ሚስቴና መንግስቴ – /ዮሐንስ ሞላ/
ሚስቴና መንግስቴ —————- አንቺንስ አፍቅሬሽ… ጭንቅላቴን ፈተሽ የምትገጣጥሚ፣ ቀልቤን የምትገፊ፣ ቀኔን የምትቀሚ፣ ሕይወት ምትቀምሚ፤ የሳቄ የበላይ፣ የእንባዬ ጠባቂ ድብርቴን አፍላቂ፣ ደስታዬን አርቃቂ፤ በወደድኩሽ ቅጽበት፥ ‘ልሁን’ ባልኩኝ ባልሽ፣ ‘ሁኚ’ ባልኩሽ ሚስቴ አካሌ፣ ሕይወቴ፤ …ብትሆኚ ድክመቴ፤ ሲሻሽ በቁራጭ ቃል፥ ከሰማይ ከፍ አርገሽ …
ሚስቴና መንግስቴ —————- አንቺንስ አፍቅሬሽ… ጭንቅላቴን ፈተሽ የምትገጣጥሚ፣ ቀልቤን የምትገፊ፣ ቀኔን የምትቀሚ፣ ሕይወት ምትቀምሚ፤ የሳቄ የበላይ፣ የእንባዬ ጠባቂ ድብርቴን አፍላቂ፣ ደስታዬን አርቃቂ፤ በወደድኩሽ ቅጽበት፥ ‘ልሁን’ ባልኩኝ ባልሽ፣ ‘ሁኚ’ ባልኩሽ ሚስቴ አካሌ፣ ሕይወቴ፤ …ብትሆኚ ድክመቴ፤ ሲሻሽ በቁራጭ ቃል፥ ከሰማይ ከፍ አርገሽ …
ዳግማዊት ማ.ሌ.ሊ.ት Amdom Gebreslas **************** በኣሁኑ ወቅት በሃገራችን ኣጋጥሞ ያለው ኣሰቃቂ ድርቅ 8.2 ሚልዮን ህዝብ እጆቹ ለተመፅዋችነት እንዲ ዘረጋ፣ ፈጣን ምላሽ ካላገኘም ለታላቅ እልቂት ሊዳረግ እንደሚችል ግልፅ ሆነዋል። ይህ ኣስቸኳይ እርዳታ የሚያስፈልገው የህዝብ ቁጥር በሳምንታት ውስጥ በከፍተኛ ፍጥነት ሽቅብ እየጨመረ …
ዳግማዊት ማ.ሌ.ሊ.ት – በሃገራችን ኣጋጥሞ ያለው ኣሰቃቂ ድርቅ ፈጣን ምላሽ ካላገኘም ለታላቅ እልቂት ሊዳረግ እንደሚችል ግልፅ ሆነዋል። Read more »
ብዙ ጊዜ በብዙኃን መገናኛዎች ሳዳምጥና ስመለከት አንድ እጅግ የሚገርመኝን ነገር በተደጋጋሚ አዳምጣለሁ እመለከታለሁ፡፡ ነገሩ ምን መሰላቹህ፡- በስደትም በሥራም በተለያየ ምክንያት ከሀገር ወጥተው በባዕድ ሀገራት የሚኖሩ ወገኖቻችን በተለይም ፕሮቴስታንቶች (ተቃዋሚዎች) እንዲያ በምቾት በድሎት የሚኖሩበትን ሀገር “እግዚአብሔር አብዝቶ የባረከው ሀገር!” በማለት በተደጋጋሚ ይገልጻሉ፡፡ የእኛ ሀገር ደግሞ ሕዝብ በረሀብ በችግር በስቃይ የሚኖርበት ሀገር ስለሆነች እግዚአብሔር የረገማት የጠላት ሀገር […]
The post የተባረኩ ሀገራት ወይስ የተረገሙ? የተባረኩ ሕዝቦች ወይስ የተረገሙ? appeared first on ሳተናው .
ጥቅምት ፭ (አምት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽንን ጨምሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከአናሎግ ወደ ዲጂታል ለሚደረግ የቴክኖሎጂ ሽግግር ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ቢደረግም አልተሳካም። ፕሮጀክቱ በ2001 ዓም ተጀምሮ በ3 አመታት ውስጥ መጠናቀቅ ነበረበት። ከብሮድካስት ባለስልጣን የወጣ መረጃ እንደሚጠቁመው ስራው ሊሳካ ያልቻለው በሙስናና በብልሹ አሰራር ምክንያት ነው። ሀገር አቀፍ የሬዲዮና የቴሌቭዥን የማስፋፊያ …
ጥቅምት ፭ (አምት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአገሪቱ የሚታየው የኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦት እጥረት ካለፉት ስድስት ወራት ወዲህ ለታየው አጠቃላይ የዋጋ ንረት መባባስ አንድ ምክንያት መሆኑን ከንግድ ሚኒስቴር የተገኘ አንድ የጥናት ሰነድ ጠቆመ፡፡ በምግብ ነክ ምርቶች ላይ ማለትም በምግብ ዘይት፣ ዱቄት፣ ፓስታና ሞኮረኒ፣ በዳቦ ምርቶች ላይ የተሰማሩ አነስተኛና መካከለኛ አንዱስትሪዎች በኤሌክትሪክ እጥረት ምክንያት ከማማረት አቅማቸው …
ጥቅምት ፭ (አምት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አንደኛ ተከሳሽ ሶሊያና ሽመልስ በሌለችበት፣ሶስተኛ ተከሳሽ ናትናኤል ፈለቀ ፣ አምስተኛ ተከሳሽ አጥናፍ ብርሃኔ፣ስድስተኛ ተከሳሽ አቤል ዋበላ፣ መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነጻ የተሰናበቱ ሲሆን፣ ሁለተኛ ተከሳሽ በፍቃዱ ኃይሉ ከሽብር ክስ ነፃ የተባለ ቢሆንም ማአከላዊ ምርመራ በኃይል እና በማሰቃየት የሰጠው ቃል ላይ አመፅ እንዳነሳሳ አምኗል በሚል በወንጀል ህጉ 257 መሰረት እንዲከላከል …
ጥቅምት ፭ (አምት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ማንነታቸው ያልተገለጸው የ61 አመቱ ኢትዮጵያዊ አምሰተልፊን በምትባል ከተማ ውስጥ የተያዙ ሲሆን፣ ግለሰቡን ወደ ኢትዮጵያ ይመለሱ ወይም አይመለሱ የሚልውን ውሳኔ ለመስጠት ፍርድ ቤቱ የ90 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ሰጥቷል። ግለሰቡ በደብረማርቆስና መተከል አውራጃዎች በርካታ ሰዎችን መግደላቸውንና ማሰራቸውን በውጭ አገር ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን መረጃ መሰብሰቡን ፖሊስ አስታውቋል። በግለሰቡ ላይ ቀድም ብሎ …
ጥቅምት ፭ (አምት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጋዜጠኛ፣ዲፕሎማትና የታሪክ ተመራማሪ የነበሩት የቀድሞ አምባሳደር ዘውዴ ረታ ባለፈው ሳምንት እንግሊዝ ለንደን ውስጥ መንገድ ላይ በመውደቃቸው ባጋጠማቸው ድንገተኛ አደጋ ምክንያት ሕይወታቸው አልፏል። አምባሳደር ዘውዴ በአዲስ አበባ ከተማ ነሐሴ 7ቀን 1927 ዓ.ም በወቅቱ ሥጋ ቤት ሠፈር ተብሎ በሚጠራውና በአሁኑ ወቅት ኦርማ ጋራዥ በሚባለው አካባቢ የተወለዱ ሲሆን የሦስት ልጆች …
ኢሳት ዜና (ጥቅምት 5፡ 2008) የፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድቤት በሽብርተኛ ወንጀል ክስ፣ የክስ ሂደታቸው በመታየት ላይ የነበሩ አራት ጦማሪያን ከተከሰሱበት የሽብር ወንጀል መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነጻ እንዲሰናበቱ ዛሬ አርብ ወሰነ። በጦማሪያኑ ላይ የመጀመሪያ ዙር ውሳኔውን ይሰጣል ተብሎ የተጠበቀው ፍርድ ቤቱ በጦማሪያኑ ክሳቸውን መከላከል ሳያስፈልጋቸው በአንድ አመት በላይ የቆየው የእስር ጊዜያቸው አብቅቶ በነጻ እንዲሰናበቱ ትዕዛዝ መስጠቱ ታውቋል። ይሁንና …
ዞን ዘጠኝ በመባል በሚታወቁት አራት የድረገጽ ጸሐፍት እና አንድ ጋዜጠኛ ላይ በሽብርተኝነት የቀረበባቸዉን ክስ ፍርድ ቤት ዛሬ ዉድቅ አደረገ። ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ ላይ የቀረበዉ ማስረጃ ሁሉ ደካማ መሆኑን ማመልከቱን የፈረንሳይ የዜና ወኪል ከአዲስ አበባ ዘግቧል።
VOA ከምሽቱ አንድ ሰዓት የአማርኛ ዜና – Listen
የፍትሕና ልዕልና ጋዜጦች፣ እንዲሁም የፋክትና የአዲስ ታይምስ መፅሔቶች ባለቤትና አዘጋጅ የነበረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሣለኝ ከታሠረ ፤ ጥቅምት 3 ቀን 2008 ዓ.ም አንድ ዓመቱን ደፍኗል፡፡ የተመስገን ጤና አሳሳቢ መሆኑን ቤተሰቡቹ ገልጸዋል፡፡ ማረሚያ ቤቱ ግን ተመስገን ሕክምና እያገኘ መሆኑን ጤናማም እንደሆነ ይናገራል፡፡
#Ethiopia #Freezone9bloggers እውነት አሸነፈች:: ለሁላችንም እንኳን ደስ አለን:: የዞን ዘጠኝ ጦማሪያን ሰላሳ ስምንተኛው የካንጋሮ ፍርድ ቤት የ539 ቀናት የብይን ድራማ :: ከተለያዩ አለማቀፍ ሚድያዎች የመጡ ጋዜጠኞች ዲፕሎማቶች የጦማርያኑ ቤተሰቦች እና ወዳጆች እንዲሁም አገር ወዳ ወገን ወዳድ የሆኑ በርካታ ኢትዮጵያውያን የዞን …
ለ539 ቀናት የተንገላቱት የዞን ዘጠኝ ጦማርያን የቀረበባቸው ክስ ምንም ደጋፊ ማስረጃ ስላሌለው ነጻ ወጥተዋል:: Read more »
ጌቱ ኃይሉ
መቼም ሰው ይናገራል። እኔ ደግሞ ጆሮ ፈጥሮብኛልና እሰማለሁ። የምሰማውና የማዳምጠው ግን ይለያያል።
ባለፈው ሰሞን ቁጥር 00 ሰውዬ ሲናገሩ ሰማሁ፣ “የዛሬ አሥር ዓመት ከ80 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን ሥራ እናስይዛለን” ብለው ሲናገሩ ሰማሁ።
ነፃነት ዘለቀ

እንደምን ሰነበታችሁ። እንኳን ለአዲሱ ዓመት የ2008 ዓ.ም. ሁለተኛ ወር “ለጥቅምት አንድ አጥንት” በሠላም አደረሳቹ። ጥቅምት ብርዳምና ንፋሳም ነው። ዘንድሮም እንደዛው ነው። የአዲስ አበባ የሰሞኑ ብርድ ሚስት ያሳቅፋል። ግን ስንገናኝ ሠላምታ የማንለዋወጠው ለምንድነው? ብዙ መጣጥጥፍ ጸሐፊዎች ይህን ወግ ልማድ ረስተው በቀጥታ ሊያስተላልፉት ወደሚፈልገጉት ቁም ነገር ይገባሉ – ያበሳጩኛል። “እንዴት ሰነበታችሁ” ማለት ማንን ገደለ?
ጌቱ ኃይሉ
መቼም ሰው ይናገራል። እኔ ደግሞ ጆሮ ፈጥሮብኛልና እሰማለሁ። የምሰማውና የማዳምጠው ግን ይለያያል።
ባለፈው ሰሞን ቁጥር 00 ሰውዬ ሲናገሩ ሰማሁ፣ “የዛሬ አሥር ዓመት ከ80 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን ሥራ እናስይዛለን” ብለው ሲናገሩ ሰማሁ።
Minilik Salsawi – የወያኔው ጉጅሌ አገዛዝ የፕሮፓጋንዳ ወፍጮ የሆነው ራዲዮ ፋና የአገሪቱ አጠቃላይ ምርት 1 ነጥብ 24 ትሪሊየን ብር ደረሰ የዜጎች የነፍስ ወከፍ ገቢ 691 የአሜሪካ ዶላር መድረሱን እየደሰኮረ ይገኛል::እኛ እስከምናውቀው ድረስ 1.24 ትሪሊዮን ብር የአገሪት አጠቃላይ ምርት ሳይሆን በአገሪቱ …
የሃሰት ፕሮፓጋንዳ – የቁጥር ቁልል – መሬት ላይ ያለው እውነት – ራዲዮ ፋና (ምንሊክ ሳልሳዊ) Read more »
ኢሳት ዜና (ጥቅምት 4 ፣ 2008) በኢትዮጵያ በተለያዩ ስራዎች ላይ ተሰማርተው የሚገኙ የቻይና ኩባንያዎች በኢትዮጵያዊያን ሰራተኞች ላይ የሚፈጽመው በደል ከአቅም በላይ እየሆነ መምጣቱን የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ፌደሬሽን ገለጠ። በኢትዮጵያዊያን ሊሰሩ የሚችሉ ቀላል ስራዎች በውጪ አገር ዜጎች እየተሰሩ እንደሚገኙ ያስታወቀው ፌደሬሽኑ 20 የሚሆኑ የቻይና ኩባንያዎች ሰራተኞቻቸው በማህበር እንዳይደራጁ ተጽዕኖ አሳድረው እንደሚገኙ አመልክቷል። በተለይ በኮንስትራክሽን ዘርፍ ላይ ተሰማርተው …
ጥቅምት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ካለፈው አመት ጀምሮ እንደ አዲስ በተጀመረው የሰራዊት ምልመላ የተፈለገውን የሰራዊት ቁጥር ማግኘት የተቸገረው መንግስት፣ ሰሞኑን ደግሞ በአንዳንድ ክልሎች የመከላከያ ሰራዊት አባላት በመኪና ላይ ሆነው ወጣቱ ለውትድርና እንደሚዘገብ በመቀስቀስ ላይ ናቸው። ከዚህ ቀደም ለእያንዳንዱ ቀበሌና ወረዳ የተሰጠው ኮታ ሊሟላ ባለመቻሉ፣ መንግስት በስራ ስልጠና ስም ወጣቶችን በመቀስቀስ ያለፍላጎታቸው እንዲዘምቱ …
ጥቅምት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሞተር ሳይክል ሰዎችን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ህይወታቸውን የሚመሩ 500 ያክል ወጣቶች ስራ እንዲያቆሙ በመታዘዛቸው ችግር ላይ መውደቃቸውን ተናግረዋል። ሰራተኞቹ በድንገት አቁሙ በመባላቸው፣ ቤተሰቦቻቸውን ለማስተዳደር ተቸግረዋል። መንግስት አማራጭ ስራ ሳይፈጥር በድንገት ስራ አቁሙ ማለቱ ተገቢ አይደለም በሚል ወጣቶቹ ያስነሱትን ተቃውሞ ተከትሎ የወረዳው ባለስልጣናት ተጨማሪ የማስጠንቀቂያ ጊዜ ሰጥተዋል። አንድ …
ጥቅምት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በተከዜ ወንዝ ጫፍ ላይ የምትኘውና የዋግና የበለሳ ነዋሪዎች መተላለፊያ የሆነችው አርባ ፀጓር ወረዳ ደርግን ለመጣል በተደረገው የትግል ወቅት የኢህአፓና የኢሕዲን መተላለፊያ መስመር የነበረች ሲሆን በወቅቱ የድሮው ኢሕዲን የአሁኑ ብአዴን ታጋዮች የነበሩት ለሕዝቡ የኑሮ ለውጥና ዴሞክራሲያ ስርዓት እንደሚገነቡ ቃል በመግባታቸው ነዋሪው ሸማቂዎቹን በማገዝ ከለላ ይሰጣቸው የነበረ ሲሆን ድል …
ጥቅምት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢትዮጵያ ስፖርት ፌዴሬሽን በሰሜን አሜሪካ፥ ESFNA በካናዳ የቶሮንቶን ከተማ የ2016 የስፖርት ክብረ በዓል ዓስተናጋጅ እንድትሆን መርጧል። ውሳኔው የተላለፈው፥ በኢትዮ-ስታር ቶሮንቶ የእግር ኳስ ክለብ ዓስተባባሪነት በቶሮንቶ ካናዳ በተዘጋጀው፥ የESFNA ዓመታዊ ጉባኤ የኢትዮጵያ ስፖርት ፌዴሬሽን በሰሜን አሜሪካ የክለብ ተዎካዮችና የቦርዱ ዓመራር ዓባላት በተገናኙበት፥ ባሳለፍነው ቅዳሜና እሁድ October 10 እና …
ጥቅምት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በስምጥ ሸለቆ ውስጥ የሚገኙት የቱርካና ሃይቅና የኦሞ ወንዝ ኢትዮጵያ በምትከተለው የኢንዱስትሪ ዘመቻ ምክንያት የመድረቅ እና የአየር ንብረት መዛባት አደጋን ማስከተሉንና በዚህም ለውጥ ሳቢያ የአካባቢው ነዋሪዎች ስጋት ውስጥ መሆናቸውን ሂውማንራይትስ ወች በጥናት ሪፖርቱ አመልቷል። በሰሜናዊ ምዕራብ ኬንያ በኢትዮጵያ ድንበር አካባቢ የሚገኘው የቱርካና ሃይቅ በዓለማችን በስምጥ ሸለቆ ውስጥ ከሚገኙት …
ከምሽቱ አንድ ሰዓት የአማርኛ ዜና – Listen
– ወያኔ መስጊዶችን መዋጮ ሊጠይቅ ነው – የወያኔ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ተብየው በፖለቲካ መሪዎች ላይ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጠ – የሱማሊያ የጦር ጉዳተኞች ኬኒያ መሆናቸው ተገለጸ – የግብፅ የወያኔና የሱዳን የአባይ ግድብ ድርድር ሊቀጥል ነው – በማላዊ እስር ቤት ታግተው የሚገኙ …
ወያኔ መስጊዶችን መዋጮ ሊጠይቅ ነው:: – በማላዊ እስር ቤት ታግተው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ከፈተኛ ስቃይ እየደረሰባቸው ነው Read more »
አንድ ዜጋ በገዛ አገሩ አንገቱን ቀና አድርጎ በነፃነት መራመድ የሚችለው መብቱ ሲከበርለትና እሱም የሚፈለግበትን ግዴታውን ሲወጣ ነው፡፡ ይህ ግዴታውን የሚወጣ ዜጋ ፍትሕ ሲነፈግና መብቱ ሲጣስ ግን ዜግነቱን ይጠራጠራል፡፡ ስለልማት፣ ስለዕድገትና ብልፅግና ቢወራ አይሰማም፡፡ በጉልበተኞች ንብረታቸውን የተቀሙ ዜጎች ፍትሕ ሲጠይቁ ተነፍገው …
ዛሬ ጧት አንድ የብአዴን ባለስልጣን ፍፁም የበታችነት ስሜቱን በሚሳብቅ መልኩ “ብአዴን ከአንድ ጀግና ህዝብ የራሱን ዐላማ አንግቦ የተነሳ፣ ብዙ ጀብዶች የፈፀመ፣ ብዙ መስዋዕትነት የከፈለ፣ በራሱ ዐላማ የቆመ ፓርቲ እንጅ የማንም ተለጣፊ ሆኖ አያውቅም” ሲል ኢቢሲ ሰማሁ፡፡ እሰየው! እንዳፉ ያድርግለት! እውነት …
ይድረስ ለኩሩዋ የሃገሬ ሴት በሙሉ በሙሉ መስዋእትነት ከፍለን ይህን ሃገር አጥፊ ቡድን እናስወግድ። አንቺ የኢትዮጵያ ዉብ ሴትሆይ፤ አንቺ በሃገርሽ ስራ አጥተሽ በየአረብ ሃገሩ የምትንከራተቺው የኢትዮጵያ ኩሩ ሴት፤ አንቺ በሃገርሽ ለሃገርሽ ሰርቶ ለመኖር ተምረሽ ስራ አጥተሽ የምትንከራተችው ኢትዮጵያዊት፤ አንቺ በስርአቱ አስተዳደር …
ይድረስ ለኩሩዋ የሃገሬ ሴት በሙሉ መስዋእትነት ከፍለን ይህን ሃገር አጥፊ ቡድን እናስወግድ። Read more »
ኢሕአዴግ ያቋቋመው ፍፁማዊ አምባገነን መንግስት ለኢትዮጵያ መሠረታዊ ችግሮች መፍትሔ ሊሰጥ አይችልም!! ============== ከኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ የተሰጠ መግለጫ የኢፌድሪ ሕገ መንግስት አንቀፅ 54/1፣የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ሁሉ አቀፍ፣ ነፃ፣ ቀጥተኛና ትክክለኛ በሆነ፣ ድምፅ በምስጢር በሚሰጥበት የምርጫ ስርዓት በየአምስት …
ኢሕአዴግ ያቋቋመው ፍፁማዊ አምባገነን መንግስት ለኢትዮጵያ መሠረታዊ ችግሮች መፍትሔ ሊሰጥ አይችልም!! Read more »
#Ethiopia : በምርጫ እና በብልጫ የምታደምጡት የናንተው የኢትዮጵያ ወጣቶች ድምፅ ለዚህ ሳምንት የመራረጥናቸውን ዜናዎች እና መጣጥፎችን ቀልብን ከሚስቡ ሙዚቃዎች ጋር አዋዝተን ቀርበናል። መልካም ጊዜ… [youtube http://www.youtube.com/watch?v=2OrTNwGiwSg]
በኢትዮጵያ የአስችኳይ ረድኤት ፈላጊዎች ቁጥር 8.2 ሚልዮን የደረሰ ሲሆን ወደ $596. 4 ሚልዮን ዶላር የሚሆን እርዳታ እንደሚያስፈልግ ታወቀ።
-ህወሃት መራሹ ኢህአዴግ ዳግም የመጅሊስ ግልበጣ ለማድረግ በተባረሩ ሰራተኞች ተጻፈ የተባለ የመጅሊሶችን ገበና የሚያጋልጥ አስደንጋጭ ደብዳቤ እንዲሰራጭ አደረገ ልዩ ዘገባ ይዘናል http://goo.gl/R36eUa -በሜዳወላቦ ዩንቨርስቲ በኒቃብና በሶላት ሁለት ተማሪዎች ተባበረሩ በኒቃብ ምክኒያት የተባረረችው ተማሪ ከቢቢኤን ጋር ቆይታ አድርጋለች ሁሉም ሊነቃ በቃ …
ህወሃት መራሹ ኢህአዴግ ዳግም የመጅሊስ ግልበጣ ለማድረግ አስደንጋጭ ደብዳቤ እንዲሰራጭ አደረገ:: Read more »
በልጅግ ዓሊ
“ደግ ደጉን ስናጣ፣ ኀዘኑ መረረ
ሞት አምላኩ ከድቶት፣ ገሎት በነበረ።”
– የሠፈራችን ሙሾ አውራጅ
እነሆ ጋሼ ሙሉጌታ ዐረፈ። ከዚህ ምስቅልቅሉና ቅጥ አምባሩ ከወጣ ዓለም በአካል ተለየ። ጋሼ ሙሉጌታ ከእንግዲህ የሀገሩን አፈር በሞቱ እንኳ ላይቀምስ ነው። ዛሬ የሰው ሀገር አፈር ለብሶ በዝምታ ማሸለቡን መርጧል። ሀገሩን እንደናፈቀ የተለያት ቢሆንም ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚሸጋገር ትምህርት ሰጥቶን አልፏል።
ጥቅምት ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በገጠሪቱ ኢትዮጵያ የሚገኙ 8 ሚሊዮን 200 ሺ ኢትዮጵያውያን አስቸኳይ የምግብ እርዳታ እንደሚሹ፣ በከተማ ውስጥ የሚኖሩ 4 ሚሊዮን ተረጅዎች እንዳሉ በመንግስት እና በአለማቀፍ ድርጅቶች ይፋ ከሆነ በሁዋላ፣ የአለማቀፍ ድርጅቶች መንግስት ለልማት በሚል የመደበውን ገንዘብ የዜጎቹን ነፍስ ለመታገድ እንዲያውለው ጠይቀዋል። እስከሚቀጥለው ታህሳስ ወር ድረስ ምግብ ገዝቶ ለማቅረብ የሚያስፈልገው 12 …
ጥቅምት ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ካለፈው እሁድ ጀምሮ በኢትዮጵያውያንና በሱዳን መንግስት ወታደሮች መካከል የተነሳው ጦርነት መቀጠሉን ከአካባቢው የደረሱን መረጃዎች ያመለካታሉ።ኢትዮጵያውያን ታጣቂዎች፣ ከዚህ ቀደም ማንነታቸው ያልታወቁ የሱዳን ታጣቂዎች 8 ኢትዮጵያውያንን ለሹፌርነት እንቀጥራችሁዋለን በማለት በአሰቃቂ ሁኔታ ከመኪና ላይ አውርደው መግደላቸውን ተከትሎ፣ ኢትዮጵያውያኑ በወሰዱት አጸፋ እርምጃ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ የሱዳን ወታደሮችን ገድለዋል። የሱዳን መንግስት ተጨማሪ …
ጥቅምት ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ክልል በሲዳማ ዞን በማልጋ ወረዳ ፣ ወታራና ጉጉማ በሚባሉ አካባቢዎች ከ2004 ዓም ጀምሮ በእየአመቱ የሚቀሰቀሰው ግጭት ሰሞኑን አገርሽቶ፣ እስካሁን 2 ሰዎች በከባድ ሁኔታ ተጎድተው አዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል ሲገቡ፣ መጠኑ ያልታወቀ ንብረትም ወድሟል። በቦንኬ ጎሳና በጉኑፋ ጎሳዎች መካከል የተነሳው ግጭት መንስኤ የአንዱ አካባቢ ተወላጅ ሌላውን ማስተዳደር አይችልም …
ጥቅምት ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመግባት ሲሞክሩ በማላ ዊ የድንበር ጠባቂዎች የተያዙ ከ317 በላይ ኢትጵያዊያን ስደተኞች በተለያዩ እስርቤቶች ውስጥ የሚገኙ ሲሆን በእስር ቤት ውስጥ ሰቆቃ እየተፈፀመባቸው መሆኑን አጃን ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል። የማላዊ ፍርድ ቤት በስደተኞች ላይ የእስር ቅጣትና ስድሳ አምስት የአሜሪካን ዶላር መቀጮ የጣለባቸው ሲሆን ፣ አብዛሃኞቹ ከስድስት ወራት …
ጥቅምት ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሽብር ወንጀል ተከሰው በ19ኛው ወንጀል ችሎት ነጻ የተባሉት የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ሃብታሙ አያሌው፣ የሰማያዊ ፓርቲ የምክር ቤት ም/ል ሰብሳቢ የነበረው የሽዋስ አሰፋ፣ የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ም/ል ስብሳቢና የደቡብ ተወካይ የነበረው ዳንኤል ሽበሺ እንዲሁም አብርሃም ሰለሞን ፣ ዛሬ ጠ/ፍርድ ቤት ቀርበው፣ በአቃቢ ህግ የተጠየቀባቸው ይግባኝ …
ጥቅምት ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ ክልል በፍቼ ከተማ የትራንስፖርት አገልግሎት መስሪያ ቤትስራችንን በአግባቡ ሊያሰራን አልቻለም በሚል ምክንያት የባጃጅ አሽከርካሪዎች ከትናንት ጀምረው የስራማቆም አድማ አድርገዋል። የከተማው መንገድ ትራንስፖርት ባጃጅ ለመንዳት የታክሲ አንድ ፈቃድ መያዝ ያስፈልጋል የሚል መመሪያ ያወጣ ሲሆን፣ በሶስተኛ መንጃ ፈቃድ ሲያሽከረክር የተገኘ ሹፌር 2 ሺ 500 ብር ይቀጣል። የቅጣቱን መጠንና …
VOA ከምሽቱ አንድ ሰዓት የአማርኛ ዜና listen
በቲፒ የታገቱ ፖሊሶችን ለማስለቀቅ የኃይል እርምጃ ይወሰዳል ተባለ :: ========= ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅትና የዓለም ባንክ የወያኔ የብድር መጠን አሳሳቢ ነው አሉ :: ======== በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ምዝበራው ጦፏል :: ============= and more Others information [youtube http://www.youtube.com/watch?v=___4F1lmtAY]
Amdom Gebreslasie – ራስዋ የማታደርገውን ነገር ለዓፋር ክልላዊ መንግስት ኣስተዳዳሪ እሷ ኣጋር ብላ የምትጠራው ኣብዴፖ ለዓመታት በሊቀ መንበርነት የመራው ዓሊ ሴሮ ከሊቀ መንበርነቱና ኣስተዳዳሪነቱ ለማንሳት ስትሞክር በኣፍዋ ሽኖባታል። ጉዳዩ በያዝነው ዓመት ህወሓትና ራሷ ጠፍጥፋ የሰራቻቸው የኢህኣዴግ ኣባል ድርጅቶች ጉባኤዎቻቸው ኣካሂደው …
የዓፋር ክልል ርእሰ መስተዳድር ዓሊ ሴሮ ህወሓትን ኣናትዋን ብሎ ቀልቧን ገፎ ልቧን ኣዝሮ መለሳት። Read more »
በኣብራሃ ደስታ፣ ሃብታሙ ኣያሌው፣ የሺዋስ ኣሰፋና ዳንኤል ሺበሺ ክስ ላይ ዛሬ 03/02/2008 ዓ/ም የተሰየመው የጠቅላይ ፍርድቤት ችሎት ለጥቅምት 17 /2/ 2008ዓ/ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጠ። የፍርድቤቱ ውሎ ከጉንበት ሰባት የተባለ ኣሸባሪ ቡድን ግንኙነት ፈጥራቹሃል የሚል ክስ ሲሆን ሲሆን የኣብራሃ ደስታ በልዩ …
ሃብታሙ ኣያሌው ኣብረሃ ደስታ የሺዋስ ኣሰፋና ዳንኤል ሺበሺ ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጣቸው። Read more »
Minilik Salsawi – በጥልቀት አትኩሮት እንዳይሰጠው እየተሸፋፈን እየተድበሰበሰ ያለው በሃገራችን ውስጥ የተከሰተው ድርቅ ስምንት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ሕዝብ በሞት አፋፍ ላይ እንደሚገኝ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሚወጡ ሪፖርቶች እየጠቆሙ ነው:: የወያኔው አገዛዝ በሕዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን የረሃብ አድጋ ተድበስብሶ ተደብቆ እንዲቀር …
ስምንት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ሕዝብ በሞት አፋፍ ላይ ይገኛል::(ምንሊክ ሳልሳዊ) Read more »
ባለፈው ቅዳሜ በተነሳው ግጭት ከፖሊስና ከመከላከያ አንዳንድ ወታደሮች ቆስለዋል። የግጭቱ መንስኤ ሁለት የመከላከያ ፖሊስ አባላት በፖሊሶች መደብደባቸው ነው። ከዚህ ቀደም አንድ ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ ፍቼ አካባቢ ሰፍሮ የሚገኘውን የመከላከያ ሰራዊት አባል ከገደለው በሁዋላ፣ በመከላከያና በፖሊስ መካከል ለወራት የዘለቀ ቁርሾ እንዲፈጠር አድርጓል። ባለፈው ቅዳሜ ሁለት የመከላከያ ሰራዊት አባላት በከተማው እየተዝናኑ በነበረበት ወቅት፣ ፖሊሶቹ የደበደቡዋቸው ሲሆን፣ የመከላከያ […]![]()

– ጠቅላላ የሚያስፈልገው የዕርዳታ መጠን 12 ቢሊዮን ብር ደርሷል
– አራት ቢሊዮን ብር ከመንግሥት ካዝና ወጪ መደረጉ ተጠቁሟል
በድርቅ ምክንያት አስቸኳይ የዕለት ደራሽ የምግብ ዕርዳታ የሚፈልጉ ዜጎች ቁጥር 8.2 ሚሊዮን መድረሱን መንግሥት ይፋ አደረገ፡፡ ለጋሾች አስፈላጊውን ዕርዳታ እያቀረቡ
አለመሆኑን መንግሥት ሲያስታውቅ፣ በጠቅላላው አስከፊነቱ እየተባባሰ ለመጣው ድርቅ 12 ቢሊዮን ብር ወይም 600 ሚሊዮን ዶላር ገደማ እንደሚያስፈልግ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ኤጀንሲዎች ይፋ አድርገዋል፡፡
ጥቅምት 1 ቀን 2008 ዓ.ም. ከለጋሽ አገሮች፣ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ኤጀንሲዎችና መንግሥታዊ ካልሆኑ ለጋሾች ጋር በተደረገ የሁለትዮሽ ስብሰባ ላይ የብሔራዊ አደጋ መካከልና ዝግጁነት ኮሚቴ ጸሐፊ አቶ ምትኩ ካሳ እንዳስታወቁት፣ በኤልኒኖ ክስተት ምክንያት በበልግና በመኸር (ክረምት) የዝናብ ሥርጭት በመዛባቱ 8.2 ሚሊዮን ሰዎች አስቸኳይ የዕለት ደራሽ ዕርዳታ ያስፈልጋቸዋል፡፡
‹‹የበልግ ዝናብ መዛባት ከመኸር ዝናብ መስተጓጎል ጋር ተዳምረው የፈጠሩት ችግር ነው፡፡ ብዙ ጊዜ ግን በልግ በሚዛባበት ወቅት መኸር ጥሩ ይሆን ነበር፡፡ ለወትሮው በመኸር አምራች የሆኑ አካባቢዎች ለችግር ስለማይጋለጡ የተረጂዎች ቁጥር ዝቅ ያለ ነበር፡፡ አሁን ግን የሁለቱም መዛባት ችግሩን ፈጥሯል፡፡ ከዚህ ባሻገር ከጥር እስከ ሰኔ ወር በሚተገበረው ሴፍቲኔት ፕሮግራም ታቅፈው የነበሩ 4.4 ሚሊዮን ሰዎችም በ8.2 ሚሊዮን አኃዝ ውስጥ ይገኛሉ፤›› ያሉት አቶ ምትኩ፣ ከጥር ወር በኋላ በመደበኛው የሴፍቲኔት ፕሮግራም ተጠቃሚ የሆኑት ሰዎች ከዕለት ደራሽ ተረጂዎች ሲለዩ፣ አስቸኳይ የምግብ ዕርዳታ የሚቀርብላቸው ሰዎች ቁጥር እንደሚቀንስ አስረድተዋል፡፡
ባለፈው የበልግ ግምገማ ተካሂዶ ነሐሴ 12 ቀን 2007 ዓ.ም. ይፋ በተደረገው አኃዝ መሠረት የተረጂዎች ቁጥር 4.5 ሚሊዮን እንደነበር መገለጹን ያስታወሱት አቶ ምትኩ፣ ይህ አኃዝ ይፋ ከተደረገ በኋላ መንግሥት በአብዛኛው ምላሽ ሲሰጥ መቆየቱን፣ በተወሰነ ደረጃ የዓለም ምግብ ፕሮግራምና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አካል ያልሆኑ ድርጅቶች ማለትም በካቶሊክ ሪሊፍ ሶሳይቲ ሥር የሚንቀሳቀሱ ተቋማት ለድርቅ ጉዳተኞች ድጋፍ ሲያደርጉ መቆየታቸው ተገልጿል፡፡ የበልጉ ዝናብ በመዛባቱ የተከሰተው የምግብ እጥረት 4.5 ሚሊዮኖችን ጉዳት ላይ ጥሏል ቢባልም፣ የክረምቱ ዝናብም በኢልኒኖ ሳቢያ ዘግይቶ ከመግባት ባሻገር በመጠንና በሥርጭት ስለተዛባ የዕለት ደራሽ ዕርዳታ ፈላጊዎች ቁጥር ከ4.5 ሚሊዮን ወደ 7.4 ሚሊዮን፣ ቀጥሎም ወደ 7.7 ሚሊዮን ሊደርስ ችሏል፡፡ በአሁኑ ወቅት ግን የዕርዳታ ፈላጊዎች ቁጥር 8.2 ሚሊዮን መድረሱ ታይቷል ያሉት አቶ ምትኩ፣ ይህ ቁጥር ከዚህ ቀደም በሴፍቲኔት ፕሮግራም የታቀፉት 4.4 ሚሊዮን ሰዎች ያካተተ እንደሆነም አስታውቀዋል፡፡
አቶ ምትኩ በሪፖርተር ተጠይቀው እንዳብራሩት፣ መንግሥት ከራሱ መጠባበቂያ ፈንድና ከክልሎች በተዋጣ በጀት አራት ቢሊዮን ብር ወይም 192 ሚሊዮን ዶላር ለዕርዳታ ማዋሉንና እንደሚቀጥልበትም ገልጸዋል፡፡ መንግሥት ለአስቸኳይ ዕርዳታ እየዋለ ካለው ገንዘብ ውስጥ አብዛኛውን ከፌደራል መጠባባቂያ ፈንድ ቢያወጣም፣ ክልሎችም በራሳቸው ከያዟቸው የመጠባበቂያ ፈንድ በጀት ለድርቁ ሰለባዎች ማዋላቸው ተነግሯል፡፡
የኦሮሚያ ክልል 565 ሚሊዮን ብር በክልሉ ለተጎዱ ሰዎች ሲያውል፣ የአፋር ክልል በበኩሉ 100 ሚሊዮን ብር በመመደብ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል ተብሏል፡፡ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደርም ተመሳሳይ ዕርምጃ በመውሰድ ተጎጂዎችን እየታደገ መሆኑ ተገልጿል፡፡ በከፍተኛ መጠን የድርቅ ተጎጂዎች ካሉባቸው ክልሎች መካከል አፋር ትልቁን ቦታ ይይዛል፡፡ ሶማሌ ክልልም በተጎጂነት ከፍተኛውን ድርሻ ከሚይዙት ክልሎች ውስጥ ሲካተት የደቡብ፣ የአማራና የትግራይ ክልሎችም በድርቅ ምክንያት ተጎጂዎች የሚገኙባቸው ሆነዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ እስካሁን ለተረጂዎች የተገዛውን 450 ሺሕ ሜትሪክ ቶን ስንዴ ጨምሮ አንድ ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ስንዴ እንደሚገዛ ይፋ አድርገዋል፡፡ በጠቅላላው ከ620 ሺሕ ሜትሪክ ቶን በላይ ስንዴ ለመግዛት ዓለም አቀፍ ጨረታ መውጣቱን አቶ ምትኩ አስታውቀዋል፡፡
ይህም ቢባል ግን ከዚህ ቀደም በተመድ የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ጥሪ ያቀረበበት አስቸኳይ የዕርዳታ መጠን 450 ሚሊዮን ዶላር (ከ9.4 ቢሊዮን ብር በላይ) ሊያስፈልግ እንደሚችል የሚጠቁም እንደነበር መዘገቡ ይታወሳል፡፡ እስካሁን ግን ይህ ነው የሚባል ድጋፍ አለመገኘቱን መንግሥት አስታውቋል፡፡ አቶ ምትኩ በጽሕፈት ቤታቸው ካነጋገሯቸው የውጭ ዕርዳታ ለጋሾች መካከል የእንግሊዝ ዓለም አቀፍ ልማት መሥሪያ ቤት (ዴፊድ) 45 ሚሊዮን ፓውንድ (ከ1.4 ቢሊዮን ብር በላይ)፣ የስዊዝ ትብብር ተቋም ሰባት ሚሊዮን የስዊዝ ፍራንክ (152.74 ሚሊዮን ብር) ለመለገስ ቃል ከመግባታቸው ውጪ፣ ሌሎቹ ተቋማት ዕርዳታ ለመስጠት ፍላጎት እንዳላቸው ከመግለጽ በቀር ቃል የገቡት የገንዘብ መጠን አልነበረም፡፡
መንግሥት ድርቅ ያስከተለው ከባድ አደጋ ከቁጥጥሩ ውጪ እንዳልሆነ ለለጋሽ አገሮች፣ ለተመድ ኤጀንሲዎች ተወካዮችና ለዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅቶች ያብራሩት አቶ ምትኩ፣ በአንፃሩ ከእነዚህ አካላት የተጠበቀውን ያህል ምላሽ አለመገኘቱን ጠቅሰዋል፡፡ የሰብዓዊ ዕርዳታ ከዓለም አቀፍ ለጋሾች ማግኘት አስቸጋሪ ከሆነባቸው ምክንያቶች መካከል፣ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የተከሰቱ ቀውሶች የኢትዮጵያን የድርቅና የሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦት ቸል እንዲባል ሰበብ መሆናቸውን ሲገልጹ ተደምጠዋል፡፡
በዓለም የምግብ ፕሮግራም የቀጣናው አስተባባሪና በብሔራዊ አደጋ መከላከልና ዝግጁነት ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ጆን አይሊፍ የተመራው የለጋሾች ቡድን፣ በኢትዮጵያ የተከሰተው አስከፊ የድርቅ አደጋ አስቸኳይ ምላሽ እንደሚያስፈልገው ከስምምነት በመድረስ፣ በጥቅምት ወር ማብቂያና በኅዳር ወር መጀመሪያ አካባቢ ተጠቃሎ ይፋ እንደሚወጣ የሚጠበቀውን ሪፖርት በመንተራስ፣ የጉዳተኞች መጠንና የሚያስፈልገው የገንዘብ መጠን ምን ያህል እንደሚሆን በግልጽ እንደሚታወቅ ገልጸዋል፡፡
ይህም ሆኖ በጠቅላላው ለኢትዮጵያ የድርቅ ሰላባዎች ያስፈልጋል ከተባለው 12 ቢሊዮን ብር ውስጥ እስካሁን 258 ሚሊዮን ዶላር ወይም ከ5.1 ቢሊዮን ብር በላይ ከለጋሾች ቢገኝም ጥቅም ላይ በመዋሉ የምግብ፣ የተጨማሪ ምግብ አቅርቦት፣ የግብርና ዘርፍ ላይ ለህልውና የሚያስፈልጉ ምግብ ነክ አቅርቦቶች ከፍተኛ እጥረት መከሰቱን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሕፃናት ፈንድ (ዩኒሴፍ) ለሪፖርተር በላከው መግለጫ ይፋ አድርጓል፡፡ በዚህ መሠረት በመጪዎቹ ሦስት ወራት ውስጥ ለሰብዓዊ ድጋፎች በአስቸኳይ የሚያስፈልገው የገንዘብ መጠን 237 ሚሊዮን ዶላር ወይም ከ4.7 ቢሊዮን ብር በላይ እንደሆነ ዩኒሴፍ ይፋ አድርጓል፡፡ ከዚህ ባሻገር ለልማት ከተያዘው በጀት መንግሥት ወደ አስቸኳይ ዕርዳታ መዋል እንዳለበት ዩኒሴፍ አሳስቧል፡፡ የዴንማርክ ኤምባሲም የዩኒሴፍ ጥያቄን አስተጋብቷል፡፡ በዓለም ላይ በተከሰቱት ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ አደጋዎች ሳቢያ የዕርዳታ ሽሚያ በማጋጠሙ፣ መንግሥት ለልማት ሥራዎች ከሚያውለው ፈንድ ውስጥ ለድርቁ ተጎጂዎች የሚውል ገንዘብ እንዲመድብ ጠይቋል፡፡
ሴቭ ዘ ችልድረን ኢትዮጵያ ለለጋሾች ቡድን እንዳስታወቀው፣ በኢትዮጵያ የተከሰተው ድርቅ የከረረ መሆኑን፣ መንግሥት ምላሽ የሰጠበት መንገድ ከወትሮው የተለየና ያልተለመደ ፍጥነት የታየበት እንደሆነ አስታውቋል፡፡ ሆኖም አስቸኳይ ዕርዳታ ካልተገኘ ግን አስከፊ የምግብ እጥረት ሊከሰት እንደሚችል ሥጋቱን ይፋ አድርጓል፡፡ የካናዳ ኤምባሲና የአሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት ኤጀንሲ (ዩኤስኤአይዲ) መንግሥት መረጃ በመስጠትና ድርቅ በከሰተባቸው አካባቢዎች ፈጣን ግምገማ በማካሄድ ያገኛቸውን ውጤቶች በማሠራጨት በኩል ጥሩ ሥራ መሥራቱን ገልጸዋል፡፡ አቶ ምትኩ በበኩላቸው ዘንድሮ በተከሰው ድርቅ መንግሥት ትልቁን ድርሻ በመያዝ የዕለት ደራሽ ዕርዳታ ከማቅረብ በተጨማሪ፣ ዕለታዊ መረጃዎችን ለለጋሾች በመስጠት ግልጽነት የተሞላበት ግንኙነት መመሥረቱን አስታውቀዋል፡፡

የመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲ በተለይ ሰሞኑን ለተሾሙ ሚኒስትሮችና የተወካዮች ምክር ቤት አባላትን ጨምሮ፣ ከምክትል ዋና ዳይሬክተር በላይ ሹመት በሚሰጣቸው የመንግሥት ተሿሚዎች የሚሰጠው በቂ ቤት እንደሌለው አስታወቀ፡፡
በሌላ በኩል ላለፉት 24 ዓመታት አዳዲስ መኖርያ ቤቶችን እንዳይገነባ የተደረገው የመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲ፣ ለተሿሚዎች የሚያቀርበው መኖርያ ቤት በማጣቱ ነባር ነዋሪዎችን ለማስለቀቅ መዘጋጀቱን ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የተቋሙ ከፍተኛ ባለሙያ ገለጹ፡፡
ከ600 በላይ የመንግሥት ተሿሚዎች የመኖርያ ቤት ጥያቄ አቅርበው ምላሽ እየተጠባበቁ ቢሆንም፣ ኤጀንሲው ለተሿሚዎች የሚያቀርበው መኖርያ ቤት በማጣቱ ሦስት አማራጭን ለከተማ ልማትና ቤቶች ሚኒስቴር አቅርቧል፡፡
የመጀመርያው አማራጭ ለዘመናት በኪራይ ቤት ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ግለሰቦችን ማፈናቀል ነው፡፡ ሁለተኛው አማራጭ በቤት ልማት ፕሮግራሞች እየተገነቡ ያሉ ኮንዶሚኒየሞችና ከግለሰቦች ደግሞ ሪል ስቴት ቤቶችን መግዛት ነው፡፡ ሦስተኛው አማራጭ በራሱ አቅምና በጀት መኖርያ ቤቶችን መገንባት የሚሉት መሆናቸው ታውቋል፡፡
ነገር ግን የተሿሚዎቹ የመኖርያ ቤት ፍላጎት አጣዳፊ በመሆኑና የመኖርያ ቤት ግዢም ሆነ ግንባታ አማራጮች ወቅታዊ ምላሽ ለመስጠት የማያስችሉ በመሆናቸው፣ ኤጀንሲው ትኩረቱን ተከራዮችን ማፈናቀል ላይ ማድረጉ እየተነገረ መሆኑን ጥቅምት 2 ቀን 2008 ዓ.ም. በግዮን ሆቴል በተደረገ ስብሰባ ላይ የተገኙ ተሳታፊዎች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
ኤጀንሲው ‹‹የተሻሻለው የቤቶች አስተዳደር በግል ርዕስ ባወጣው መመርያ ቁጥር 41/2007 አንቀጽ 3 ለመንግሥት ተሿሚዎች (ብቻ) ቤቶች እንደሚሰጥ አስቀምጧል፡፡ ከእነዚህ ውስጥም ለፌዴራል መንግሥት፣ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ ከኃላፊነት ለሚነሱ ባለሥልጣናት መኖርያ ቤት ይሰጣል ይላል፡፡ በመመርያው ለነዋሪዎች መኖርያ ቤት እንደሚሰጥ የሚገለጽ አንቀጽ አልተቀመጠም፡፡
በዚህ መሠረት ከመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲ በግለሰብ ደረጃ ቤት መከራየት የሚታሰብ አለመሆኑን በርካታ ነዋሪዎች እየተናገሩ ነው፡፡ ከዚህ ባሻገርም የኤጀንሲው ነባር ተከራዮች የመፈናቀል አደጋ እያንጃበበብን ነው በማለት ሥጋታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ፡፡
በአሁኑ ወቅት ይህ አደጋ ሊያንዣብብ የቻለው ለመንግሥት ባለሥልጣናት አዲስ ሹመት ከመሰጠቱ በተጨማሪ፣ ለአምስት ዓመታት ያገለገሉ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የሥራ ጊዜያቸውን ጨርሰው በአዲስ መተካታቸው ነው፡፡ ይህ ሁኔታ አሳሳቢ ሊሆን የቻለው በርካታ አዳዲስ ተሿሚዎች የመኖርያ ቤት ጥያቄ እያቀረቡ ሲሆን፣ ከነባሮቹ የፓርላማ ነዋሪዎች መኖርያ ቤቶች ውስጥ 155 የሚሆኑት አገልግሎት ለመስጠት የማይችሉ በመሆናቸው ልዋጭ ያስፈልጋል በመባሉ ነው፡፡
ይህ ጉዳይ ገኖ ባይወጣም የመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲ በ2008 የሥራ ዕቅድ ላይ ከተከራይ ደንበኞቹና ከባለድርሻ አካላት ጋር ጥቅምት 2 ቀን 2008 ዓ.ም. በግዮን ሆቴል ባደረገው ውይይት በተወሰነ ደረጃ ተነስቷል፡፡
ውይይቱን በንግግር የከፈቱት የመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ኃይለ ማርያም ዓለም ሰገድ፣ ‹‹የመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲ ከዚህ በኋላ ቤት የሚያቀርበው ለመንግሥት ተሿሚዎች ብቻ ነው፤›› ካሉ በኋላ፣ ኤጀንሲው 17 ሺሕ ቤቶችን እንደሚያስተዳድር ገልጸዋል፡፡ ከእነዚህ ቤቶች ውስጥ የሲኤምሲ አፓርታማዎችን ጨምሮ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የሚኖሩባቸው 141 አፓርትመንቶች ሲኖሩት፣ እነዚህ አፓርትመንቶች 5,294 ቤቶች አሏቸው፡፡ ኤጀንሲው እነዚህን አፓርትመንቶች ለማስተዳደር አዲስ መመርያ ማዘጋጀቱን አቶ ኃይለ ማርያም አስታውቀዋል፡፡
የአፓርትመንት አስተዳደር፣ አጠቃቀምና አጠባበቅ ረቂቅ መመርያ ላይ፣ በኤጀንሲው ደንበኞች በተቋቋሙ የአፓርታማ ነዋሪዎች ማኅበራት ተወክለው ከተገኙና ከተለያዩ አካላት ከተወከሉ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል፡፡
ተከራዮች የተከራዩትን ቤት እንዴት መያዝ እንዳለባቸው ማለትም የንፅህና አጠባበቅ፣ በየሕንፃዎቹ ላይ የተከራዩ ደንበኞች አንዱ የሌላውን መብት ሳይነካ የሕንፃውን ደኅንነት ጠብቀው መኖር እንዳለባቸውና ችግር የሚፈጥር ካለ ቤቱን እስከማስለቀቅ የሚደርስ ቅጣት እንደሚጣልበት በዝርዝር በረቂቅ መመርያው ተካተዋል፡፡
ኤጀንሲው፣ ‹‹የደንበኞቼን ደኅንነት ለመጠበቅ የቤቴን ደኅንነት መጠበቅ ግዴታ አለብኝ›› በማለት የሕንፃዎቹን ውበትና ንፅህና ለመጠበቅ ያዘጋጀውን ረቂቅ መመርያ ለተወያዩ ካስተዋወቀ በኋላ፣ መድረኩን ለተሳታፊዎች ክፍት አድርጓል፡፡
የውይይቱ ተሳታፊዎች የመመርያው መዘጋጀት ጥሩ መሆኑን በጥቅሉ ከተናገሩ በኋላ ትኩረት የሰጡት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ፣ ‹‹የመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲ ከዚህ በኋላ የሚሠራው ለመንግሥት ተሿሚ ኃላፊዎች ብቻ ነው፤›› ለሚለው ጉዳይ ነው፡፡ ‹‹ቤት የምንሰጠው ለመንግሥት ባለሥልጣናት ብቻ ነው መባሉ ያሠጋናል፡፡ እናንተ ከቤታችን ልትወጡ ነው የሚል አባባል ይመስላል፤›› ያሉት ተሳታፊዎቹ ምን ማለት እንደሆነ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ጠይቀው፣ ኤጀንሲው ልብ ሊል የሚገባው የቤት ተከራዮች ታክስ እየከፈሉ አገልግሎት ማግኘት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
ኤጀንሲው ተከራዮችን ሊያዳምጥና ያለባቸው ችግርም ሊመለከት እንደሚገባ ተናግረው፣ ፅዳትንና ዕድሳትን በሚመለከት በረቂቅ መመርያው ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ መቀመጡ ተገቢ በመሆኑ፣ ከኤጀንሲው ጋር ተባብረው ለመሥራት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
አንዳንዶቹ ሕንፃዎች ለተለያዩ አገልግሎቶች እየዋሉ በመሆናቸው፣ ኤጀንሲው በጥቃቅን ሥራዎች ላይ ማተኮሩን ተወት አድርጎ የትኛው ሕንፃ ለንግድ፣ የትኛው ለመኖሪያና ለቢሮ መዋል እንዳለበት በመለያየት ሥርዓት እንዲያሲዝላቸው ጠይቀዋል፡፡ ኤጀንሲው ከደንበኞቹ በሚቀርቡለት ጥያቄዎች ላይ ተገቢና አፋጣኝ ምላሽ እንደማይሰጥ የተናገሩት የውይይቱ ተካፋዮች፣ በምርኩዝ የሚሄዱ ጥበቃዎችን ቀጥሮ ሁሉም ነገር የተሟላለት ሕንፃ እንዳከራየ አድርጎ የሚናገረው ተገቢ እንዳልሆነ አስረድተዋል፡፡
በውይይቱ ተሳታፊዎች ለተነሱት ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽ የሰጡት የኤጀንሲው የተለያዩ ክፍሎች ኃላፊዎች እንደገለጹት፣ ቤቶች ለመንግሥት ተሿሚዎች ይሰጣሉ ማለት፣ ነባር ተከራዮች ይፈናቀላሉ ማለት አለመሆኑን ተናግረዋል፡፡ በአንድ አፓርትመንት ውስጥ ብዙ ተከራዮች ስላሉ፣ ወደ ሕንፃዎቹ ማን እንደሚገባ፣ ማን እንደሚወጣና ማን ነዋሪ እንደሆነ ለይቶ ለማወቅ፣ እንደሁም በዓለም ደረጃ ሥጋት እየፈጠሩ ያሉ አንዳንድ ችግሮች በዚህም እንዳይከሰቱ የደንበኞቹንም ደኅንነት ለመጠበቅ ጭምር መሆኑን፣ የኤጀንሲው ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ይገዙ አስረድተዋል፡፡
ኤጀንሲው ያስጨነቀው የደንበኞቹን ደኅንነት እንዴት መጠበቅ እንዳለበት መሆኑን የሚያሳየው ለ40 ዓመታት በነበረው የኪራይ ተመን አከራይቶ እንደሚገኝ ገልጸው፣ ደንበኞች የሕንፃዎችን ደኅነነት ጠብቀው እንዲኖሩና በአብዛኛው መታደስ ያለባቸው ሕንፃዎች ስላሉ ተባብሮ ለማደስ እንዲቻል ለማድረግ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ዝቅ ባለ የኪራይ ዋጋ የተከራየ ደንበኛ የቤቱን፣ የግቢውንና የአካባቢውን ንፅህና መጠበቅ እንዳለበትም አክለዋል፡፡
ለዜጎች ነፃነት ለመታገል ከመኖሪያ ቤታቸው ወደ ትግል ቦታ ወጥተው የነበሩ ታጋዮች በመንገድና በቱቦ ሥር እየኖሩ ባለበት ሁኔታ፣ በአራትና በስድስት ብር የተከራዩ የኤጀንሲው ደንበኞች የቤቱን ንፅህና አለመጠበቃቸው አሳዛኝ መሆኑን የገለጹት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ኃይለ ማርያም፣ ከኤጀንሲው ባከራዩት ቤት አሥር ሕንፃ የሚያስገነባ ሀብት ያገኙ ነጋዴዎች አንድ ጋሎን ቀለም መግዛት አቅቷቸው ሕንፃው ቆሽሾ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡
በዋሽንግተን ዲሲ ውስጥ የምትገኘውን ርዕሰ አድባራት ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያንን ወያኔ በሚቆጣጠረው ሲኖዶስ ስር በቀጥታ ለማስገባት ስውር አጀንዳ አሸምቀው የተለያየ ምክንያት በመስጠት ምዕመንና በማወክና በማወናበድ ሲበጠብጡ የነበሩ ግለሰቦች በዛሬው ዕለት ሰብርው ገብተው የያዙትን ቤተክርስቲያን ለቀው እንዲወጡ የተበየነባቸው መሆኑን ከስፍራው …
በዶክተር አክሊሉ የሚመራው ቡድን በህገወጥ መንገድ የተቆጣጠረውን ቤተክርስቲያን ለቆ እንዲወጣ ተፈረደበት Read more »
የአንጎል የደም ሥሮች ደም የማዘዋወር ሥራቸውን ሲያቋርጡ አለያም በአንጎል ውስጥ ደም ሲፈስ የሚከሰት ድንገተኛና አደገኛ የሕመም ሁኔታ ነው።
የሕመሙን ምልክቶች፤ ለድንገቱ አጋላጭ የሆኑትን ሌሎች የሕመም ዓይነቶች፥ የመከላከያ አማራጮችና እንዲሁም አጣዳፊ የሕክምና እርዳታና ሊገኙ የሚችሉ ውጤቶች የሚመረምር ተከታታይ ዝግጅት ነው።
በሕክምናው ዘይቤ “ስትሮክ” (Stroke) በሚለው መጠሪያው የሚታወቀውን የዚህን የጤና ሁከት ምንነት ጨምሮ ሌሎች ተዛማች ጥያቄዎች የሚመልሱት በዚህ በዩናይትድ ስቴትስ በአትላንታ ከተማ በነርቭና በአንጎል ሕክምና አማካሪ ሃኪምነት በማገልገል ላይ የሚገኙት ዶ/ር ዳንኤል ተስፋዬ ናቸው።