳሉ፡፡ ይህን ተከትሎ የአማራ ብሔር ተወላጆች በሚል የተደራጁ ወገኖች በቋራ፣ ሺንፋ፣ ነጋዴ በሃርና ገንዳ ውሃ በተባሉ አካባቢዎች የሚኖሩ ቅማንቶችን እያባረሩ ቤት ንብረት ማቃጠል እንደጀመሩ ይገልፃሉ፡፡
ከእነዚህ አካባቢ የተባረሩ ሰዎች በአሁኑ ወቅት ጭልጋ ውስጥ በየድንኳኑ ተጠልለው የአካባቢው ህብረተሰብ የእለት ጉርስ እያቀረበላቸው እንደሚገኝና ሰሞኑን ምክትል ጠ/ሚኒስትር ደመቀ መኮንንን ጨምሮ የክልሉ ባለስልጣናት ህዝቡን ሰብስበው እንዳወያዩ ምንጮቻችን ጠቁመዋል፡፡
በዚህም የተነሳ በአካባቢው ውጥረት መንገሱን የሚጠቅሱት ምንጮች፤ ሰዎች ከቤት መውጣት እንደተሳናቸውና በየመንገዱ ጦር፣ ገጀራ፣ ቢለዋ፣ መጥረቢያና የጦር መሳሪያዎች የያዙ ሰዎች እንደሚዟዟሩ ተናግረዋል፡፡ ይሁን እንጂ ትናንት በአንፃሩ ሠላማዊ እንቅስቃሴ እንደነበር ምንጮቻችን ጠቁመዋል፡፡
በገጠር አካባቢዎች ተደራጅተው ለጠብ የተዘጋጁ የቅማንት ተወላጆችን መበተን እንዳልተቻለ የሚጠቅሱት የሚናገሩት ምንጮች፤ የመንግስት ባለስልጣናት ከህዝቡ ጋር ባደረጉት ውይይት ግን ከዚህ በኋላ በግጭቱ ተሳታፊ የሚሆኑና ፀብ የሚጭሩ አካላት ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ መናገራቸን ጠቅሰዋል፡፡ ህብረተሰቡም የእርስ በእርስ ግጭት ውስጥ ላለመግባት ተስማምቷል ተብሏል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ሰሞኑን ከኢቢሲ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ፤ ከቅማንት ብሄረሰብ የማንነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ጋር በተያያዘ የሚከሰቱ ግጭቶች በመንግስት ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ጠቁመው የአካባቢውን ሰላም በሚያውኩት ላይ የማያዳግም እርምጃ እንደሚወሰድ መግለፃቸው ይታወሳል፡፡

ንቅናቄያችን የተቋቋመበት ዋነኛ አላማ የአማራን ህዝብ ህልውና መታደግ ነው።በመሆኑም አሁን በመላው ኢትዮጵያ በአማራው ላይ የሚደርሰው የዘር ማጥፋት ወንጀል ሽፋን እየተሰጠው ከመቼውም በላቀ ሁኔታ ተጠናክሮ በመቀጠሉ የሚከተሉትን አቋም እንድንይዝ አስገድደውናል። ፩- በመላው ኢትዮጵያ የሚገኝ የአማራ ተወላጅ እራሱን ከጥቃት ለመከላከል እርምጃ ቢወስድ …

ከአማራ‬ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ Read more »

የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ሒውማን ራይትስ ዎች ትናንት ባወጣው መግለጫ በኢትዮጵያ የኦሮሚያ ክልል በተቀሰቀሰውና ሣምንታትን ባስቆጠረው ተቃውሞ ቢያንስ 75 ሰዎች መገደላቸውን እና በርካቶች መቁሰላቸውን አስታወቀ።