(በኃይሌ ሙሉ) ምርጫ 2002 ከመካሄዱ በፊት በተፈጠረ አለመግባባት በፍርድ ቤት እስከመካሰስ የደረሱት፣ በኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው የሚመራው አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲና በፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም የሚመራው ‹‹መርህ ይከበር›› የተሰኘው ቡድን ችግራቸውን ለመፍታት እየተነጋገሩ መሆኑ ታወቀ፡፡

(በኃይሌ ሙሉ) በሱዳን መንግሥትና በሱዳን ሕዝቦች ነፃነት ንቅናቄ መካከል የተፈረመው ሁሉን አቀፍ የሰላም ስምምነት አፈጻጸምንና በሶማሊያ ጉዳይ ላይ ለመወያየት ትናንት በአዲስ አበባ ሸራተን አዲስ የተሰበሰቡት የምሥራቅ አፍሪካ በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) መሪዎች፣ ዕምቅ የነዳጅ ሀብት ባላት አወዛጋቢዋ የአቤይ ግዛት ጉዳይ ላይ …

አዲስ አበባ ላይም መፍትሔ ያጣው የአቤይ ግዛት ስጋት Read more »

(በውድነህ ዘነበ) የአዲስ አበባ ፍትሕ ቢሮ ከሪል ስቴት ልማት ጋር በተያያዘ ተፈጠረው ላለው ሕገወጥ ተግባር፣ በሕግ መጠየቅ አለባቸው ያላቸውን አልሚዎችና በቀድሞ የአስተዳደሩ ሠራተኞች ላይ ክስ ለመመስረት የሚያስችለውን መረጃ እየሰበሰበ መሆኑን፣ አንድ የአስተዳደሩ ከፍተኛ ባለሥልጣን ለሪፖርተር ገለጹ፡፡

• ምድር ባቡር የመፍረስ አደጋ አንዣቦበታል (በውድነህ ዘነበ) የኢትዮ ጂቡቲ ምድር ባቡር ድርጅት ኢትዮጵያውያን ሠራተኞች አዲስ ወደተቋቋመው የብረታ ብረትና ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን መሥሪያ ቤት እንዲዛወሩ ተወሰነ፡፡

(በምዕራፍ ብርሃኔ) የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ከህዳር 8 ቀን 2003 ዓ.ም. ጀምሮ የምግብና የትምህርት አድማ የመቱ ከመቶ በላይ የሆኑ ተማሪዎችን (ደቀመዛሙርት) ወደ ትምህርት ገበታቸው የማይመለሱና ከሆነና የኮሌጁን ምግብ የማይመገቡ ከሆነ፣ የኮሌጁን ንብረት አስረክበው ክሊራንስ በማስፈረም የትምህርት ተቋሙን በአስቸኳይ ለቀው እንዲወጡ …

መንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎቹ አድማቸውን ካላቆሙ ይባረራሉ አለ Read more »

(ዳዊት ታዬ) ላለፉት ተከታታይ አሥራ አምስት ዓመታት የአዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ የውጭ ኦዲተር በመሆን ሲያገለግል የቆየው የእንግሊዙ ኤ.ኤ ብሮሜድ ኩባንያ ውል ተቋርጦ፣ መንግሥታዊው የኦዲት አገልግሎት ኮርፖሬሽን የአዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ ኦዲተር ሆኖ እንዲሾም በባለአክሲዮኖች ተወሰነ፡፡

(በታምሩ ጽጌ) በተለየዩ ክልሎች ንግድ ፈቃድ አውጥተው በማንኛውም ክልል በመዘዋወር የኮንስትራክሽን ሥራዎችን በመሥራት ላይ የሚገኙ በርካታ የሕንፃ ተቋራጮች፣ በ2003 ዓ.ም. በኦሮሚያ ክልል በሚወጡ የኮንስትራክሽን ጨረታዎች ላይ እንዳይሳተፉ መታገዳቸውን ገለጹ፡፡

– የሥነ ምግባር መኮንኑን ጨምሮ አምስት ሠራተኞች ከሥራ ታግደዋል (በብርቱካን ፈንታ) የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሠራተኞች በመሥሪያ ቤቱ ውስጥ የተከሰቱ ሙስናዎችን በማጋለጣችን ከኅዳር 1 ቀን 2003 ዓ.ም. ጀምሮ ከሥራ ታገድን በማለት ለሪፖርተር ገለጹ፡፡

(በውድነህ ዘነበ) ቀደም ሲል በፌዴራል ትራንስፖርት ባለሥልጣን መሥሪያ ቤት ሲመራ የቆየው የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤትና አንበሳ አውቶቡስ ድርጅት ወደ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እንዲመለሱ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ተወሰነ፡፡

  – በ‹‹ነፋስ አመጣሽ ገቢ›› ላይ ግብር መጣል ይችላል (በኃይሌ ሙሉ) የአገሪቱ ኢኮኖሚ ከሚያመነጨው ሀብት መንግሥት ተገቢውን ግብር እንዲሰበሰብ የሚያስችል የገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጅ ጸደቀ፡፡

(በታምሩ ጽጌ) በአዲስ አበባ በየካ ክፍለ ከተማ በቀድሞው ቀበሌ 09/10 ነዋሪ የሆኑ የአንድ ቤተሰብ አባላት በአንድ የኖሮዌይ ዜጋ ተደጋጋሚ በደል እንደደረሰባቸውና ፍትሕ እንዳጡ በመግለጽ መንግሥት መፍትሔ እንዲሰጣቸው እየተማጸኑ ነው፡፡

ውድነህ ዘነበ | ሪፖርተር የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሁለት ክፍለ ከተሞች በሚገኙ የኢንዱስትሪ ዞኖች ውስጥ ቦታ ወስደው ባላለሙና ከተፈቀደላቸው ዓላማ ውጭ ቦታውን በሚገለገሉ አልሚዎች ላይ ዕርምጃ መውሰድ ጀመረ፡፡ ከስድስት ዓመት በፊት ከአስተዳደሩ ጋር በገቡት ውል መሠረት ግንባታ ያላካሄዱ፣ ግንባታ ያካሄዱትም …

ኩማ ደመቅሳ የአዲስ አበባ አስተዳደር በባለሃብቶች ላይ ዘመቻ ጀመረ Read more »

(በጥበበ ሥላሴ ጥጋቡ) ከወራት በኋላ በካንኩን ሜክሲኮ በሚደረገው የዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ ድርድር ከኮፐንሀገን የተሻለ ሊሆን እንደሚችል፣ ከትናንት በስቲያ በአፍሪካ ኅብረት በተደረገው የአፍሪካ አገሮችና መንግሥታት መሪዎች የአየር ንብረት ለውጥ ኮሚቴ ስብሰባ ላይ ተገለጸ፡፡

(በታምሩ ጽጌ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሕገወጥ በሆነ መንገድ መሬት አስፋፍተው ያጠሩ፣ የገዙና በሕጋዊ መንገድም ወስደው ማልማት ካልጀመሩ አልሚዎች ጋር በተያያዘ በወቅቱ የነበሩ የአስተዳደሩ ሠራተኞች በሕግ እንደሚጠየቁ ገለጸ፡፡

(በብርሃኑ ፈቃደ) አክሰስ ካፒታል የኢትዮጵያ የኤክስፖርት አፈጻጸምን አስመልክቶ በቅርቡ ይፋ ባደረገው ጥናት፣ ቻይና የኢትዮጵያን ጫት ተቀባይ ከሆኑት አገሮች በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡

(በውድነህ ዘነበ) አቶ አርከበ ዕቁባይ የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ አማካሪ ሆነው ከተሾሙ በኋላ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት በአገሪቱ የሚካሄዱ ግንባታዎችን የመምራት ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል፡፡

(በዳዊት ታዬ) የአዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ በዓለም ዓቀፍ ባንክ ዘርፍ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ምትኩ አቡሹ ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ ብሔራዊ ባንክ ትእዛዝ ማስተላለፉንና በባንኩ ፕሬዚዳንት ላይም ምርመራ ተካሂዶ እስከ ኅዳር 6 ቀን 2003 ዓ.ም. ሪፖርት እንዲያቀርብ መታዘዙ ተገለጸ፡፡

– ዓቃቤ ሕግ ያቀረበው የሞት ቅጣት ይግባኝ ውድቅ ተደረገ – የዓቃቤ ሕግ ይግባኝ በከፊል፣ የፍርደኞቹ ሙሉ በሙሉ ውድቅ ተደረገ– የብ/ጄ ተፈራ ማሞና የአቶ አሳምነው ጽጌ ንብረት እዲወረስ ታዘዘ (በታምሩ ጽጌ)

(በቃለየሱስ በቀለ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከሐምሌ 2002 እስከ መስከረም 2003 ዓ.ም. ባሉት ሦስት ወራት ጊዜ ውስጥ በተለያዩ ክልሎች በባሕላዊ መንገድ ተመርቶ በነጋዴዎች አማካኝነት የቀረበለትን 50 ሚሊዮን ዶላር ዋጋ ያለው 1,350 ኪሎ ግራም የሚመዝን ጥሬ ወርቅ እንደገዛ ታወቀ፡፡

(በአስራት ሥዩም) ሙሉ ወጪያቸውን ከመንግሥት በሚገኙ ድጐማዎች የሚሸፍኑት የመንግሥት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት፣ ከትምህርቱ በተጓዳኝ እንደ የግል ንግድ ተቋም ሆነው ተጨማሪ ገቢ ማመንጨት መጀመር አለባቸው ተባለ፡፡

– ግንባታው በሁለት ዓመታት ይጠናቀቃል (በታምሩ ጽጌ) በኢትዮጵያ የንግዱን ማኅበረሰብና የስካንዲኒቪያን አገሮች (ስዊድን፣ ዴንማርክ፣ ፊንላንድና ኖርዌይ) ባለሀብቶችን ለማገናኘት የሚያስችል ዘመናዊ የንግድ ማዕከል ሊገነባ መሆኑ ታወቀ፡፡

– የብ/ጄ ተፈራ ማሞና የአቶ አሳምነው ጽጌ ንብረት ይወረስ ተባለ– በነፃ የተሰናበቱት አራት ግለሰቦች ጥፋተኛ ተባሉ (በታምሩ ጽጌ) የሥር ፍርድ ቤት ያስተላለፈባቸውን የዕድሜ ልክ እሥራት ላይ ‹‹ቅር ተሰኝቻለሁ›› በሚል የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ በሞት እንዲቀጡለት ይግባኝ የጠየቀባቸው አምስት የግንቦት 7 ፍርደኞች …

ሰበር ዜና ፡ በግንቦት 7 ፍርደኞች ላይ የተጠየቀው የሞት ቅጣት ውድቅ ተደረገ Read more »

(በብርቱካን ፈንታ) የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ባለፈው ሰኞ የአውሮፓ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን ያቀረበውን ሪፖርት አስመልክቶ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ኢሕአዴግ ይቅርታ እንዲጠይቅ፣ ካሳ እንዲከፍልና ምርጫው እንዲደገም ጥሪ አቀረበ፡፡

ባለፈው ሰኞ የአውሮፓ ኅብረት የምርጫ ታዛቢዎች ልዑክ ያወጣውን የመጨረሻ ሪፖርት የኢትዮጵያ መንግሥት ተቀባይነት የሌለው በማለት አጣጥሎታል፡፡በትናንትናው ዕለት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ የአውሮፓ ኅብረት የምርጫ ታዛቢዎች ቡድን ያወጣው ሪፖርት የኢትዮጵያን የዴሞክራሲ ሒደት ያላገናዘበና የተሳሳተ የፖለቲካ ግንዛቤን የያዘ በመሆኑ ለሁለተኛ ጊዜ …

መንግሥት ያጣጣለው የአውሮፓ ኅብረት የምርጫ ሪፖርት Read more »

(በውድነህ ዘነበ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት በሊዝ የሚሸጥበት የአካባቢ ዋጋ ደረጃ ማሻሻያ ለማድረግ የሚያስችለውን ጥናት፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለማስጠናት ድርድር መጀመሩን የከተማው አንድ ከፍተኛ ባለሥልጣን ለሪፖርተር ገለጹ፡፡

– ‹‹ይዘጋ›› የሚለው የመጀመሪያ ደረጃና የጠቅላይ ፍርድ ቤቶች ውሳኔ ጸንቷል (በታምሩ ጽጌ) ዶ/ር አሰገደች ላቀው (ባለቤት)፣ ዶ/ር ጌታቸው ተፈራ፣ ሲስተር አበባ ኪዳኔ፣ ሲስተር ወጋየሁ ዓለሙና አረፈ ዓይኔ ገብረ እግዚአብሔር የአሰገደች የእናቶችና ሕፃናት ሆስፒታል ሠራተኞች ሲሆኑ

(በታምሩ ጽጌ) የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ‹‹የፍርድ ቤት ትዕዛዝ በመጣስ ለስምንት ወራት ያህል አስሮ አቆይቷቸዋል›› በተባሉ ተከሳሾች ምክንያት በትናንትናው ዕለት በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት 10ኛ ወንጀል ችሎት ቀርቦ መልስ ሰጠ፡፡

(በመላኩ ደምሴ) የኢትዮጵያን የከፍተኛ ትምህርት ጥራት ወደተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር የፖሊሲ አማራጮችን የሚዳስስና የውሳኔ ሐሳቦችን የሚያቀርብ ኮንፈረንስ በመጪው ማክሰኞና ረቡዕ አዲስ አበባ ውስጥ ሊካሄድ ነው፡፡