የኦሮሞ ህዝብ ጥያቄ ከዚህች ከኣዲስ ኣበባዋ የመሬት ነጠቃ ጥያቄ በጅጉ ገዝፎ የሄደ ነው። ከፍተኛው ጥያቄ የመልካም ኣስተዳደር ጥያቄ ነው። በመጀመሪያ ህወሃት ይህን ዘረኛ ፖለቲካውን ተሸክሞ ኣዲስ ኣበባ ከገባ በሁዋላ በተለይ ኦሮሞንና ኣማራን ጸጥ ኣድርጎ ለመግዛት የተጠቀመው ዘዴ በነዚህ ክልሎች ውስጥ ከታች እስከ ላይ ያሉትን ባለ ስልጣናት በኣልተማሩና የማስተዳደር ችሎታ በሌላቸው ነገር ግን ታዛዥ ብቻ በሆኑ […]

ሀገራችን መሬት ላይ እንድ ሌላ ግዙፍ የርሀብና የችጋር ዳመና እያንዣበበ ነው። አንዳንድ ቦታም ግዳይ መጣል መጀመሩን እየሰማን ነው። ይህ ችግር በሰብዓዊ ዕውቀትና ሀይል የሚፈታ ሆኖ ለምንድነው እንዲህ እየተመላለሰ የሚጎበኘን? ሌሎች ሀገሮች ተመሳሳይ የአየር ሁኔታ ችግር እየገጠማቸው እንደኛ ለአዋራጅ ጉስቁልናና ልመና አልተዳረጉም። እኛ ጋ ምን የተሰወረብን ነገር አለ? የአፍሪካ የውሀ ሰገነት የምትባልና ከማንም የማይተናነስ የተፈጥሮ ጸጋ […]

የዚህ ታላቅ ሰው ድንገተኛ ዜና-ዕረፍት ህሊናዬን ዘልቆ አናውጦታል ፣ ለጥቂት አፍታዎች ተደነባብሬ ነበር፣ እስከ አሁንም ውስጤን በምናቤ ሳሰላስለው የሰቀቀን ስሜት እንደ ዋጠኝ አለሁ። ታላቅ ዋጋ የምትሰጡት ፣ ፋይዳ ያለው የአገር ፣ የህዝብ እና የታሪክ ስንከሳር የታጨቀበት ግዙፍ መርከብ በማእበል ተመቶ ባህር ውስጥ የመስመጥ አደጋ ደረሰበት የሚል ዜና የሰማሁ መሰለኝ። የዕውቀት ክምችት ፣ የዳበረ ልምድ ፣ […]

የአእምሮ ህመምተኛ የሆኑ ወላጅ እናት አሉት፡፡ወጥቶ እስኪገባ በስስት የሚጠብቁት ሁለት ልጆቹን በተመለከተ ቁጥር የሚወርሷት አገር ብዙ የችግር ቋጠሮዎችን እንደተሸከመች ያስተውልና ነገን ስለ ልጆቹ ‹‹ብሩህ ››ለማድረግ ስጋውን፣አእምሮውንና መንፈሱን ያድሳል፡፡በትግሉ ውስጥ የሚያደክሙ ‹‹ምን አገባኝን የሚያስመኙ››ብዙ መሰናክሎች ቢደቀኑበትም ስንታየሁ ለበቃኝ ‹‹ግንባሩን ››አያጥፍም፡፡ በአንድ ወቅት ኢመደበኛ በሆነ ጭውውት መሐል የእነ ናትናኤል መኮንን ጉዳይ ተነስቶ ‹‹እቤቴ ገብቼ ልጆቼን በናፍቆት ስስማቸው […]

ሕግ መንግስቱ በሚፈቅደው መሰረት ሰላማዊና ሕጋዊ በሆነ መንገድ መብታቸዉን ለማስከበር ፣ ተደራጅተው ሲንቀሳቀሱ፣ ወንጀል ሳይፈጽሙ በዉሸት ክስ በወህኒ በግፍና በጭካኔ እየሰቃዩ ያሉ የአንድነት አባለት ብዙ ናቸው። ባለፉት ሁለት ቀናት ብቻ ቢያንስ ፣ ለማረጋገጥ የቻልነው ከአምስት በላይ አንድነቶች ታስረዋል፡ 1. አንድዋለም አራጌ ( ም/ፕሬዘዳነት) 2. ሃብታሙ አያሌው (የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊና የሚሊዮኖች ድምጽ ሰብሳቢ) 3. አለነ […]

ሁለት ሕጻናት አሉት። የመጀመሪያ ወንድ ልጁ ሩህ ይባላል። ከአራት አመታት በፊት፣ ልጁን ከትምህርት ቤት ሊያወጣ ወደዚያ ሲያመራ ታጣቂዎች ከበቡት። እየሰደቡ፣ እየደበደቡ ወደ ወህኒ ወሰዱት። አንድ ፖሊስ ይበቃ ነበር። ግን የለየለት ነፈሰ ገዳይ የሚይዙ ይመስል፣ ይሄን አንድ ሰላማዊ የልጅ አባት ለመያዝ ተረባረቡ። አይ ጭካኔ ! ይህ ሰው አንዱዋለም አራጌ ነው። የአንድነት ፓርቲ ምክትል ፕሬዘዳነት የነበረ፣ አንጋፋ […]

አስቴር ስዩም ትባላለች ። በጎንደር ምእራብ አርማጭሆ የቀድሞው አንድነት ፓርቲ አመራር አባል ነች። የማስተርስ ዲግሪዋን ከዩኒቨርሲቲ በማእረግ ተቀብላለች፡ ላመነችበት ነገር ወደኋላ የማትል የጣይቱ ልጅ መሆኗን ለመረዳት ብዙ ጊዜ አላስፈለግም። ስትናገር ቁጥብ ናት ። ከመናገር ማዳመጥን ታስቀድማለች ።ታዲያ ይህች ባለትዳርና አንድ ልጅ እናት የሆነች የነፃነት ታጋይ፣ ከገዢው መደብ ካድሬዎች፣ የተለያዩ ማባበያዎች ቢቀርብላትም ሳይማር ያስተማረኝን እና ገዢዎቻችን […]

ወያኔ ሃብታሙ አያሌው ላይ ላቀረበው ክስ፣ ምንም አይነት መረጃ የለዉም ። ክሱ በአብዛኛው “በኢሳት ፣ በዚህ ራዲዮ፣ በዚያ ፓል ቶክ ክፍል … ቃለ መጠይቅ አደረገ ..” ወዘተረፈ የሚል ነው። ኢሳት ላይ እጅግ በጣም በርካታ ኢትዮጵያዊያን እና የዉጭ አገር ዜጎች ቀርበዋል። ቪኪ ሃደልሰንን፣ ዶር መራራ ጉዲናን፣ ኢንጂነር ይልቃል ጌትነትን፣ የሃይማኖት አባቶችን፣ አርቲስቶችን መጥቀስ ይቻላል። አንድ ንግግር […]

ያልተዘመረላት፣ ያልተነገረላት ጀግና ኢትዮጵያዊት ሴት ናት። እንዴሌሎች “እኔ ምን አገባኝ ? አርፌ ልቀመጥ” ብላ፣ ባርነትንና ዉርደትን አሜን ብላ ተቀብላ፣ ሕሊናዋን ሸጣ፣ የገዢው ፓርቲ አዉደልዳይ ሆዳም ካድሬና አገልጋይ ሆና ፣ በዘረኘንትና በጠባብነት በሽታ ተለክፋ መኖር ትችል ነበር። ግን አላደረገችውም። ከደቡብ ክልል ከወላይታ ሶዶ ናት። ሃይለማሪያም ደሳለኝ መጣሁበት ካለው። እንደ ሃይለማሪያም ደሳለኝ የሌሎች አሽከር አልሆነችም። እንደ ኃይለማሪያም […]

የአንዲት ትሁት ኢትዮጵያዊት ባላቤትና የልጅ አባት ነዉ። የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ብሄራዊ ምክር ቤት ወጣት አመራር አባል ነበር። በፓርቲዉ ዉስጥ፣ በዉጤት ላይ የተመሰረተ፣ የሰለጠነ ሰላማዊ ፖለቲካ ያራምድ የነበረውን በወያኔ ሕጋዊነትን በጉልበት የተነጠቀ የአንድነት ፓርቲ አደራጅ ነበር። በሐሰት የሽብርተኝነት ክስ ይከሰሳል። ምንም እንኳን በአገራችን የሕግ ስርዓት እንደሌለ ቢታወቅም፣ የአገዛዙን ሕገ-አራዊነትን ለማጋለጥ ሲል፣ ራሱን ለመከላከል ሞከረ። ሕግን […]

ጀግናችንን ፍቱልን!! ይህ በፎቶው ላይ የምትመለከቱት የነፃነት ታጋይ የቀድሞው አንድነት ፓርቲ መስራች አባል፣ የወረዳ 2/14 ሰብሳቢ እንዲሁም የብሄራዊ ምክር ቤት አባል ነው:: ለሰው ልጆች ያለውን አክብሮት እና ፍቅር የትግል አጋሮቹ እንዲሁም የስራ ባልደረቦቹ እና እውቀቱን ሳይሰስት የሚለግሳቸው ተማሪዎቹ ምስክርነት የሚሰጡለት የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ::ናትናኤል መኮንን ይባላል:: በቅርብ የምናውቀው ጓደኞቹ ሆድዬ በሚል ቅፅል ስም እንጠራዋለን። ለሰው […]

አቶ ብርሃኑ ወንድማገኝ በነአንዱዋለም አራጌ ላይ ክስ ያቀረበ አቃቤ ሕግ ነው። ይህ የሕግ ሰው ነኝ ባይ ካድሬ፣ በወያኔ ኢቲቪ ቀርቦ «አንዱዋለም አራጌን በተመለከተ፣ የግንቦት ሰባትን ተእልኮ ለማስፈጸም አገር ዉስጥ በሕቡእ (ስዉር) ይንቀሳቀሳል። በሰላማዊ ትግል እንታገላለን የሚሉ የፓርቲዎችን ሽፋን አድርጎ ሲንቀሳቀስ የነበረ በመሆኑ በቂ ማስረጃ አቅርበናል» ሲል ነበር የተናገረው። አንዱዋለም ያደረጋቸው የነበሩ እንቅስቃሴዎችን በሙሉ ሲያደርግ የነበረው […]

የታሰሩትን ማሰብ፣ ለታሰሩት መቆም ፖለቲካ ብቻ ሳይሆን ሰብዓዊነት ነው። ዜጎች በዉሸት ሲታሰሩ፣ ፍትህ አጥተው ሲጉላሉ፣ ሐሳባቸውን በነጻነት በመናገራቸው ብቻ ወንጀለኛ ወይንም ሽብርተኛ ተብለው ስታሰሩ፣ በእስር ቤት ራቁታቸውን ሆነው ሲደበደቡ፣ ወንዶች ብልታቸው ሲቀጠቀጥ ፣ ሴቶች በወንድ መርማሪዎቻቸው ፊት ጅምናስቲክ እንዲሰሩ ተደረጎ ክብራቸዉን የሚነካ ነገር ሲፈጸምባቸው፣ በፍርድ ቤት ፍትህ ማግኘት ሳይቻል ሲቀር፣ ዳኞች ከደህንነቶች “ይሄን ፍረዱ፣ ይሄን […]

የቀድሞው አንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራር የነበረውና አገዛዙ ጥርስ ውስጥ በመግባቱ ‹‹ሽብርተኛ›› በመባል የእድሜ ልክ እስራት የተበየነበት ወጣቱ ፖለቲከኛ አንዷለም አራጌ ሁለተኛ የሆነውን የፖለቲካ መፅሐፍ ቃሊቲ እስር ቤት ሆኖ አበርክቷል፡፡ ቁርጠኛና የፅናት ተምሳሌት እንደሆነ የሚነገርለት አንዷለም ከዚህ በፊት ‹‹ያልተሄደበት መንገድ›› የሚል መፅሐፍ ከታጨቁባት እንድ ክፍል ውስጥ ሆኖ በማይመች ሁኔታ እስረኞች ሲተኙና በብርድ ልብስ ተሸፍኖ በመፃፍ ለሕትመት […]

የኢትዮጵያ ሰላማዊ ትግል አራማጆች፤ ከሌሎች ሰላማዊ ትግል አራማጆች የምንማረው በክፍል አንድ፤ የሰላማዊ ትግሉ በአሁኑ ሰዓት በኢትዮጵያ ምን እንደሆነ ገልጫለሁ። በክፍል ሁለት ደግሞ፤ ስለሰላማዊ ትግሉ ያለንን ግንዛቤ አሳይቻለሁ። በዚሁ በሶስተኛው ክፍል ላይ፤ በኢትዮጵያ የሚካሄደው ሰላማዊ ትግል፤ ከሌሎች ከዚህ ቀደም የሰላማዊ ትግል ካካሄያዱ ሀገሮች የምንማረውን ተመክሮ እዘረዝራለሁ። ሰላማዊ ትግሉ፤ ዕለት በዕለት በገዥው ወገንተኛ አምባገነን ገዥ መንግሥት ፊት […]

ወያኔ ጭንቅ ውስጥ ሲገባ አጣብቂኙ አላላውስ ሲለው ከሚወስዳቸው እርምጃዎች አንዱ እስረኞችን መፍታት ነው::በዛሬው እለትም የተደረገው ይህ ነው:: የውጪ ሃይሎች ጫና የኦባማ ወደ አፍሪካ ሕብረት መምጣት እና ተመሳሳይ የሆኑ ጉዳዮች እንዲሁም በአራቱም አቅጣጫ የተስፈነጠረው የባሩድ ሽታ ጦርነት ለመጀመር ሕዝብን ማማከር የሚሉ አባዜ ተደማምረው ዛሬ ቂሊንጦ ወያኔን አውልውታል:: ሁለት እና ሶስት እስረኛ አሊያም አስር እና ሃያ እስረኛ […]

የኢትዮጵያ ነጻ ፕሬስ ጋዜጠኞችን “አሸባሪዎች” ብሎ በማሰር እና ከአገር እንዲሰደዱ በማድረግ የኢህአዴግ መንግስት ያላቋረጠ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን ሲፈጽም ቆይቷል። ይህን የሰብአዊ መብት መተላለፍ በመቃወም፤ በአገር ውስጥ እና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ድምጽ ለሌላቸው ድምጽ በመሆን ወገናቸን ታድገዋል። ሃሳባቸውን በነጻነት በመግለጻቸው ብቻ፤ “አሸባሪ” ተብለው በእስር ሲማቅቁ ከነበሩት ጋዜጠኞች እና ጦማርያን መካከል ተስፋለም ወልደየስ፣ ዘላለም ክብረት፣ አስማማው ሀ/ጊዮርጊስ፣ […]

በመበስበስ አደጋ ውስጥ የተዘፈቀው እና ማጣፊያው ያጠረው የወያኔው አምባገነን ቡድን ለስልጣኑ እድሜ መርዘም ከምእራባውያን ጉያ መወሸቁን እና አስፈላጊውን የእድሜ ማስረሚያ ለማግኘት ፈቃዳቸውን ለመፈጸም እየተደራደረ መሆኑ ታውቋል:: በዚህም መሰረት እስካሁን ድረስ በቀረቡ የውይይት ሃሳቦች ላይ ሁለቱን በሂደት ላይ ቢያስኬደውም ምእራባውያን ዲፕሎማቶች ግን መተማመኛ እንፈልጋለን ሲሉ አጥብቀው ወጥረው ይዘውታል የሚሉ መረጃዎች ተገኝተዋል:: ከድርድሮቹ ሁለቱን ማለትም ተቃዋሚዎችን በመጭው […]

ለኢህአፓ ሲምፖዝየም የቀረበ ወዴት እየሄድን ነው? § ዛሬ፣ የኢትዮጵያን ህልውና የሚፈታተኑ፣/ መኖሯን የማይሹ፣/ ከቻሉም የየራሳቸውን የጎጥ መንግስታት ለማቋቋም የሚፈልጉ ኃይሎች አጋጣሚው እስከሚፈጠርላቸው እየጠበቁ ነው። § ዛሬ ኢህአዴግ በሚከተለው ፖሊሲ ኢትዮጵያ ለክፋ አደጋ እየተጋለጠች ነው። § ዛሬ፣ በዘር የተደራጁ ኃይሎች አመቺ አጋጣሚ እየጠበቁ ናቸው። § ዛሬ እነ አይሲስና መሰል ኃይሎች ምን እንዳዘጋጁልን አናውቅም። አርፈው እንደማይተኙ ግን […]

በድርጅት ከዚያም ከፍ ብሎ በመንግስት ደረጃና በሃገር ደረጃ ግምገማ ማድረግ ወሳኝ ጉዳይ እንደሆነ ሁሉ ያምናል። የኣንድ ድርጅት ብቃትም በግምገማው ችሎታና ጥራት ሊለካ ይችላል።የኣንድ ሃገር የፖለቲካ መረጋጋት በፖለቲካ ለሂቆቹ የጠራ የሃገር የምናብ ስእልና ብስለት ሊለካም ይችላል። የፖለቲካ ቤቶች ሲኮለኮሉ፣ ፖሊሲዎች ሲቀረጹ ከፍ ያለ ግምገማን ይጠይቃል። ሃገሪቱ ያለፈችበትን የህይወት ጎዳና፣ የገጠማትን ችግር መንስዔና ውጤቶች በሰፊው መገምገም ለሚመሰረቱ […]

በክፍል አንድ፤ የሰላማዊ ትግሉ በአሁኑ ሰዓት በኢትዮጵያ ምን እንደሆነ ገልጫለሁ። በዚሁ ላይ፤ የሰላማዊ ትግሉ ከተወዳዳሪ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ ጋር ያለውን ልዩነት አሳይቻለሁ። በተጨማሪ ደግሞ፤ የሰላማዊ ትግሉ የሚካሄደው በአንድ የሕዝባዊ ንቅናቄ ድርጅት ሥር ብቻ መሆኑንና፤ አማራጭና ተለዋጭ እንደሌለው አስምሬበታለሁ። በሂደቱ መሰባሰቢያ የሆኑትን ሀገር አቀፍ የትግል ዕሴቶች አስቀምጫለሁ። በዚህ ክፍል ሁለት ደግሞ፤ ስለተሳሳተው የሰላማዊ ትግሉ ግንዛቤያችን አስረዳለሁ። ባጠቃላይ፤ […]

ምርጫው ወያኔ በሚፈልገው እንደውም ባቀደው መንገድ አጠናቋል። “እረጭ ያለ ምርጫ”። እስከቅርብ ጊዜ እንዲደርሰን የተደረገው መረጃ ምርጫውን በመቶ ፐርሰንት ማሸነፋቸውን ነበር። አሁን ለይቶለታል። በመቶ ፐርሰንት ማሸነፋቸውን ብቻ ሳይሆን በተወሰኑት ምርጫ ጣቢያዎች ላይ አገኘንም የሚሉት ድምጽም በተመሳሳይ መቶ ፐርሰንት እንደሆነም ነው። ሌብነቱ እንዳለ ሆኖ ምርጫውን ከዚህ በተሻለና በሚመስል መንገድ ከውኖ በመንግስትነት ለመቀጠል መሞከሩን የሚያውቁት ነበር። አልፈለጉትም እንጂ […]

ብቻውን ሆኖ ከጥግ ቆሞ ይቆዝማል። ጸጉሩን እየፈተለ ይናደዳል . . . ብቻውን ያልጎመጉማል። ትንሽ ቆይቶ ያለቅሳል። ለጉድ! ያነባዋል። ሰው እንዳለ እንደሌለ አካባቢውን ይቃኛል። ገና ወደዚህ አካባቢ እንደመጣ ሲብስበት በሰው ፊት ያለቅስ ነበር። አሁን አሁን ግን ሲያለቅስ ሰው ሲያየው አይወድም። መጀመሪያ አካባቢ ጎረቤቶቹ ሲያለቅስ ሲመለከቱ ያጽናኑት ነበር። በኋላ ግን ቀውሷል ብለው ደመደሙ። እንዲያው በደፈናው ግማሾቹ ፍቅር […]

እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለትግሬዎች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለኦሮሞዎች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለአማራዎች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለሶማሌዎች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለአፋሮች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለኦጋዴኖች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለአኙዋኮች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለሲዳማዎች ጥብቅና […]

‘የአፍሪቃ ድሃ ባይጠግብም እንኳ ቀምሶ ካደረ ይበቃዋል’ አይነት ንቀት የተሞላው የምዕራቡ አለም ምልከታ ከመቼውም ጊዜ በከፋ መልኩ አፍጦና አግጦ እየታየ ነው፡፡ በርሃባችንና በእርስ በእርስ መናቆራችን ለዘመናት ሲነግዱበትም ሲማረሩበትም ቆይተዋል፡፡ ዛሬ ዛሬ የመጫወቻው ካርድ ተቀይሮ ለአፍሪቃ አንባገነኖች አንድ ቃል ተለጥፎላቸው ካሳላፍነው ታሪክ ምናልባትም በከፋ መልኩ ጉዟችንን ቀጥለናል፤ የኋሊት ይሁን ወደፊት እርግጠኛ አይደለሁም፡፡ ነገር ግን የምዕራቡ አለም […]

ኢትዮጵያዊያን፤ ተከታታይ አምባገነን መሪዎችን ከነአገልጋዮቻቸው ለማስወገድና የሕዝቡን የሥልጣን ባለቤትነት ለማረጋገጥ የምናደርገው ትግል፤ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተላለፈ ነው። በ ፲፱፻፷፮ ዓመተ ምህረት ሕዝቡ የተነሳባቸው የመብትና የመሬት ባለቤትነት ጥያቄዎች አሁንም አልተመለሱም። ይኼው ሃምሳ ዓመት አለፈው። ይባስ ብሎ ሕዝቡን የመንግሥት አገልጋይ አድርጎ የሚጠቀም ጠባብ አምባገነን ገዢ፤ በሀገራችን ነግሷል። ይኼን መንግሥት ለማስወገድ የሚደረገው ትግል ማዕከል የለውም። በሀገር ቤት ከፍተኛውን […]

በሕብረተሰባች ውስጥ ንዝህላልነት ወይም ዳተኛነት ጎልቶ ይታያል፤ ራሱን፣ ትውልዱን ፣ሀገሩን ጭምር፣ለዘለቄታው ለሚጠቅሙ ጉዳዮች ላይ ያለው ተሣትፎ የቀዘቀዘ ነው። መንስዔውን ለመግለጽ በተረጋገጠ እውነት ላይ የተመሠረተ ማስረጃ የለኝም። ሆኖም በጋራም ሆነ በተናጠል ለሚመራበት፣ የፖለቲካ ሥርዐት በአሉታም ሆነ በአዎንታ ፍላጎቱን በነፃነት መግልጽ አይችልም፤ ላለፉት ሁለተ አሥርት ዓመታት በቁርጥኝነት ራሱን ገልፆ ለራሴም ለሀገሬም ይጠቅማሉ በሎ ያመነበትን ይዞ የቀጠለበት ሁኔታ […]

በጭካኔ ጥበብ ተንኮል የተካኑ፤ ስብዕናን ያጡ ለውነት የመከኑ፤ በሐሰት ተጠምቀው በውሸት የፀደቁ፤ በሌላው መከራ ሳቁ ተሳለቁ:: ሊጥሉት ሞክረው አልወድቅም ቢላቸው፤ ቀጥቅጠው ገደሉት በፈሪ ዱላቸው። በድቅድቅ ጨለማ ተስፋ በታጣበት፤ የነፃነት ትግል በደበዘዘበት፤ ሣሙኤል አወቀ እንደሻማ በርቷል፤ ለወገኑ ክብር በሕይወቱ ከፍሏል። ፈለጉን ተከተል አደራ ብሎሃል፤ ደሙ ከአጥናፍ አጥናፍ ይጣራል ይጮሃል፤ እምቢ በል ወገኔ ተነሣ ይልሃል፤ ፀጥ ያለው […]

“ለማንኛውም የምከፍለው ዋጋ ለለሃገሬና ለነፃነት ነው፡፡ በአካል ብታሰርም ህሊናዬ አይታሰርም፡፡ ከገደሉኝም ትግሌን አደራ!!! አገራችን የወያኔ ዘረኞች ብቻ መፈንጫ መሆን የለባትም! ትግላችን የነፃነት፤ ጉዞአችን ጎርባጣ፤ መድረሻችን ነፃነት፤ ታሪካችን ዘላለማዊ ነው፡፡” ሳሙኤል አወቀ ፊስቡክ ገፅ ላይ የተገኘ ሰኔ 8/2ዐዐ7 ዓ.ም፡፡ ምስራቅ ጎጃም ግንደ ወይን 1978 ዓ/ም ተወልዶ – በህግ የዲፕሎማ እና ዲግሪውን ሰርቷል፡፡ ሣሙኤል አወቀ የሠማያዊ ፓርቲ […]

በሽብርተኝነት ክስ ተመስርቶባቸው የሚገኙትና ጉዳያቸው እየታየ የሚገኘው እነዘላለም ወርቅአገኘሁ ከረፋዱ 4፡30 ላይ ልደት በሚገኘው 19ኛ ወንጀል ችሎት ቀረቡ፡፡ ችሎቱ ዛሬ ተሰይሞ የነበረው በተከሳሾቹ ላይ አቃቤ ህግ ባቀረበው የሰነድና የሰው ማስረጃ ላይ ብይን ለመስጠት እንደሆነ ያወሱት የመሃል ዳኛው ሸለመ በቀለ፣ አቃቤ ህግ ለአራተኛ ጊዜ ተጨማሪ ማስረጃዎችን እንዳቀረብ ጊዜ ይሰጠኝ በሚል ያቀረበው ጥያቄ ችሎቱ ያልተቀበለው በመሆኑ ውድቅ […]

ማስታወሻ ፥ (የዚህን ጽሁፍ መሰረታዊ ይዘት በቅርቡ በተካሔደው ኢሳት ባዘጋጀው ጉባዔ ላይ አቅርቤው ነበር። የኢትዮጵያን ሁኔታዎች አዘውትሮ እንደሚከታተል ኢትዮጵያዊ በሀገራችን የሰፈነው ዘግናኝ ድህነት የፈጠረውን አሳዛኝና አዋራጅ ስደትና ወደፊትም መፍትሔ ካልተበጀ ሊፈጥር የሚችለውን ችግር ገምቼ የባሰ ድህነት ውስጥም ሳንዘፈቅ ችግሩን ምን ብናደርግ ነው መቋቋም የሚቻለው በሚለው ጥያቄ ላይ ሳሰላስል የመጣልኝ ሀሳብ ነው። የሰጠሁት የመፍትሄ ሃሳብ በጉባዔው […]

ከሁሉም በማስቀደም የከበረ ሰላምታዬ በያላችሁበት ይድረሳችሁ። በዋነኛነት ይህንን ደብዳቤ ልጽፍ ያነሳሳኝ ሰሞኑን በአንድ በጥላሁን ገሰሰ ስም የሚነግድ “መስፍን” በዙ የተባለ ተራና ስብእና የጎደለው አጭበርባሪ ግልሰብ ታማኝ በየነ ለምን ክብርና ሽልማት አገኘ በሚል በአደባባይ “ታማኝ በየነ ገዳይ እና ከፋፋይ” ነው ከማለት አልፎ ግለሰቡ በጥላሁን ገሰሰ ስም (Tilahun Gesesse TV / TGTV) በሚለቀው እውር ድንብሩ በወጣ ቪዲዮ […]

የሺዋስ አሰፋ ከተቀመጠበት አልነሳም አለ ‹‹ምስክሬ ላይ ዛቻ እና ድብደባ ስለተፈጸመ ምስክርነቱ በዝግ ችሎት ይሁን›› አቃቤ ሕግ ‹‹በማስረጃ ባልተረጋገጠ አቤቱታ ችሎት በዝግ ሊታይ አይገባም›› የተከሳሽ ጠበቆች ‹‹ሞት የሚያስቀጣ ክስ ቀርቦብን ጉዳያችን በአደባባይ መታየት አለበት፤ እናንተ ብቻ አይደላችሁም ፈራጆች…›› ዳንኤል ሺበሺ ‹‹ምስክርነቱ በዝግ ችሎት የሚታይ ከሆነ ዛሬውኑ የምትፈርዱብንን ተቀብለን ለመመለስ ዝግጁ ነን›› ሀብታሙ አያሌው ‹‹የአቃቤ ህግን […]

የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ፤ የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ንቅናቄና የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ሰላማዊ ንቅናቄ ደጋፊዎች ኅብረት ጋር በተደረጉ ተከታታይ የሁለትዮሽ ውይይቶችና ስምምነቶች፡ ህዝባችን ላለፉት 24 ዓመታት ያለነፃነት በህወሓት የግፍ አገዛዝ ሥር ፍዳውን የሚያይበት ዋና ምክንያት፤ ሕዝብን መሠረት ያደረገና ብሄራዊ ጥቅምን ያስቀደመ፤ በአንድ ማዕከል የሚንቀሳቀስ ሁሉን አቀፍ የአማራጭ አካል በማቋቋም ሥርዓቱን ለማስወገድ […]

ገና ከጅምሩ፣ የተቃዋሚ ፓርቲወችን በመበታተን፣ መሪዎችንና አባላቶቻቸውን በማሰር፣ በማሳደድና በማዋከብ፤ ነጻ የሃሳብ ልውውጥ እንዳይኖርና አማራጭ ሃሳቦች ለህዝብ እንዳይደርሱ ነጻ የመገናኛ ብዙሃን ጋዜጠኞችንና ጦማራውያንን በግፍ ወደ እስር ቤት በመወርወርና የሚወዷትን ሀገራቸውን ጥለው እንዲሰደዱ በማድረግ፤ ከአገዛዙ ጋር እጅና ጓንት ሆኖ በጭቆና መሣርያነት የሚያገለግለውን የምርጫ ቦርድ በመጠቀም ተቃዋሚ ፓርቲዎችን በማፈራረስ የጀመረው ምርጫ ተብየ በትናንቱ እለት ተካሂዷል። በዚህ ምርጫ […]