በአማራ ከልል የህወሀት ጉዳይ አስፈፃሚ የሆነው የብአዴን ኮሚኒኬሽን ሐላፊ አቶ ንጉሱ ጥላሁን የስርጭት አድማሱ በአዲስ አበባና ዙሪያ ብቻ በተገደበው ሸገር ኤፍ.ኤፍ.ኤም ራዲዮ ቀርበው ‹‹ሕዝባዊ ንቅናቄ እያደረገ ባለው የአማራ ክልል ህዝብ ላይ የመከላካያ ሰራዊት እርምጃ እንዲወሰድ ታዟል›› ብለዋል!! ይህ የዘር ፍጅት የታወጀው በምእራብውያን አጋዥነት በቆመው የህወሀት ስርዓት መሆኑ አፅእኖት ሊሰጠው ይገባል!! በተያያዘ ዜናም ዛሬ ማምሻውን ሀይለማሪያም ደሳለኝ […]

ነሐሴ 22/2008 ዓም ከባህርዳር አካባቢ ተነስቶ በሀሙሲት አድርጎ በደብረታቦር አድርጎ ወደ መቀሌ በመጓዝ ላይ የነበረ ወታደሮችን የጫነ ኦራል ጉመራ ወንዝ ላይ በጀግኖቹ የጎንደር ወጣቶች ጉመራ ወንዝ ላይ ድልድዩን በመዘርጋታቸው መሻገር ባለመቻሉ መሄጃ ያጣው ሠራዊት ወደ ጎንደር ለመመለስ ተገዷል ከጉማራ ሸሽቶ ወደ ጎንደር ሲሮጥ ሌሎቹ ጀግኖች ርብ ወንዝን በመዘርጋት መውጫ ቀዳዳ አሳጥተው እየተንከራተተ እንደሚገኝ ታውቋል. ወረታ […]

በአሁኑ ሰዓት ደብረማርቆስ ከተማ በአጋዚ ወታደር መወረሯን መረጃ ደርሶናል፡፡ ከፍተኛ ውጥረት ላይ ትገኛለች፡፡ ማርቆስን ጥቁር ደመና ተጭኗታል፡፡ ህዝቡ በከፍተኛ ተጠንቀቅ ላይ ይገኛል፡፡ ለአጋዚ ወታደር የምግብና የመጠጥ አቅርቦት የሚሰጥ ሆቴል ካለ ህዝቡ እርምጃ ለመውሰድ እንደሚገደድ አስጠንቅቋል፡፡ ባለፈው በተደረገው ከፍተኛ ህዝባዊ ተቃውሞ የትልቅ ሆቴል ህዝባዊ ወገንተኝነቱን ወደ ጎን በማለት የሰረታው ስህተት ዋጋ እያስከፈለው ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ ዋናው […]

የሰሜን ጎንደር ዞን አድማ በታኝ ም/አዛዥ ኢንስፐክተር መልካሙ የሺዋስ ረዕቡ ዕለት ከስራ ተሰናበቱ። በአንገረብ ወህኒ ቤት ኮ/ል ደመቀን ለመውሰድ የተከፈተውን ዘመቻ ያከሸፈው የሰሜን ጎንደር ልዩ ሃይል አካል የሆነው የአድማ በታኝ ጦር ም/አዛዥ ኢንስፔክተር መልካሙ ”ህዝባችን ላይ አንተኩስም” በማለት የሚመሩትን ጦር አቋም እንዲይዝ አድርገዋል። በዚህም ከስራ ተባረዋል። ጦሩ ግን ከጎናቸው ነው። Filed under: NEWS

የካናዳ መንግስት በኢትጵያ ያለው ሁኔታ አሳስቦት የኢትዮጵያ የፖለቲካ ስደተኞች ወደ ሀገራቸው ቢመልሱ አዳጋ ያጋጥማቸዋል በማለት ለካናዳ መንግስት የፖለቲካ ጥገኝነት የጠየቁ አካሎች ጉዳያቸው እንደገና እንዲታይላቸው አጽድቋል። ህወሃት ትግሬን አምልጠው አገራቸውን ተነጥቀው ለካናዳ መንግስት ላመለከቱ ስደተኞች ሰናይ ዜና ነው። Filed under: NEWS

ዛሬ ጎንደር የሆነውን ተከታትለናል። ኮሎኔሉ አልቀረቡም። የህዝቡ ቁጣ ያስደነገጠው መንግስት በይፋ ያልተከፈተውን ችሎት ለሚቀጥለው ሳምንት ማስተላለፉን በውስጥ ታውቋል። እንደሰማነው ሁኔታው ያሰጋው መንግስት ኮሎኔሉ ከሚገኙበት ወህኒ ቤት ቀጠሮ ያለው እስረኛ በሙሉ እንዳይወጣ ተደርጓል። ሌላው የእሳቸውን ጉዳይ ወደ አዲስ አበባ ለመወስድ የህወሀት ደህንነቶች ጫና ፈጥረው ፋይሉ ወደ ፌደራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት እንዲዛወር ተወስኗል። የጎንደር ፍርድ ቤት እጅ […]

የኢትዮጵያ የብሐራዊ መረጃንና መከላከያ ሰራዊትን ወታደራዊ ደህንነት ዋቢ ባደረገ መልኩ በጎንደር የአማራ ህዝብ ላይ ጥቃት ለመፈጸም የሚጠይቅ ረቂቅ እንዲጸድቅ ለሚመለከተዉ ተባባሪ አካል ተሰናድቶ ቀርቧል። በዚህ ረቂቅ ዉስጥ የሐገሪቷ ክልላዊ መንግስታት እና የኢሃዲግ እህትማማች ድርጅቶች ወይም ፓርቲዎች አመጹን ማዉገዛቸዉ አበክሮ የተገለጸ ሲሆን በጎንደር የተቀናጁ የሽብር ሐይሎች መንግስት በህጋዊ መንገድ የሚፈልጋቸዉን ግለሰቦች ለህግ እንዳይገዙ ሽፋን በመስጠት በመከላከያ […]

ጎንደር ምሽቱን ውጥረት ውስጥ ናት። ሕዝቡና የህወሓት ደኅንነቶች ተፋጠዋል። የወልቃይት የማንነት ጥያቄ የሕዝብ ተወካይ እና የኮሚቴ አባል የሆኑትን ኮለኔል ደመቀ ዘውዱን በምሽት አፈኖ ለመውሰድ የትግራይ ክልል ደኅንነቶች አንገረብ እስር ቤትን ከበውታል። ሕዝቡ ኮለኔሉ ተላልፈው የሚሰጡት በሬሳችን ላይ ይሆናል እያለ ነው። በከተማዋ የተለያዩ አቅጣጫዎች የተኩስ ድምጽ ይሰማል!!!Filed under: NEWS

በታንዛኒያ በሕገወጥ ስደተኝነት ተፈርዶባቸው በእስር የቆዩ 74 ኢትዮጵያዊያን በኬንያ ድንበር ከተማ ታቬታ ተጥለዋል። ድርጊቱ ያስቆጣት ኬንያ “በዓለምአቀፍ ሕግ የታንዛኒያን ሸክም የምቀበልበት እዳ የለብኝም” በማለት አውግዛ ባሳለፍነው ማክሰኞ ከእስር የተፈቱትን ኢትዮጵያዊያን ወደ ታንዛኒያ እንደምትመልስ ገልጻለች። ታንዛንያ እስረኞቹን ወደሀገራቸው ኢትዮጵያ ከመመለስ ይልቅ ወደ ኬንያ ወስዳ የመልቀቋ ምክንያት የታወቀ ነገር የለም (ምንጭ:- ኒውስ24) Filed under: NEWS

በዛሬው እለት በ6/07/08 የአዲስ አበባና የአዳማ ዩኒቨርስቲዎች ሞትን በታጠቁ የወያኔ ጦረኞች ተከበዋል፡፡በተለይ ትላንትና ምሽቱን በአዳማ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ ክፍሎች በእሳት ሲጋዩ ማደራቸውን ከቦታው የደረሰን መረጃ ያመለክታል። እንዲሁም ዛሬ ጠዋት 1፡30 አከባቢ ላይ ትጥቃቸውን የታጠቁ የፌደራል ፖሊስ አባላት ጃንሜዳ ከሚገኘው የማዘዣ ጣቢያቸው በከባድ የጭነት መኪናዎች በገፍ እየተጫኑ የአዲስ አበባን ዩኒቨርሲቲ 6ኪሎ ካምፓስ ሲወሩ አርፍደዋል። ገጀሌው የወያኔ መንግስት ከየአቅጣጫው የሚወረወርብትን […]

የኦሮሞ ሕዝብ ያነሳውን ጥያቄ ተከትሎ በሕወሓት መንግስት የኦሮሞን ህዝብ እንዲያረጋጉ ተልከው በየሚዲያው እየወጡ ሲያስተባብሉ የከረሙት የኦህዴድ ማዕከላዊ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኦቦ ዳባ ደበሌ ከስልጣናቸው ተነስተው ወደ ኦሮሚያ የትምህርት ቢሮ ተዘዋውረዋል:: በርሳቸው ቦታ ላይም በሕወሓት መንግስት ተላላኪነታቸው “ኦቦ ገብረመድህን” የሚል ስም የተሰጠው አቶ በከር ሻሌ ይህን ቁልፍ ስልጣን መረከቡን  ምንጮች ገልጸዋል:: አቶ በከር ሻሌ ከዚህ ቀደም […]

በባ/ዳር ከተማ በትናንትናው አለት ምሽት ላይ አንድ ጎይቶም ተወልደ የተባለ የወያኔ ደህንነት በባህርዳር ከተማ ወጣቶች ተደብድቦ ቀበሌ 12 ዲሽ ቦይ ውሰጥ ተከቶ በመገኘቱ የተበሳጩት የወያኔ ደህንነቶች ታጣቂወችን እና ፖሊሶችን በማሰማራት እና በመስተባበር ዛሬ ረፋዱ 4 ሰአት ገደማ ላይ ከ300 በላይ በመንገድ ላይ በገሩፕ ሲሄዱ ያገኞቸውን ወጣቶች እየደበደቡ በመኪና እየጫኑ ወደ ተለያ ፖሊስ ጣቢያ በመውሰድ እንዳሰሮቸው […]

በአርባምንጭ ከተማ ብዙ ወጣቶች የግንቦት 7 አባል ናችሁ በሚል ሰበብ ተጠርጥረው ዕርቃናቸውን ግርፋትና የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንደተፈጸሙባቸው ከስፍራው የደረሰን ዜና አመለከተ። 20 አመት እድሜ ላይ የሚገኙ ዮሴፍ ይስሃቅና፣ እንዳሻው ወንድይፍራው ከዚህ በፊት በአርባምንጭ ከተማ ከጓደኞቻቸው ጋር ሲዝናኑ ተይዘው ከታሰሩ በኋላ እያንዳንዳቸው በ2ሺ ብር ዋስትና እንደተለቀቁ፣ “ወያኔን ሰድበዋል፣ ከአርበኞች ግንቦት ሰባት ግንኙነት አላቸው” በሚል ሰበብ እንደተደበደቡ […]

በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በተመሠረተባቸው ክስ ምክንያት በእስር ላይ የሚገኙት የትድሀር ኤክስካቬሺን ኤንድ ኧርዝ ሙቪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ዋና ሥራ አስኪያጅ እስራኤላዊው ሚናሼ ሌቭ ዮሴፍ፣ በሌላ የውጭ አገር እስረኛ ተደብድበው ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ተጠቆመ፡፡ ሚስተር ዮሴፍ በእስር ላይ በሚገኙበት በአዲስ አበባ ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር እስር ቤት ውስጥ ታኅሳስ 13 ቀን 2008 ዓ.ም. ጉዳት የደረሰባቸው፣ የሱዳን […]

ከህዝብ ተቃውሞ ጋር በተያያዘ ድርጅቱ ውስጥ ብዙ መከፋፈል እንደተፈጠረ ከዛው ከድርጅቱ ኣባሎች ሚስጥር ማፈትለክ ጀምሯል። 1፡በስርቆትና በወገን ባብሮ ኣደግ ጠ/ሚ ከዚ በፊት በይፋ ባይሆንም ስብሰባን ኣግጣሚ ኣድርጎ የተናገራቸው ትግራይን ጨምሮ መላ ሃገሪትዋ ላይ ብልሽውና ላይ የተዘፈቁ ሌባነታቸውን ለመሸፋፈንና ስማቸውን ለማደስ በኦህዴድ ኣባላት ላይ ዘምተዋል። ይህም ኣልበቃ ብሏቸው መከላከያና ፖሊስ ውስጥ ብዙ ወሳኝ ባይሆንም ኣደጋ ሊጥሉ […]

የህንዱ ካሩቱሪ ግሎባል ሊሚትድ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተበደረውን 55.8 ሚሊዮን ብር አልከፍልም ስላለ የወሰደውን 100 ሺሕ ሔክታር፣ መጋዘን፣ የሠራተኞች ተገጣጣሚ ቤትን ለጨረታ ቢያቀርብም እስካሁን በሃራጅ ተሽጦ ባንኩ ሊያገኘው የቻለው 2.6 ሚሊዮን ብር ብቻ ነው። የካሩቱሪ ዳይሬክተር ራማክሪሽና ካሩቱሪ ለ100 ሺህ ሔክታር ሊዝ መሬት አንድ ጊዜ የሚከፈል 5.6 ሚሊዮን ዶላር በባንክ እንዳይከፍል ታዞ በጥሬ ገንዘብ ጉዳዩ […]

የደንነት መስሪያ ቤቱ በሚንስትሮች ምክር ቤት በኩል ለጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያ የሰባት ቀን የጌዜ ገደብ የተሰጠው ማስጠንቀቂያ ማስተላለፉ ታውቆአል። የደህንነት መስሪያ ቤቱ በሀገሪቱ ውስጥ ሳይታሰብ የፈነዳውን አመፅ ለመቆጣጠር ምን አይነት እርምጃ መወሰድ እንዳለበት ሙሉ ስምምነት ላይ መድረስ አልችል ብሎ ሲወዛገብ መሰንበቱ ሲታወቅ ዛሪ ከጥዋት ጁምሮ ሲአካሂድ በዋለው ውይይት ላይ ግን ማንኛውንም አይነት ሀይል ተጠቅሞ አመፁን ለመቆጣጠር […]

ከጥቂቅ ደቂቃዎች በፊት ለዘ-ሐበሻ በደረሰው ዜና መሠረት በልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት አካባቢ ከፍተኛ የተኩስ ነውጥ ነበር:: የዚህ የተኩስ መነሻ ከልደታ ፍርድ ቤት እስረኞች ስላመለጡ ነው ተብሏል፡፡የአይን እማኞች እንደሚገልጹት ቁጥራቸው በውል ባይታወቅም እስረኞች ያመለጡ ሲሆን አክባቢው ተረብሾ ይገኛል፡፡ የአይን እማኞች እንደሚገልጹት እስረኞች አምልጠዋል በሚል ከሃያ በላይ የጥይት ድምጾችን ሰምተዋል፡፡ በተለይም በዛሬው ዕለት በዚሁ ፍርድ ቤት መምህር […]

እነ በረከተ መርገምት እና እነ ደመቀ መኮነን እንዲሁም ሌሎች ባለስልጣናት የሚመራ ብዛታቸው ሰባት የሚሆኑ ልዑካን ወደ መተማ ከተማ ትናንት ከቀኑ ሰባት ሰዓት ላይ ሂደዋል በስምንት የፌዴራል ፓሊስ ፓትሮል እየታጀቡ አቅንተዋል ። ከሱዳን ጋር በተሸጠው መሬት ሊመክሩ እንደሆነ የውስጥ አዋቂ በሆኑ ሰዎች መረጃው ደርሶኛል ። በዚህ ጉዳይ ላይ የመተማ ከተማ እና የሸህዲ ከተማ ነዋሪዎች በግፍ በጭነት […]

በቋራ፣በመተማና በሸንፋ በአካባቢዉ ታጣቂ አማጺያንና በመንግስት ታጣቂዎች መካከል ሳምንቱን ሙሉ የተኩስ ልዉዉጥ አለመቋረጡን፣ የሞቱ ሰዎች መኞራቸዉ፣መንገድ መዘጋቱን የአካባቢው ነዋሪዎች ለቢቢኤን ገልጸዋል። በምእራብ ትግራይ ወልቃይት ጠገዴን ወደ አማራዉ መስተዳድር ለመመለስ የሚደረገዉ ጥረት ተጠናክሮ ቀጥሏል። ይህንንኑ በመስጋት ብአዴን የወልቃይት ህዝብንና ኢህአዴግን ለማሸማገል የሚያደርገዉ ጥረት ተቀባይነት እንዳላገኘ ታዉቋል። የወልቃይት ተወላጆች ለቢቢኤን እንደገለጹት ሽምግልና ህዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ የህዝብ […]

Everything is destroyed or burned at Sola Grow, a company that grows seedlings. When protests in Ethiopia, three Dutch agricultural businesses as well as destroyed. A rose grower, a seed company and a grass and livestock farm were targeted by violent protesters. “Our guards have their guns empty shot in the air, but the attack was […]

ትናንት በባኮ ከፍተኛ ተቃውሞ ተቀስቅሶ ከተማይቱ በተኩስ ስትናጥ ቆይታለች ። ወደ ነቀምት ያመሩ የነበሩ የህዝብ ማመላለሻ አውቶብሶች በባኮ ለማለፍ ተቸግረው ባኮ መግቢያ ላይ ለመገተር ተገደዋል ። በባኮ ተቃውሞ የፖሊስ መኪኖችና ድርጅቶች ተቃጥለዋል ።የአጋዚ ልዩ ኃይሎች ባኮ ከገቡ በኋላ የግብርና ኮሌጁን በመቆጣጠር ከመቶ በላይ ተማሪዎችን በኦራል መኪና ጭነዉ ከከተማዋ ውጪ በመውሰድ ፎቶግራፍና እና ቪድዮ ቀርፀዋቸዋል፡፡ ተማሪዎቹን […]

ከአዲስ አበባ ጎንደር የገቡት የአገዛዙ ባለስልጣናት የህወሓቱ አባይ ፀሀዬ፣ የህወሓት ተላላኪ የሆነው ብአዴን ቁንጮዎች በረከት ስምዖንና አዲሱ ለገሰ ናቸው፡፡ የክልሉ ሹም ገዱ አንዳርጋቸውም በአጃቢነት ተገኝቷል፡፡ አባይ፣ በረከትና አዲሱ በትናንትናው ዕለት የዞኑን ካቢኔ አባላትና ጥቂት የስርዓቱ ደጋፊ የሆኑ የከተማው ነዋሪዎችን በጎሃ ሆቴል ሰብስበው በጎንደር ስለሰፈነው አለመረጋጋት፣ አመፅና ጦርነት ለማነጋገር ሞክረው “ይህ ሁሉ ችግር ከደረሰና ሁኔታው ከቁጥጥር […]

በአዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል ውስጥ መብራት ለሀያ ሰዓታት ያህል በመቋረጡ ምክንያት በፅኑ ህክምና ክፍል (ICU) ውስጥ የነበሩ ሦስት ህሙማን ለሞት ተዳረጉ፡፡ ህዳር 20 ምሽት ላይ ለ20 ሰዓታት መብራት ተቋርጦ በመቆየቱና የሆስፒታሉ ጀነሬተር ተበላሽቶ በመቀመጡ የተነሳ በፅኑ ህክምና ክፍል የነበሩ አንዲት ወላድ እናትና ሁለት ሌሎች ህሙማን ህይወታቸው እንዳለፈ ምንጮች ገልፀዋል፡፡ ከይርጋለም ከተማ ወደ ሆስፒታሉ ሪፈር ተደርጋ […]

በከፍተኛ ድርቅ ተመትተው ነዋሪዎቻቸው ክፉኛ ለጠኔ ተጋልጠው የሚልሱት የሚቀምሱት በማጣታቸው ከሞት አፋፍ ላይ ሆነው የሚገኙባቸው አምስቱ ቀበሌዎች ጨጨሆ፣ ፈንጠርያ፣ ቀንጠብጣ፣ አይጠላ እና እንድ ሌላ ለጊዜው ስሙን ያላወቅነው ቀበሌ ናቸው፡፡ በሰሜን ጎንደር የወገራ ወረዳዎቹን ሶሚያ፣ ጓሪ፣ ግጭሆ እና ቧግሽ የተባሉትን አራት ቀበሌዎች ጨምሮ እስካሁን ዘጠኝ ቀበሌዎች ክፉኛ በድርቅ ተመትተው ከ50ሺህ እስከ 60 ሺህ ህዝብ ተርቦ የስደትና […]

በትናንትናው ዕለት አመሻሽ ላይ አስሩ የፌደራል ፖሊሶች መጀመሪያ አንድ አይሱዙ የጭነት መኪና በኃይል በማስገደድ አስቁመው የተሳፈሩ ሲሆን መኪናው መንቀሳቀስ ሲጀምር “የጫንካቸውን ፖሊሶች አራግፍ አለያ ከነንብረትህ አብረህ ትጋያለህ!” የሚል የስልክ ማስጠንቀቂያ መልዕክት ለአሽከርካሪው በመድረሱ አሽከርካሪው መኪናውን አቁሞ ፖሊሶቹን “አልሄድም” ይላቸዋል፡፡ ቀጥሎም ፌደራል ፖሊሶቹ ሾፌሩን ለማንገራገር ሞክረው ትዕዛዛቸውን በቀላሉ ሊቀበል ባለመቻሉ ስልክ ተደዋውለው ሌላ ላንድ ክሩዘር መኪና […]

ራያ ቆቦ አካባቢ በኢትዮጵያ እጅግ ለም ከሚባሉ መሬቶች አንዱ ነው። ወያኔ በምስራቁ አቅጣጫ ከዓለታማ ክልላቸው ባሸገር ያሉትን ለም የወሎ ወረዳዎች ከወሰዱ ቆዩ ኮረም፣መሆኒ፣ራያ፣አዘቦ….ልጆቹም የአማርኛ መጻህፍቶች እየተቃጠሉ በትግርኛ እንዲማሩ ተደረገ። አሁን ደግሞ ዓይን ባወጣ መልኩ ቆቦ ወረዳን ለመዋጥ አሰፍስፏል። ድንበራችን አለውሃ ድረስ ነው የሚለውን ትርክት በየቀኑ ከሊቅ እስከ ደቀቅ የሚያነበንቡት ነው። የህወሀት ማባበያ የሚሆኑ አሳሂ ስልቶችም […]

ካለፈው አመት የፈረንጆቹ ሰኔ ወር መባቻ ላይ ወደ ኤርትራ ሲጓዙ የመን(ሰነኣ ) አለም አቀፍ አወሮፕላን ጣቢያ ላይ ታፈነው ለ አዲስ አበባ መንግስት ተላለፈው የተሰጡት እና ቀደም ሲልም በሌሉበት ኢትዮጵያ ውስጥ በ 2009 አኤአ የሞት ፍርድ የተፈረደባቸው የግንቦት 7ቱ ዋና ጸሃፊ የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እጣ ፈንታ ያሳሰበው አንድ ታዋቂ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት የእንግሊዝ መንግስት “ለጥቅሙ […]

ባለፈው ቅዳሜ በተነሳው ግጭት ከፖሊስና ከመከላከያ አንዳንድ ወታደሮች ቆስለዋል። የግጭቱ መንስኤ ሁለት የመከላከያ ፖሊስ አባላት በፖሊሶች መደብደባቸው ነው። ከዚህ ቀደም አንድ ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ ፍቼ አካባቢ ሰፍሮ የሚገኘውን የመከላከያ ሰራዊት አባል ከገደለው በሁዋላ፣ በመከላከያና በፖሊስ መካከል ለወራት የዘለቀ ቁርሾ እንዲፈጠር አድርጓል። ባለፈው ቅዳሜ ሁለት የመከላከያ ሰራዊት አባላት በከተማው እየተዝናኑ በነበረበት ወቅት፣ ፖሊሶቹ የደበደቡዋቸው ሲሆን፣ የመከላከያ […]

የላይ አርማጭሆ ገበሬዎች በህወሓት አገዛዝ ፌደራልና ልዩ ኃይል ፖሊሶች በገፍ እየታፈሱ ወደ እስር ቤት እየተጋዙ ነው፡፡ ዘረኛው እና ፋሽስቱ የህወሓት አገዛዝ ከፌደራል ፖሊስ፣ ከልዩ ኃይል እና ከመከላከያ ተመርጦ የተውጣጣ ሰራዊት በላይ አርማጭሆ በሚገኙ የገጠር ቀበሌዎች ማለትም በሙሴ ባንብ በጃኒካው፣ በገንበራ እና በሌሎች በርካታ አካባቢዎች ያሰራጨ ሲሆን ከሦስቱ ክፍሎች የተጣመረው ኃይል በየገበሬው መንደር ተሰግስጎ በማሸበር በመሳሪያ […]

አቶ ሬድዋን ሁሴን በሃሰት ሲምሉለት የነበረውን ወንበር አጥተዋል።… ☞ ሃይለማርያም ከኒውዮርክ መልስ ሁለት ቀን ከመኖሪያቸው እንዳይወጡ ከሰው እንዳይገናኙ ተደርገዋል።… ☞ ጥያቄ የሚያበዙት አቶ አለማየሁ ተገኑ እና አቶ ሶፊያን አህመድ ከአሽከርነት ቦታቸው ተነስተዋል።… ☞ ትግላችን ላይ በማተኮር ሕወሓትን ከነአሽከሮቹ ልናጠፋቸው ይገባል። . የሕወሓት አሻንጉሊት የሆነው ሃይለማርያም ደሳለኝ በትናንትናው እለት ባቀረበው የቸብ ቸብ ካቢኔ መሰረት ሕወሓት የጦር […]

በማይጨው ከተማ ያሉት 11 ሉኳንዳ ቤቶች ለከተማዋ ኑዋሪ የሚያቀርቡት ስጋ ለማሳረድ ወደ ማይጨው ቄራ የተዘጋጁት ከብቶች ይዘው እንዲመለሱ ተደርገዋል። የመታገዱ ምክንያ በቄራው የከብቶች ምርመራ የሚያካሂድ ዶክተር “ለእርዱ የሚበቃ ውሃ ስለ ሌለ ከብቶቻቹ ይዛቹ ተመለሱ” የሚል ትእዛዝ መስጠቱን ተከትሎ መሆኑ ባለሉኳንዳዎች ገልፀዋል። በመስቀል በዓል የማጨው ህዝብ የሚቀመስ ስጋ ማግኘት ኣልቻለም። በውሃ እጥረት ምክንያት ማይጨው በኣለ መስቀሉ […]

”ከሚያዚያ ወር ጀምሮ የ7ዓመት ግምገማ እያደረግን ቆይተናል። በዚህም ሞላ በፖለቲካ አመራር ድርጅቱን አዳክሞታል የሚል ድምዳሜ ላይ ደርሰናል። ሰራዊቱ የአመራር ለውጥ በሚፈልግበት ጊዜ ላይ በተካሄደው በዚሁ ግምገማ ሞላ ከፍተኛ ተቀውሞ ከድርጅቱ አመራሮችና አባላት ደርሶበታል። ” ”ይዞ የወጣው ታጋይ ቁጥሩ ተጋኗል። ያም ቢሆን ለስራ ተብለው(የኪነት ቡድኑ ለበዓል) የተታለለ ነው። በተቻለን መጠን አብዛኛውን መልሰናል። የተዋጋው ከእኛው ጋር ነው። […]

የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) በመቀሌ ከተማ ባደረገው ስብሰባ ላይ በጥንቃቄ ተመርጠው የተጠሩ ታማኝ ካድሬዎችና አባላት የተቃውሞ ድምጻቸውን አሰሙ፡፡ የትግራይ ፌስቡክ ተጠቃሚዎች አብዮታዊ እርምጃ ሊወሰድባቸው መሆኑ በአባይ ወልዱ የሚመራው የህወሓት አንጃ አሳወቀ። አንጃው ይህንን አብዮታዊ እርምጃ እንደሚወስድ ያሳወቀው “12ተኛ ጉባኤ እንዴት አለፈ …?” በሚል አጀንዳ በየመንግሥት መስርያ ቤቶች፣ ከመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች፣ የክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች […]

የትግራይ ክልል ሲቪል ሰርቪስ ሃላፊና የክልሉ ዳኞች ሰብሳቢ የሆኑት ወ/ሮ ትርፉ ኪዳነማሪያም በሙስና ስለተገመገሙ ከሃላፊነታቸው መውረድ አለባቸው ሲሉ የህወሓት ጉባኤተኞች የወሰኑትን ውሳኔ እስከ አሁን ድረስ እንዳልተተገበረ ተገለፀ። እንደ ምንጮቻችን መረጃ መሰረት የአባይ ወልዱ ሚስት የሆኑት ወ/ሮ ትርፉ ኪዳነማሪያም ላለፉት አመታት የትግራይ ክልል የሲቪል ሰርቪስ ሃላፊ ሆነው በሰሩበት ጊዜ በመስሪያ ቤቱ አዳዲስ ለውጦች ባለማምጣታቸው የተነሳና ጊዜው […]

Hailemaraim visits graduating troops
የወያኔ ኢህአዴግ ስርአት መከላከያ ሰራዊት ለአባይ ግድብ መስሪያ ገንዘብ እንዲያዋጡ ለቀረበላቸው ጥሪ። እንዳልተቀበሉት ምንጮቻችን ከመከላከያ ውስጥ ገለፁ፣በምንጮቻችን መረጃ መሰረት።- የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት እንደ አዲስ ለአባይ ግድብ መስሪያ የሚሆን በሚል ገንዘብ እንዲያዋጡ በአመራሮቻቸው ለቀረበላቸው ጥሪ። አንቀበልም ማለታቸውን የገለፀው መረጃው። ለቀረበው ጥሪ ሳይቀበሉት የቀሩበት ምክንያትም “ ባለፉት ጊዚያት በተደጋጋሚ የከፈልነውን ገንዘብ ቦንድ ይሰጣቸኋል ተብለን እስከ አሁን ድረስ […]

የትግራይ ነፃነት ግንባር /ህወኃት/ ገና ከፅንስሱ ሲነሳ ለሙን የሰሜን ወሎን፣ ምዕራባዊ ጎንደርን እና ምዕራባዊ ጎጃምን በማካተት ታላቁን የትግራይ ሪፐብሊክ መመስረት ግብ አድርጎ መመስረቱና ለዚህም አላማው ስኬት የቻለውን ሁሉ በማድረግ ላይ እንድሚገኝ የሚታወቅ ነገር ነው። በተለይም በወልቃይት፣ ፀገዴና አርማጭሆ ያካሄደው መስፋፍት በአካባቢው ነዋሪ ህዝብ ላይ ትውልድ ይቅር የማይለው ግፍ ፈጽሟል፡ አሁንም የመስፋፋት ህልሙን እውን ለማድረግና ቀሪ […]

የአርበኞች ግንቦት 7 የውስጥ አርበኞች ህወሓት “ክልል አንድ” እያለ በሚጠራው በጎንደር-ወልቃይት ደጃች ሜዳ ወረዳ አቤራ ቀበሌ ስልኪ ዳግባ በተባለው ቦታ ነሃሴ 23 2007 ዓ.ም በህወሓት መከላከያ ኃይል ላይ ድንገተኛ የተኩስ ውርጅብኝ በመክፈት ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ ወታደሮችን ገድለውና አቁስለው ድል ተቀዳጅተዋል፡፡ በአርበኞች ግንቦት 7 የውስጥ አርበኞችና በህወሓት የመከላከያ ሰራዊት መካከል የተካሄደው ድንገተኛ የሆነ ከባድ ፍልሚያ እኩለ […]

‹‹ችሎቱ ታሪካዊ ስህተት እየሰራ ነው›› አቶ ሀብታሙ አያሌው በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር አቶ ሀብታሙ አያሌው ነሀሴ 14/2007 ዓ.ም ከፍተኛው ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ከተከሰሰበት የሽብር ወንጀል ነጻ ነው በማለት ከእስር እንዲፈታ የሰጠው ትዕዛዝ ተከብሮ እንዲፈታ ትዕዛዝ እንዲሰጥለት ለከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት ያቀረበው አቤቱታ ውድቅ ተደርጓል፡፡ ዛሬ ነሀሴ 29/2007 ዓ.ም ልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ተረኛ […]

በአሜሪካ መንግስት ኦፊሳላዊ ድረ ገጽ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ጉዳይ አስተባባሪነት በዓለም ላይ ለተመረጡ 20 ሴት የፖለቲካ እስረኞች ለአንድ ወር የሚቆይ ዘመቻና ማስታወሻ ሊደረግላቸው ነው፡፡ ከ20ዎቹ ሴት የፖለቲካ እስረኞች መካከል ሦስቱ ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ፣ ሁሉም የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ናቸው፡፡ ከዛሬ 20 አመት በፊት ሴቶችን ለማብቃት፣ የጾታ እኩልነትን ለማስፈን እና የልጃ ገረዶችን ሰብዓዊ መብት ለማስጠበቅ የቤጂንግ መርሃ […]

ዓባይ ፀሃየ ለሀ ወ ሓ ት ኢ ህ ኣ ደ ግ በሊቀመንበር በድርጅት ሃላፊነት እጅግ ብዙ ኣጃቢና የህወሓት ሎሌ ፓርቲዎች ፈጥረዋል:: በመንግስት መዋቅር በፈደራል ጉዳዮች በስኳር ኢንዱስትሪዎች በጠቅላይ ምኒስቴር አማካሪነት ሰርተዋል:: 40 ዓመት ሙሉ በስልጣን በነበሩበት ቡዙ ስራዎች ፈፅመዋል:: በተለይ በሀወሓት ኢህአደግ ስርኣት ውስጥ ዘርፈብዙ የመልካም ዓስተዳደር የፍትህ የሰብኣዊ ዲሞክራሲ መብቶች መጠበቅ ተጥሰዋል:: በ5 ዙር […]

ወደ እንግሊዝ ሃገር የሚያስኬዳቸውን ቪዛ ተከልክለው ወደዚያው ሊያደርጉት የነበረው ጉዞ የተስተጓጎለባቸው የሰብአዊ መብት ተሟጋቹ ፕሮፌሰር መስፍን ዛሬ ዋሽንግተን ዲሲ መግባታቸውን በስፍራው የሚገኙ የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች አስታወቁ:: በቅርቡ ‘አዳፍኔ’ የተሰኘ ‘አወዛጋቢ’ መጽሐፍ ለንባብ ያበቁት እኚሁ ፕሮፌሰር ዛሬ ዋሽንግተን ዱሉስ ኤርፖርት ሲደርሱ ወዳጆቻቸው ሞቅ ያለ አቀባበል እንዳደረጉላቸው የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች አስታውቀዋል:: ፕሮፌሰር መስፍን በአሜሪካ ቆይታቸው አዲሱ መጽሓፋቸውን በዋሽንግተን ዲሲ […]

ከሰሞኑ የተቆሰቆሰዉን ጦርነት ለመከታተልና ለማጥራት በሚል የተንቀሳቀሱ የወያኔ አንጃ ወታደሮች ቡድን ጥቃት እየደረሰባቸዉ ይገኛሉ፡ ወያኔ በአዲግራትና ከማይ ጻይ ተወርዋሪ አየር መንደርደሪያ ሰፈሮች ባሻገር በተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች እያለፈና እየዘለለ የሚደርስበትን ጥቃት ለማድበስበስ በየስፍራዉ የመከላከያ ሰራዊቱ ስልጠና ላይ ነዉና የተኩስ ድምጽ ብትሰሙም እንዳትደናገጡ እያለ ከባለፈዉ መጋቢት ወር አንስቶ ወረቀት እየለጤፈና እየደሰኮረ ይገኛል። አንድ ማንነቱን ሊገልጽ ያልፈለገ የወያኔ […]

᎐ተከላከሉ ከተባሉት ተከሳሾች መካከል አራቱ ሴቶች በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር መንግስት ሚያዝያ 14/2007 ዓ.ም በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ጠርቶት በነበረው ሰላማዊ ሰልፍ ወቅት ለእስር ተዳርገው ‹‹ስብሰባ በማወክና በማነሳሳት›› የተከሰሱት እነ ሚካኤል ያሬድ ለሦስተኛ ጊዜ መከላከያ ምስክሮቻቸውን አቅርበው የነበር ቢሆንም ፍርድ ቤቱ ለጥቅምት 8/2008 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቶባቸዋል፡፡ ዛሬ ነሀሴ 28/2007 ዓ.ም በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ […]

  የቀድሞው አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ወጣት ሀብታሙ አያሌውና ሌሎች የፖለቲካ አመራሮች የልደታ ከፍተኛ ፍ/ቤት ከተመሰረተባቸው ክስ በነፃ ካሰናበታቸው በኋላ ነገ በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በተለይ ሀብታሙ አያሌው እንደሚቀርብ ባለቤቱ ወ/ሮ ቤተልሔም ገለፀች፡፡ ቤተልሔም እንደተናገረችው ባለቤቷ በነፃ እንዲሰናበት ከፍተኛው ፍርድ ቤት ከወሰነ በኋላ ባልታወቀ ሁኔታ እስርቤቱ አለቅም ማለቱንና ላልተለቀቀበት አግባብ ምንም አይነት […]

በሶማሊያ ሀገር ህይወታቸው እያለፈ ያሉ የኢትዮጵያ ወታደሮች ቁጥራቸው እየጨመረ ነው እየተላኩና ህይወታቸው እያለፈ የሚገኙትን የኢትዮጵያ ወታደሮች ከቀን ወደ ቀን ቁጥራቸው እየጨመረ እንደሆነ ከተለያዩ ያገራችን አካባቢዎች የደረሰን መረጃ አስታወቀ.በሶማሊያ ሃገር እየሞቱ ያሉትን የኢትዮጵያ ወታደሮች ቁጥራቸው ከግዜ ወደ ግዜ እየጨመረ ባለበት በአሁኑ ሰዓት የሟቾቹ ቤተሰብ በየግዜው በቴለፎን መርዶ እየደረሳቸው እንደሆነ የገለፀው መረጃው በተለይም የኦሮሚያ ክልል ህዝብ ለምንድነው […]

በስምንት ግራም ቶሪየም 100 አመት ያህል መኪና ሊያስነዳ የሚችል ማዕድን አግኝቼያለሁ. ሃኪም ንጉሴ አሰፋ. “አገር አቀፍ የባህል መድኃኒትና የህክምና ቀን” በኢትዮጵያ የምግብ መድሃኒትንና የጤና እንክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን ከአለም የጤናድርጅት ጋር በመተባበር ከትላንት በስቲያን በሃርመኒ ሆቴል ባካሄደው ስብሰባ ላይ ላለፉት ሃያ አመታት በባህል የህክምና ሙያ ላይ የቆዪት ሃኪም ንጉሴ አሰፋ ላለፋት 15 አመታት በቶሪየም ማዕድን […]

አብዛኛው ሰው በሀገሩ ኑሮ ሲጠበው፣ በሀገሩ ሰላም ሲያጣ ፣ በሀገሩ ነገሮች አልሆኑለት ሲሉ ራሱን ሊለውጥ አለያም ይደርስብኛል ሲል የሚሰጋበት ሰብአዊ መብት ረገጣ ሽሽት ወደስደት ይወጣል። አንዳንዱ እድለኛ ታስጠልለኛለች ብሎ ያላት ምድር ስቃ ትቀበለዋለች አንዳንዱን ደግሞ ህይወቱ የባሰ ቅጥአንባሩ ይጠፋውና ምነው በዚያው የሀገሬ ጅብ በበላኝ ሲል ይማረራል ለአንዳንዶች ግን ያስጠልለናል ካሉት ቦታ ሳይደርሱ በመንገድ ይቀራሉ! አንዱ […]

ሰበር መረጃ “ዛሬ ጠዋት አርበኞች ግንቦት ሰባት ባሳቻ በሰነዘረው ጥቃት ስፍር ቁጥር የሌለው የወያኔ ጋሻጃግሬዎች ሲደመሰሱ ገሚሱ ትግራይ ቦርደር ሆስፒታል እየተባለ ወደ ሚጠራዉ የህክምና ተቋም ቁስለኛ ወታደሮች ለህክምና ሲትም መዋሉን ከስፍራው ያይን ምስክር በተለይም ለ አፈትላኪ ዜና ምንጭ ዘግይቶ አድርሶናል። ይህበንዲህ እንዳለ ማይ ጻይ እየተባለ ከሚጠራዉ አካባቢ የሚነሱ ሄሊኮፍተሮች በአየር መቃወሚያ ወሰን ኢላማ ዉስጥ ገብተዋል።በተያያዘም […]

ወያኔ በመቶወቹ የሚቆጠሩ የ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙህራንን ጠራርጎ ካበረና በካደሬ ከሞላው ጀምሮ ዩኒቨርስቲው በሙስና ከመጨማለቁና የካድሬ መፈንጫ ከመሆኑ ባሻገር ወያኔ ስልጣን ከያዘ ጀምሮ ኦዲት ተደርጎ የማይታወቅ ሲሆን ከሰሞኑ ደግሞ የዩኒቨርስቲው ዶርሚተሪወች ወደ ግለሰቦች መኖርያና ክራይ እየተቀየሩ ስለመሆኑ ውስጥ አወቅ ምንጮች ዘግበዋል።ይህ በንዲህ እንዳለ የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር አድማሱ ፀጋየና ምክትላቸው ዶ/ር ጄሉ ኦመር ከሀገር መውጣታቸውን […]