ኢሳት ዜና (ጥቅምት 2 ፣ 2015) የህዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ (ህወሐት ) ማእከላዊ ኮሚቴ ከአመታት በፊት በጡረታ የተገለሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ታጋዮች በድጋሚ እንዲደራጁ አዘዘ። ባለፈው እሁድ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በመቀሌ ከተማ ጉባኤ ያካሄደው የህወሀት ማእከላዊ ኮሚቴ፣ በትጥቅ ትግሉ ወቅት እንዲሁም በጡረታ ሰበብ የተሰናበቱ ታጋዮች ዳግም የማደራጀት ስራ እንዲካሄድ ወስኗል። ከአመታት በፊት በእድሜና በተለያዩ ምክኒያቶች …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ኢሳት ዜና (ጥቅምት 2 ፣ 2008 ዓም) በኢትዮጵያና ግብጽ መካከል በአባይ ግድብ ዙሪያ ሊካሄድ የነበረው ድርድር መዘግየትን ተከትሎ፣ የግብፁ ፕሬዚዳንት አብደል ፋታህ አልሲሲ ከሱዳን ጋር የሚመክር የልዑካን ቡድን ወደ ሃገሪቱ ላኩ። በሃገሪቱ የመስኖ ልማት ሚኒስትር ሆሳም ሞግሃዚ የተመራው ይኸው ልዩ የልዑካን ቡድን፣ ከፕሬዚዳን አልሲሲ የተላከን ልዩ መልዕክት በመያዝ ከሱዳን ባለስልጣናት ጋር ለመምከር ካርቱም መግባቱን አል-አህራም …

ኢሳት ዜና (ጥቅምት 2, 2008ዓም) በቅርቡ ወደሶማሊያ የተሰማራው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በደቡባዊ የሃገሪቱ ክፍል ለሁለተኛ ሳምንት ከባድ ውጊያ ኣያካሄደ ኣንደሚገኝ የሶማሊያ ወታደራዊ ባለስልጣናት ትናንት ገለጹ። ለሁለተኛ ሳምንት ቀጥሎ የሚገኘው ግጭት ልዩ ስሙ አልዩ ዲዮ በተባለ ደቡባዊ ምዕራብ የሶማሊያ አካባቢ እየተካሄደ እንደሚገኝ እነዚሁ ወታደራዊ ባለስልጣናት ለጋዜጠኞች አስታውቀዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስቴር በበኩሉ በአካባቢው እየተካሄደ ባለው ውጊያ፣ የኢትዮጵያ …

ጥቅምት ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መንግስትና አለማቀፍ ድርጅቶች በሰጡት መረጃ መሰረት የተረጂው ጠቅላላ ቁጥር 8 ነጥብ 2 ሚሊየን ደርሷል፡፡ መረጃዎች ግን ከዚህ በላይ መሆኑን ያመለክታሉ። የተጠቀሰው አሃዝ ቀደም ሲል በሴፍቲኔት ፕሮግራም ታቅፈው የሚረዱ ወደ 3 ነጥብ 8 ሚሊየን ኢትዮጵያዊን ወገኖችን ይጨምራል ተብሎአል። ይሁን እንጅ መንግስት ያዘጋጀው እና አለማቀፍ ለጋሽ ድርጅቶች የሚጠቅሱት ሰነድ …

ጥቅምት ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን አዳ በርጋ ወረዳ 30 ወጣቶች በኦሮምያ ልዩ ሃይሎች በሌሊት ታፍነው መወሰዳቸውን ሂውማን ራይትስ ሊግ ኦፍ ዘ ሆርን ኦፍ አፍሪካ ገለጸ። ድርጅቱ ለኢሳት በላከው መግለጫ አብዛኞቹ የታሰሩት ወጣቶች የናይጀሪያዊው ባለሀብት ንብረት የሆነው የዳንጎቴ ሲሚንቶ ፋብሪካ ሰራተኞች እና ለእረፍት ወደ ቤተሰቦቻቸው የሄዱ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች …

ጥቅምት ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሽብር ወንጀል ተከሶ በእስር ላይ የሚገኘው ታዋቂው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የእስር ቤት አስተዳዳሪዎች በሚያሳድሩበት ጫና ለተጨማሪ ስቃይ እየተዳረገ መሆኑን የሙያ አጋሮቹ ተናግረዋል። የቀለም ቀንድ ጋዜጣ ስራ አስኪያጅ አቶ አበበ ውቤ እንደገለጹት፣ እስክንድርን ከሁለት የቅርብ የቤተሰብ አባላት ውጭ ሌሎች ሰዎች እንዳይጥቁት ተከልክለዋል። በሃይማኖት አባቶችም ሆነ በጠበቃ እንደማይጎበኝ የገለጸው …

ጥቅምት ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኦህዴድ ላለፉት 2 አመታት ከተማዋን ሲመሩ የነበሩትን አቶ አብርሃም አዱላን ወደ ክልል ቢሮ በማዛወር የሻሸመኔ ከንቲባ የሆኑትን ለከተማዋ ከንቲባ አድርጎ ሾሟል። አዲሱ ከንቲባ በሻሸመኔ የሚገኙ ሙስሊም ኢትዮጵያውያንን በማሰቃት የሚወነጀሉ ሲሆን፣ ለአዳማ የተወሳሰበ ችግር መፍትሄ ያመጣሉ ተብሎ እንደማይታመን ምንጮች ይገልጻሉ። ነባሩ ከንቲባ፣ በደባል ሱሶች በመጠመድ ያለፉትን ሁለት አመታት …

Minilik Salsawi – መቸም ራስን ማወቅ ራስን ማግኘት የመሰለ ነገር የለም::ይህ እውቀት አዘል ለሆነ ለበሰለ ሰው ይገባዋል:: ስሜትና ፕሮፓጋንዳ ለተደበላለቁበት ጫፍ አንባቢ ዘራፍ ባይ ደግሞ ላይዋጥለት ይችላል::የለውጥ ሃይል ነን የምንል ከሆነ ቆም ብለን ራሳችንን ልንዳብስ ይገባል ልንፈትሽም ይገባል:: ሃገር እየፈረሰ …

ጥፋተኞችም እኛ … መፍትሄዎችም እኛው …..የለውጥ ሃይሎች ነን የምንል ቆም ብለን ልናስብ ይገባል:: Read more »

በኦነግ አባልነት የእድሜ ልክ እስራት የተፈረደባት አሊማ አብዲ መሃመድ እንዳትማር ተከለከለች ‪#Ethiopia #Oromo በ2004 ዓ.ም በኦሮሞ ነፃአውጭ ግንባር (ኦነግ) አባልነት ተጠርጥራ ከታሰረች በኋላ የእድሜ ልክ እስራት የተፈረደባት አሊማ አብዲ መሃመድ እንዳትማር መከልከሏን ለማወቅ ተችሏል፡፡ በቃሊቲ ማረሚያ ቤት የምትገኘው አሊማ (ቢፍቱ) …

በኦነግ አባልነት የእድሜ ልክ እስራት የተፈረደባት አሊማ አብዲ መሃመድ እንዳትማር ተከለከለች ‪ Read more »

«ሱዳን የወደብ መሬት ሰጠችን » Samuel Zewoin ልክ የዛሬ አምስት አመት ገደማ በ October 2010 ፔሩ ወደብ አልባ ለሆነችው ቦሊቪያ ለንግድ ለመዝናኛ እና ለባህር ሐይል ግልጋሎት የሚሆን ቁራሽ የባህር ጠረፍ መሬት ለ 99 አመት በሊዝ መልክ በመስጠት ስምምነት ተፈራርመው ነበር። …

«ሱዳን የወደብ መሬት ሰጠችን » ወደብ ተገነባ አንዳች ነገር ቢፈጠር አንደ አሰብ ቢሊዮኖችን ለባዕድ ልናስረክብ ? Read more »

የባንክ ዘራፊ የሆነው እና ከኢኖቫ ፋየርፋክስ ሆስፒታል እጅግ በሚገርም ሁኔታ ያመለጠው ከዘጠኝ ሰአታት አደን በኋላ በቁጥጥር ስር የዋለው ኢትዮጵያዊው ወሰን አሳዬ የሰላሳ ሁለት አመት ፍርድ መከናነቡን የፍትህ ባለስልጣናት አስታውቀዋል:: የአርባ ሶት አመት እድሜ ባለጸጋው ወሰን አሳዬ ላይ አቃቢ ሕግ እንዳለው …

በቨርጅንያ ከእስር አምልጦ የነበረው ባንክ ዘራፊ ኢትዮጵያዊው ወሰን አሳዬ 32 ዓመት ተፈረደበት። Read more »

ቅጥ አንባሩ የጠፋው የኢትዮጵያችን ፖለቲካ በዋነኝነት የሚጎድለው ልክ ያልሆነን ነገር ልክ አይደለም ማለት ያለመቻል ነው፡፡ በግል አስተያየት ልክ አይደለም ብሎ መቆም ደግሞ ዋጋ ያስከፍላል፡፡ የተሳሳተ ውሳኔ ባለቤቶች በድጋሚ ጥፋታቸውን በጥፋት ለማረም ሌላ ስህተት ይደግማሉ፡፡ አሰተያየትን በአሰተያየት ለመመለስ ይከብዳቸዋል፡፡ የዚህ ደግሞ …

ኢህአዴግ በሚጠራው መድረክ አለመገኘት ማንን ይጠቅማል? ግርማ ሠይፉ ማሩ Read more »

ወንድማችን ሃብታሙ አያሌዉ በጠና ታሞ ትናንት ምሽት ዘዉዲቱ ሆስፒታል ለህክምና ገብቷል፡፡የህመሙ ምክንያት ለቤተሰቡ ያልተገለጸ ሲሆን ባለቤቱም ገብታ እንድትጥቀዉ ያልተፈቀደላት መሆኑን (እንባ ባላባሩት አይኖችዋ ዘለላዎችን እያፈሰሰች በለቅሶ ታጅባ) ትናገራለች፡፡ሰሞኑን በሙሉ ጤና እንደነበር ቂሊንጦ እስር ቤት ሄደዉ የጠየቁት ጎዶች ይናገራሉ፡፡

Habtamu ayalew . abrha desta .yeshiwas . daniel shibeshi in Ethiopian Prison

ጀግኖቹ የነፃነት ታጋዮች ኣብራሃ ደስታ፣ ሃብታሙ ኣያሌው፣ የሺዋስ ኣሰፋና ዳኒኤል ሺበሺ ነገ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ። ጀግኖቹ የተመሰረተባቸው የሽብርተኝነት ክስ “… መሰረት የሌለው ውንጀላ ነው ሰዎቹም ከክሱ ነፃ ናቸው…” ብለው ዳኞች ውሳኔ የሰጡት ሲሆኑ ዓቃቢ ህግ ይግባኝ በመጠየቁ ክእስር ሳይለቀቁ ቀርተዋል። …

ኣብራሃ ደስታ፣ ሃብታሙ ኣያሌው፣ የሺዋስ ኣሰፋና ዳኒኤል ሺበሺ ነገ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ። Read more »

ዛሬ ወደአንድ ሆስፒታል ጎራ ብየ ነበር ….(አይዞን በሰላም ነው) እና የገረመኝን ነገር አስተዋልኩ ባለቤቱን ጨምሮ አራት ዶክተሮች አሉ አራቱም ከአንድ ብሔር የወጡ ለመሆናቸው የአነጋገራቸው ቅላፄና ስማቸው ይገልፃል …. የገረመኝ ይሄ አይደለም ነርሶቹ ሁሉም በሚባል ሁኔታ ከአንድ ብሄር የወጡ መሆናቸውን ማወቅ …

ይሄ ነገር ዘረኝነት ይሆን እንዴ፡) (አሌክስ አብርሃም) Read more »

እስከ 360 ሺሕ ብር ከፍተኛ ውዝፍ ያለባቸው ተከራዮች እንደሚገኙበት ታውቋል በቤተ ዘመድ የተሸፋፈነው የክፍያው አሰባሰብ የአስተዳደር ጉባኤ አባላቱን አወቃቅሷል በፍሳሽ እና በቃጠሎ አደጋ የተጎዳው ሕንጻ ከዕድሳት ዕጦት ደኅንነቱ ለአደጋ ተጋልጧል *          *          * ሓላፊው፣ በደንቡ መሠረት ለአስተዳደር ጉባኤው የሒሳብ ሪፖርት አቅርበው አያውቁም የበጀት ዓመቱ የኻያ በመቶ የፈሰስ …

ዜጎች በተራ ‹‹ወንጀል›› 14 ከዚህ አለፍ ሲል 28 ቀን እየተቀጠሩ በሚመላለሱበትና በሚጉላሉበት ሀገር፣ አባሪው እንኳ ባልተያዘበት ሁኔታ፣ ይህ ነው የሚባል ምርመራ ሳይደረግ የሳሙኤል አወቀ ገዳይ በ17 ቀን ውስጥ 19 አመት እስራት እንደተፈረደበት ተሰምቷል፡፡ ትናንት ችሎቱን የተከታተሉት ሰዎች በግምት ከምሽቱ ሶስት ሰዓት አካባቢ አዲስ አበባ ለሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች የነበረውን ድራማ በስልክ ሪፖርት ያደርጋሉ፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ […]

The post የሳሙኤልን ገዳይ መደበቅ ያልቻለው ድራማ – ጌታቸው ሺፈራው appeared first on ሳተናው .

የኢትዮጵያ መንግሥት በቀጣይ አምስት አመታት ተግባራዊ ሊያደርጋቸው ባቀዳቸው ነጥቦች ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ሐይለማርያም ደሳለኝ ከተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ጋር ዕርብ ዕለት ተወያይተዋል።

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ጥቅምት ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ለአመት የዘለቀው የቴፒ ግጭት በአካባቢው ለሰፈረው የፌደራል ፖሊስ እና ለፌደራል ባለስልጣናት እንቆቅልሽ ሆነ በቀጠለበት በዚህ ወቅት፣ ባለፈው ቅዳሜ ከሌሊቱ 6 ሰአት ከ45 ደቂቃ ላይ ሚሊኒየም ጎዳና ላይ ወይም ሚካኤል አካባቢ ካሳሁን የተባለ የከተማው ፖሊስ አባል ተገድሏል። ፖሊሱ በቅርቡ ለከተማው ተመድቦ የመጣ ነበር። እርምጃውን የወሰዱት ራሳቸውን የቴፒ ወጣቶች …

ጥቅምት ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባለፈው ቅዳሜ በተነሳው ግጭት ከፖሊስና ከመከላከያ አንዳንድ ወታደሮች ቆስለዋል። የግጭቱ መንስኤ ሁለት የመከላከያ ፖሊስ አባላት በፖሊሶች መደብደባቸው ነው። ከዚህ ቀደም አንድ ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ ፍቼ አካባቢ ሰፍሮ የሚገኘውን የመከላከያ ሰራዊት አባል ከገደለው በሁዋላ፣ በመከላከያና በፖሊስ መካከል ለወራት የዘለቀ ቁርሾ እንዲፈጠር አድርጓል። ባለፈው ቅዳሜ ሁለት የመከላከያ ሰራዊት አባላት …

ጥቅምት ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሃገሪቱ ከሚገኙ አምራች አካባቢዎች አንዱ በሆነው በየዓመቱ ከሰኔ እስከ ህዳር ወር ድረስ ከፍተኛ የሰራተኛ ቁጥር የሚያስተናግደው የምዕራብ አርማጮኾ ወረዳ ውስጥ በሚገኙ ቀበሌዎች የሚገኙ የጤና ተቋማት ተገቢውን አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችላቸውን በጀት የክልሉ መንግስት ባለመመደቡ በየአመቱ ተገቢውን አገልግሎት መስጠት እንዳልቻሉ የወረዳው የጤና አመራሮችና ባለሙያዎች ተናገረዋል፡፡ በምዕራብ አርማጮኾ ወረዳ ያለው …

 አስታማሚ ባለማግኘታቸው ጭንቀት ውስጥ ገብተዋል –115 ዶላር ብቻ ሲከፈላቸው መቆየታቸውንም ይናገራሉ (በዛብህና በየነ እውነተኛ ስማቸው ለዚህ ጽሁፍ ሲባል ተለውጧል) ሁለቱም በሐያዎቹ አጋማሽ የዕድሜ ክልል ውስጥ ይገኛሉ፤አገራቸውን በወታደርነት ለማገልገል ቅጥር የፈጸሙት ከዛሬ ስድስትና አራት አመታት በፊት ነው፡፡የትውልድ አካባቢያቸው የነበሩትን ዲላና ሆሳህናን …

በሶማሊያ የተጎዱ ኢትዮጵያዊያን የሰላም አስከባሪዎች በኬንያ ሆስፒታል ተረስተዋል Read more »

ኢትዮጵያ አምና ወደዚያው ከላከችው ስጋ 58.8 ሚ ዶላር አግኝታለች
     የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የኢትዮጵያ የስጋ ምርት ወደ ግዛቷ እንዳይገባ ከአንድ ሳምንት በፊት ጥላው የነበረችውን ማዕቀብ ማንሳቷን ተርኪሽ ዊክሊ ድረገጽ ትናንት ዘገበ፡፡
ከሳምንት በፊት ከኢትዮጵያ ሰባት ስጋ ላኪ ኩባንያዎች ወደ አገሪቱ ከገባው 36 ቶን የበግ ስጋ ጋር በተያያዘ የተፈጠረውን ችግር ተከትሎ አገሪቱ የኢትዮጵያ የስጋ ምርት ወደ ግዛቷ እንዳይገባ ገደብ ጥላ እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፣ ከሚመለከታቸው የኢትዮጵያ መንግስት አካላት ጋር በመነጋገር ችግሩን መፍታት መቻሉን ገልጧል፡፡
ይህን ተከትሎም የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የኢትዮጵያ የስጋ ምርት ወደ ግዛቷ እንዳይገባ የጣለችውን ማዕቀብ ማንሳቷንና አገሪቱ ያሳለፈችው ውሳኔ በዘርፉ የተሰማሩ ኢትዮጵያውያንን እንዳስደሰተ ዘገባው አስረድቷል፡፡
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የኢትዮጵያን የስጋ ምርት በስፋት በመግዛት ቀዳሚዋ አገር እንደሆነችና ኢትዮጵያ ወደ ተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ከምትልከው የምግብ ኤክስፖርት ምርት በአመት በአማካይ 30 ሚሊዮን ዶላር ገቢ እንደምታገኝም ገልጧል፡፡
ኢትዮጵያ ባለፈው አመት ወደ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ከላከችው 11.692 ቶን የስጋ ምርት 58.8 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷንም ዘገባው አክሎ አስታውሷል፡፡

የካናዳዋ ቶሮንቶ ከተማ የመጪውን አመት 2016 በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያውያን የእግርኳስ ፌስትቫል እንደምታዘጋጅ ESFNA አስታወቀ::ከአስረአመስት አመት በኋላ የቶሮንቶ ከተማ ይህን ፌስትቫል ስታዘጋጅ የመጀመሪያዋ ሲሆን በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያውያን የእግር ኳስ ማህበር ደስታውን ገልጾ በቶሮንቶ ኢትዮጵያውን ኩራት እንደሚሰማው ተናግሯል:: ማንኛውንም የጉዞ እና የፕሮግራሙን …

ቶሮንቶ የመጪው አመት 2016 በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያውያን የእግር ኳስ ፌስትቫል ታስተናግዳለች:: Read more »

ጉዳዩን ለአለም የሚያሳውቅ ገለልተኛ አካል እንዲቋቋም ጠይቋል
                                
    ሠማያዊ ፓርቲ፤ በኢትዮጵያ የተከሰተው “ረሃብ”፤ ከገዥው ፓርቲ የፖሊሲ ውድቀት የመነጨ ነው በማለት ችግሩን ለአለም የሚያሳውቅ ገለልተኛ አካል እንዲቋቋምና አለማቀፉ ህብረተሰብ እርዳታውን እንዲለግስ ጠየቀ፡፡ ፓርቲው ከትናንት በስቲያ “ረሃቡ የገዥው ፓርቲ የፖሊሲ ውድቀት ነው!” በሚል ርዕስ በሠጠው መግለጫ፤ ችግሩ ከተፈጠረ በኋላ አለማቀፉ ማህበረሰብ ለዜጐች እርዳታ እንዳያቀርብ መንግስት ጉዳዩን ሲሸፋፍን ቆይቷል ሲል ተችቷል፡፡
“መንግስት የኋላ ኋላ ከአቅሙ በላይ ሲሆንበት ችግሩ እንደተከሰተ ቢገልጽም ዜጐች ተገቢውን እርዳታ በሚያገኙበት መልኩ እርምጃ እየተወሰደ አይደለም” ብሏል ፓርቲው በመግለጫው፡፡ የተከሰተው ችግር የፖሊሲ ውድቀትን ያመላክታል ያለው ሰማያዊ ፓርቲ፤ ገዥው ፓርቲ ቆሜለታለሁ የሚለውን አርሶ አደርና አርብቶ አደር ህይወት ለማሻሻል የረባ ስራ እንዳልሠራ ማረጋገጫ ነው ብሏል፡፡ “ግብርናው ኢኮኖሚውን ይመራል የሚለው በተግባር አልታየም፤ ምክንያቱም ሚሊዮኖች በየአመቱ ለ“ረሃብ” ችግር መጋለጣቸውን ቀጥለዋል” ሲል ገልጿል ፓርቲው፡፡
ለተከሰተው ሀገራዊ ችግር መንግስት አፋጣኝ እርምጃዎችን እንዲወስድ ያሳሰበው ሰማያዊ ፓርቲ፤ ስለ ችግሩ ለኢትዮጵያውያንና ለአለም አቀፍ ማህበረሰብ የሚያስረዳ ገለልተኛ አካል ተቋቁሞ፤ በችግሩ ለተጠቁ ዜጐች መፍትሔ እንዲፈለግ ጠይቋል፡፡
የምግብ እጥረቱ (ረሃቡ) ከተፈጠረባቸው አካባቢዎች መረጃ በማሰባሰብና በማጣራት ለህዝብ በየጊዜው እንደሚያሳውቅ የገለፀው ፓርቲው፤ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ኢትዮጵያውያንና የአለም ህብረተሰብ ከተጐጂዎች ጐን እንዲቆሙ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡
መንግስት በበኩሉ፤ ችግሩ የተፈጠረው በአለማቀፍ ደረጃ ከተከሰተው የአየር ፀባይ ለውጥ (ኤሊኖ) ጋር ተያይዞ መሆኑን በመግለፅ፣ በአገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች ዝናብ ባለመዝነቡ የምግብ እጥረት ቢያጋጥምም “ረሃብ” አለመከሰቱን በተደጋጋሚ አስታውቋል፡፡

     በቅርቡ በሳዑዲ አረቢያ በሃጂ ስነስርአት ወቅት በተፈጠረ መጨናነቅ ህይወታቸውን ያጡ ኢትዮጵያውያን ቁጥር 47 መድረሱን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ገልጿል፡፡
ባለፈው መስከረም 13 ቀን 2008 በሳዑዲ አረቢያ ሚና አካባቢ በደረሰ አደጋ ከ1ሺህ በላይ የተለያዩ ሀገር የሃይማኖታዊ ስነ ስርአቱ ተሳታፊዎች ህይወታቸውን ባጡበት ወቅት ኢትዮጵያውያን ላይ አደጋ ስለመድረሱ ወዲያው ማወቅ ያልተቻለ ሲሆን ከቀናት በኋላ 2 ኢትዮጵያን ህይወታቸው ማለፉ ተዘግቦ እንደነበርና ኋላም የሟቾች ቁጥር ወደ 31 ማደጉ ይታወቃል፡፡ ከትናንት በስቲያ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ቁጥሩ 47 መድረሱንና ተጐድተው ሆስፒታል ገብተው ከነበሩት 26 ኢትዮጵያውያን 24 ተሽሏቸው ከሆስፒታል ሲወጡ፣ 2ቱ ተኝተው ህክምና እየተከታተሉ መሆኑ ታውቋል፡፡
ለሃጅ ስነስርአት ወደ ሳዑዲ አረቢያ ሄደው የነበሩ ከ1ሺህ 100 በላይ አማኞች መመለሳቸውንም ምክር ቤቱ አስታውቋል፡፡ በዘንድሮ የሃጂ ስነስርአት ላይ 10ሺ ኢትዮጵያውያን መሣተፋቸውም ታውቋል፡፡

የእስካሁኑ ሳያንስ አሁንም ይጨፈርብን? – (ከኢትዮጵያ ልጅ) የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን (ኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን) የኤርትራ ቴሌቪዥን ሆነ እንዴ? ያስባለኝን ጥያቄ እንዳነሳ ያደረገኝ በነሐሴ መጨረሻና በጳጉሜን ወራት በተለያዩ ቀናት ደጋግሞ የኤርትራ ስደተኞች በስደት በሰፈሩበት ቦታ ላይ የነፃነት ትግል የጀመሩበትን 54ኛ ዓመት በዓል በኢትዮጵያ …

ወያኔ የሻዕቢያ ጉዳይ ፈጻሚና ተላላኪ ነው – ተጠያቂነት ይኑር በአገር አይቀለድ፡፡ – ለኢትዮጵያውያን ትልቅ ቁስለት ነው Read more »

ጌታዬ! ላንተ ያለኝ ፍቅር ላንተ ያለኝ ክብር ምን ያህል እንደሆን… ተወው አልነግርህም ብትሆንም ኩራቴ ምስጢር አርጎት ይቆይ ልጉም አንደበቴ። ስላንተ ‘ሚያወራ የሚናገር አፌ ሰውን ካበሳጨ የፍቅሬ ጥግጋት በቃላት ተሰፍሮ በክፉ ካሳጨ ይቅር አልነግርህም…… እስካልቆረቆረኝ የተፈናጠጥኩት የፍቅርህ ኮርቻ ዝም………… ብዬ ልውደድህ …

*** ምስጢር ነው!*** Tigist Alemneh Read more »

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች ጋር ተወያዩ

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ላይ ከአገር አቀፍ ፓርቲዎች አመራሮች ጋር ውይይት አደረጉ፡፡

ባለፈው ዓርብና ቅዳሜ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክስ ኮሚሽን አዳራሽ በተካሄደ ስብሰባ ላይ ጥሪ የተደረገላቸው 22 የፖለቲካ ፓርቲዎች በውይይቱ ላይ ተሳትፈዋል፡፡ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) እና ሰማያዊ ፓርቲ ‘በዕድገትና በልማት አጀንዳዎች ላይ ከመወያየታችን በፊት፣ በሌሎች አጠቃላይ ፖለቲካዊና አገራዊ ጉዳዮች ላይ መወያየት መቅደም አለበት’ በማለት በስብሰባው እንደማይካፈሉ በማስታወቃቸው በአዳራሹ ሳይገኙ ቀርተዋል፡፡ ባለፈው ዓርብ  በመጀመሪያው የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አፈጻጸም ላይ በሚኒስቴር ዴኤታ ማዕረግ የብሔራዊ የፕላን ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ጌታቸው አደም አማካይነት ማብራሪያ የቀረበ ሲሆን፣ በዕቅዱ አጠቃላይ አፈጻጸሞችና ጉድለቶች ላይ ከተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችና ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ምላሽ ሰጥተዋል፡፡    

 

በዚህ አውድ ለማቅረብ የተገደድኩበትን ዘግናኝ ታሪክ፣ ወደር በሌለው አስከፊነቱ የተነሳ ለንባብ ባላበቃው በወደድኩ ነበር፡፡ ግና! ይህ መንግስታዊ የጭካኔ ተግባር፣ ዛሬም በምስኪን ዜጎች ላይ እየተፈፀመና ብዙዎችን ሰለባ እያደረገ በመሆኑ ህዝቡ ይህን ሊሸሸግ እየተሞከረ ያለውን መከራ ተረድቶ ሥርዓቱን በአደባባይ ዓመፅ “ሃይ!” ይል …

የኢትዮጵያ መንግሥት ገመና – ጋዜጠኛ ተመስገን ደሣለኝ (ከዝዋይ እስር ቤት) Read more »

  በአሥር ደረጃዎች ተከፋፍሎ ለገበያ ሲቀርብ የነበረው የኢትዮጵያ ቡና ምርት ወደ ስድስት ደረጃዎች ዝቅ ብሎ ለግብይት እንዲበቃ ተወሰነ፡፡

 ከኢትዮጵያ ምርት ገበያ የተገኘው መረጃ እንደሚያስረዳው፣ እስካሁን የአገሪቱ የቡና ምርት በአሥር ደረጃዎች ተከፋፍሎ እንደየደረጃው  ዋጋ እየተሰጠው ሲሸጥ ቆይቷል፡፡

ይህ የደረጃ አሰጣጥ ግን ለአሠራርም ሆነ የአገሪቱ የቡና ምርት ሊያገኝ የሚገባውን ዋጋ እንዳያገኝ በማድረጉ በአዲስ አሠራር እንዲለወጥ ተደርጓል፡፡ በቡና ደረጃዎች አሰጣጥ ላይ የተደረገ ጥናት አዋጭ የሚሆነው አሥር የነበሩትን የቡና ደረጃዎች ዝቅ ማድረግ እንደሚገባ ነው፡፡ 

በዚህ መሠረት የተደረገውን ጥናት የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለሥልጣንና ንግድ ሚኒስቴር በመቀበላቸው፣ የ2008 ዓ.ም. የቡና ምርት ከሚገባበት ከታኅሳስ ወር ጀምሮ የኢትዮጵያ ቡና በስድስት ደረጃዎች ተከፋፍሎ ለገበያ እንዲቀርብ መወሰኑን፣ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ኤርሚያስ እሸቱ አረጋግጠዋል፡፡

እንደ አቶ ኤርሚያስ ገለጻ፣ በዚህ ውሳኔ መሠረት ለምሳሌ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ተብሎ ደረጃ ይሰጣቸው የነበሩትን በአንድ ደረጃ ማጠቃለል ያስችላል፡፡ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ የሚሰጣቸው የቡና ዓይነቶች ዋጋ ልዩነት ተቀራራቢ በመሆኑ በአንድ ዋጋ እንዲሸጡ ያስችላል፡፡ የተሻለ ዋጋም ያስገኛል፡፡ በመጋዘን አሠራርም አሥር ቦታዎች ከፋፍሎ ከማስቀመጥ በስድስት ቦታዎች ማስቀመጥ ጊዜና ጉልበትን ይቆጥባል ብለዋል፡፡

በአዲሱ የምርት ዘመን ከታኅሳስ 2008 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆነው ይህ አሠራር፣ በቡና አቅራቢዎችም መደገፉን የምርት ገበያው መረጃ ያመለክታል፡፡

ከአንድ እስከ አምስት ደረጃ የተሰጣቸው ለኤክስፖርት የሚቀርቡ ሲሆን፣ ደረጃ ስድስት የተሰጠው ቡና ደግሞ ለአገር ውስጥ ገበያ የሚውል ነው፡፡

 

 ኤርትራ ዝቅተኛ የኢንተርኔት ተጠቃሚ በመሆን አለምን ትመራለች
   በኢትዮጵያ የኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚ የሆነው ከአጠቃላዩ ህዝብ 1.7 በመቶ የሚሆነው ብቻ ነው መባሉን የአሜሪካው የቢዝነስ መጽሄት ፎርቹን ዘገበ፡፡ኢንተርኔት ላይቭ ስታትስ የተባለው አለማቀፍ ተቋም ያወጣውን መረጃ ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ እጅግ ዝቅተኛ የኢንተርኔት አገልግሎት አቅርቦት ካላቸው አስር የአለማችን አገራት መካከል ስምንቱ በአፍሪካ አህጉር እንደሚገኙና ኢትዮጵያም አንዷ እንደሆነች በጥናት ተረጋግጧል፡፡በኢንተርኔት አገልግሎት አቅርቦት ዝቅተኛነት ከአለማችን ቀዳሚውን ስፍራ የምትይዘው ኤርትራ መሆኗን የጠቆመው ዘገባው፣ ከአገሪቱ ህዝብ የአገልግሎት ተጠቃሚ የሆነው 0.91 በመቶ ብቻ መሆኑን ገልጧል፡፡ከአውስትራሊያ በስተሰሜን የምትገኘው ቲሞር ሌሴቴ ደሴት በ1 በመቶ፣ ማይንማር በ1.16 በመቶ፣ ብሩንዲ በ1.39 በመቶ እንዲሁም ሴራሊዮን በ1.49 በመቶ በኢንተርኔት አቅርቦት ዝቅተኛነት እስከ አምስተኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል ተብሏል፡፡  ሶማሊያ በ1.51 በመቶ፣ ኒጀር በ1.61 በመቶ፣ ኢትዮጵያና ጊኒ በ1.7 በመቶ እንዲሁም ኮንጎ በ1.92 በመቶ እንደሚከተሉም ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡

ግርማዊ እቴጌ መነን መጋቢት 25 ቀን 1883 ዓም በወሎ ጠ/ግዛት በአምባሰል አውራጃ ልዩ ስሙ ዕጎ ከተባለው ቀበሌ ከጃንጥራር አስፋውና ከወ/ሮ ስሀን ሚካኤል ተወለዱ። እቴጌ መነን በልጅነት ዘመናቸው በእናት በእባታው ቤት መምህር ተቀጥሮላቸው አማርኛ ማንበብና መፃፍ ጠንቅቀው አወቁ። በተጏዳኝ ልዩ ልዩ የቤት ባልትና ሙያዎችን ተምረው በማጠናቀቃቸው የቤት ራስ ለመባል በቅተዋል፡፡ በ1892 ማለትም በተወለዱ በአሥረኛ አመታቸው ለመጀመሪያ […]

The post ስለ እቴጌ መነን በጨረፍታ (ከስሜነህ ጌታነህ) appeared first on ሳተናው .

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

  መንግስት በጠራው ውይይት ላይ ዋናዎቹ ተቃዋሚዎች አልተሳተፉም
  •  ፓርቲዎቹ መቅደም ይገባቸዋል ሏቸውን ጉዳዮች አስቀምጠዋል

         መንግስት በነደፈው የ2ኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ውይይት ላይ ትናንትናና ዛሬ ተቃዋሚዎች እየመከሩ ሲሆን ዋናዎቹ ተቃዋሚዎች መድረክ፣ ሠማያዊ እና መኢአድ በውይይቱ ላይ አልተሳተፉም፡፡
መንግስት ለሁሉም ተቃዋሚ ፓርቲዎች 20 አባሎቻቸውን አርብና ቅዳሜ በሚደረግ ውይይት ላይ እንዲያሳትፉ በደብዳቤ ያሳወቀ ሲሆን ኢዴፓን ጨምሮ ሌሎች ተቃዋሚ ፓርቲዎች በውይይቱ መሳተፋቸውን ሲያረጋግጡ ዋናዎቹ ተቃዋሚዎች ግን ቅድመ ሁኔታዎችን በማስቀመጥ በውይይቱ ሳይሳተፉ ቀርተዋል፡፡
ሠማያዊ ፓርቲ የመንግስት እቅድ ላይ ለውይይት ከመቀመጤ በፊት በብዙሃን ፓርቲ ዲሞክራሲ፣ በሰብአዊ መብት አያያዝ፣ የነፃ መገናኛ ብዙሃንና ሲቪክ ማህበራትን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ መወያየት አለብኝ ሲል በቀጥታ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በፃፈው የምላሽ ደብዳቤ አስታውቋል፡፡
“በኢትዮጵያ ሰላምና እድገት እቅድ ላይ ከመወያየት በፊት በተጠቀሱት ጉዳዮች ላይ መወያየት አስፈላጊ ነው” ያለው የፓርቲው መግለጫ፤ መሠረታዊ ጉዳዮች መፍትሔ ባልተበጀላቸው ሁኔታ በዕቅዱ ዝርዝር አፈፃፀም ላይ መወያየት ለኢትዮጵያ እድገትና ብልጽግና ያመጣል ብሎ እንደማያምን በደብዳቤው አመልክቷል፡፡
የመላው ኢትዮጵያውያን አንድነት ድርጅት (መኢአድ) በበኩሉ፤ በውይይቱ ላይ እንዲሳተፉ ከመንግስት በቀረበለት ጥሪ ላይ ስራ አስፈፃሚ ተሰብስቦ መቅደም ያለባቸው ብሔራዊ ጉዳዮች አሉ በማለት ከመሳተፍ መቆጠብን እንደመረጠ ለአዲስ አድማስ አስታውቋል፡፡ ፓርቲው ስብሰባው ላይ ለመሳተፋ የማይችልባቸውን ሶስት ምክንያቶች ጠቅሷል፡፡ የብሔራዊ እርቅና መግባባት ላይ ያተኮረ ስብሰባ በቅድሚያ እንዲጠራም ጠይቋል፡፡
ግዙፉ ብሔራዊ እቅድ ሁሉንም አሣታፊ በሆነ መልኩ ከግብ እንዲደርስ መጀመሪያ ሁሉንም ተቃዋሚ ያሳተፈ የብሔራዊ መግባባትና እርቅ ጉባኤ መጠራት አለበት ያለው ፓርቲው፤ “የልማት መሠረቱ የዜጐችን ሰብአዊ መብት መጠበቅ ስለሆነ የመኢአድ አባላትም ሆኑ ሌሎች የተቃዋሚ አባላት እየተሰቃዩ፣ እየተሳደዱ፣ እየተዋከቡ ባለበትና አጠቃላይ የሰብአዊ መብታቸው በተገፋበት ሁኔታ እንዲሁም ዜጐች ክልልህ አይደለም በሚል እየተፈናቀሉ፣ በስብሰባው ላይ መገኘት ፍሬ ሊሰጥ የሚችል አይደለም” ብሏል፡፡ የሚካሄደው ውይይት ለሠፊው የኢትዮጵያ ህዝብ በሚዲያዎች በቀጥታ የሚሠራጭ ባለመሆኑ ሃሳባችን ተቆራርጦ የተሳሳተ መልዕክት ሊተላለፍ ይችላል በሚል ስጋት ከውይይቱ ራሱን ያገለለው ደግሞ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ነው፡፡
ትናንት በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የስብሰባ አዳራሽ በተደረገው የመጀመሪያ ቀን ውይይት መክፈቻ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ የተገኙ ሲሆን “የተለያዩ የፖለቲካ አቋሞች ቢኖሩም ያለን አንድ አገር በመሆኑ ሁሉም አካላት በአገሪቱ ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ መወያየትና ግብአት መስጠት አስፈላጊ ነው” ብለዋል፡፡ በጠዋቱ ክፍለ ጊዜ በመጀመሪያው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን አፈፃፀም ላይ በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የብሔራዊ ፕላን ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ጌታቸው አደም ጽሑፍ ካቀረቡ በኋላ የፓርቲ ተወካዮቹ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡
የኢዴፓ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ጫኔ ከበደ፤ የውይይት መድረኩ መዘጋጀቱ መልካም መሆኑን ጠቅሰው በመጀመሪያው የእቅድ ዘመን ላይ ተመዘገበ ተብሎ የቀረበው የኢኮኖሚ እድገት አሃዝ ላይ ጥርጣሬ እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡ በተለይ የትምህርት ጥራትን ከማስጠበቅና ግብርናን ከማዘመን አንፃር የሚቀሩ ስራዎች እንዳሉ ጠቅሰዋል፡፡ የቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ተወካይ በበኩላቸው፤ የኑሮ ውድነቱ ላይ መንግስት ትኩረት አድርጐ አልሠራም፤ በቀጣይ በትኩረት ሊሠራ ይገባል ያሉ ሲሆን የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ ተወካይ ደግሞ ከመሠረተ ልማት ግንባታና ከሃብት ብክነት ጋር የተያያዙ አስተያየቶች ሰጥተዋል፡፡ ትናንት በመጀመሪያው የእቅድ አፈፃፀም ላይ ውይይት ሲደረግ የዋለ ሲሆን በዛሬው እለት በቀጣይ ሊተገበር በታሰበው ሁለተኛው እቅድ ላይ ውይይት ይካሄዳል ተብሏል፡፡ በውይይት መድረኩ ላይ ኢዴፓ፣ አንድነት፣ ቅንጅት እና ኢራፓን ጨምሮ 20 ያህል ሀገር አቀፍ ፓርቲዎች ተሣታፊ መሆናቸውም ታውቋል፡፡

Amdom Gebreslasie የመንግስት ኣካላት ይሁኑ ኣይሁኑ ለህዝቡ ግልፅ ያልሆኑ ኣካላት በክልተ ኣውላዕሎ ወረዳ የሚገኘው የዮዲት ጉዲት ( ጋዕዋ ) መቃብርና በዙርያው የሚገኙ ተዛማጅ ቅርሶች ወዳልታወቀ ቦታ ነቅለው ሊወስዱ ሲሞክሩ ከኣከባቢው ህዝብ ጋር ተጋጭተዋል። መቃብሩ የሚገኝበት ወረዳ ክልተ ኣውላዕሎ፣ ኣይናለም ቀበሌ፣ …

በትግራይ ክልተ ኣውላዕሎ የህዝባ ቁጣ ተቀሰቀሰ። Read more »

በቅርቡ በሳዑዲ አረቢያ በሃጂ ስነስርአት ወቅት በተፈጠረ መጨናነቅ ህይወታቸውን ያጡ ኢትዮጵያውያን ቁጥር 47 መድረሱን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ገልጿል፡፡ ባለፈው መስከረም 13 ቀን 2008 በሳዑዲ አረቢያ ሚና አካባቢ በደረሰ አደጋ ከ1ሺህ በላይ የተለያዩ ሀገር የሃይማኖታዊ ስነ ስርአቱ ተሳታፊዎች …

በሃጂ ስነስርአት ላይ የሞቱ ኢትዮጵያውያን ቁጥር 47 ደርሷል Read more »

ፓርቲዎቹ መቅደም ይገባቸዋል ሏቸውን ጉዳዮች አስቀምጠዋል የኢህአዴግ  መንግስት በነደፈው የ2ኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ውይይት ላይ ትናንትናና ዛሬ ተቃዋሚዎች እየመከሩ ሲሆን ዋናዎቹ ተቃዋሚዎች መድረክ፣ ሠማያዊ እና መኢአድ በውይይቱ ላይ አልተሳተፉም፡፡ መንግስት ለሁሉም ተቃዋሚ ፓርቲዎች 20 አባሎቻቸውን አርብና ቅዳሜ በሚደረግ ውይይት ላይ እንዲያሳትፉ …

የኢህአዴግ መንግሥት በጠራው ውይይት ላይ ዋናዎቹ ተቃዋሚዎች አልተሳተፉም:: ታማኝ ተቃዋሚዎች ተሳትፈዋል:: Read more »

የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ፤ ሰሞኑን የተቋቋመው አዲሱ የኢህአዴግ መንግስት፣ ለኢትዮጵያ መሠረታዊ ችግሮች መፍትሔ ሊሰጥ አይችልም አለ፡፡ “የህዝብን ይሁንታ አግኝቶ ውክልና ያለው መንግስት አይደለም” ሲልም መድረክ ተቃውሟል፡፡ ከትናንት በስቲያ በጽ/ቤቱ ለሀገር ውስጥና ለውጭ መገናኛ ብዙሃን መግለጫ የሰጠው መድረክ፤ ኢህአዴግ ለአዲሱ …

መድረክ፤ አዲሱ የኢህአዴግ መንግሥት ለሀገሪቱ ችግሮች መፍትሄ አይሠጥም አለ Read more »

– የኢትዮጵያ ጠቅላላ የብድር መጠን ከ30 ቢሊዮን ዶላር በላይ ወይም ከ1.2 ትሪሊዮን ብር በላይ ነው:: – የአገሪቱ የብድር ዕዳ ከጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት አንፃር ሃምሳ ከመቶ ደርሷል:: – የዋጋ ግሽበት ከሚጠበቀው በላይ የእጥፍ እጥፍ አሻቅቧል:: – በፋይናንስ አቋሞች ላይ ቁጥጥር …

የወያኔ ባለስልጣናት እና አማካሪዎቻቸው ውሸታቸውን አጧጡፈውታል::እውን የብድር እዳ ክምችት አያሳስብም? (ምንሊክ ሳልሳዊ) Read more »

የሜ/ጄ አበበ ተ/ሃይማኖት በጣም ረጅም ፅሁፍ በርካታ ሂሶችን ያነሳ ነው! የህወሕት ልሳን በክልልና የፌደራል ተቇማት ስፖንሰር እየተደረጉ ተቃዋሚዎችን እንደሚወነጅሉ መከላከያው በፖለቲካው እንደተዘፈቀ ይተቻል! ፍርድ እንደጠፋ ይሄሳል! መቶ ፐርሰንት አስቂኝ ብቻ ሳይሆን አደገኛ ነው ይላል! እውን ኢትዮጵያ ፓርላማ አላት? ብሎ ይጠይቃል! …

ብልሹ አስተዳደርን የዴሞክራሲ ምህዳር በማስፋትና በተቋማት ግንባታ (ሜ/ጄ አበበ ተ/ሃይማኖት “ጆቤ”) Read more »

ከአዲስ አበባ በሰሜን ምሥራቅ አቅጣጫ ሲጓዙ የአማራ ክልል ሰሜን ሸዋና ኦሮሞ ብሔረሰብ ዞንን ያገኛሉ፡፡ እነዚህ ሁለት ዞኖች ሞቃታማና ዓመቱን ሙሉ የሚፈስ የውኃ ሀብት ያላቸው ናቸው፡፡በእነዚህ አካባቢዎች ከሚበቅሉ የግብርና ምርቶች መካከል በቆሎ፣ ማሽላ፣ ማሾ፣ ሽንኩርትና ትምባሆ ቅጠል ይገኙበታል፡፡ የአካባቢው አርሶ አደሮች …

የኦሮሞ ዞን አርሶ አደሮች ኡኡታ – “…..የሚያዋጣንን ማብቀል አልቻልንም ::” Read more »

አቶ ኢሳያስ በታዲያስ አዲስ ጋዜጠኞች ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለምን ቻይና እንደቀጠረ ሲጠየቁ ፣ በፈረንጅኛ እንዲህ ነበር ያሉት <<China is the biggest humanity >> ፣ በመጀመሪያ ይህ አርፍተ ነገር ምን ማለት ነው ? ብሎ መጠየቅ አይቻልም ። ሁለተኛ ምንም ማለት …

ቻይንዬ ቻይንዬ ፣ ቻይኑካ ፣ ቻይንሻ (ሄኖክ የሺጥላ ) Read more »

  ዶክተር ጌታቸው መታፈሪያ በዋሽንግተን ዲሲ ውስጥ በምትገኘው ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በቅርቡ የተከሰተውን ድርጊት መነሻውንና ሁኔታውን አስመልክተው የባለ አደራዎች ቦርድን አቋምና ውሳኔ በዝርዝር አስረደተዋል። በዚህም መሠረት የችግሩን መነሻ በሚከተሉት አራት ነጥቦች አስፍረዋል፤ 1) …

ከዲሲ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የባለ አደራዎች ቦርድ የተሰጠ መግለጫ Read more »

ዘውዴ ረታ - የታሪኩ ቀንድ ስብራት (1927 – 2008)

‹‹… ዘውዴ! ከእኛ ጋር ተመሳሳይ ከሆነው ትውልድ መካከል እንደ አንተ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን መንግሥት አመራር በቅርብ የማየትና የመረዳት ዕድል ያገኘ ብዙ ሰው የለም፡፡ ቀጥሎ ደግሞ ያየውንና የተረዳውን፣ ጣዕም ባለው ጽሑፍ

አብራርቶ ለመግለጽ ተሰጥኦ ያለው እንደ አንተ የመሰለ ጸሐፊ ብዙ የለም፡፡ ስለዚህ በእኔ አመለካከት ሁለት የተጣመሩ ዕድሎች በአንተ እጅ ተይዘው ይገኛሉ፡፡ እነዚህም ታሪኩን የማወቅና የጽሕፈት ችሎታህ ናቸው፡፡ ስለዚህ እኔ አጥብቄ አደራ የምልህ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን መንግሥት ጉዳይ አንተ ዕድል አጋጥሞህ ያየኸውንና ከአዋቂዎች ዘንድ ቀርበህ ያጠናኸውን እውነተኛውን ታሪክ ገልጠህ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ጻፍለት፡፡ ለዚህ ሕዝብ ከአንተ በኩል ከዚህ የበለጠ የምታደርግለት ሊኖር አይችልም፡፡ አንተም አስበህ የጀመርከውን ለመፈጸም እግዚአብሔር ይርዳህ፡፡ … እኛም ወዳጆችህ፣ ዕድሜና ጤና አግኝተን የምትደክምበትን ለማንበብ ያብቃን…›› 

ከአሥራ ሁለት ዓመታት በፊት ነበር ታዋቂው የታሪክ ምሁር ፕሮፌሰር መርዕድ ወልደ አረጋይ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት አመራርን በቅርቡ የማወቅ ዕድል ለነበራቸው፣ ከእልፍኝ እስከ አደባባይ ከንጉሠ ነገሥቱ ያልተለዩትን ዘውዴ ረታን እውነተኛው ታሪክ ገልጠህ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ጻፍለት ብለው የተማፀኗቸው፡፡ 

ይህን የማበረታቻ ምክር መቼም ያልረሱት ዘውዴ ረታ አምና እጅግ ግዙፍ የሆነውን ‹‹የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት›› አንደኛ መጽሐፍ ከነገሡበት 1923 እስከ 1948 ዓ.ም. ድረስ የሚሸፍነውን ታሪክ ለንባብ አደባባይ ያዋሉት፡፡ 

የአዲሱ መጽሐፋቸውንም የተለየ ፋይዳም እንዲህ አስቀምጠውታል፡፡ ‹‹እንግዲህ ማንም ሰው በቀላሉ እንደሚረዳው ኢትዮጵያ የነፃነት ችግር ያጋጠማት በሁለት ኮሎኒያሊስት በሆኑ አገሮች ነው፡፡ የመጀመሪያው የፋሽስቱ የሙሶሊኒ የግፍ ወረራ ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ ነፃ አውጪዎች ነን ብለው በመጡት ወዳጆቻችን በምንላቸው በእንግሊዞች ወታደራዊ የሞግዚት አስተዳደር የተፈጸመብን በደል ነው፡፡ ከእነዚህ ከሁለቱም ኮሎኒያሊስቶች የኢትዮጵያን ነፃነት ለማስመለስ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት የደረሰበት መከራና ፈተና በቀላሉ የሚገመት አይደለም፡፡ ይህን ሁሉ በተለይ አዲሱ ትውልድ እንዲያውቀው ስለሚያስፈልግ፣ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ታሪኩ በተቻለ መጠን ተዘርዝሮ ቀርቦለታል፡፡›› 

ጋዜጠኛ፣ ዲፕሎማትና ስመጥር የታሪክ ጸሐፊ (ሦስት ዓይና) የነበሩት አምባሳደር ዘውዴ ረታ በዘመናዊት ኢትዮጵያ ታሪክ ከዳግማዊ አፄ ምኒልክ ዕረፍት በኋላ የነበረውን የልጅ ኢያሱን፣ የንግሥት ዘውዲቱ፣ ብሎም የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመን ታሪክ ትክክለኛውን ሒደት የዘመኑም ሆነ መጪው ትውልድ ማወቅ ያስፈልጋል በሚል ነበር የታሪክ መጽሐፋቸውን ‹‹ተፈሪ መኰንን ረዥሙ የሥልጣን ጉዞ›› ለኅትመት ያበቁት፡፡ ‹‹በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት የኤርትራ ጉዳይ 1941-1963›› ሌላው በመረጃና በማስረጃ የተደገፈ ታሪካዊ መጽሐፍንም እነሆ ብለዋል፡፡ 

የኤርትራን ጉዳይ የተመለከተው መጽሐፋቸው ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ እንዲገነዘበው በዶ/ር ኃይሉ ሃብቱ አማካይነት “THE ERITREAN QUESTION” በሚል ተተርጉሞ ለሕትመት ዝግጁ መሆኑም ይነገራል፡፡ 

የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ሕገ መንግሥቱ ከተሻሻለበት ከ1948 ዓ.ም. በኋላ የነበረውን በለውጥ የታጀበው ዓቢይ ዘመን የሚያወሳውን መጽሐፍ በማዘጋጀት ላይ ነበሩ አምባሳደር ዘውዴ ረታ፡፡ በተለይ በለንደን (እንግሊዝ)፣ ፓሪስ (ፈረንሣይ) እና ሮም (ኢጣሊያ) ኢትዮጵያን የሚመለከቱ ስለ ዘመነ ኃይለ ሥላሴ የሚያወሱ ሚስጥራዊ ሰነዶች በቅርቡ ክፍት መሆናቸውን ተከትሎ፣ ጥናትና ምርምር ለማድረግ ነበር መስከረም 12 ቀን 2008 ዓ.ም. ወደ ባሕር ማዶ ያቀኑት፡፡ ያለሙት የዘመናት ሕልም እውን ሳያደርጉት ተቀጨ እንጂ፡፡ ሞት ቀደማቸው፡፡ የጥናታቸው ቀዳሚ መነሻ ባደረጉት ለንደን ከተማ መስከረም 26 ቀን 2008 ዓ.ም. በድንገት አርፈዋል፡፡ 

በኢጣሊያና በቱኒዚያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው ያገለገሉት አቶ ዘውዴ ረት የተወለዱት በአዲስ አበባ ከተማ በ1927 ዓ.ም. ነው፡፡ የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን የተከታተሉት በፊት ደጃዝማች ገብረ ማርያም የአርበኞች ትምህርት ቤት በሚባለው፣ ከዚያም ሊሴ ገብረ ማርያም በተባለው ትምህርት ቤት ነበር፡፡ በኢትዮጵያ ሬዲዮ አንባቢነትና በቤተ መንግሥት ዜና አቅራቢነት ተቀጥረው ያገለገሉ ሲሆን፣ በፈረንሣይም በጋዜጠኝነት ተመርቀዋል፡፡ በኢትዮጵያ ድምፅ ዕለታዊ ጋዜጣና ወርኃዊው መነን መጽሔት ዳይሬክተርም ነበሩ፡፡ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የፓን አፍሪካን ኒውስ ኤጀንሲ ፕሬዚዳንት፣ የማስታወቂያ ረዳት ሚኒስትር፣ የውጭ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትርም ነበሩ፡፡ በዘመነ ደርግ የስደት ዘመናቸውም በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ውስጥ በዓለም አቀፍ የእርሻ ልማት ፈንድ የመንግሥታት ግንኙነትና የፖለቲካ ኃላፊ ሆነው ለ13 ዓመታት አገልግለዋል፡፡ 

ሦስት ዓይናው ዘውዴ ረታ በኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ለሃያ ሁለት ዓመት በላይ ላበረከቱት ውጤታማ ተግባር ከንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት የምኒልክ የመኰንን ደረጃና የኢትዮጵያ የክብር ኮከብ አዛዥ መኰንን ኒሻን ተሸልመዋል፡፡ ከተለያዩ አገሮችም ኒሻኖችን የተሸለሙ ሲሆን፣ ከቅርብ ዓመታት ወዲህም በባሕር ማዶና በአገር ውስጥም ልዩ ልዩ ሽልማቶች ተበርክተውላቸዋል፡፡ 

ከ49 ዓመት በፊት ከወይዘሮ ገሊላ ተፈራ ጋር ጋብቻ መሥርተው ሦስት ልጆች ያፈሩት አምባሳደር ዘውዴ አስከሬን፣ በሳምንቱ መገባደጃ ከእንግሊዝ መጥቶ ሥርዓተ ቀብራቸው በአዲስ አበባ እንደሚፈጸም ከቤተሰቦቻቸው የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ 

 

Minilik Salsawi – ህዝቦች እኩልነት ያልተረጋገጠባት ኢትዮጵያ የብሄር ብሄረሰብ መብቶች ለይስሙላ በሚሰበኩባት አገር ዜጎች ህግ ይከበር ብቻ ስላሉ በሌላው አለም ታይቶ በማይታወቅ መልኩ አሸባሪ ተብለው ወህኒ የሚወርዱባት ኢትዮጵያ የሃይማኖት ምሁራን ከአያት ቅድማያቶቻቸውን የተረከቡትን እምነታቸውን በነጻነት ለማካሄድ ሲሰሩ ታፍሰው ለእስር የተዳረጉባት …

እያለማን ነው እየሰራን ነው በሚል ሽፋን ዜጎችን ማሳደድ መግደል ማፈንና ማሰር ላይ የተሰማራ ጁንታ (ምንሊክ ሳልሳዊ‬) Read more »

ፌስቡክ አንዳንዴ ጨርቁን ጥሎ ያብዳል። እብደቱ ገጀራ እስከማቀበል ሊደርስ ይችላል። እንደዚህ ሲሆን በተቻለ መጠን ጥግ ይዘህ አሰላስል፤ አብረህ እንዳታብድ ተጠንቀቅ። አንዳንዴ ደግሞ ፌስቡክ ወፈፌ ይሆናል። ወፍፎ ያወፍፍሃል። አብረህ ትወፍፍና “ግን ምን ነካኝ?” ብለህ ራስህን ትጠይቃለህ። አንዳንዴም መረን የለቀቀ ባለጌ ያደርግሃል። …

ወፈፌው ፌስቡክ… (ትንሽ ቀልዳዘል ምክር) – ዳንኤል ተፈራ Read more »