በባህር ዳር ከተማ የሚታየው የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ነዋሪውን አስመርሯል
ታኀሳስ ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከክረምቱ መግባት ጀምሮ በከተማዋ በተደጋጋሚ የሚታየው የመብራት መቆራረጥ ነዋሪውን ያስመረረ ሲሆን፣ በአስቸኳይ ጥገና መስክ የተሰማሩት ሰራተኞች የሚጠቀሙበት መኪና ከአስርት አመታት በፊት የነበረ አሮጌ ከመሆኑም በላይ በቁጥርም አንድ ብቻ መሆኑ ስራውን እንዳወሳሰበው ባለሙያዎቹ ተናግረዋል፡፡ የደንበኞች ቁጥር እየበዛ በሄደ ቁጥር ያሉት ገመዶች የኤሌክትሪክ ኃይሉን መሸከም ባለመቻላቸው መቀየር ሲገባቸው …