እንዴት ሰነበታችሁሳ! የሚቀጥለው ደብዳቤ አገር ቤት ያለ ‘ግራ የገባው’ የአገር ልጅ ለ‘ዳያስፖራው’ አብሮ አደጉ ጽፎት ሊሆን ይችላል ተብሎ ‘ቢታሰብም’ ችግር የለውም፡፡ ለውድ አብሮ አደጌ፣ እንደምን ከረምክልኝ፡፡ እኛ እግዚአብሔር ይመስገን ደህና ነን፡፡ እውነት፣ እውነት እልሀለሁ በሰው የላክኸው የቃል መልእክት ሲደርሰኝ ገረመኝም፣ …

‘ግራ የገባው’ የአገር ልጅ ለ‘ዳያስፖራው’ አብሮ አደጉ ……. ኤፍሬም እንዳለ Read more »

   አንድ ጥጃ የሚያሳድግ ሰው ነበር፡፡ ጥጃውን ሲፈልግ ጆሮውን ይጎትተዋል፣ ሲፈልግ በዱላ ይዠልጠዋል፣ ሲፈልግ ጨው እያላሰ ይስበዋል፣ ሲፈልግ ደግሞ በገመድ አሥሮ ያስከትለዋል፡፡ በዚህ መንገድ ሄዶ ጥጃው አደገና  ወይፈን ሆኖ ቀንድ አበቀለ፡፡ የጥጃውም ባለቤት እንደለመደው በዱላ ሊመታው፣ ጆሮውን ሊጎትተው፣ በዱላም ሊዠልጠው …

የጆሮና የቀንድ ዘመን! ዲ/ን ዳንኤል ክብረት Read more »

    ባለፈው ሳምንት፤ ከእሸቴ አሰፋ ጋር የአድዋን ድል በጊዮርጊስ እያከበርን ነበር፡፡ እሸቴ ታሪክ እያስተማረኝ ነበር፡፡ ‹‹በጠቢቡ ሰለሞን›› ጠረጴዛ ተቀምጠናል፡፡ በዙሪያችን ብዙ ሰው አለ፡፡ በዚህ መሐል ለደረጀ ደወልንለት፡፡ ከደረጀ ደስታ ጋር በስልክ ተነጋገርኩ፡፡ ከረጅም ጊዜ በኋላ ድምፁን ሰማሁት፡፡ ድምፁን ስሰማው፤ ‹‹አፈረሱት …

‹‹ወንዶች ያልተጠናቀቁ ሴቶች ናቸው›› ተፈሪ መኮንን Read more »

ተንጋለው ቢተፉ : ተመልሶ ባፉ – ወያኔን ማመን ቀብሮ ነው::ቀብሮ ብቻ ሳይሆን አቃጥሎ አመድ አድርጎ ነው:: ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎OromoProtests‬ ‪#‎EPRDF‬ ‪#‎EthiopianOppositionparties‬ ‪#‎MinilikSalsawi‬ Minilik Salsawi – Ethiopian DJ – ከሶማሊያ ከኬንያ እና ከደቡብ ሱዳን እያስኮበለሉ ልዩ ሃይል እና የፌዴራል ፖሊስ አድርጎ በመቅጠር …

ተንጋለው ቢተፉ : ተመልሶ ባፉ – ወያኔን ማመን ቀብሮ ነው::ቀብሮ ብቻ ሳይሆን አቃጥሎ አመድ አድርጎ ነው:: Read more »

በአገራችን እየተነሱ ያሉ ግጭቶች መኢአድን በእጅጉ አሳስቦታል! ከመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ I. የኢህአዴግ መንግሥት በ1983 ዓ.ም ሥልጣን ከመያዙ በፊት የኢትዮጵያ ሕዝብ በተወለደበት ቀዬ፣ በዘሩና በቋንቋው ሳይሆን በኢትዮጵያዊ ማንነቱ በመኩራት በአንድነትና በመተባበር የአገሩን ዳር ድንበር ሲያስከብርና አገሩን ሲገነባ …

በአገራችን እየተነሱ ያሉ ግጭቶች መኢአድን በእጅጉ አሳስቦታል! ከመኢአድ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ Read more »

“የንግግር ነጻነትን በማረጋግጥና ዲሞክራሲያዊ እርምጃዎችን በማጎልበት የኢትዮጵያ መንግስት ቀደም ሲል የወሰዳቸውን አዎንታዊ እርምጃዎች እንዲያጠናክ እያሳሰብን፤ በነጻ ድምጾች ላይ የሚፈጸመው አፈና ይህን መሰሉን አዎንታዊ እርምጃ ማደናቀፍ ብቻ ሳይሆን፤ የልማትና የምጣኔ ሃብት እድገትንም የሚገታ መሆኑን መጠቆም እንፈልጋለን።” የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር። …

በኢትዮጵያ በፕሬስ ነጻነትና በተቃዋሚዎች ላይ የሚደርገው ጫና እንደሚያሳስባት ዩናይትድ ስቴትስ አስታወቀች Read more »

በታዋቂው ድምፃዊ አቤል ሙሉጌታ ተደርሶ፣ዳይሬክት የተደረገው “ሽረት” ፊልም መጋቢት 24 በብሔራዊ ቲያትር እንደሚመረቅ ተገለፀ፡፡ የ1 ሰዓትከ30 ደቂቃ ርዝማኔ ባለው በዚህ ፊልም ላይ ራሱአቤል ሙሉጌታ፣ ሰላማዊት አስማማው፣ መቅደስ ባዬና ዮናስ አሰፋን ጨምሮ በርካታ ተዋናዮች የተሳተፉበት ሲሆን ፊልሙ ልብ አንጠልጣይ እንደሆነ ታውቋል፡፡ …

የድምፃዊ አቤል ሙሉጌታ “ሽረት”ፊልም ለእይታ ሊበቃ ነው Read more »

በአርባምንጭ ሆስፒታል ከ140 በላይ ህሙማን ህክምና እየተሰጣቸው ነው በደቡብ ክልል አርባምንጭ ዙሪያ አማሮና አባያ ወረዳዎች በኦሮሚያ ክልል በቦረና ዞን ገላን ወረዳና በሶማሌ ክልል ሞያሌ ወረዳዎች ላይ የኮሌራ ወረርሽኝ መከሰቱን የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ ሚኒስቴር መ/ቤቱ ሰሞኑን በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ …

በደቡብ፣ በኦሮሚያና በሶማሌ ክልሎች የኮሌራ ወረርሽኝ መከሰቱ ተነገረ Read more »

Addis Admass : ኤጀንሲዎች ህጻናትን እየላኩ ገንዘብ በመሰብሰብ ተጠምደዋል ተብሏል የዴንማርክ የማህበራዊ ጉዳዮችና የአገር ውስጥ ሚኒስቴር፤ በኢትዮጵያውያ የሚታየው የጉዲፈቻ አሰራር ያልተገባና ህጻናትን ወደ ውጭ አገራት በመላክ ገንዘብ መሰብሰብ ላይ ያተኮረ መሆኑ በጥናት መረጋገጡን ጠቁሞ፣ ከአሁን በኋላ ኢትዮጵያውያን ህጻናትን በጉዲፈቻ ላለመቀበል …

ዴንማርክ ኢትዮጵያውያን ህጻናትን በጉዲፈቻ መውሰዷን አቆመች Read more »

መቀመጫውን በጋምቢያ ያደረገው የአፍሪካ የሰብአዊ መብት ፍ/ቤት፤ በ13 አመቷ ለተደፈረች ኢትዮጵያዊት ታዳጊ መንግስት ተገቢውን ፍትህ እንድታገኝ አላደረገም በሚል የ150ሺህ ዶላር የሞራል ካሳ ለተጎጂዋ እንዲከፍል መወሰኑን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ ከ13 ዓመት በፊት የተደፈረችው ታዳጊዋ፤ በወቅቱ ለፍ/ቤት ተደፍሬያለሁ ብላ አቤት ብትልም ፍ/ቤቱ ከመደፈሯ …

በ13 ዓመቷ ለተደፈረችው ታዳጊ መንግሥት 150 ሺ ዶላር እንዲከፍል ተወሰነበት Read more »

የለት ” ነገራችንን “አትንሳን (አሌክስ አብርሃም) አንዲት ወጣት የኢትዮጲያ መንግስትን ፍርድ ቤት ገተረችው!! እንደምን አደራችሁ ጓዶች,,,, እኔ ሰላም ነኝ! ! ቢቢሲ በዛሬ ወጉ አንድ አስገራሚ ዜና አትቷል,,,, እኛም ያገራችን ጉዳይ በመሆኑ ወዲህ አምጥተነዋል! ! ያስሚን ሐሰን ትባላለች ኢትዮጲያዊት ናት,,, አያቷ …

አንዲት ወጣት የኢትዮጲያ መንግስትን ፍርድ ቤት ገተረችው!! የለት ” ነገራችንን “አትንሳን (አሌክስ አብርሃም) Read more »

ይገረም አለሙ

People has been taken by federal police in south Ethiopia, Sumra.  በደቡብ ኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የሱምራ ብሔረሰብ አባላትን በገመድ አስሮ እየደበደበ አሰቃየ

ሰሞኑን በደቡብ ኢትዮጵያ በሚኖሩ ዜጎች ላይ የተፈጸመን የባሪያ ፍንገላን ዘመን የሚያስታውስ ኢሰብዓዊ ድርጊት የሚያሳይ ፎቶ በማኅበራዊ ድረ-ገጽ ተሰራጭቶ አጀኢብ ጉድ ብለናል። ነገሩ ትናንትን እየረሳን ዛሬ ለሚያጋጥመን ነገር አዲስ እየሆንን ጉድ ጉድ ለምንለው ለእኛ ነው እንጂ አዲስነቱ ለወያኔ ከበረሃ ጀምሮ አብሮት የኖረ ተግባሩ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

የኦሕዴድና የብአዴን አባላት ራሳቸውን ነጻ የሚያወጡበት ግዜ ላይ መሆናቸውን ሊገነዘቡ ይገባል:ነገን አትፍሩት! ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎EPRDF‬ ‪#‎TPLF‬ ‪#‎ANDM‬ ‪#‎OPDO‬ ‪#‎MinilikSalsawi‬ ‪#‎Freedom‬ ‪#‎Change‬ Minilik Salsawi – Ethiopian DJ – የኦሕዴድ ይሁን የብአዴን አባላት በባርነት ውስጥ መሆናቸው እሙን ነው:;ሃሳባቸውን በነጻነት መግለጽ አይችሉም ወክለነዋል ስለሚሉት …

የኦሕዴድና የብአዴን አባላት ራሳቸውን ነጻ የሚያወጡበት ግዜ ላይ መሆናቸውን ሊገነዘቡ ይገባል:ነገን አትፍሩት! Read more »

የግድያ ዛቻ በዓረና ኣባላት ላይ፥ **~*~*~*~*~*~*~** በትግራይ ምዕራባዊ ዞን ራውያን ከተማ ኑዋሪ የሆኑት ኣቶ ሓዱሽ ገብረእግዚኣብሄር ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ስልክ እየደወሉ የግድያ ዛቻ እየደረሰባቸው ነው። “ሰዎቹ ፅህፈት ቤቱ ዘግተህ ለመንግስት ይቅርታ ካልጠየቅህ በራስህ ሞት እንደፈረድክ ቁጠረው” የሚል ዛቻ እያደረሱባቸው ይገኛሉ። …

ሕወሓት መራሹ አገዛዝ በአረና ትግራይ አባል ላይ የግድያ ዛቻ ሽብር ፈጸመ:: Read more »

ተስፋዬ ገብረአብ

Prof. Ephraim Isaac ፕሮፌሠር ኤፍሬም ይስኃቅ

ዝነኛው አሸማጋይ ፕሮፌሠር ኤፍሬም ይስኃቅ መሰንበቻቸውን ሥራ እንደበዛባቸው ተሰምቷል። የኦሮሞን ህዝብ አመጽና ጥያቄ በሰላም ለመጨረስ እዚህም እዚያም እየደዋወሉ ልብ የሚነኩ እግዚአብሔራዊ ቃላት ተናግረዋል። የፕሮፌሠሩ ጥረት በደፈናው የሚነቀፍ ባይሆንም አይሳካላቸውም። የሽማግሌው የእርቅ መንገድ ጥሎ ማለፍ ይዘት እንዳለው ካለፈ ድርጊታቸው ትምህርት ተገኝቷል። በተጨማሪ ድርድር ወይም እርቅ ሲታሰብ መላ የኢትዮጵያን ህዝብ የመብት ጥያቄዎች ታሳቢ በማድረግ እንጂ፤ ጉልበት ካገኘው ኃይል ጋር ብቻ የመደራደር ዝንባሌ ያለፈውን ስህተት መድገም ይሆናል። በመሰረቱ ወያኔ በስውር ሽማግሌ መላክ መጀመሩ ጊዜ ለመግዛት ካልሆነ ከልብ እርቅና መደራደር ፈልጎ እንደማይሆን ይገመታል። ከፋፍሎ የማዳከም የህወሓት አካሄድ ገና ድሮ ተባኖበታል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ይገረም አለሙ

TPLF / ህወሓት

ወያኔዎች ለትግል በረሃ ገባን የሚሉበት ግዜ የንጉሡ ሥርዓት ፈርሶ ኢትዮጵያ ወዴት እንደምትሄድ አይደለም የት ላይ እንደቆመች እንኳን በቅጡ ያልየበት ወቅት ስለነበር፤ ለብሶት ዳርጎ ወደ ጫካ የሚያስኬድ ቀርቶ ከተማ ተቀምጦ ለማኩረፍ የሚያበቃ በደል ነበር ለማለት አይቻልም። ስለሆነም ወያኔዎች በዛን ወቅት ለትግል የተነሱት የአጼ ዮሐንስን ቤተ መንግሥት ይዘው የትግራይን መንግሥት የመመስረት ህልማቸውን ለማሳካት መንግሥት አልባው ወቅት ምቹ ሆኖ ስለታያቸው ነበር። ቢዘገይም ካሰቡት በላይ ተሳክቶላቸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም፡- ነጻነት ለሀገሬ)

Ethiopian taxi drivers strike

በአሜሪካ “ባለሦስት-ጥፋት ሕግ“ እያሉ ይጠሩታል። ወንጀለኞች ሦስት ከባድ ወይም ደግሞ አስከፊ ወንጀሎችን የሰሩ ከሆነ ከ25 ዓመት እስከ እድሜ ልክ እስራት የሚያደርስ ቅጣት ይበየንባቸዋል።

ዘ-ህወሓት በኢትዮጵያ የታክሲ አሽከርካሪ ሾፌሮች ላይ ጦርነት አውጇል!

ሙሉውን አስነብበኝ …

[የኮንዶሚኒየም ቤት ሰብሮ የገባ የክቡር ሚኒስትሩ የቅርብ ዘመድ ደወለላቸው]   ሰላም ጋሼ፡፡ ምን ፈለግክ ደግሞ? ኧረ ጉድ ፈልቷል ጋሼ፡፡ የምን ጉድ ነው? ብጥብጥ ተፈጥሯል ስልህ፡፡ አንተ ብጥብጡ ውስጥ አለህበት እንዴ? የትኛው ብጥብጥ? ይኼ በየከተማው የሚካሄደው ውስጥ ነዋ፡፡ ኧረ ሌላ ብጥብጥ …

አዲስ አበባ በኮንዶሚኒየም ቤቶች ላይ የተደረገ ቆጠራና ማጣራት ባለስልጣናትን አስቆጣ:: Read more »

በቅርቡ ለኤርትራ አዋሳኝ ከሆነ ነው ከትግራይ ክልል በተለይ ፅርዓያ ግርማይ ተብሎ ከሚታወቀው አካባቢ በርከት ያሉ ኢትዮጵያውያን በኤርትራ ታጣቂ ኃይሎች ተጠልፈው ተወስደው ነበር፡፡ በባህላዊ መንገድ ወርቅ ከሚወጣበት ካፍታ ሁመራ ወረዳ ወርቅ በማውጣት ላይ ከነበሩ ቁጥራቸው በርከት ያሉ ኢትዮጵያውያን ከንጋቱ 12 ሰዓት …

ኤርትራ ውስጥ የሚማቅቁት ኢትዮጵያውያን Read more »

ከ300 ሺ በላይ የሚሆኑ የኮንሶ ማህበረሰብ አባላት የአስተዳደር ጥያቄ መጠየቃቸውን ተከትሎ፣ በአካባቢው የሚታየው ውጥረት እንደቀጠለ ባለበት በዚህ ሰዓት ፣ የማህበረሰቡ ባህላዊ መሪ የሆኑት አቶ ካላ ገዛሃኝ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ አርባምንጭ ከተማ ውስጥ ታስረው እንደሚገኙ ከኮሚቴ አባላት መካከል አንዱ ገልጸዋል። ሌሎች …

የኮንሶ ባህላዊ ንጉስን ጨምሮ ከ200 ያላነሱ ሰዎች ታሰሩ (ኢሳት) Read more »

“በተቃዋሚ የፖለቲካ መሪዎች የሚፈጸመው አፈና አሳስቦናል።” አምስት የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት አባላት ለፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ የጻፉት ደብዳቤ። ዋሽንግተን ዲሲ — አምስት የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት አባላት አንድ በእስር ላይ የሚገኙት የቀድሞው የጋምቤላ አስተዳዳሪእንዲለቀቁ፤ የጠየቁበትን ደብዳቤ በትላንትናው ዕለት ለዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ባራክ …

አምስት የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት አባላት በኢትዮጵያ ጉዳይ ለፕሬዝዳንት ኦባማ ደብዳቤ ጻፉ Read more »

የአሌክሳንደሪያ፣ ቨርጂኒያ ሐመረኖህ ኪዳነ ምሕረት የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክን እንደ ግል ንብረቱ በመያዝ በዕብሪት አብጦ ያሻውን የሚያደርገው ታደሰ ሲሳይ ሥልጣነ ክህነቱን ከተገፈፈና ከተወገዘ ሁለት ዓመታት እንዳለፉት የደረሰን መረጃ ያመለክታል። ይህ ግለሰብ የፈጸመው ዝሙት በማስረጃ ስለተረጋገጠ ከሁለት ዓመታት በፊት ሥልጣነ ክህነቱን የተገፈፈ ቢሆንም አሁንም …

ታደሰ ሲሳይ ሥልጣነ ክህነቱን ከተገፈፈ ሁለት ዓመታት ተቆጠሩ Read more »

ሕዝብና መንግሥት እንዲወያዩ ጥሪ ቀረበ፤ ጸሎትና ምሕላ ታወጀ፤ ስለ ሶሻል ሚዲያና ድርቁ ማሳሰቢያ ተሰጠ!
 (ደጀ ሰላም፤ ማርች 9/2016፤ የካቲት 30/2008 ዓ.ም )፦ የብፁዕ አቡነ ናትናኤልን እረፍትና ቀብር ተከትሎ ከየሀገረ ሰብከታቸው የመጡ አበው የቅ/ሲኖዶስ አባላትን መሰባሰብ ተከትሎ የተጠራው አስቸኳይ ጉባኤ እንደተካሄደ መዘገቡ ይታወሳል። የተሐድሶ ድረ ገጾች “ማህበረ ቅዱሳን ያስጠራው ስብሰባ ነበረ፤ ከሸፈ” ሲሉ ኦርቶዶክሳውያን የጡመራ መድረኮች ደግሞ ፓትርያርኩ የሚያካሒዱትን የቤተ ክህነቱን አስተዳደርና አሠራር እንዲሁም የቅ/ሲኖዶስን የበላይነት የሚያስተሐቅር ርምጃ እንዲያስተካክሉ ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው በሰፊው ዘግበዋል። ከመጋረጃ ጀርባ በዝግ በር ያለው እልህ አስጨራሽ ስብሰባ ካለቀ በኋላ የወጣው መግለጫ ብዙ ቁምነገሮች ይዞ እናገኘዋለን። ከነዚህም ውስጥ ሕዝብና መንግሥት እንዲወያዩ ጥሪ መቅረቡን፤ ጸሎትና ምሕላ መታወጁን፤ ስለ ሶሻል ሚዲያና ድርቁ ማሳሰቢያ መሰጠቱን ማንሣት ይቻላል።

የፖለቲካው አስተዳደር ከብረት የጠነከረ እጅ ጨምድዶ በያዘው ቤተ ክህነት ውስጥ የሚደረጉ ነገሮችን በላይላይ ንባብ ብቻ አነብንቦ ማለፍ ትክክለኛ ትርጉምን አያስገኝም። ለአገራቸውና ለሃይማኖታቸው ቁርጠኛ የሆኑ አባቶች የሚያደርጉትን እውነተኛ እንቅስቃሴ ሳይረዱ በመቅረት ያልሆነ ትርጉም ወደመውሰድ ሊመራም ይችላል። ከዚህ አንጻር ቅዱስ ሲኖዶሱ የወሰነውና ለሕዝብ ይፋ የተደረገው መግለጫ አበረታች ውሳኔዎችን የያዘ መሆኑን መገንዘብ ይገባናል።

ለአብነት ያህል፤ አሁን በአገራችን ያለውን ቅጥ ያጣ የመንግሥት ጭፍጨፋ እና የንብረት ውድመት፤ እንዲሁም የሕዝብ ተቃውሞ “በአንዳንድ ክልሎችና ከተሞች የሚታየው አለመረጋጋት ሁሉንም የሚያሳስብ ሆኖ አግኝተነዋል” ተብሎ ተገልጧል። ትርጉሙ“ውጥረቱ ከፍያለ ለውጥ ሊወልድ የተዘጋጀ አገራዊ ምጥ ነው” ማለት ነው። መንግሥት በሚዲያዎቹ ዕለት ተዕለት ሊያሳየን ከሚሞክረው ሥዕል ጋር እጅግ የተራራቀ ነው። “አይዟችን፤ አገር አማን ነው” የሚለውን ማሞኛ ሕዝቡም አባቶችም አልተቀበሉትም።

አሁን ያለው ችግር ተራ ችግር ሳይሆን ክቡር የሰው ልጅን ነፍስ እያጠፋ ያለ መሆኑን ቅዱስ ሲኖዶሱ ግሩም የሆነ ግንዛቤ አግኝቷል። “በተፈጠረው ሁከትና ብጥብጥ ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን የሀብትና የንብረት ውድመት፣ በተለይም የሕዝብ መገልገያ የሆኑ የእምነት ተቋማት መቃጠል የተሰማንን ሐዘን እንገልጻለን” ብለዋል። በርግጥም በየክፍለ ሀገሩ የሚኖሩ አባቶች እንደመሆናቸው ያለውን ችግር በቅርብ ያውቁታል። “ባሳለፍናቸው ሳምንታት በተከሠተው ሁኔታ ሕይወታቸውን ያጡ ወገኖች በመሪር ሐዘንና በጸሎት እናስባቸዋለን” ማለታቸው የሕዝቡ ስቃይ ምን ያህል እንደተሰማቸው ማሳያ ነው። መፍትሔውንም አጠይመው ለመግለጽ “ሁላችሁም ልጆቻቸን መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ወንድ፣ ሴት፣ ወጣት፣ ሽማግሌ ሳትሉ ችግራችሁን ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለሚመለከተው እንድታቀርቡ፣ መንግሥትም የሕዝቡን ችግርና ሰላማዊ ጥያቄ በመገንዘብ መፍትሔ በመስጠትና ሰላም ለማምጣት እያደረገ ያለውን የዕለት ከዕለት ጥረት እንዲቀጥልበት” ጥሪ ማቅረባቸውን ልብ ይሏል። በርግጥ የሕዝቡን ሰላማዊ ጥያቄ በጭካኔ እየጨፈለቀ ያለው ማን መሆኑ ጠፍቷቸው አይደለም። ነገሩን ለማጠየም መሞከራቸው እንጂ።

ሌላው ይበል የሚያሰኘው የመግለጫቸው አካል መንግሥት ከቁጥጥር ውጪ የሆነ ረሃብ እንደሌላ ለማሳመን የሚዳክርበትን የችጋሩን ጉዳይ ያቀረቡበት መንገድ ነው። “ሕዝባችንና ሀገራችን በርኀብ፣ በድኅነትና በበሽታ ቸነፈር በተቸገረበት ወቅት” የሚለው ሐረግ ብዙ ይናገራል። “ቸነፈር” ተራ ቃል አይደለም። ከባድ በሽታን የሚወክል ቃል ነው። የረሃቡንና የችጋሩን ጽኑዕነት በበሽታው ቃል ለማስቀመጥ የሞከሩ እንጂ ይህንን ያህል ከባድ የሆነ በሽታ ገብቶ ስለርሱ ለመናገር የፈለጉ አይመስልም።

ሶሻል ሚዲያው በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ውስጥ አንድ ቦታ አግኝቶ የመግለጫ አካል ለመሆን በቅቷል። የሶሻል ሚዲያውን ሁኔታ በንቃት የሚከታተሉ ብዙ ብጹዓን አባቶች እንዳሉ ግልጽ ነው። የሚጻፈውንና የሚነገረውን ነገር በቅጡ ይገነዘባሉ፤ የሕዝቡንም የልብ ትርታ ያውቃሉ ማለት ነው። በርግጥ ፈር የለቀቁ አንዳንድ አፍራሽ የሶሻል ሚዲያ እንቅስቃሴዎች እንዳሳሰቧቸውም ግልጽ ነው። “ኅብረተሰቡን የሚለያይና የሚያራርቅ መረጃ (ኢንፎርሜሽን) ዕለት ዕለት ብታስነብቡት ትርፉ መራራቅን እንጂ መቀራረብን፤ መለያየትን እንጂ መግባባትን አያመጣም” ማለታቸው በግርድፉ ስናየው ትክክል ነው። ይሁን እንጂ ሶሻል ሚዲያው ባይኖር ኖሮ የመንግሥትን ቅጥ ያጣ ጭፍጨፋ እና ኢሰብዓዊ ተግባሮች ልንረዳ የምንችልበት ምንም አጋጣሚ አይኖርም ነበር። ስለ ጭፍጨፋው አትናገሩ ሳይሆን ጭፍጨፋውን አቁሙ የሚለው መፍትሔ ትክክለኛ ይሆናል።

በአጠቃላይ ብፁዓን አባቶቻችን ያስተላለፉት ውሳኔ ይበል የሚያሰኝ እና ከዚህ ቀደም በጉባኤ እየተናገሩ በመግለጫ ላይ ግን እንዳይገለጽ የሚጣልባቸውን ገደብ አልፈው ሐሳባቸውን ለምእመናቸው ለማድረስ መጣራቸውን የሚያሳይ ትልቅ እመርታ ነው። ቅዱስ ፓትርያርኩ ከአበው ሊቃነ ጳጳሳት ጋር ቢሠሩ እና ምእመናቸውን ከክፉ ለመታደግ ቢሞክሩ ያስመሰግናቸዋል። ከዚህ በፊት እንጀመሩት በማፍረስ ተግባራቸው ቢገፉም የራሳቸውን ስምና ታሪክ ከማጉደፍ ያለፈ የሚያመጡት ለውጥ እንደማይኖር ከቀዳሚያቸው ሊማሩ ይገባቸዋል። ምእመናንም አባቶቻቸው የሚናገሩትን ንግግር ምንነት ለመረዳት በመጣር፣ እነርሱ ያሉበትን ችግር በመገንዘብና አባቶቻቸውን ለመርዳት በመሞከር የልጅነት ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባቸዋል። ፈረንጆች “reading between the lines” እንደሚሉት ከተጻፈው ነገር በላይ ያለውን ትርጉምም ለመረዳት መሞከር ይገባቸዋል። “ፊደል ይገድላል ትርጓሜ ያድናል” እንዲል። ዘመኑን በተርታ ንባብ ሳይሆን በትርጉም እንረዳው።

ቸር ወሬ ያሰማን፤

አሜን      

================== የመግለጫውን ሙሉ ቃል ከዚህ እንደሚከተለው ማንበብ ይቻላል። ======

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

“ኅሡ ሰላማ ለብሔር እስመ በሰላመ ዚአሃ ይከውን ሰላምክሙ”

(የአገርን ሰላም እሹ ፈልጉ የአገራችሁ ሰላም የእናንተ ሰላም ነውና)

 የተወደዳችሁ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት፤

የሀገርና የወገን ፍቅር ያለው ሕዝብ፥ ሰላም ከእግዚአብሔር መሆኑን ያውቃል፤ ሰላም ለሰው ልጆች ከማናቸውም መሠረታውያን ፍላጎቶች በላይ ተቀዳሚ ጉዳይ ነው፡፡

ኢትዮጵያ ሀገራችን የተለያዩ ሃይማኖቶች፣ ብሔር፣ ብሔረሰቦች ተቻችለውና ተረዳድተው የሚኖሩባት የዓለም ምሳሌ ናት፡፡ ይህን ዓለምን የሚያስደንቅ ገጽታችንን ማንኛውም ኢትዮጵያዊ እንዲከተለው ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

የተወደዳችሁ ኢትዮጵያውያን፣ ኢትዮጵያውያት፤

ኢትዮጵያ አህጉረ ሰላም (የሰላም አገሮች) ከሚባሉት ከዓለም አገሮች አንዷ ስትሆን በአሁኑ ጊዜ በአንዳንድ ክልሎችና ከተሞች የሚታየው አለመረጋጋት ሁሉንም የሚያሳሳብ ሆኖ አግኝተነዋል፡፡

ከዚህም ጋር ባለፍናቸው ሳምንታት በተከሠተው ያልተጠበቀ ችግር፡

1.በአንዳንድ አካባቢ የሰው ሕይወት ሲጠፋ፤ ትምህርት ቤቶች ሲዘጉ፤ የንግድ ተቋማት፣ የሕዝብና የመንግሥት ንብረት ሲወድም፤ የሕዝባችን የዕለት ከዕለት ኑሮ ሲናጋ ሁሉም ኅብረተሰብ የችግሩ ተጠቂ ሆኗል፤ የዚህ ዓይነቱ ድርጊት በዚህ ሁኔታ ከቀጠለ የሕዝባችን ህልውናና የትውልዱም የወደፊት ዕድል አደጋ ላይ ሊወድቅ ይችላል፡፡

2.ባሳለፍናቸው ሳምንታት በተከሠተው ሁኔታ ሕይወታቸውን ያጡ ወገኖች በመሪር ሐዘንና በጸሎት እናስባቸዋለን፡፡ ስለዚህ ሁላችሁም ልጆቻቸን መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ወንድ፣ ሴት፣ ወጣት፣ ሽማግሌ ሳትሉ ችግራችሁን ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለሚመለከተው እንድታቀርቡ፣ መንግሥትም የሕዝቡን ችግርና ሰላማዊ ጥያቄ በመገንዘብ መፍትሔ በመስጠትና ሰላም ለማምጣት እያደረገ ያለውን የዕለት ከዕለት ጥረት እንዲቀጥልበት በቤተ ክርስቲያናችን ስም እናሳስባለን፡፡

3. ሕዝባችንና ሀገራችን በርኀብ፣ በድኅነትና በበሽታ ቸነፈር በተቸገረበት ወቅት የኢትዮጵያ ሕዝብ በአንድነት መሠረታዊ ወደሆነው የልማት የሰላምና የድርቅ ጉዳይ በማተኮር መልስ ሰጭ መሆን ይገባዋል ብለን በጽኑ እናምናለን፡፡

4. ወገኖቻችን ሆይ፣ በአሁኑ ጊዜ የወቅቱ የኤሌክትሮኒክስ መገናኛ (ብሎገሮችና የፌስቡክ) ተጠቃሚዎች በሙሉ ኢትዮጵያውያን ከሞያችሁ ከዕውቀታችሁ ተጠቃሚዎች የመሆን ምኞታቸው የላቀ ነው፡፡ ሆኖም መልካሙንና ለዕድገት የሚያግዛቸውን ዕውቀት እንጂ ኅብረተሰቡን የሚለያይና የሚያራርቅ መረጃ (ኢንፎርሜሽን) ዕለት ዕለት ብታስነብቡት ትርፉ መራራቅን እንጂ መቀራረብን፤ መለያየትን እንጂ መግባባትን አያመጣም፤ ከዚህ አንጻር የእናንተም ጥረትና ድካም ከንቱ ሆኖ ይቀራል፡፡ በመሆኑም የተከበረ ዕውቀታችሁን፣ ሞያችሁን፤ ለሕዝባችን ፍቅርና አንድነት፤ ለሀገራችን ሰላምና ዕድገት እንድታውሉት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትጠይቃለች፡፡

የተወደዳችሁ ኢትዮጵያውያን፤

ተቻችሎና ተረዳድቶ የመኖር የተቀደሰ ነባር ባህላችንን የሚያጎድፍ ማናቸውንም አስተሳሰብና እንቅስቃሴ በአንድነት መቋቋም እንደሚገባ አበክረን እየገለጽን፣ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት ወገኖቻችን በሙሉ፣ በተለይም አገር ተረካቢ ትውልድ የሆናችሁ ወጣቶች፣ ሁከትና ብጥብጥብን ከሚያስከትሉ መጥፎ ድርጊቶች እንድትቆጠቡ፤ ለአገር ሰላምና ልማት ጠንክራችሁ እንድትቆሙ በልዑል እግዚአብሔር ስም አጥብቀን እያሳሰብን በተፈጠረው ሁከትና ብጥብጥ ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን የሀብትና የንብረት ውድመት፣ በተለይም የሕዝብ መገልገያ የሆኑ የእምነት ተቋማት መቃጠል የተሰማንን ሐዘን እንገልጻለን፡፡

ይልቁንም ከሁሉም በላይ ሁሉን ማድረግ የሚችል እግዚአብሔር አምላካችን፤ ለኢትዮጵያ ለሀገራችን ሕዝቦች ሰላሙን፣ ፍቅሩን፣ አንድነቱን ይስጥልን ዘንድ፤ ድርቁን ረኀቡን አስታግሦ መጪው ጊዜ ዝናመ በረከቱን ይሰጠን ዘንድ በያዝነው በዐቢይ ጾም ሱባኤ ጸሎተ ምሕላ በመላ ሀገሪቱ ባሉት ገዳማትና አድባራት የገጠር አብያተ ክርስቲያናት እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያን ይባርክ::

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ

የካቲት ፳፱ ቀን ፳፻፰ ..

አዲስ አበባ

Deje Selam is a venue of news, views and opinions about or related to the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. [email protected]

የሳምንቱ አጀንዳ — ገዱ አንዳርጋቸው ከአማራ ክልል – ብልጦች አይደለም ብልጣ ብልጦች ግን አይሸውዱንም:: ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎Amhara‬ ‪#‎Tigray‬ ‪#‎TPLF‬ ‪#‎ANDM‬ ‪#‎ገዱ_አንዳርጋቸው‬ ‪#‎MinilikSalsawi‬ Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – አጣብቂኙ አላላውስ ሲለው ሕወሓት አጀንዳ ፈጠራ እና ማምታታቱን ማዘናጋቱን ተክኖበታል::ሕዝቡ ለእለት ኑሮው ስለሚጣደፍ የተባለውን …

የሳምንቱ አጀንዳ — ገዱ አንዳርጋቸው ከአማራ ክልል – ብልጦች አይደለም ብልጣ ብልጦች ግን አይሸውዱንም:: Read more »

የቆሸሸው የበሰበሰው ኢሕአዴጋዊ አስተሳሰብ እንጂ ሕዝብና ግድያ ይቁም ያሉ ግለሰቦች አይደሉም:: ‪ የቆሸሸው የበሰበሰው ኢሕአዴጋዊ አስተሳሰብ እንጂ ሕዝብና ግድያ ይቁም ያሉ ግለሰቦች አይደሉም:: Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – አንድ መቶ በአንድ መቶ ምርጫውን አሸንፌአለሁ የሚለው ኢሕኣዴጋዊ ማጭበርበርን ተከትሎ በተለያዩ አከባቢዎች …

የቆሸሸው የበሰበሰው ኢሕአዴጋዊ አስተሳሰብ እንጂ ሕዝብና ግድያ ይቁም ያሉ ግለሰቦች አይደሉም:: Read more »

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ሦስተኛ ፍትሐ ብሔር ችሎት፣ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሐሪ የፓርቲውን ማኅተም እንዳይጠቀሙ አሳልፎት የነበረውን የዕግድ ውሳኔ የካቲት 22 ቀን 2008 ዓ.ም. በሰጠው ውሳኔ አነሳ፡፡ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት …

ፍርድ ቤት የመኢአድ ፕሬዚዳንት የፓርቲውን ማኅተም እንዳይጠቀሙ አሳልፎት የነበረው ዕግድ ተነሳ Read more »

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለፉት አሥር ዓመታት የገነባቸውን የ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ያሉበትን ደረጃ ለማወቅ በጀመረው ቆጠራ፣ በሕወሓት ካድሬዎች  በርካታ ሕገወጥ ተግባራት የተፈጸሙባቸው ቤቶች መኖራቸው ታወቀ፡፡ የካቲት 21 ቀን 2008 ዓ.ም. የተጀመረው ቆጠራ ሳምንቱን የያዘ ሲሆን፣ ይቆጠራሉ ከተባሉት 104,258 ቤቶች …

የሕወሓት ካድሬዎች በኮንዶሚኒየም ቤቶች ላይ የሚያደርጉት ሕገወጥ ተግባር በቆጠራ ተደረሰበት:: Read more »

‹‹አዕምራዊ ንብረቱ በውርስ መተላለፉን የሚያሳይ ማስረጃ የለም››  ኤፍሬም ታምሩ ድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የአዕምራዊ ንብረት ጥበቃ አዋጅን በመተላለፍ፣ በውርስ የተላለፈን የፈጠራ ሥራ ያለምንም ፈቃድ ለግል ጥቅሙ አውሏል ተብሎ ክስ ተመሠረተበት፡፡ ኤፍሬም ሕግ በመተላለፍ የገንዘብና የሞራል ጉዳት አድርሷል ተብሎ  በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ …

ድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ በውርስ የተላለፈን የፈጠራ ሥራ ያለምንም ፈቃድ ለግል ጥቅሙ አውሏል ተብሎ ክስ ተመሠረተበት፡፡ Read more »

መስመራችን ያስመዘገባቸውን አንፀባራቂ ድሎች ያቆሸሹ በሚል ኦሕዴድ በተፅዕኖ ፈጣሪነታቸው የሚታወቁ አመራሮቹን ማባረሩን ቀጥሏል::የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦሕዴድ) በኦሮሚያ በርካታ አካባቢዎች የተፈጠረውን ችግር ለማጥራት ሰሞኑን ባካሄደው የማዕከላዊ ኮሚቴ ጉባዔ፣ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የነበሩትን የክልሉን የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘለዓለም ጀማነህን እስከ …

መስመራችን ያስመዘገባቸውን አንፀባራቂ ድሎች ያቆሸሹ በሚል ኦሕዴድ በተፅዕኖ ፈጣሪነታቸው የሚታወቁ አመራሮቹን ማባረሩን ቀጥሏል Read more »

ክንፉ አሰፋ

Jawar Mohamed ጃዋር መሐመድ

መገናኛ ብዙኀንን መቼ እና እንዴት መጠቀም እንዳለበት ጠንቅቆ ያውቃል። የሚፈልገውን ነገር ሁሉ ከፈጸመ በኋላ ግን እንደ በረሃ ተኩላ እያደፈጠ ይናከሳል። ሲናከስ ደግሞ ማንንም አይምርም። ውለታ የሚባል ነገር አያውቅም። ይሉኝታ አይነካካውም። እፍረትም በእርሱ ዘንድ የለችም። ከቶውን መቀበል እንጂ መስጠትን አያውቅም። አስር ተቀብሎ በዜሮ የሚሸኝ ጀግና ነው። በዚህ ተግባሩ አድናቂው ነኝ። “እኔ-ነኝ” ያለ የዲሲ ፖለቲከኛን ሳይቀር ከአንዴም ሁለቴ እንደማስቲካ እያኘከ መትፋቱን እንመሰክራለን። የጡት አባቱ የሆነው ኦነግንም ቢሆን ‘A Critical Assessment of the Oromo Liberation Front” በሚለው መጣጥፉ እንዳይሆን እንዳይሆን አድርጎ የጠረበ ፍጡር ነው። ይህ ሰው እንደገና ተመልሶ የ”ነፍጠኛውን ሜድያ” ለመጠቀም የማይሞክርበት ምክንያትም የለም።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ሁለት የዓለምአቀፍ ጋዜጠኞች እና አስተርጓሚያቸው በኦሮሚያ ተቃውሞና ድርቅ ዙሪያ ዘገባ ለማቅረብ በተንቀሳቀሱበት ወቅት፤ በጸጥታ ሃይሎች ተይዘው ተመለሱ። ጋዜጠኞቹ ለ24 ሰዓታት ታስረው ተለቀዋል። ዋሽንግተን ዲሲ —  በኢትዮጵያ ሁለት ዓለምአቀፍ ጋዜጠኞችና አስተርጓሚያቸው በኦሮሚያ የተከሰተው ድርቅና የተቃውሞ ሰልፍ ላይ ዘገባ ለማቅረብ ሲንቀሳቀሱ ለ24 …

በኦሮሚያ ዘገባ ለማቅረብ የተንቀሳቀሱ ጋዜጠኞች በቁጥጥር ስር ውለው ተለቀቁ:: (VOA) Read more »

ቅ/ሲኖዶስ: በመላው ገዳማት፣ አድባራትና የገጠር አብያተ ክርስቲያናት ጸሎተ ምሕላ እንዲደረግ ዐወጀ፤ “ባሳለፍናቸው ሳምንታት ሕይወታቸውን ያጡ ወገኖችን በመሪር ሐዘንና በጸሎት እናስባቸዋለን” በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ ኅሡ ሰላማ ለብሔር እስመ …

ቅ/ሲኖዶስ: በመላው ገዳማት፣ አድባራትና የገጠር አብያተ ክርስቲያናት ጸሎተ ምሕላ እንዲደረግ ዐወጀ:: Read more »

ዳዊት ዳባ

ዛሬ እየሰፋ እየገዘፈና ጉልበት እያገኘ የመጣው ህዝባዊ እንቢታ ከዐረቡ ሀገሩ ህዝባዊ አልገዛም ባይነት የጀመረ ይመስለኛል። ያኔ ከዚህ ሥርዓት በዚህም መንገድ መገላገልም ይቻላል ለካ? የሚለው እሰቦት በአዕምሮው ያልዞረ ኢትዮጵያዊ ነበር ለማለት አይቻልም። የሥርዓቱም ደጋፊዎችም ቢሆኑ በግልባጩ እንቅልፍ ያጡበት ጉዳይ ነበር። አልገዛም ባይነቱ በኛ ሀገር ይሄ-ያ ይጎድለዋል። ይህ አደጋ አለው። በዚህ አንመሳሰልም ይሉ የነበሩትም ቢሆን ግምት ውስጥ አስገብተው አስበውበት ስለነበር ነው። ኃላፊነት ወስደው ይሠሩበት የጀመሩ ስብስቦች እርግፍ አድርገው ቢተዉትም። ድርጅቶች የስትራተጂ ለውጥ ቢያደርጉና ትኩረታቸው ወደሌላ ቢያዘነብልም ሂደቱ የሚገታ አልሆነም።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ይገረም አለሙ

SMNE announced the formation of the Ethiopian Council for Reconciliation and the Restorative of Justice (ECRRJ) at a public meeting held at the Sheraton Hotel in Silver Springs, Maryland (February 14, 2016)

በአቶ ኦባንግ ሜቶ በሚመራው ድርጅት አዘጋጅነት በተጠራ ጉባኤ ላይ የተገኙ ኢትዮጵያውያን ስብሰባቸውን ያጠናቀቁት በሀገራችን ዕርቅ አስፈላጊ መሆኑ ላይ በመተማመንና ለዚህም ተግባራዊነት ዕርቅን ከራስ መጀመር እንደሚገባ አጽንኦት በመሰጠት መሆኑን ሰምተናል። የእስከዛሬው ተሞክሮአችን ተግባራዊነቱን እንድንጠራጠር ቢያደርገንም የአሰባሳቢዎቹ ተግባርም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የደረሱበት ድምዳሜ የሚደነቅ ብቻ ሳይሆን ለተግባራዊነቱ ድጋፍ ሊቸረው የሚገባ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ተስፋዬ ገብረአብ

በዓለማችን ላይ ወጣቶች በአንድ ልብ የተሳተፉበት ያልተሳካ የአብዮት ታሪክ አናውቅም። የጊዜ ጉዳይ ብቻ ነው። ይህችን እየፃፍኩ ሳለ የማያቋርጥ፣ የተቀናጀ የአመፅ ዜና ከኢትዮ-ኦሮሚያ እየሰማሁ ነበር። ዝምታው ማብቃቱ ግልፅ ነበር። የኦሮሚያ ወጣቶች የሥርዓቱን ታጣቂ ኃይል በጦርና በጠመንጃ ይፋለሙት ይዘዋል። ከሻሸመኔ ወደ አዲስ አበባ መንገድ ተዘግቶአል። ልማደኛዋ ኮፈሌ ጦር ሜዳ ሆናለች። ብረት ለበስ ጦር ኮፈሌና ሻሸመኔ ገብቷል። በጥቅሉ ወለጋና ሐረርጌ ፀጥታ የለም። ሱሉልታ ብሶበታል። ጭራሽ ገበሬዎቹ ያስለቀቁትን መሬት መከፋፈል ጀምረዋል። ደራ ነፃ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች ታፈሱ:: የአግኣዚ ጦር በወለጋ ዩንቨርስቲ ዶርም በመግባት ተማሪዎችን ደበደቡ ። ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎Oromoprotests‬ ‪#‎WellegaUniversty‬ ‪#‎MinilikSalsawi‬ ‪#‎RDH‬ በወለጋ ዩንቨርስቲ ለሊቱን የአግኣዚ ወታደሮች ተማሪዎችን ጨለማን ተገን አድርገው ሲደበድቡ እንደነበር ታወቀ:: ከነዚህ ተማሪዎች ውስጥ 49 ከፉኛ የመቁሰል አደጋ እና ለህይወታቸው …

አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች ታፈሱ:: የአግኣዚ ጦር በወለጋ ዩንቨርስቲ ዶርም በመግባት ተማሪዎችን ደበደቡ ። Read more »

ግርማ ካሳ

የምታዩት ፎቶ ምን ያህል በኦሮሚያ ያለው እንቅስቃሴ በአክራሪዎች፣ በኦነጋውያን እንደተጠለፈ የሚያሳይ ነው

ከ25 ዓመታት በፊት ህወሓት/ኢህአዴግ ከፋፍሎ ለመግዛት በሚል የዘረጋው የዘር ፖለቲካ ወይንም የነርሱን አባባል ልጠቀምና “የብሔር ብሔረሰቦች” ፖለቲካ፣ ብዙዎች ኢትዮጵያን እንደ ሀገር ሊያጠፋ የሚችል ትልቅ አደጋ “time bomb” እንደሚሆን ሲያስጠነቅቁ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ይገረም አለሙ

ወያኔ ብአዴንና ኦህዴድ የሚባሉ አገልጋዮቸን ፈጥሮ፣ ኢትዮጵያውያንን በጎሣ አከፋፍሎና ለአገዛዙ እንዲመቸው አድርጎ አደላድሎ ለ17 ዓመታት የተዋጋለትን ዓላማውን ተግባራዊ ከማድረግ አልፎ ሃያ አራት ዓመታት በሥልጣን መቆየት በመቻሉ ሊደነቅ ይገባል። ለዴሞክራሲ እንታገላለን የሚሉ እንደ ወፍ ዘራሽ በየቦታው በቅለው ሳይለያዩ ተለያይተው፣ ሳይነጋገሩ ተጣልተው፣ የቃላት እንጂ የተግባር ሰውነት ርቆአቸው ሃያ አምስት ዓመታት ስንዝር መራመድ ባልቻሉበት ወያኔ እኩይ ዓላማውን ለማሳካት አንድነቱን አጥብቆ፣ ገመናውን ደብቆ በሌሎችም ተጠቅሞ መዝለቅ መቻሉን ማድነቅ አለመቻል የራስን ድክመት ለመቀበል አለመፍቀድ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ፖሊስ በሕገወጥ መንገድ ሰዎችን የሚያሸጋግሩ አሉ ብሎ ይጠረጥራል

Ethiopian Airlines 787 dreamliner የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አውሮፕላን

Ethiopia Zare (ሰኞ የካቲት 28 ቀን 2008 ዓ.ም. Mar. 01, 2016)፡- ከአዲስ አበባ ሌሊት ተነስቶ ዛሬ ጠዋት በስዊድን መናገሻ ስቶክሆልም በሚገኘው የአርላንዳ አየር ማረፊያ ባረፈው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አውሮፕላን የዕቃ ኮንቴይነር ውስጥ የተደበቀ የ27 ዓመት ዕድሜ ያለው አንድ ሰው መገኘቱን ፖሊስ ገለጸ። ይኸው ግለሰብ በስዊድን ጥገኝነት መጠየቁ ታውቋል። ፖሊስ በሕገወጥ መንገድ ሰዎች የሚያሸጋግሩ ወገኖች እንዳሉ ጥርጣሬ አለኝ፣ ጉዳዩን እያጣራኹ ነው አለ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

አቶ ንጉስ ገብረመድህን የተባሉ ኢትዮጵያዊ የሰው ልጅና እንስሳትን የመጉዳት መርዛማ ይዘት የሌለው የትኋን መድኃኒት ቀምመው አዘጓጅተዋል። የመድኃኒት ቅመማ እና የሕብረተሰብ ጤና ሳይንስ ባለሞያ አቶ ንጉስ ከሦስት ንጥረ ነገሮች ቀምመው ያዘጋጁት ይህ መድኃኒት በአንድ የገጠር መንደር ውስጥ ተሞክሮ ውጤታማ መሆኑን ተረጋግጧል። …

የፀረ ትኋን መድኃኒት በኢትዮጵያ – VOA Read more »

የኮንሶ ግጭት ተባብሶ ቀጥሏል– የሰው ህይወት አልፏል// የኮንሶ ህዝብ የጀመረውን የአከላለል ጥያቄ ጋር በተያያዘ በህዝቡ ላይ በደቡብ ልዩ ኃይልና መከላከያ ሰራዊት እየደረሰ ያለው የአፈና ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ በዚሁ መሰረት በከተማው የሰፈረው ታጣቂ ከከተማዋ አጎራባች ቀበሌዎች እየዘመተ በህዝቡ የተዘጉ መንገዶችን ለማስከፈት …

የኮንሶ ግጭት ተባብሶ ቀጥሏል– የሰው ህይወት አልፏል Read more »

የእስራኤሉ ትልቅ ባንክ ” ባንክ ሃፖአሊም” ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በ 200 ሚሊዮን ዶላር የስኳር ፋብሪካ እንደሚገነባ ውሉንም እንደተፈራረሙ ግሎቡስ የተሰኘው የ እስራኤሉ የቢዝነስ ጋዜጣ ትናንት ዘግቧል ። ይህ በ እንዲህ እንዳለ ከዚህ ውል በስተጀርባ ለስኳር ፋብሪካ መሬታችን አንሰጥም ያሉ የሱርማ …

የእስራኤሉ ትልቅ ባንክ ” ባንክ ሃፖአሊም” ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በ 200 ሚሊዮን ዶላር የስኳር ፋብሪካ እንደሚገነባ ውሉንም ተፈራረሙ Read more »

የሰማያዊ አባላትን ጨምሮ 13 ሰዎች የሽብር ክስ ተመሰረተባቸው በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር የሰማያዊ ፓርቲ አባላትን ጨምሮ 13 ሰዎች ዛሬ የካቲት 27/2008 ዓ.ም በፌደራል አቃቤ ህግ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸዋል፡፡ በጋሞ ጎፋ ዞን የሰማያዊ ፓርቲ አደራጅ በሆነው አቶ ሉሉ መሰለ ስም በተከፈተው የክስ …

የሰማያዊ አባላትን ጨምሮ 13 ሰዎች የሽብር ክስ ተመሰረተባቸው Read more »

“ኢትዮጵያ ውስጥ የብዙኃን አስተሳሰብ ተጨፍልቋል” ባለፉት 4 ወራት በኦሮሚያ ክልል የተፈጠረውን ተቃውሞና ግጭት እንዲሁም በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተከሰቱ ብጥብጦችን አስመልክቶ አንጋፋው ፖለቲከኛ አቶ ልደቱ አያሌው፤ከአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አለማየሁ አንበሴ ጋር በነበራቸው ቆይታ የሚከተለውን ትንታኔ ሰጥተዋል ዘንድሮ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ለምን …

አቶ ልደቱ አያሌው – በወቅታዊ የአገሪቱ ፖለቲካ ዙሪያ Read more »

• የቴዲ አፍሮ ኮንሰርት ለ3ኛ ጊዜ የተከለከለበትን ምክንያት ማወቅ ናፈቀኝ!! • የሙዚቃ ኮንሰርቱን ከአዲስ አበባ ይልቅ ናይሮቢ ማቅረብ ይቀላል • “የከተማውን ትራንስፖርት ከታክሲ ተፅዕኖ ለማውጣት”… ታስቧል Addis Admass / ከአራት ወራት በላይ የዘለቀው የኦሮምያ ተቃውሞና ግጭት (የፖለቲካ ቀውስ ሊባል ይችላል!) …

የሙዚቃ ኮንሰርትም እንደተቃውሞ ሰልፍ ይከለከላል! ( ኤልያስ ፖለቲካ በፈገግታ ) Read more »

News Ethiopia Wetatoch Dimts March 07, 2016 መረጃ ሙሉ ያደርጋል ለዚህ ደግሞ የኢትዮጵያ ወጣቶች ድምፅ ሳምንታዊ ዜናዎችን እንዲሁም መጣጥፎችን ለስለስ ካሉ ሙዚቃዎች ጋር ይዘንላችሁ ቀርበናል አብራችሁን ሁኑ ። [youtube http://www.youtube.com/watch?v=OqbST1cG5MU]

የደቡብ ጎንደር ከተሞች የአሽከርካሪዎች የስራ ማቆም አድማ ተጀመረ:: ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎DriversStrike‬ ‪#‎Gonder‬ ‪#‎Debretabor‬ ‪#‎Alember‬ ‪#‎Gaynet‬ Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) በጎንደር ክፍለሃገር ጋይንት አለም በር ክምርድንጋይ እና ደብረታቦር የስራ ማቆም አድማ ሙሉ በሙሉ መደረጉ ከረፋፈደ ተረጋግጧል::በአለም በር በፌደራል ፖሊሶች የተከበበች ሲሆን ከፍተኛ …

የደቡብ ጎንደር ከተሞች የአሽከርካሪዎች የስራ ማቆም አድማ ተጀመረ:: Read more »

በአፍሪካ አሜሪካውያን የሲቪል መብቶች ትግል ውስጥ እና በደቡብ አፍሪካ ነባር ጥቁሮች ከመጤ አፍሪካነሮች የተነጠቁትን የዕኩል ሰውነት መብት ለማስመለስ ሲታገሉ፣ ጥቂት የማይባሉ ነጮች (ወይም አፍሪካነሮች) የትግላቸው አጋር ሁነውላቸው ነበር። ሌሎች ጥቂቶች በደሎቹን ምክንያታዊና ተገቢ ለማድረግ (to justify) ተከራክረዋል። ብዙኃኑ ግን በገለልተኝነት እና በስጋት ተመልክተውታል። ከጥቁሮቹ ታጋዮች መካከልም ከፊሎቹ ለዕኩል የሰውነት ማዕረግ ታግለዋል። ከፊሎቹ ነጮቹን ለመበቀል ታግለዋል። ዞሮ፣ ዞሮ ግን ሁሉም ነባሩን ትርክት እና ተቀባይነት የነበረውን (mainstream) አስተሳሰብ ማፈራረስ ነበራቸው። በዚህ ግዜ ነጮቹ ቀድሞ የነበራቸውን የተለየ መብት ከጥቁሮች ጋር መጋራታቸው መብታቸውን እንደመነጠቅ ቆጥረውታል። ለምሳሌ ቅድሚያ ይሰጣቸው የነበረውን አገልግሎት ከጥቁሮች ዕኩል እንዳደራረሳቸው እየተሰለፉ እንዲያገኙ መገደዳቸውን እንደመብት ነጠቃ ይቆጥሩታል።

እነዚህ ተግዳሮቶች መገፋፋት ይፈጥሩ ነበር። በዚህ ሳቢያ ከነጮቹም፣ ከጥቁሮቹም ወገን አብረን መኖር አንችልም የሚል ሰውነትን የመጠራጠር ዝንባሌ ታይቷል። በአሜሪካ እነማልኮም ኤክስ ይመሩት የነበሩት እንቅስቃሴ የነጭ የሆነውን ሁሉ መጠየፍን እንደስትራቴጂ የቆጠረ ነው። የነሱ ተቃራኒ ዕኩያ የሚባለው ኬኬኬ የሚባሉት የነጮች ጥቁር ተጠያፊ ቡድን ነው። የማልኮሜክስ ‘ኔሽን ኦቭ ኢስላም’ እና ‘ኩ ክላክስ ክላን’ አንዴ ስምምነት ላይ ደርሰው ነበር። ጥቁሮቹም ነጭ የማያዩበት የጥቁር ዓለም፣ ነጮቹም ጥቁር የማያዩበት የነጭ ዓለም ሊመሠርቱ። አንዱ ሌላኛውን ለማግለል እንደመስማማት።

በቀድሞዋ አሜሪካ ሰሜኖቹ “ነጻ አገሮች” ሲሆኑ ደቡቦቹ “ባሪያ አሳዳሪ” ነበሩ። ሶሻሊስቶቹ በወቅቱ በሰሜን የነበረውን የጭሰኝነት ሁኔታ እያዩ በሰሜን ያለው የጭቁን ሠራተኞች ሁኔታ እና በደቡብ ያለው የባሪያዎች ሁኔታ አንድ ነው እስከማለት የሚደፍሩ ነበሩ – በመደብ ጭቆና ትንተና። ነገር ግን በወቅቱ ከደቡብ ባርነት ኮብልለው ወደሰሜን ጭሰኝነት የሚፈልሱ እልፍ ሰዎች ቢኖሩም፣ ከሰሜን ጭሰኝነት ወደደቡብ ባርነት የኮበለሉ ሰዎች አልነበሩም።

ሌላኛው ፈታኝ ነገር ያንን ጥቁሮችን የሚያንኳስስ ስርዓት የሚደግፉ ጥቁሮች መኖራቸው ለነጭ አስተባባዮች ምቹ ሁኔታ መፍጠሩ ነበር። ማልኮም ኤክስ በባርነት የነበሩ ጥቁሮችን በሁለት ይከፍላቸው ነበር። የቤት እና የመስክ ኔግሮዎች (house and field negroes) ብሎ። የቤት ኔግሮዎቹ ጥቁር ቢሆኑም ከጌታው የሚተርፈውን ከስር ከስር የመቋደስ ዕድሉ ነበራቸው (they were privileged)። ተመችቷቸዋል። ስለዚህ፣ አብዛኛውን ፍዳ እንደሚቀምሱት የመስክ ኔግሮዎች ስርዓቱን አይቃወሙትም፣ እንዲያውም በደሉን በሰበብ ያለባብሱለታል።

እንዲህ ዓይነቱ የታሪክ ትርክት መገፋፋት ኋላ ላይ የዕኩል ሰውነት ማዕረግ ለማግኘት ይታገሉ ለነበሩት ለነማርቲን ሉተር ኪንግ ፈታኝ ነበር። በግለታሪኩ ላይ ኪንግ የሲቪል መብቶች ትግሉ አንዱ ፈተና ይህ እንደነበር ገልጿል። መጨረሻ ላይ ስኬታማ የሆነው ግን፣ የአግላዮቹ ሳይሆን የአካታቾቹ ትግል ነው። ጥቁሮቹ ዕኩል መብቱን ሲያገኙ ቀድሞ ነጮቹ ይፈሩት እንደነበረው ዓይነት ጥፋት አልደረሰም።

በደቡብ አፍሪካ ኤኤንሲ ጥቁሮች ብቻ ሳይሆን ነጮችንም በአባልነት ይቀበል ነበር። የነማርቲን ሉተር ኪንግ እንቅስቃሴም በርካታ ነጭ አጋሮች ነበሩት። ማልኮም ኤክስ ከመገደሉ ጥቂት ቀደም ብሎ ስለሚፀፅተው ነገር ሲናገር አንዲት ታዳጊ ልጅ ጠቅሷል። ከዓመታት በፊት ማልኮም የአግላዩ ትግል ሊቀ ጳጳስ እይያለ አንዲት የ10 ዓመት ሕፃን ልጅ እቅፍ አበባ ይዛ ለጥቁሮች ትግል አጋርነቷን ለማሳየት ስትወጣ ‘ሂጅ ከዚህ፤ እኛ ከነጮች ጋር አጋርነት የለንም’ ብሎ አባሯት ነበር። ኋላ፣ እየበሰለ ሲመጣ ተፀፅቷል።

እኛ አገር በማወቅም ይሁን ባለማወቅ የፆታን ጨምሮ፣ ከፊሉ በመደብ፣ ከፊሉ በማንነት፣ ከፊሉ በመደብ እና በማንነት ምክንያት በሚሉት መሠረት (መሠረቱን ባለሙያዎች በጥናት ሊበይኑልን ሲገባ እኛ ባላዋቂነት ጭቃ እየተለቃለቅንበት እንገኛለን፣ ለማንኛውም) ለዘመናት በገዢዎች እና በተገዢዎች መካከል (ወይም ዘመንና በሕል ባፈረጠማቸው እና ባንኳሰሳቸው የማኅበረሰብ ክፍሎች /ምሳሌ ወንዶች እና ሴቶች/) ለደረሱት በደሎች እና በዘለቄታው ላስከተሉት በማንነት ላይ የተመሠረተ የተጠቃሚነት ጉዳትን ለማስተካከል (undoing sustained system of repression) አንዱ የሌላው አጋር በመሆን አካታች የመብት ትግል በማድረግ ፈንታ አግላይ ትግል እያደረግን ሁሉንም አሸናፊ የሚያደርግ አማራጭ እያለን፣ ሁሉንም ተሸናፊ የሚያደርገውን አማራጭ እየተከተልን እንገኛን።

ብዙ ጊዜ አጋርነትን አለመከተል ጦስ አለው። “ችግር የለም” በሚል በክህደት (denial) የተጀመረው፣ ወደፍረጃ ወይም መጥሌ (prejudice) ያድግና ውጤቱ የእርስበርስ እልቂት ይሆናል። ለዕኩል ዕድል እና መብት የሚታገሉት ቡድኖች በአግላይ ትርክት ጠላት የሚል ሥም የሚያወጡለት ቡድን ስለሚኖረው “ተቃራኒያችን” የሚሉትን ወገን ይገፋሉ። በሌላ በኩል ያንኛው ወገንም አንዳንድ ነባር ጥቅሞቼ ሊሸረሸሩብኝ ነው፣ ከሌሎች የዕኩል ባለመብቶች ጋር ልጋራው ነው በማለት የአፀፋ ግፊት ይገፋሉ።

የአንዱ እምነት ተከታይ ይሄ በደል ነበረብኝ፣ አለብኝ፣ በዘዴ እንዲቀጥል እየተደረገብኝ ነው ሲል፤ አንዱ ብሔርተኛ በማንነቴ ምክንያት እንዲህ ዓይነት በደል ይደርስብኝ ነበር፣ አሁንም አለብኝ፣ በዚህ አካሔድ ወደፊትም በደሉ ይቀጥልብኛል ሲል፤ አንዷ ሴት በመሆኔ ብቻ ወንዶች በቀላሉ የሚያገኙትን መብትና ዕድል ተነፈግኩ ስትል፣ «እኔ አለሁልህ/ሽ» በማለት ሰው ሠራሽ የእምነት እና የማንነት ድንበሮችን መስበር ካልቻልን ለሰውነት ማዕረግ ብቁ ነን ማለት አይቻልም። ተበዳይም በአርቲፊሻል ሰበቦች ላይ ተመሥርቶ ‘አንተማ በድለኸኛል፣ ወግድልኝ’ ካለ ትግሉ የሚገባውን የሰውነት ማዕረግ ለማግኘት ሳይሆን በተራው የሌሎችን ለመግፈፍ ነው ማለት ነው። ዳር ላይ ቁሞ ችግሩን ለመፍታት የሚፍጨረጨሩትን ፀጉር እየሰነጠቁ በማብጠልጠልም ግድግዳው አይፈርስም። የሚከፋፍለን ግድግዳ ፈርሶ፥ የሚያቀራርበን ድልድይ የሚሠራው እያንዳንዳችን ሌሎች በሚያደርጉት ትግል ውስጥ አጋርነታችንን በተግባር መግለጽ ስንችል ነው።

መጤ ሃይማኖት፣ ከመጤ ሃይማኖት በመምረጥ፣ (ግን በመሠረቱ ለገዢዎቹ ዋናው ሃይማኖቱ ሳይሆን በሥመ ሥዩመ–ፈጣሪነት የገዢነት ዕድል እና ተገዢ የማግኘት ጥረት ነው።) በወንዜ ማንነት ላይ በመመሥረት አገር ሲገዙ የነበሩ ሰዎች በነበሩበት አገር ውስጥ ያንን የሚያስተባብሉ (justify-ers) መኖራቸው አይገርምም። ይልቁን ከዚያ የአስተሳሰብ እስራት ወጥቶ ሰው ሆኖ መገኘት ነው ቁም ነገሩ።

ከገዢዎች እስራት ነጻ ከመውጣት በፊት ከገዛ ኋላ ቀር አስተሳሰባችን ነጻ መውጣት ይኖርብናል። መሬት የረገጠ ለውጥ ሊያመጡ እውነተኛውን ሥራ እየሠሩ ላሉት አጋር መሆን ካቃተን፣ ቢያንስ አደናቃፊ ላለመሆን መጣር ነው።

·        በስደት በሚገኙ አባቶች ጉባኤ አድርገው መግለጫ አውጥተዋል፤

·        “የቤተ ከርስቲያን ችግር” ያሉት በርግጥ ችግር ነውን?

·         ከመካከላቸው ያሉትና በእምነታቸው ነቅ የሌለባቸው አባቶች ለምን ዝምታን መረጡ?

·        “በስደት ባለው ሲኖዶስ ሥር ላሉ አብያተ ክርስቲያናት አገልጋዮችና ምእመናን” ከፍ ያለ ታሪካዊ ጊዜ ነው፤

 (ደጀ ሰላም፤ ማርች 6/2016፤ የካቲት 27/2008 ዓ.ም )፦ በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት እና በዋናው ጠቅላይ ቤተክህነት ስር የሚገኙ የተለያዩ ካህናት “ጊዜው ተመችቶናል” በሚል ጦርነት በከፈቱበት በዚህ ወቅት በስደት በሚገኙ አባቶች የሚመራው ቤተ ክህነት አባላት የሆኑ ካህናትም ሰሞኑን ጉባዔ ማድረጋቸውንና የአቋም መግለጫ ማውጣታቸውን አስታውቀዋል (መግለጫውን በመጨረሻ ያገኙታል):: እነዚሁ “ሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ” በሚባለውና በ4ኛው ፓትርያርክ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ በሚመራው ክፍል ሥር የሚገኙ ካህናት ያደረጉት ጉባዔ ከየካቲት 21-25/2008 ዓ.ም (ከፌብሩዋሪ 29 እስከ ማርች 4/2016 መሆኑ ነው) ድረስ የተካሄደ መሆኑን “ቆሞስ አባ ጽጌ ድንግል ደገፋው፤ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ” በሚል ፊርማና ማኅተም የወጣው መግለጫ ያትታል። ታዲያ ስለምን ተነጋገሩ? ውሳኔያቸውስ ምን ይሆን?

በሦስት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ትምህርት መሰጠቱን ከባለ 4 ገጹ መግለጫ ለማወቅ ተችሏል። “1ኛ. “ትምህርተ ኖሎት”፤ 2ኛ.  “የቤተ ክርስቲያን ፈተና ትላንት እና ዛሬ”፤ 3ኛ. “አምልኮተ እግዚአብሔር እና ሥርዓቱ” በሚሉ ርዕሶች። አስተማሩ የተባሉት እነማን መሆናቸውን መግለጫው ባይጠቅስም ያወጡትን የጋራ መግለጫው በስምንት ቁጥሮች ከፍሎ አቅርቧል። ቁጥር 1 የመግለጫው አካል “ራሱን ማኅበረ ቅዱሳን ብሎ የሚጠራው አካል” በስደት የሚገኙ አባቶች ላይ (በስም ጠቅሶ ደግሞ ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ ላይ) “በቅርቡ በጀመረው የስም ማጥፋት ዘመቻ፣ በማን አለብኝነት የመከፋፈል ሥራ እየሠራ ይገኛል” ሲል ይከሳል።

በሰሜን አሜሪካ በመካሄድ ላይ ያለውን “ጸረ ተሐድሶ የስልክ ጉባዔዎች” የማኅበረ ቅዱሳን ጉባዔ ነው በሚል በስሕተት ወይም ደግሞ ሆን ብለው “ጠላት መጣባችሁ” በሚል ምዕመናንን ለማስተባበር የተጠቀሙበት ሊሆን እንደሚችል መገመት ቢቻልም ማኅበረ ቅዱሳን “በቅርቡ የስም ማጥፋት ዘመቻ ያደረገው” የት እና በምን ሁኔታ ነው የሚለውን ምንም አላብራሩም።

በቁጥር ሁለት መግለጫቸውም ከላይ በቁጥር አንድ የጀመሩትን በማብራራት “በየአጥቢያችን የተሰገሰጉ የማኅበሩ አባላት ረብሻዎችን ሊያስነሱብን ነው” የሚል ሥጋታቸውንና ጭንቀታቸውን ገልጸዋል። ቁጥር ሦስትም የዚያው ተጨማሪ ሆኖ ማኅበረ ቅዱሳን ላይ ያነጣጠረ ውንጀላቸው እስከ ቁጥር 6 ድረስ ይዘልቃል። በሐሳብ ደረጃ ስንመለከታቸው የመግለጫው ፍሬ ሐሳቦች በአዲስ አበባ ሀ/ስብከትና በጠቅላይ ቤተ ክህነት ውስጥ ባሉ ሙሰኛ እና የተሐድሶ አስተምህሮ አራማጆች ተደጋግመው የሚገለጹትን ውንጀላዎች የደገሙ ሆነው እናገኛቸዋለን።

ቁጥር ሰባት ላይ “የሐሰት ትምህርት የሚያስተምሩ፤ እኛ ክርስቲያን አይደለንም፣ ጠላት ያወጣልን ስም ነው፣” የሚሉ ያሏቸውን ሰዎች ተቃውመዋል። እንዲህ እያሉ የሚያስተምሩት እነማን እንደሆኑ፤ ማንነታቸውን እና ምንነታቸውን ምን እንደሆነ አስረግጠው ሳያስረዱ በደፈናው ይቃወማሉ። ምእመናንን ከእነርሱ ለመጠበቅ በሚል ማስጠንቀቂያ ለመስጠትም ይሞክራሉ። ስለ ማኅበረ ቅዱሳን ብቻ መግለጫ ሰጡ እንዳይባሉ ያስገቡት ይመስልባቸዋል።

በመጨረሻ፣ እንዳይቀር እንዳይቀር በሚል ጉባኤው “ራሳቸውን ተሓድሶ ነን በሚል የፕሮቴስታንቶችን ትምህርት በቤተ ክርስቲያን ትምህርት ስም የሚያስተምሩ መሆናቸውን በሚዲያ ከለቀቁት የስሕተት ትምህርት ጉባኤው ተረድቷል” ካሉ በኋላ ጉባኤው ስለተረዳው ነገር እና ስለ አቋሙ ገለጥ አድርጎ ሳያብራራ በደፈናው “ትምህርታዊ መልስ በመስጠት ቤተ ክርስቲያንን ለመጠበቅ ተግቶ ለመሥራት ጉባኤው ተስማምቷል” በሚል ቤተ ክርስቲያናችንን በማመስ ላይ ስለሚገኘው ተሐድሶ ለማንሣት ይሞክራሉ።

ጉባኤው ለየትኛው ጉዳይ ክብደት ሰጥቶ ተነጋገረ? ዋናው የጉባኤው ዓላማስ ምን ነበር የሚለውን ለመረዳት ከስምንት ነጥቦች (መግቢያውን ሳይጨምር) መላልሶ ያነሣውን ጉዳይ መረዳት በቂ ነው። ይህንንም በማያሻማ ሁኔታ “በዚህ ዘመን ቤተ ክርስቲያናችን የተጋረጠባት ትልቅ አደጋ ምንድነው” ብሎ ይጠይቅና “ራሱን ማኅበረ ቅዱሳን ብሎ የሚጠራው ቡድን ነው” ሲል ራሱ ይመልሳል። (ገጽ 2)

ይህ ማኅበረ ቅዱሳን ላይ ያነጣጠረው ዘመቻ አስደናቂ የማይሆነው ከጉባዔው ተሳታፊዎች ቀንደኞቹ በተሐድሶ ትምህርታቸው የሚነቀፉት ሰዎች መሆናቸውን ልብ ሲሉ ነው። እነዚህ ግለሰቦች ኢትዮጵያ ከሚገኘውና በዋናው ቤተ ክህነት እግሩን አንሰራፍቶ ከተቀመጠው የተሐድሶ ክፍላቸው ጋር በመቀናጀት በአንድ ሰሞን፣ አንድ ዓይነት መግለጫ በማውጣትና ነገሮችን ከሥሩ አይመረምርም የሚሉትን ምእመን ለማደናገር ሞክረዋል።

ይሁን እንጂ እነርሱ እንዳሰቡት ሳይሆን በተለያየ የፖለቲካ አመለካከታቸው በሀገር ውስጥ ያለውን መንግሥት የሚቃወሙ፣ በፓትርያርክ አባ ማትያስ የሚመራውን ቤተ ክህነት እና ራሳቸውን ፓትርያርኩንም የማይቀበሉ እየመሰሉ ነገር ግን እጅና ጓንት ሆነው እንደሚሠሩ በትክክል አሳይተዋል። በቤተ ክርስቲያናችን የተፈጠረው የአባቶች ልዩነት እና ሁለት ሲኖዶስ የሚባል ችግር እንዳይቀረፍ በዚህም በዚያም ሆነው የሚያከላክሉ ሰዎችን በተሐድሶ ጉዳይ ላይ አብረው ሲሰሩ መመልከታችን “ግርግር ለሌባ ያመቻል” የሚለውን ተረት አስታውሶናል። በአባቶች መለያየት ያተረፈው አካል ማን መሆኑ ግልጽ እየወጣ ነው።

ሌላውን ትልቅ ቁምነገር “በርግጥ የቤተ ክርስቲያናችን ትልቁ ችግር በቃ ይኸው ነው? የገዳማት መበተን፣ የመምህራን መቸገር፣ የምእመናን ቁጥር ከጊዜ ጊዜ እየቆረቆዘ መምጣት፣ የአጽራረ ቤተ ክርስቲያን መጠንከር፣ የምእመናን በዘረኛ መንግስት ቁም ስቅላቸውን ማየት፣ ከቀዬያቸው መፈናቀል፣ መታሰር፣ መገረፍ እና መገደል፤ የቤተ ክህነት አስዳደርን የጨበጡ ብዙ ሙሰኛና ዘራፊ ሰዎች የቤተ ክርስቲያኒቱን ሀብት በጠራራ ፀሐይ መዝረፋቸው ወዘተ እንደ ችግር እንዴት ሳይታያቸው ቀረ?

በዓላማ የተሐድሶን እምነት የሚያስፋፉትና በዚህ ጉባኤ ላይ መኖራቸውን በፎቶግራፎች ያየናቸው ሰዎች ዓላማቸው ነውና “ያስቸገረን ማኅበረ ቅዱሳን ነው” ቢሉ ብዙም አይደንቅም። ሌሎቹ አባቶች፣ በሃይማኖታቸው የማይጠረጠሩትና ወልድ ዋሕድ ብለው የሚያምኑት ግን አሁንም ዝምታን የመረጡትና አጃቢ ሆነው የቀረቡት በይሉኝታ ነው፣ ባለማወቅ ነው፣ ወይስ በርግጥም የቤተ ክርስቲያን ችግር ምንነቱን አያውቀቱትም ወይም ዘንግተውታል?

ሊሰመርበት የሚገባው ሌላው ጉዳይ በአገር ቤት ከሕወሐት ወያኔ ጋር እጅና ጓንት ሆኖ አገራችንን እና ቤተ ክርስቲያናችንን በማፍረስ ላይ ያለው የተሐድሶ ቡድን በውጪ አገር ደግሞ የተቃውሞው ኃይል አካል መስሎ ለመታየት የቻለበት ሁኔታ ነው። በዚህ ዘዴያቸው ከኢትዮጵያውያን ሬዲዮኖች እስከ ድረ ገጾች ድረስ “የነጻነት ኃይል” መስለው ለመታየት ከመቻላቸውም በላይ በፖለቲካ እያሳከሩ እምነታቸውን ለማስፋፋት በመጣር ላይ ይገኛሉ። ይህ ጽሑፍ በሚዘጋጅበት ወቅት እንኳን ይህ የቤተ ክርስቲያንን ችግር ምንነት በተንሸዋረረ መልኩ ለማሳየት እና ምእመናን የአቅማቸውን እንዳያደርጉ አቅጣጫ የሚያስቀይር መግለጫ በhttp://ecadforum.com/Amharic/archives/16224/ድረ ገጽ ላይ ወጥቷል። ሌሎቹም ይከተላሉ፤ ሬዲዮኖቹም ይህንን የተሳሳተ አስተሳሰብ ሲያንጸባርቁ ይገኛሉ።

ነገ ነጻነት በኢትዮጵያ ሲመለስና ሕዝብ የመረጠው አስተዳደር ሲተከል እንኳን ዛሬ “ተቃዋሚ መስለው” የቀረቡት እነዚህ ኃይሎች ቤተ ክህነቱን ለመቆጣጠርና የአገራችንንና የቤተ ክርስቲያናችንን መከራ ለማክበድ እነሆ ተዘጋጅተዋል። ነጻነት ናፋቂው ክፍል በዚህ ጸረ ተዋሕዶ ክፍል በመታለል እስከ መቼ የአፍራሽ ተግባራቸው አካል ይሆናል?

እነሆ አሁን “በስደት ባለው ሲኖዶስ ሥር ላሉ አብያተ ክርስቲያናት አገልጋዮችና ምእመናን” ከፍ ያለ ታሪካዊ ጥያቄ መቅረቡን ሊገነዘቡት ይገባል። ከወንዝ ልጅነት ባለፈ በመካከላቸው ያለውን ጸረ ተዋሕዶ ቡድን ሊመለከቱ ይገባቸዋል። በርግጥም አሁንም “ተሐድሶ የሚባል የለም፤ ማኅበረ ቅዱሳን ነው የፈጠረው” በሚለው ማባበያ የሚታለሉ አይመስለንም። በርግጥ ይህንን ማስጠንቀቂያ ችላ ብለው ካለፉ እጅግም ባልራቁ ዓመታት ተሐድሶ ምእመናኑን በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያሉ ፕሮቴስታንቶች አድርጎ ያገኙታል። ያን ጊዜ ለመመለስ እጅግ ያስቸግራል። ከሕንድ ታሪክ እንማር፤ እንንቃ።

ማስጠንቀቂያ፦ በዚህ ጉባኤ ላይ የተገኙትን አባቶች በጅምላ ተሐድሶ ናቸው አለማለታችን ግልጽ ቢሆንም ደግመን ለማሳሰብ እንወዳለን። ነገር በማመሳሰል ያልተባለውን ተባለ ለሚሉት መናፍቃን ዕድል አንሰጣቸውም።

መልካም ዐቢይ ጾም

ቸር ወሬ ያሰማን፤

አሜን      

        

Deje Selam is a venue of news, views and opinions about or related to the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. [email protected]

አውሮፓ አርግዞ ለመውለድ ፋሽት ሲሰላ ዘመኑ ሲያምጥ የቆየበት 12 ዓመቱ በሰማኒያ ስምንት። ጣልያን ቢቀላውጥ ከምኒልክ ቤት እቴጌ ጣይቱ ፊት ነሥተውት ውሀ አጠጥተው አፈር አስበሉት። ፒያትሮ ቶሴሊ እና ባራቴሪ ባለጥቁር ሸሚዝ ምንደኛ አስካሪ ሊደፍሩሽ አልቻሉም አገራችን ኩሪ የድል አምባ አድዋ ዘለዓለም …

አድዋ የድል አምባ (ተፈራ ድንበሩ) Read more »