የአውሮፓ ሕብረት ልዩ የልኡካን ቡድን አባላት ከተቃዋሚ መሪዎች ጋር ተወያዩ::
የአውሮፓ ሕብረት ልዩ የልኡካን ቡድን አባላት ከተቃዋሚ መሪዎች ጋር ተወያዩ::
የአውሮፓ ህብረት ልዑካን ቡዲን የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት እና የኢትዮጵያ ፈደራላዊ ዲሞክራሰሰዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) ሊቀመንበር ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ ጋር በወቅታዊ የኢትዮጵያ ጉዳዮች ላይ ተነጋገረ።
ዛሬ 30/03/2016 ማምሻውን በአድስ አበባ በተካሄደው ስብሰባ ላይ ኢ/ር ይልቃል በሀገሪቷ ውስጥ በየቀኑ ሰዎች በመንግስት እየተገደሉ ባሉበት በአሁኑ ወቅት ስለመድብለ ፓርቲ እና ስለነፃ ፕሬስ ማውራት ቅንጦት ነው በማለት ሀገርቱ ያለችበትን ወቅታዊ ሁነታ ለልኡካኑ አብራሪተዋል።
ልዑካኑ በእስካሁኑ ቆይታቸው ከውጭ ጉዳይ ሚንስተር፣ከፈደራል ጉዳይ ሚንስተር እና የከኢ/ፈ/ድ/ሪ ፓርላማ አፈጉባኤ ጋር የተወያየ ሲሆን በጉብኝታቸው ማጠናቀቅያ ላይ ለሚዲያዎች መግለጫ እንደሚሰጡ ይጠበቃል።
