‹ሀገር ማለት ሰው ነው›፤ እስኪ ሙት በለኝ! – ዳንኤል ክብረት
ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገርሙኝ ዘፈኖች አንዱ ‹ሀገር ማለት ሰው ነው› የሚለው ነው፡፡ እሥራኤላዊና ጂፕሲ ይህንን ቢሰሙ ምን ይሉ ይሆን? እላለሁ፡፡ አይሁድ በመላው ዓለም ለ1900 ዓመታት ያህል ተበታትነው ሲኖሩ በየአካባቢው ሰው ነበራቸው፤ያውም እንደ ብረት የጠነከረ ማኅበረሰብ፤ ሀገር ግን አልነበራቸውም፡፡ ሀገር ማለት ሰው …
ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገርሙኝ ዘፈኖች አንዱ ‹ሀገር ማለት ሰው ነው› የሚለው ነው፡፡ እሥራኤላዊና ጂፕሲ ይህንን ቢሰሙ ምን ይሉ ይሆን? እላለሁ፡፡ አይሁድ በመላው ዓለም ለ1900 ዓመታት ያህል ተበታትነው ሲኖሩ በየአካባቢው ሰው ነበራቸው፤ያውም እንደ ብረት የጠነከረ ማኅበረሰብ፤ ሀገር ግን አልነበራቸውም፡፡ ሀገር ማለት ሰው …
የኢትዮጵያ መንግስት ለመሰረተ-ልማት ግንባታዎች ከቻይና ብቻ 17.6 ቢሊዮን ዶላር ተበድሯል። የኢትዮጵያ መንግስት ለሰፋፊ የመሰረተ-ልማት ግንባታዎች እና የማምረቻ ዘርፉን ለማሳደግ ከውጭ አገራት የሚበደረው ገንዘብ መጠን ያሰጋቸው ባለሙያዎች ግን ከአመት አመት በሚጨምረው ብድር ምክንያት አገሪቱ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ያሰጋታል እያሉ ነው።
የኢትዮጵያ መንግስት ተግባራዊ እንቅስቃሴ ማድረግ እንደሚጠበቅበት ዩናይትድ ስቴትስ አስታውቃለች የዩናይትድ ስቴይትስ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የዴሞክራሲ ሰብዓዊ መብትና የስራ ጉዳዮች ረዳትሚኒስትር ቶም ማሊኖውስኪ በዚህና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ ከኢትዮጵያ ባለስልጣኖች ጋርተወያይተዋል። …………………. የኦሮሚያ ህዝብ ተገቢ ብሶቶች እንዳሉት የተቀበለው የኢትዮጵያ መንግስት፤ ተግባራዊ …
እንደሚታወቀው ብአዴን ከኢሕአፓ ተነጥለው ለወያኔ ባደሩ ሰዎች በወያኔ እገዛና ክትትል ከተመሰረተው ኢሕዴን የወጣ ድርጅት ነው:: ኢህዴን ህብረብሄር የነበረ ድርጅት ስለነበር እንዲህ ያለ ድርጅት በወያኔ የፖለቲካ እምነት ዘንድ ተቀባይነት አልነበረውም:: በጎሳ ላይ የተመሰረተ ፌደራሊዝም ብቸኛ አማራጭ ነው ብሎ የሚያምነው ወያኔ የህብረብሄራዊ …
የወያኔ የደህንነት ተቋም በመረጃ ድርቅ ተመታ:: ዳግም ግምገማ ሊገባ ነው:: #Ethiopia #EthiopianSecurity #EPRDF #OromoProtests #Miniliksalsawi Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – ለደህንነት ተቋም ቢሮ ቅርብ የሆኑ ምንጮች የኦሮሚያ ክልል የሕዝብ ተቃውሞ ከፈነዳ በኋላ ባሉት ጊዜያት በመላው ሃገሪቱ እንደ ውሃ ይፈስ የነበረው …
የወያኔ የደህንነት ተቋም በመረጃ ድርቅ ተመታ:: ዳግም ግምገማ ሊገባ ነው:: Read more »
የአውሮፓ ሕብረት ልዩ የልኡካን ቡድን አባላት ከተቃዋሚ መሪዎች ጋር ተወያዩ:: የአውሮፓ ህብረት ልዑካን ቡዲን የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት እና የኢትዮጵያ ፈደራላዊ ዲሞክራሰሰዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) ሊቀመንበር ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ ጋር በወቅታዊ የኢትዮጵያ ጉዳዮች ላይ ተነጋገረ። ዛሬ 30/03/2016 ማምሻውን …
የአውሮፓ ሕብረት ልዩ የልኡካን ቡድን አባላት ከተቃዋሚ መሪዎች ጋር ተወያዩ:: Read more »
ታሳሪዎቹ ላለፉት አምስት ቀናት ፍርድ ቤት እንዳልቀረቡ ዘጋቢያችን መለስካቸው አምሃ ያደረሰን ዘገባ ጠቁሟል።
ኣማራ ሲሞት ሌላ ኣማራ ሲፈራ ( ሄኖክ የሺጥላ ) እነዚህን ከስር የምትመለከቷቸውን ፎቶዎች ወዳጆቼ ከባህር ዳር ዛሬ ሌሊት ላኩልኝ። ስለ ፎቶዎቹ ምንነት ባጭሩ ላስቀምጥ ተደብዳቢው — አማራ! ደብዳቢው— ወያኔ ትግሬ! የድብደባው ምክንያት— አማራ መሆን! ተጠያቂ —የለም!!! ይህንን ለማስቆም የሚቆም አማራ— …
ፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም፣ ነጻነት ለሀገሬ)

(እ.ኤ.አ መጋቢት 27/2016 በማሪዮት ጆርጅታዎን ከተማ (ዋሽንግተን ዲሲ) ቪዥን ኢትዮጵያ በተባለው ድርጅት አስተባባሪነት “ስለወደፊቷ ኢትዮጵያ፡ ሽግግር፣ ዴሞክራሲ እና ብሔራዊ አንድነት ጉባኤ” በሚል ርዕስ በእንግሊዝኛው ቅጅ ከቀረበው ንግግር የተወሰደ ነው።) …
“ስለወዲፊቷ ኢትዮጵያ፡ ሽግግር፣ ዴሞክራሲ እና ብሔራዊ አንድነት ጉባኤ” በሚል ርዕስ ስለተዘጋጀው ጉባኤ ቪዥን ኢትዮጵያን እና የጉባኤውን አስተባባሪዎች በሙሉ ለማመስገን እፈልጋለሁ።
አስፋ ጫቦ

ትዝታ ነው የሚርበን
ላናገኘው ላይጠግብን ብሏል ወዳጄ የነበረው ጸጋዬ ገብረ መድኅን
ለመሆኑት ትዝታ ምንድነው? ዘፈፍን ነው? እንጉርጉሮ? ኩርኮራ? ማላዘን?ሐሳብ ልጓም የለውምና እንዳሻው ወደላይ ወደታች፤ ወደውስጥ ወደውጭ፤ ወደፊት ወደኋላ፣ ወደየሚታይ ወደሊታይ ወደማይቻል ይሔዳል፤ ይጓዛል፤ ይተናል፤ ይበናል፤ ይመላለሳል፣ ይመለሳልም። “ማን አለኝ ከልካይ!” መሆኑ ነው።
ክንፉ አሰፋ

የሆላንድ ዜምብላ[1] ጋዜጠኞች የኦሮሞ ፀሐፊው የሆነውን ያሶ ካባባን ይዘው ወደ ጊንጪ ያመራሉ። እግረመንገድ ላይ የሚያገኟቸው ገበሬዎችም ሲጠይቋቸው በምስሉ ይታያል። እነዚያ በቀያቸው ማረፍያ እንኳን የሌላቸው ገበሬዎች የጋዜጠኞቹን መኪና ከብበው እንዲህ ሲሉ ይደመጣሉ። “መሬታችንን ቀምተው ለነጮች ሰጡብን። እኛንም በታተኑን …”
ፕ/ር ጌታቸው ኃይሌ

የክርስቲያኖቹ መጽሐፍ “ግብር ለሚገባው (ሹም) ግብር ገብሩ” ይላል። ግብር ለማይገባው እንደወያኔ ላለ ገዢ ግን ግብር ስለማይገባው አንዲት ቀይ ቤሳ አታቅምሱት ማለቱ ነው። ጊዜ ስለሰጠው ቀምቶ ይወስዳል። ግን ብዕሬ ስቦኝ ነው እንጂ ለማለት የፈለግሁት እንኳን “አድናቆት ለሚገባቸው የኦሮምኛ ተናጋሪ የጎሣ ፖለቲከኞች አድናቆት ስጧቸው” ለማለት ነበር።
ግርማ ካሳ

ሁለት ወንድማማቾች ናቸው። ቃየን እና አቤል ይባላሉ። በዘፍጥረት ምዕራፍ 4 ላይ የተጻፈው ነው። “ቃየን አቤልን ና ወደ ሜዳ እንሂድ አለው። በሜዳም ሳሉ ቃየን በወንድሙ አቤል ላይ ተነሳበት። ገደለውም” ይለናል ቃሉ። ደም ፈሰሰ። የወንድም ደም በወንድም እጅ። እግዚአብሔር በሆነው ነገር አዘነ። ለቃየንም ጥያቄ አቀረበለት። “ወንድምህ አቤል ወዴት ነው?” አለው። ቃየንም መለስ “ እኔ የወንድሜ ጠባቂ ነኝን?” አለ።
በኦሮሚያ ክልል ተቃውሞ አገርሽቷል:: #Ethiopia #Oromoprotests #Harerge #Arsi #OMN #MinilikSalsawi Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) በኦሮሚያ ክልል በኢሊባቦር ሃረርጌ እና አርሲ ተቃውሞዎች ዳግም መቀስቀሳቸው የተሰማ ሲሆን በአርሲ እና በኢሊባቦር የተማሪዎች ተቃውሞ መቀጠሉ ሲታወቅ በምእራብ ሃረርጌ ፋዲስ ወረዳ ለሁለተኛ ቀን ተቃውሞ ቀጥሎ …
የአክሰስ ሪል ስቴት መሥራችና የቦርድ ሊቀመንበር አቶ ኤርሚያስ አመልጋ፣ በባንክ የሚያዙበት በቂ ስንቅ (ገንዘብ) ሳይኖራቸው ለስድስት ግለሰቦች በድምሩ ከ4.8 ሚሊዮን ብር በላይ ደረቅ ቼክ በመስጠት ወንጀል በተመሠረተባቸው ክስና በሥር ፍርድ ቤት ተፈቅዶላቸው በታገደው የዋስትና ጉዳይ ላይ ብይን ለመስጠት ለረቡዕና ለሐሙስ …
የአክሰስ ሪል ስቴት መሥራችና የቦርድ ሊቀመንበር አቶ ኤርሚያስ አመልጋ መታመማቸውንና የሚወስዱት መድኃኒት መርዝ እንደሆነባቸው ተናገሩ Read more »
– ቴሌ የራሱ የኃይል አማራጭ እንዲኖረው ይደረጋል ብለዋል በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ተነስቶ በነበረው ተቃውሞ ወቅት የመንግሥት ድረ ገጾችን ሰብሮ የመግባት ጥቃት መፈጸሙን፣ የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረ ሚካኤል ለፓርላማው ገለጹ፡፡ የተሰነዘሩት ጥቃቶች በአብዛኛው ያተኮሩት በወረዳ ኔት ድረ …
በኦሮሚያ በተከሰተው ተቃውሞ ወቅት የመንግሥት ድረ ገጾችን ሰብሮ የመግባት ጥቃት መፈጸሙን ዶ/ር ደብረጽዮን ገለጹ Read more »
– ስህተቱ የፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ነው ተብሏል የአዲስ አበባ የቤቶች ልማት ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት የግንባታ ዘርፍ ማስተባበሪያ ምክትል ሥራ አስኪያጅ፣ በስህተት ታስረው አንድ ቀን ካደሩ በኋላ ተፈቱ፡፡ ምክትል ሥራ አስኪያጁ አቶ ተክሉ ፍቅሩ መጋቢት 17 ቀን 2008 …
የቤንሻንጉል የቅማንት ይሁን የወልቃይት ሕዝብ ችግር የሚፈታው ሕወሓታዊ ፕሮፓጋንዳና ሕዝበ-ውሳኔ አይደለም:: #Ethiopia #Amharaprotests #Welkait #Qimant #Benshangul Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) እያደር ጉድ ከሕወሓት ኩሬ ይተናል::ሕወሓቶች ስለቤሻንጉል ወልቃይትና ቅማንት ሕዝብ እያሞጠሞጡ ነው::የቤንሻንጉል ይሁን የወልቃይት ይሁን የቅማንት ሕዝብ ከትግራይ ክልል ጋር መሆን …
የቤንሻንጉል የቅማንት ይሁን የወልቃይት ሕዝብ ችግር የሚፈታው ሕወሓታዊ ፕሮፓጋንዳና ሕዝበ-ውሳኔ አይደለም:: Read more »
የሰማያዊ ፓርቲ ኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚቴ በአመራሮች ዕገዳ ላይ ውሳኔ ሊሰጥ ነው የሰማያዊ ፓርቲ የሥነ ሥርዓት ኮሚቴ በወሰደው አምስት የፓርቲውን ከፍተኛ አመራሮች የማሰናበትና የማገድ ውሳኔን በተመለከተ፣ የፓርቲው የኦዲትና የኢንስፔክሽን ኮሚቴ የመጨረሻውን ውሳኔ ረቡዕ መጋቢት 21 ቀን 2008 ዓ.ም. እንደሚሰጥ፣ የኮሚቴው ሰብሳቢ …
የሰማያዊ ፓርቲ ኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚቴ በአመራሮች ዕገዳ ላይ ውሳኔ ሊሰጥ ነው Read more »
News Ethiopia Wetatoch Dimts March 29, 2016 መረጃ ሙሉ ያደርጋል ለዚህ ደግሞ የኢትዮጵያ ወጣቶች ድምፅ ሳምንታዊ ዜናዎችን እንዲሁም መጣጥፎችን ለስለስ ካሉ ሙዚቃዎች ጋር ይዘንላችሁ ቀርበናል አብራችሁን ሁኑ ። [youtube http://www.youtube.com/watch?v=qxFzuoxTgIY&w=640&h=360]
ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ እዳ ይፈለጋል የተባለው የኦሮሚኛ ዘፋኝ አርቲስት ቀመር የሱፍ በጋዜጣ ተጠራ:: በኦሮሚኛ ዘፈኑ የሚታወቀው አርቲስት ቀመር የሱፍ ላይ የወያኔ የገቢዎች እና ጉምሩክ ባለስልጣን ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ እዳ ይፈለግበታል ብሎ ክስ እንደመሰረተበትና በአድራሻው ሊገኝ ስላልቻለ በጋዜጣ እንዲጠራለት …
ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ እዳ ይፈለጋል የተባለው የኦሮሚኛ ዘፋኝ አርቲስት ቀመር የሱፍ በጋዜጣ ተጠራ:: Read more »
በየነ ሞገስ ጽሁፌን በእውነተኛ ኑዛዜ ልጀምረው፡፡ ሰሞኑን በመጽሐፍት አዟሪዎች እጅ ‹በዓሉ ግርማ – ሕይወቱና ሥራዎቹ› በሚል ርዕስ የቀረበ መጽሐፍ ተመልክቼ ነበር፡፡ በዓሉን በተመለከተ ብዛት ያላቸውን ጋዜጦች፣ መጽሐፍት፣ መጽሔቶችና የተለያዩ ጹሑፎች የተመለከትኩና ቃለ መጠይቆች የሰማሁ መሆኔን በማመን ‹ምን አዲስ ነገር ይኖራል?› …
“የትግራይ ወጣት ልቡ ሸፍተዋል”……ህወሓት “የትግራይ ወጣት ልቡ ሸፍተዋል በተለይ ፌስቡክ የሚጠቀም ከ እኛ(ህወሓት) ርቆ ሂደዋል” የሚል ድምዳሜ የቀረበው በመቐለ ከተማ በተካሄደው የዞኑ የወጣቶች ኮንፈረስ ነው። የህወሓት መሪዎች ሰሞኑን የመቐለ ወጣት የባጃጅ ሹፌሮች ለኣራት ቀናት በማመፃቸው ከፍተኛ ድንጋጤ የፈጠረባቸው ሲሆን፡ ለወጣቱ …
የሰማያዊ ፓርቲ ውዝግብ ቀጥሏል::ፓርቲውን ለማፍረስ የታቀደ ሴራ ነው:: #Ethiopia @Semayawiparty #Blueparty #Kelemkend #MinilikSalsawi Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – የስነ ስርዓት ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ የሆኑት ሻምበል ካሳሁን እንዳሉት … ምንም አይነት የተጭበረበረ ገንዘብ እንደሌለና ነገር ግን ሆን ተብሎ ፓርቲውን ለማፍረስ የታቀደ …
የኖርዌይ ከለላ ጠያቂዎች ድርጅት ከፍተኛ አማካሪና የሕግ ባለሞያ በፖለቲካ ውስጥ ተሳትፎ ያላቸው ስደተኞች ስጋታቸው ተገቢ ነው ይላሉ። ዋሽንግተን ዲሲ — VOA Amharic ያቀረቡት የጥገኝነት ጥያቄ ተቀባይነት ያላገኘላቸው 800 ኢትዮጵያውያን እና 60 ሕፃናትን የኖርዌይ መንግሥት በግዳጅ ወደ ኢትዮጵያ እመልሳለሁ ማለቱ ከፍተኛ …
የኖርዌይ መንግሥት 800 ኢትዮጵያውያን እና 60 ሕፃናትን ወደ ኢትዮጵያ ሊመልስ ነው Read more »
በሰሜን ጎንደር በቋራ ሽንፋና አካባቢው ከዚህ በፊት ወያኔ በለኮሰው የአማራን እና ቅማንት ማህበርሰብ ላይ ለማጋጨት በፈፀመው ሴራ ላይ ለማክሸፍ ህዝብን ያረጋጉ እና ያሰባስቡ በነበሩ ግለሰብፕች ላይ አፈሳ እና እስራት ማድረጉ ይታወቃል ከነዚህም ሰለባዎች መካከል 1- መ/ አለቃ ደጀኔ ወርቁ 2- …
“ከክፉ ተወልጂ ስፈጭ አደሩኩ ” የሰማያዊ ፓርቲ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ይድነቃቸው ከበደ . ብዙ ነገር እየተባለ ነው ፤ የተባለው ሁሉ ለመቀበል ወይም ላለመቀበል የእራስ አረዳድ የሚኖረው አሰተዋአዖኦ ቀላል አይደለም። ከዚህ በኃላ የፓርቲያችን አባላት እና ደጋፊዎች ማወቅ የሚገባቸውን እንዲያውቁት መደረግ …
“ከክፉ ተወልጂ ስፈጭ አደሩኩ ” የሰማያዊ ፓርቲ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ይድነቃቸው ከበደ Read more »
የኦሞ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ኅብረት ም/ሊቀመንበርና የዞኑ ጽ/ቤት ቤት ኃላፊ አቶ ዓለማዬሁ መኮንንና በንቁ የፖለቲካ ተሳትፎው የሚታወቀው አባል አቶ አብረሃም ብዙነህ በጂንካ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው እንደሚገኙ ተረጋግጧል፡፡ እስራቱ የተፈጸመው መጋቢት 17 ቀን 2008 ዓ.ም ቤታቸው ከማለዳው 12 ሰዓት እስከረፋዱ 4፡20 ከተፈተሸ …
በደቡብ ኦሞ የኦህዲኅ መሪ አቶ ዓለማዬሁ መኮንንና አንድ ጠንካራ አባል ታሰሩ – ግርማ በቀለ Read more »
የኖርዌይ ከለላ ጠያቂዎች ድርጅት ከፍተኛ አማካሪና የሕግ ባለሞያ በፖለቲካ ውስጥ ተሳትፎ ያላቸው ስደተኞች ስጋታቸው ተገቢ ነው ይላሉ።
በበፍቃዱ ኃይሉ
የሥም ነገር ሳልወድ በግዴ ያፈላስመኛል። ሥም ተራ መለያ መጠሪያ ብቻ ነው ብዬ አልቀበልም። ምናልባት መጀመሪያ ላይ እንዲያ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን አሁን፣ ሥም በባሕልና የሥልጣኔ ዝግመተ ለውጥ ሒደት (evolution of civilizations) ውስጥ ብዙ ውስብስብ ነገሮችን እያነገበ በጊዜ ባቡር ተሳፍሮ ውስብስብ ደረጃ ላይ ደርሷል። ሥም የባሕል መገለጫ፣ የፖለቲካ አመለካከት መንፀባረቂያ፣ የወላጆች ለልጆች ውርስ ነው። ለዚያም ይመስለኛል “ሥምና ማንነት” የሚለው ጉዳይ የመጽሐፍ ምዕራፍ እና የጥናት ርዕስ ለመሆን እየበቃ ያለው። አባቶቻችን በፈረንጆች ‘የሊትሬቸር’ አጻጻፍ ደምብ ስላልጻፉልን ፍልስፍና መስለው ያልታዩን አፈላሳፊ አባባሎች አሏቸው። የሊቃውንቱ “ሥሙ ይመርሖ ኀበ ግብሩ” (ሥሙ ተግባሩን ይመራዋል) የምትለው አባባላቸው አሁን ምዕራባውያን እያጠኑት ያሉት ጉዳይ ላይ እነርሱ የደረሱበት ድምዳሜ ነው። በነገራችን ላይ በተቀራራቢ ሮማውያንም ‹nomen est omen› (ሥም ዕጣፈንታ ነው) የሚሉት አባባል አላቸው፡፡ ሳይንቲስቶች «ሰው ወደሥሙ ወይም ከሥሙ ወዲያ (እየተጎተተ ወይም እየተገፋ) የሚኖር ብኩን ፍጡር ነው» ወደማለቱ እየዳዳቸው ነው። ለመሆኑ አንድ ሰው ለመለያ ይሆነው ዘንድ የተሰጠው ሥም ማንነቱን ያሳብቃል? ባሕሪው ላይ ወይም ተግባሩስ ላይ ተፅዕኖ ያሳድራል?
የሥም ቅርፅ
ሥም ከአገር አገር ብቻ ሳይሆን ከዘመን ዘመን ቅርፁና ፀባዩን እየቀያየረ ይሄዳል። ለምሳሌ ምዕራባውያን ‘የቤተሰብ ሥም’ የሚሉት እኛ የለንም፤ አንዳንዶች የጎሳ ሥም እሱን ይተካል ይላሉ። በጊዜ መሥመር ደግሞ ለምሳሌ በኢትዮጵያ በ19ኛው ክ/ዘመን (ከ1900ቹ በፊት) የኢትዮጵያውያን ሥም የሚጻፈው (የሚገለጸው) ‘ከአያት ሥም➡ የአባት ሥም ➡ የልጅ ሥም’ በሚለው ቅደም ተከተል ነበር። ከዚያ ወዲህ ግን (‘የእከሌ ልጅ’ ዘመን አልፎ፣ ‘የእከሌ አባት’ ዘመን ሲጠባ) በተቃራኒው ተደርጓል። በቱርክ እ.ኤ.አ. ከ1943 በፊት የቤተሰብ ሥም የሚባል ነገር አልነበረም። አንዱን ሰው ከሌላኛው ለመለየት ሲባል እስከ ሦስት ሥሞች ድረስ ይወጡለትና በዚያ መደዳ (በእኛ እስከ አያት ሥም በምንለው መንገድ) ይጠራ ነበር። በዚህ የአሰያየም ስርዓት የአባትና የልጅ ሥም ምንም የሚያዛምዳቸው ነገር የለም። ለምሳሌ የቱርክ አባት የሚባለው አታቱርክ (Atatürk) ሥሙ ሙስጠፋ ከማል ነበር። አታቱርክ የተጨመረው ኋላ ለክብሩ ሲባል ነው። የአባቱ ሥም ደግሞ አሊ ሪዛ ነበር። በቱርክ የተጠፋፉ ዘመዳሞች በሥም ተፈላልገው የመገናኘት አማራጭ አልነበራቸውም ማለት ነው። በሌላው ባሕል የልጅ ሥም፣ የአባት ሥም፣ የቤተሰብ ሥም… የምንለው ነገር ዝምድና መቁጠሪያም ጭምር ነው ማለት ነው፡፡
በአገራችን በተለያዩ ማኅበረሰቦች የተለያየ ዓይነት የሥም አወጣጥ አላቸው። ለምሳሌ በጋምቤላ የአኙዋክ ብሔረሰብ ሥም አወጣጥ ሥሙን ሰምቶ ስለሰውዬው ጥቂት ቤተሰባዊ መረጃ ማግኘት ይቻላል። በአኙዋክ፣ የመጀመሪያ ልጅ ኡመድ ይባላል፤ ሁለተኛ ኡጁሉ፣ ሦስተኛ ደግሞ ኦባንግ እያለ ይቀጥላል። አንዳንዴ አባትና ልጅ አንድ ዓይነት ሥም ሊኖራቸው ይችላል። ታላላቆቹ ሴቶች ሆነው መጀመሪያ የሚወለድ ወንድ ኦማን ይባላል። ለምሳሌ እኔ ከአኙዋክ ቢሆን የተወለድኩት ኦማን እባል ነበር እንደማለት ነው።…
በአማራ ተወላጆች ዘንድ ደግሞ ትንሽ ለየት ይላል። ለምሳሌ መንዞች “ርስትና ውትድርና ይወዳሉ” ይባልላቸዋል። ይህም በሥማቸው ሳይቀር ይስተዋላል። ለምሳሌ “ሸዋጉልቱ” የመንዜ ሥም ነው። አምበርብር፣ ደምሰው፣ ዳምጠው፣ አሸብር፣ የመሳሰሉትም የመንዜ ሥሞች ናቸው። ጎንደሬ ደሞ “ሹመት ይወዳል” ይባላል። የጎንደሬ ሥሞች ሹመቴ፣ መኳንንት ወይም መኮንን የመሳሰሉት ናቸው (ወይም ነበሩ)። ቀደም ብዬ እንዳልኩት የሥም አወጣጥ እንደጊዜው ይለዋወጣል። ጎጃም የሄድን እንደሆነ ደግሞ ከልጅ እስከ አባት (ወይም አያት) ያለው ሥም ተገጣጥሞ ዓረፍተ ነገር የሚሰጥበት ጊዜ አለ። በጣም ታዋቂ ከሆኑት መካከል ብንጠቅስ እንኳ ሐዲስ ዓለምአየሁ፣ በዕውቀቱ ሥዩም፣ ፍቅር ይልቃል፣ እያደር አዲስን ማግኘት ይቻላል።
ሥም እና ፖለቲካ
ሥም የፖለቲካ መሣሪያም ነው። የአብዮቱ ሰሞን የተወለዱ ልጆች ‘አብዮት’፣ ‘ትቅደም’… የሚል ሥም ተሰጥቷቸው ዕድሜያቸውን እንኳ እንዳይደብቁ ሆነዋል። አሁንም ያ ባሕል ቀጥሎ “ሕዳሴ” ከሥም ዝርዝሮች ውስጥ ገብቷል። የኦሮሞ ብሔርተኞች ‘የአማራ’ ሥማቸውን እየቀየሩ ቢሊሱማ (ነፃነት)፣ ኒሞና (አሸናፊ) የመሳሰሉት የወጣት ‘አክቲቪስቶች’ ተመራጭ ሥሞች እየሆኑ ነው። ኦቦ ሌንጮ (“አንበሳው” እንደማለት) ለታ (ከዮሐንስ ለታ) እና ብዙዎቹ የኦነግ አንጋፋዎችም ሥሞቻቸውን በመቀየር ነው ትግላቸውን የጀመሩት። በዕውቀቱ ሥዩም የአያቱ ቀዳማይ ሥም በዻዻ መሆኑን መጥቀሱ የኦሮሞ ብሔርተኝነትን ለመተቸት እንደነፃ ፈቃድ ሆኖለታል (ወይም ተጠቅሞበታል)። ዮናታን ተስፋዬ ደግሞ የአባቱን ቀዳማይ ሥም (ቴሬሳ) ፈልጎ የተጠቀመው የኦሮሞ ብሔርተኝነትን በአዎንታዊ መንገድ መረዳቱን ለማመልከት ነበር። በተመሳሳይ በ‘ያ ትውልድ’ ዘመን ሥምን ለፖለቲካ ዓላማ ራስን ለመደበቅ ሲባል መቀየር የተለመደ ነበር። ሕወሓቶች የሞቱ ጓዶቻቸውን ሥም ይወርሱ ነበር። ለገሰ ዜናዊ መለስ ዜናዊ እንደሆኑት ማለት ነው። በሕወሓት ለፖለቲካ ዓላማ ስዩም መስፍን ከአረቦች (ሶርያዎች) እርዳታ ለማግኘት ራሳቸውን ሙስሊም አስመስለው ለማቅረብ የአባታቸውን ሥም ሙሳ ነው ብለዋል። ብዙዎቹ የኦህዴድ ሰዎችም ከምርኮ ወደትግል ሲገቡ የ“አቢሲኒያ” ሥሞቻቸውን ወደ “ኦሮሞ” ቀይረዋል።
ሥምን ለፖለቲካ አገልግሎት መቀየር በዓለም ዙሪያ የተለመደ ነው። አምባገነኑ ሞቡቱ ሴሴ ሴኮ ‘የአውሮጳውያን’ ነው ያሉትን ሥማቸውን ቀይረው ነው ሴሴ ሴኮን በማስጨመር የትግል ሥም ያገኙት። በአገራቸው ዛየር (የአሁኗ ኮንጎ) የክርስቲያን ሥም (Middle Name የሚባለው) ‘የእብራይስጥን ሥም’ ለአፍሪካውያን ሲሰጥ የተገኘ ቄስ እስከ 5 ዓመት የሚደርስ እስር እንዲቀጣ የሚያደርግ ሕግ አውጥቷል። ጥቁር አሜሪካዊው ታጋይ ማልኮም ኤክስ የቤተሰቡን ሥም በ‘X’ የተካው እና ሌሎችም አጋሮቹ እንደዚያው ያደረጉት “የነጮች” ነው ያሉትን የክርስትና ሥም ለመቃወም ነበር።
ሥም እና ሃይማኖት
መጤ ሃይማኖት ነባር ባሕሎችን ሁሉ ደምስሶ የመተካት አቅሙ ኃያል ነው። ክርስትና እና እስልምና የዓለም ሥም አወጣጥ ቅርፅን የለወጡት በዚሁ ኃይላቸው ነው። በዓለማችን ላይ በብዛት ወንዶች የሚጠሩበት ሥም ‘መሐመድ’ ነው የሚል ነገር ማንበቤ ትዝ ይለኛል። በአገራችን ወላጆች ለልጆቻቸው ሥም ሲያወጡ ወይ አምላካቸውን መጥቀስ ወይም ከቅዱስ ባለታሪኮቻቸው የአንዱን ታሪክ መጥቀስ ይቀናቸዋል። በሱፍቃድ (በእግዜር ፍቃድ)፣ ዋቅጅራ (እግዜር አለ)፣ ገብረእግዚኣብሔር (የእግዜር ሥራ)… ጥሩ ምሳሌዎች ናቸው።
በቅዱሳን ባለታሪኮች ልጅን መሰየም በተለይ አሁን አሁን ፋሽን እየሆነ መጥቷል። አገር በቀል ሥሞችን ለልጆች ማውጣት ልጆቹን “ፋራ” (ወይም “አራዳ” ያልሆኑ) የሚያሰኝ ይመስላል።
በሌላ በኩል በቀድሞ ጊዜ ለንግሥና ሲባል ሥምን መቀየር የተለመደ ነበር። ብዙ ጊዜ ንግሥናን በጳጳሳት ተቀብቶ ለማፅደቅ ሲባል በክርስትና ሥም መጠራት ደንብ ነበር። (ነገሥታት ራሳቸውን ሥዩመ-እግዚአብሔር ይሉ ነበር። ስለዚህ ንግሥና ፖለቲካዊ ብቻም ሳይሆን ሃይማኖታዊም ነበር) ተፈሪ መኮንን [ቀዳማዊ] ኃይለሥላሴ የተባሉት በዚያ መንገድ ነው። “ቴዎድሮስ የተባለ ንጉሥ እስከ እስራኤል ይገዛል” የተባለውን ትንቢት ወይም ጥንቆላ ተከትሎ ነው ካሣ ኃይሉ ራሳቸውን [ዳግማዊ] ቴዎድሮስ ብለው ያነገሡት። ቀዳማዊ ቴዎድሮስም ሥማቸውን ያገኙት በትንቢቱ መሠረት እሰከ እስራኤል የመግዛት (ካልሆነም ትንቢቱን ሰምተው በሥም የሚግገዙላቸው እንዲያገኙ) ተመኝተው ነው። አውሮጳውያን አፍሪቃዊ ኃያል የክርስቲያን መንግሥት መሥርቷል ብለው በአንዲት ደብዳቤ መነሻ ብዙ ያወሩለት የነበረውን ቄስ ዮሐንስ (Prester John) ለመሆንም ሲባል ነው እስከ አራተኛ የተደረሰው። ዐፄ ዮሓንስ እና የወሎ ሙስሊሞች የገቡበት ቁርሾ መነሻም የዐፄው እንደሥማቸው የማደር ምኞት ይመስለኛል።
ሥም እና ስርዓተ—ፆታ
ሥም ስርዓተ-ፆታን የሚገልፅበት ሁኔታም ቀላል አይደለም። ወንዶች በአማራው ተወላጅ ዘንድ በጥቅሉ ምናባዊ ጀግንነትን የሚያጎናፅፍ ሥም ይሰጣቸዋል። ለምሳሌ ወንዳፍራሽ፣ ናደው፣ ሺመክት፣ መኩሪያ፣ የመሳሰሉትን ሥሞች መጥቀስ ይቻላል። በኦሮምኛ ሌንጮ (አንበሳው)፣ ኬራንሶ (ነብሩ፣ ደፋሩ)፣ ዋንጎ (ቀበሮው) የሚሉ በኃይለኛ አራዊቶች ሥም ለወንዶች የሚሰጡ ስያሜዎች ጀግንነትን ለወንድ የማልበሱ ማኅበራዊ ትውፊት አካል ናቸው። ጫላ (ቀዳሚው)፣ ሁንዳራ/ኢራና (የበላይ)፣ ኩማራ (ሺመክት) የመሳሰሉትም የተጠቀሰውን ምናባዊ ጀግንነት አልባሽ ኦሮምኛ ስያሜዎች ናቸው። በሲዳምኛ አዳቶ (ደፋሩ)፣ ዳፉርሳ (የማይዳፈሩት) የመሳሰሉት ሥያሜዎች የላይኞቹ ዓይነት ሚና አላቸው። በሌሎቹም ቋንቋ እና ባሕሎች ውስጥ ተመሳሳይ አጠራሮች አሉ።
ለሴቶች ሲሆን ውበታቸውን፣ ወይም በቁስ የሚተመን ዋጋቸውን የሚገልፅ ሥም ይሰጣቸዋል፦ መድፈሪያሽ ወርቅ፣ ሺብሬ፣ ወርቂቱ፣ ብሪቱ፣ ሸጊቱ፣ ቆንጂት…የሴቶች ሥም አወጣጥ ሴቶችን በአትክልትና ፍራፍሬ የሚመስልበትም ጊዜ ቀላል አይደለም፤ አበባ፣ ወይኒቱ፣ ትርንጎ፣ ብርቱኳን፣ ሸዊት (በትግርኛ “እሸት” ማለት ነው) ጥቂት ምሳሌዎች ናቸው። በኦሮምኛ ቢፍቱ (ብሩህ፣ ፀሐይቱ/ጣይቱ)፣ ፋኖሴ (መብራቴ)፣ መጋሌ (ጠይም/ቆንጆ)፣ ዱንጉጄ (ሽንኩርት፣ አጭር ቆንጆ)፣ በከልቻ (ኮኮብ፣ ለዓይነ ቆንጆ) የመሳሰሉት ሥሞችና በሲዳምኛ ዳንቺሌ (ቆንጆ፣ ፀባየ ሸጋ)፣ ደራርቱ (አበባ፣ ፍካት (ኦሮምኛም ነው)) ሴትን በውበቷ የመግለፅ ትውፊታዊ ወግ ያሳያሉ።
ሥም እና የቤተሰብ ታሪክ
ሥም አንዳንዴ የሐዘን መግለጫ ነው። አባቱ (ተፀንሶ እያለ ወይም በልጅነቱ) ወይም ታላቅ ወንድሙ የሞተበት ልጅ ለምሳሌ በአማርኛ ምትኩ፣ ማስረሻ… ይባላል፤ በትግርኛ ካልኣዩ፤… ታላላቆቹ ሲወለዱ እየሞቱ እሱ ግን ያንን መሰናክል ያለፈ ልጅ ለምሳሌ በአኙዋክ ኞም ይባላል፤ በሲዳማ ሪቂዋ ይባላል።
ሥም አወጣጥ ልጁ በተወለደ ጊዜ ወላጆች የነበራቸውን ግንኙነት፣ የኢኮኖሚ ሁኔታ እና ወዘተ የሚናገርበትም ሁኔታ አለ፤ ለምሳሌ አስማማው፣ አስታርቄ… የመሳሰሉት ሥሞች ብዙ ጊዜ የሚወጡት እየተጥጣሉ (በተለይ በልጅ እጦት) የነበሩ ጥንዶች የልጅ መገኘቱን ተከትሎ ሲስማሙ ነው። ወላጆች ልጅ ሲወልዱና የጥሩ ዕድል (በተለይ የሀብት) መምጣት ከተገጣጠመ ልጃቸውን ሀብታሙ፣ ጥጋቡ፣… ብለው ሊሰይሙት ይችላሉ። በተቃራኒው ከገጠማቸው ደግሞ ያንኑ የሚያንፀባርቅ ሥም ይሰጡታል፤ ለምሳሌ ‘በድሉ’ የሚለው ሥም በዕድሉ ይደግ ከሚለው የመጣ ነው፤ ወይም ሳይታቀድ ከመጣ ነው። በኦሮሞ ትውፊት ተጨማሪ ልጅ የማይፈልጉ መሆኑን ለመግለጽ ወላጆች ለ“መጨረሻ” ልጃቸው ጉታ የሚል ሥም ያወጣሉ።
«ሥምህን ንገረኝና ማንነትን እነግርሃለሁ»
የኒው ሳይንቲስት ጋዜጠኛ ጆን ሆይላንድ “nominative determinism” (ሥም አመጣሽ ቁርጠኝነት) የሚለው ነገር አለው። ‘ሥም አመጣሽ ቁርጠኝነት’ የሚወክለው በሥማቸው ተገፍተው ለስያሜያቸው የሚስማማ ሙያ ሲከተሉ ነው። ለምሳሌ በዕውቀቱ ሥዩም ኃይለኛ ቦክሰኛ ቢሆን ኖሮ ሥሙ ከሙያው ጋር አይሰምርም እንል ነበር። በቡጢው ሥዩም ይሆን ነበርና። ስለዚህ የበዕውቀቱ ‘ሥም አመጣሽ ቁርጠኝነት’ ኋላ ቀር የሚለውን ስርዓት (social order) በነውጥ/ነፍጥ ሳይሆን በዕውቀት በመሞገት መንገሥ/መሰየም ነው።
ብዙ መንግሥቱ፣ ንጉሡ የተባሉ ሰዎች መራኄ መንግሥትነት ማዕረግ ሳያገኙ አንድ መንግሥቱ ኃይለማርያም ቦታውን መቆናጠጡ ብቻ መንግሥቱ የተባለ ሰው ሁሉ የመንግሥት ኃላፊ ይሆናል ማለት ባይቻልም ሥማቸው ግብራቸውን ቀድሞ እንዲመራው በማድረጉ ረገድ ተፅዕኖ መፍጠር ይችላል በሚለው ግን መስማማት እንችላለን፡፡
በአማራው ማኅበረሰብ ዘንድ ‹ደመላሽ› የሚለው ሥም የሚሰጠው “ደም የተቃቡ” ቤተሰቦች መካከል ከአንደኛው ወገን ተበቃይ ባልነበረበት ጊዜ ለተወለደ ልጅ ነው፡፡ የዚህ ልጅ ዕጣፈንታ ባስተዳደግ ይወሰናል፡፡ ሥሙን ያወጡለት ሰዎች ሥሙን ለምን እንዳወጡለት ብቻ ሳይሆን ምን እንዲያደርግላቸው እንደሚፈልጉም ጭምር እያስተማሩት ነው፡፡ ስለሆነም፣ አድጎ “ጠላት” የሚለውን ወገን ለመግደል መሠማራቱ ሰፊ ዕድል ያለው የሕይወቱ ምዕራፍ ነው የሚሆነው፡፡
ሥም እና ማንነት ግንኙነት አላቸው የሚሉ ጥናቶች እንደሚጠቁሙት፣ “ሥማችን – ወይም ሰዎች ሥማችንን ሲሰሙ በሚያሳዩት ግብረ-መልስ ወይም የማንነት ግምት ላይ ተመሥርቶ ባሕሪያችንን ይወስናል፡፡” ወደድንም ጠላንም በሥማችን ብቻ ሰዎች ዘውጋዊ ማንነታችንን፣ የቤተሰባችንን ሁኔታ፣ እና ሌሎችም መሠረታዊ ግምቶችን ስለኛ ያሳልፋሉ፡፡ እኛም ይህንኑ ስለምንረዳ የሰዎቹን ግምት ለማጠናከር ወይም ለማስተባበል የበኩላችንን ጥረት በማወቅም፣ ባለማወቅም ማድረጋችን አይቀርም፡፡
ሥም በባለቤቱ ላይ የሚያመጣውን ማንኛወንም ዓይነት ተፅዕኖ ለመቀነስ የተለመደ-ሥም (popular name) መስጠት እንደመፍትሔ ይጠቆማል፡፡ ልጆች በሥማቸው ማንነታቸው እየተገመተ፣ እነሱም በምላሹ በሥማቸው እና ሥማቸውን ሰምተው ሰዎች በሚያሳልፉት ግምት ተፅዕኖ ሥር እየወደቁ ‹የሥማቸው ፍሬ› እንዳይሆኑ ሲባል ለልጆች በሚያድጉበት አካባቢ የተለመደ የሚባለው ዓይነት ሥም ቢሰጣቸው የገዛ ሥማቸው ሰለባ ከመሆን ይድናሉ፡፡
—
እንደ ዋቢ:-
– የነጋድራስ ገ/ሕይወት ባይከዳኝ ድርሰቶች፣
– Atatürk (biography), by Andrew Mango
– Wax and Gold, by Donald Levine
– ፍቅር እስከ መቃብርን የጻፉት «ሐዲስ» ናቸው ወይስ «ዓለማየሁ»? (የሚከራዩ አማት እና ሌሎች)፣ በዳንኤል ክብረት
– ሉኣላዊነትና ዴሞክራሲ በኢትዮጵያ፣ በገብሩ አሥራት
– ሥምና ማንነት (ከአሜን ባሻገር)፣ በበዕውቀቱ ሥዩም
– Typology of Oromo Personal Names, by Tesfaye Gudeta Gerba
– እና የተለያዩ ድረገጾች እና ሌሎችም…
‹‹ በስኳር ኮርፖሬሽን ውስጥ እየሆነ ያለው በሰራተኞች አንደበት ሲገለጽ››// በተጠናቀቀው የመጀመሪያው የህዳሴና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን (ከ 2002 እስከ 2007) በአገራችን ሊከናወኑ በዕቅድ ከተያዙ ሜጋ -ፕሮጀክቶች -እንደ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጄክቶች /የህዳሴው ግድብ የለበትም፣በድንገት የተጀመረ ነው/፣ የባቡር ትራንስፖርት መስመር ግንባታ …
በስኳር ኮርፖሬሽን ውስጥ እየሆነ ያለው በሰራተኞች አንደበት ሲገለጽ – ኢዮብ ዓለም — Read more »
አህመድ 29 ዓመቱ ነው። ከኢትዮጵያ ወደ ኬንያ፤ ከኬንያ ደግሞ በብራዚል በኩል አድርጎ ወደ ፐሩ ኢኳዶር፤ ኮሎምቢያ፤ ፓናማ ይሸጋገርና በማእከላዊ አሜሪካ ደግሞ ወራት የፈጀውን የኮስታሪካ፤ ኒካራጓ፣ ሆንዱራስ፤ ጓቲማላ፣ ከዚያ በሜክሲኮ በኩል ወደ ዩናይትድ ስቴይትስ ያደረጉትን ጉዞ ያብራራል።
እነ ዓለማዬሁ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ 60 ሰዓት አለፈ// ቤተሰብ በሄርፒስ ኮርፒስ መብት ለመጠየቅ እየተዘጋጀ ነው ፡፡ በደቡብ ኦሞ ዞን ዋና ከተማ ጂንካ ፖሊስ ጣቢያ ከቅዳሜ ጠዋት ጀምሮ የኦህዲኅ ም/ሰብሳቢ አቶ ዓለማዬሁን ጨምሮ የታሰሩት ሦስት ሰዎች በተጠረጠሩበት ጉዳይ ቃላቸውን ሳሰጡና ፍርድ …
ሕወሓት ካድሬዎቿን ይዛ ወደ አፋር ክልል ለመስፋፋት #ሽኸት_ናብ_ትግራይ_ትመለስ ዘመቻ ጀምራለች:: #Ethiopia #Afar #Shihet #Tigray #TPLF #MinilikSalsawi Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) ሕዝብ ለሕዝብ የሚያናክሰው የሕወሓት የመስፋፋት ፖሊሲ ተከዜን የወልቃይት እና ጠገዴን ምድር ከነሕዝቡ ወደ ትግራይ በማካለል በአከባቢው ከፍተኛ የፖለቲካ ቀውስ እንዲነሳ …
ሕወሓት ካድሬዎቿን ይዛ ወደ አፋር ክልል ለመስፋፋት #ሽኸት_ናብ_ትግራይ_ትመለስ ዘመቻ ጀምራለች:: Read more »
ማኅበረ ቅዱሳን “ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን አስተምህሮዋን እንጠንቅቅ፤ ድርሻችንን እንወቅ” በሚል ርዕስ በአዲስ አበባ ኤግዚብሽን ማዕከል ለ 1 ሳምንት ለማሳየት ያዘጋጀው ዐውደ ርእይ ለዕይታ ለመቅረብ ሰዓታት ሲቀሩት “ባልታወቀ አካል” ቀጭን ትዕዛዝ መታገዱን በዘመኑ ፈጣን የመገናኛ መንገዶች ከኢትዮጵያ አልፎ በመላው ዓለም …
በሕመምተኛ ልጁ ሕክምና ስም በርካታ አጥቢያዎች በ፻ሺሕዎች እያወጡ በሰጡበት ኹኔታ፥ “እኔ ሳላውቅ ስሜን ለማስጠፋት የተሠራ ነው” በሚል ምዝበራውን ለማስተባበል እየጣረ ነው ግማሽ ሚሊዮን ብር እንዲሰጠው የተወሰነበት የእንጦጦ ኪዳነ ምሕረት አስተዳደር ኮሚቴ ውሳኔ ቃለ ጉባኤ፣ በአስተዳደራዊ ውሳኔ ተሽሮ ውሳኔውን በሚያስተባብል ሌላ ቃለ …
ፓትርያርኩ: የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ጋዜጠኛ የማነ ዘመንፈስ ቅዱስን “ቀንደኛ ሌባ” አሉት Read more »
የሰማያዊ ፓርቲ ዲሲፕሊን ኮሚቴ ሊቀመንበሩን ኢንጂነር ይልቃልን እና አቶ ወረታውን አባረርኩ አለ:: #Ethiopia #EPRDF #Blueparty @Semayawiparty #MinilikSalsawi Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – ጠንካራ ፓርቲዎችን ሰርጎ ገብ አስገብቶ በመበታተን ጠንካራ አመራሮችን በመወንጀል ፓርቲዎችን አዳክሞ ብመቃብራቸው ላይ ተለጣፊ ታማኝ ተቃዋሚዎችን የሚተክለው …
የሰማያዊ ፓርቲ ዲሲፕሊን ኮሚቴ ሊቀመንበሩን ኢንጂነር ይልቃልን እና አቶ ወረታውን አባረርኩ አለ:: Read more »
የኢትዮጵያን ሙስሊሞችን እንቅስቃሴ እና ህዝበ ሙስሊሙ በፊርማው ጥያቄዬን በሰላማዊ መንገድ ያቀርቡልኛል ያላቸን ኮሚቴዎችንን አሸባሪ በማለት የሚዎነጅለው ጀሀዳዊ ሀረካት የተሰኘውን ዶክመንተሪ ፊልምን ያዘጋጀው የወያኔ ለጋሲ አስቀጣይ የሆነው ብርሀኔ ንጉሴ የተባለው ግለሰብ አዲስ የሰራው ቤዛ የተሰኘ ፊልም በማህበራዊ ሚዲያ ፊልሙን እንዳታዩ የሚል …
የጀሀዳዊ ሀረካት ዶክመንተሪ አዘጋጅ የተሰራው አዲስ ቤዛ የተሰኘ ፊልም ላይ በማህበራዊ ሚዲያ የቦይኮት ዘመቻ ተካሄደበት:: Read more »
የሕወሓት የመስፋፋት እቅድ የወለደው የእርስ በእርስ ጦርነት በተክል ድንጋይ ፈንድቷል:: #Ethiopia #AmharaProtests #Qimant #TekilDingay #Gonder #TPLF Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – ከትላንትና ጠዋት ጀምሮ የሚደርሱ መረጃዎችን ተከትሎ ለማረጋገጥ እንደተቻለው የሕወሓት የመስፋፋት ፖሊሲ እና ታላቋን ትግራይ የመመስረት አላማውን ለማሳካት ሲል የሚሰራቸው …
የሕወሓት የመስፋፋት እቅድ የወለደው የእርስ በእርስ ጦርነት በተክል ድንጋይ ፈንድቷል:: Read more »
በአሁኑ ወቅት ከቃሊቲ የማጎሪያ ካምፕ የሚወጡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በኦሮሞ ልጆች ላይ ከፍተኛ የሆነ ስቃይ እየደረሰ ሲሆን ስም ዝርዝራቸውን እና የተፈረደባቸው ጊዜ እንደሚከተለው ነው::ቀሪ መረጃዎች እና ስሞች ያሏቹህ ከታች አስፍሩበት:: 1. Masfiin Ittaanaa Fufaa……………………………….Umrii guutuu 2. Charinnet Yamanee………………………………… Umrii guutuu …
ቃሊቲ ማጎሪያ ካምፕ ውስጥ የኦሮሞ ወገኖቻችን ስቃይ ቀጥሏል::(ስም ዝርዝራቸውን ይመልከቱ) Read more »
በሀገሪቱ አሁን የተከሰተው የረሀብ አደጋ በህዝብ ቁጥርና ስፋት በታሪክ ተወዳዳሪ የለውም። አሁን የተረጂዎች ቁጥር 20 ሚሊየን ደርሷል። ለመሆኑ ረሀቡን በተመለከተ የመንግስት ምላሽ፣ የለጋሾች አቋምና በአጠቃላይ ለችግሩ የተሰጠው ትኩረት አደጋውን የሚመጥን አይመስልም። በጉዳዩ ዙሪያ ያሉ መረጃዎችን አሰባስበን ውይይት አድርገንባቸዋል። አድምጡት ተወያዩበት …
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ኢዴፓን ጨምሮ ስምንት ፓርቲዎች አባል ከሆኑበት አገር አቀፍ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምክር ቤት አባላት ጋር ሰሞኑን ተወያይተዋል። አዲስ አበባ — VOA — ተመጣጣኝ የዉክልና ሥርዓት በሚባለዉ የፓርላማ ምርጫ ሥርዓት ላይ ዉይይት እንዲደረግ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ …
ተመጣጣኝ የዉክልና ምርጫ ሥርዓት ዉይይት እንዲደረግ ይሁንታ አለ ተባለ (VOA) Read more »
ረሃብ ጊዜ አይሰጥም::ለቻይና እና ቱርክ ሸቀጦች ቅድሚያ እንዲራገፉ በማድረግ በረሃብ አለንጋ ዜጎቹን በመግረፍ የሚገድል አገዛዝ #Ethiopia #Ethiopiafamine #MinilikSalsawi Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – በምግብ እሕል ራሳችንን ችለናል እየተባለ ከውጭ አገራት 450 ሺህ ሜትሪክ ቶን የእርዳታ ስንዴ በውጪ ሃይሎች ድጋፍ መግዛት …
ረሃብ ጊዜ አይሰጥም::ለቻይና እና ቱርክ ሸቀጦች ቅድሚያ እንዲራገፉ በማድረግ በረሃብ አለንጋ ዜጎቹን በመግረፍ የሚገድል አገዛዝ Read more »
Addis Admass : ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገርሙኝ ዘፈኖች አንዱ ‹ሀገር ማለት ሰው ነው› የሚለው ነው፡፡ እሥራኤላዊና ጂፕሲ ይህንን ቢሰሙ ምን ይሉ ይሆን? እላለሁ፡፡ አይሁድ በመላው ዓለም ለ1900 ዓመታት ያህል ተበትነው ሲኖሩ በየአካባቢው ሰው ነበራቸው፤ ያውም እንደ ብረት የጠነከረ ማህረሰብ፤ ሀገር ግን …
በደቡብ ኦሞ የእነ አቶ ዓለማዬሁ እስራት ‹‹ ከአርበኞች ግንቦት 7 ›› ጋር የተያያዘ ነው// ‹‹ አይ ፍርሃት– ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ ሲያንከራትት›› ከሰዐት በፊት ባቀረብነው መረጃ የኦሞ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ኅብረት ም/ሊቀመንበር አቶ ዓለማዬሁ መኮንን፣ አንድ ጠንካራ አባልና አንድ የከተማው ነዋሪ …
በደቡብ ኦሞ የእነ አቶ ዓለማዬሁ እስራት ‹‹ ከአርበኞች ግንቦት 7 ›› ጋር ግንኑነት አላቸው በሚል ጥርጣሬ ነው:: Read more »
ባለ ባጃጆች ሰለማዊ ሰልፍ እንዳያካሂዱ ታገዱ። #BajajaProtests ¥¥¥¥¥¥¥¥¥¥¥¥ የመቐለ ባለባጃጆች እያካሄዱ ያሉት የስራ ማቆም ኣድማ ለኣራተኛ ቀኑ የቀጠለ ሲሆን ዛሬ የይቅርታ ደብዳቤና 500 ብር የመቀጮ ክፍያ እንዲከፍሉ እያስገደዷዋቸ ይገኛሉ። ይህ የመንግስት የማስገደድ ተግባር በመቃወም ሰለማዊ ሰልፍ እንዲያካሂዱ ለትግራይ ክልል ፕሬዝዳንት …
በደቡብ ኦሞ የኦህዲኅ መሪ አቶ ዓለማዬሁ መኮንንና አንድ ጠንካራ አባል ታሰሩ// • አሸባሪነትን ለህዝብ ማሸበር መጠቀም // • ከማለዳው 12፡00 ጀምሮ እስከ ረፋዱ 4፡20 ቤታቸው ሲበረበር አርፍዷል፤ • በዕለት ሁኔታ መዝገብ ሳንመዘገብ አንታሰርም ብለው እየተከራከሩ ነው፤ የኦሞ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ኅብረት …
በደቡብ ኦሞ የኦህዲኅ መሪ አቶ ዓለማዬሁ መኮንንና አንድ ጠንካራ አባል ታሰሩ Read more »
አንድ የኢትዮጵያ ጎል በ ሰባት የአልጄሪያ ጎል ተመነዘረ:: ለመሆኑ የመልሱ ውርደታችን መቼ ነው?
የባጃጅ ኣድማ 4ተኛ ቀኑ ይዟል ============= መቐለ ከተማ እየተደረገ ያለው የባጃጅ ኣድማ 4ተኛ ቀኑ ይዘዋል። Bajaj Protests መንግስት “ከ300 በላይ ባጃጆች ላጠፉት ጥፋት 500 ብር እየተቀጡ የይቅርታ ደብዳቤ ኣስተስገብተው ታፔላ እየወሰዱ ነው” በኤፍ ኤም ራዲዮዎች ቢናገም በተግባር ግን ኣድማው ተጠናክሮ …
ዶክተር መረራ በዚህ ቅዳሜና እሁድ ዋሽንግተን ዲሲ ዉስጥ የሚካሄድ ”Vision Ethiopia” የተባለ ሲቪል ማህበረሰቦችና የፓለቲካ ድርጅቶች ጉባኤ ላይ ንግግር ሊያደርጉ ወዲህ ወደ ዋሽንግተን ዲሲ ሊመጡ ነበር።