ኢትዮጵያን ሪቪው  “ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን አምባገነን አገዛዝ ማስወገድና መተካት” በሚል ርዕስ ልዩ ህዝባዊ ስብሰባ በዋሽንግተን ከተማ ውስጥ ቅዳሜ, ሴፕተምበር 3, 2011 አዘጋጅቷል። ስብሰባው የመለስ ዜናዊ አምባገነንና ፈላጭ ቆራጭ አገዛዝ በምን መንገድ ስለሚወገድበትና በማንስ ስለሚተካበት ሁኔታ ላይ ትኩረት ይሰጣል። በስብሰባው ላይ …

“ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን አምባገነን አገዛዝ ማስወገድና መተካት” በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ህዝባዊ ስብሰባ Read more »

ተሻለ መንግሥቱ ለረጂም ጊዜ ሥልጣን ላይ መቆዬት ከጣዖትነት ተለይቶ አይታይም፡፡ እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር ከ1933 እስከ 1945 የአሜሪካን ፕሬዚደንት የነበሩት ፍራንክሊን ዴ. ሩዝቬልት እስከዚያን ዘመን ድረስ በልማድ ብቻ ሲከበር የነበረውን የሁለት ዙር የሥልጣን ዘመን በጡጫ ሳይሆን በምርጫ አልፈው በአሜሪካን ሀገር …

የጣዖታት መፈራረስና ጦስ ጥምቡሳቸው Read more »

የሊቢያ ዓማጽያን መዲናይቱን ትሪፖሊ መቆጣጠራቸውን እና በባብ ኧል አዚዝያ የሚገኘውን የሊቢያ መሪ ሞአመር ኧል ጋዳፊ መኖሪያ ቤትንም መያዛቸውን ቤንጋዚ የሚገኘው የብሄራዊው የሽግግር ምክር ቤት ኃላፊ ሙስጠፋ መሀመድ አብዱል ጃሊል ገለጹ።

የፈረንጆች 2011 ዓመት ለዓረብ መሪዎች መልካም ዜና ይዞ አልመጣም፡፡ የሰሜን አፍሪካዊቷ ቱኒዝያ ዜጋ የሆነው መሐመድ ቦአዚዝ ራሱን በማቃጠል የለኮሰው አብዮት፣ ፕሬዚዳንት ቤን ዓሊን ቆይቶም የግብፁን ፕሬዚዳንት ሙባረክን ከሥልጣን አሽቀንጥሮ ጥሏል፡፡

የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ሲቋቋም ዓላማው የአፍሪካ አገሮችን ነፃነት እውን ለማድረግ፣ አፍሪካውያን እንዲተባበሩ ለማስቻልና ከነፃነት ባሻገርም አፍሪካውያን የአፍሪካን ችግር ለመፍታት በጋራ እንዲንቀሳቀሱ ለማድረግ ነው፡፡

– ኩባንያዎቹ እስከ 500 ሺሕ ሔክታር መሬት ሊጠይቁ ይችላሉ በዓለማችን ትልቁ የአበባ አምራች በሆነውና በኢትዮጵያ በ100 ሺሕ ሔክታር መሬት ላይ በተለያዩ ግብርና ምርቶች በተሰማራው በካሩቱሪ አስተባባሪነት የተመራው 30 የህንድ ኩባንያዎችን ያቀፈ የንግድ ልዑክ፣ ሁለት ቢሊዮን ዶላር በሚገመት የአግሮ ቢዝነስ ኢንቨስትመንት …

ከአዳዲስ የህንድ ኩባንያዎች የሁለት ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንት ይጠበቃል Read more »

– ሦስት ተከሳሾች በገደብ ተለቀቁ የአዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ አክሲዮን ማኅበር የቀድሞ ፕሬዚዳንት አቶ ለይኩን ብርሃኑን ጨምሮ ስምንት ተከሳሾች፣ ጥፋተኛ በተባሉበት ወንጀል ከአንድ ዓመት እስከ ሁለት ዓመት ከሁለት ወራት በሚደርስ ፅኑ እስራትና በገንዘብ በትናትናው ዕለት ተቀጡ፡፡

‹‹የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የግድ የትምህርት ባለሙያ መሆን አያስፈልግም›› ረዳት ፕሮፌሰር ወንድወሰን ታምራት የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ በቴክኒክ ትምህርት ላይ የተሰማሩ ባለሙያዎች ከግብርና ጋር ተያያዥነት ካላቸው የትምህርት መስኮችና ሥልጠናዎች ስፔሻላይዝ ያደረጉ በመሆናቸው፣ ለትምህርት ጥራት ችግር የመጀመሪያዎቹ መንስዔዎች መሆናቸውን አንድ ጥናት …

ለትምህርት ጥራት መጓደል የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ባለሙያዎች ተተቹ Read more »

• ደርባ ሚድሮክ አገልግሎት ከተቋረጠብኝ ሁለት ወር ሞላው አለ የቴሌኮም አገልግሎቶች በየጊዜው ለረጅም ጊዜያት በመቆራረጣቸው ሥራቸውን እየጎዳው መሆኑን በርካታ ኢንቨስተሮችና ነጋዴዎች አስታወቁ፡፡

የአምስት ዓመቱን የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በዕርዳታ ብቻ በሚገኝ የገንዘብ ድጋፍ ማሳካት ስለማይቻል፣ የጃፓን መንግሥት አነስተኛ ወለድ ያለው በረጅም ጊዜ የሚከፈል ብድር እንዲሰጠው የኢትዮጵያ መንግሥት ጠየቀ፡፡

የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ ወንጀል ተረኛ ችሎት በትናንትናው ዕለት ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ጀምሮ እያንዳንዳቸው በአምስት ሺሕ ብር ዋስ እንዲለቀቁ ትዕዛዝ አስተላልፎላቸው የነበሩት ዳኛና ረዳቶቻቸው የዋስትና ፈቃድ ታገደ፡፡

  እስክንድር ነጋ በዚህ ሳምንት የማካፍላችኹ ዛሬ ማክሰኞ አዲስ አበባ ውስጥ ከሚታተመው ፍኖተ -ነፃነት ጋዜጣ ጋር ያደረግኹትን ቃለምልልስ ነው።  ሙሉ ቃለ ምልልሱን ለማንበብ: www.andinet.com ኢህአዴግ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ጅምር መኖሩን በተደጋጋሚ ይገልጻል ። ፖለቲካውም፣ ኢኮኖሚውም፣ ማህበራዊ ጉዳይ ጅምር አለ፡፡ …

‹‹ህዝቡ ሠላማዊ ለውጥ ይፈልጋል፤ ጊዜው የለውጥ ነው›› Read more »

የአሠሪ እና ሠራተኞች ወሳኝ ቦርድ በከሳሽ የኢትዮ ቴሌኮም ነባር የሠራተኞች ማህበራቸው እና በተከሳሽ አዲሱ የኢትዮቴሌኮም አስተዳደር መካከል የተነሳውን ክርክር ዛሬም ተመልክቶ ብይኑን ለሚቀጥለው ሳምንት አሻግሮታል።

ይህንን ማስታወሻ የምጽፈው እለተ አርብ ነሃሴ 13 ቀን 2003 ምሽትላይ ነው. . .ጅዳ ሳውዲ አረቢያ ! አርብ እንደቀረው አለም እሁድ የአረቦች የእረፍት ቀን በመሆኑ የዋልኩት እቤት ሲሆን ከተጋደምኩበት የተነሳሁት አረፋፍ  ነበር። ማታ በተሰጠኝ መረጃ መሰረት ለዜና የሚሆኑ መረጃዎ ችን ሰባስቤ …

የኢትዮጵያውያን ስድተኞች መከራ በየመን ! (ክፍል 12)ነቢዩ ሲራክ- ከሳውዲ አረቢያ Read more »

– አቶ አባዱላ ገመዳና አቶ አዲሱ ለገሰ ይገኙበታል ዓለም አቀፍ የአመራር ኢንስቲትዩት ከግሪንዊች ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አቶ አባዱላ ገመዳንና የኢትዮጵያ አየር መንገድ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ አዲሱ ለገሰን ጨምሮ፣ 236 ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊዎችን፣ የመከላከያ ጄነራሎችንና …

ከ230 በላይ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትና የንግድ ሰዎች ተመረቁ Read more »

– ማኅበሩ ለጠቅላይ ሚኒስትሩና ለብሔራዊ ባንክ ደብዳቤ ጻፈ በደቡብ ክልል በሲዳማ ዞን የሚገኙ የቡና ገበሬዎች ባንኮች ብድር ባለማቅረባቸው ምክንያት፣ እርሻቸውን ወደ ጫት እየለወጡ መሆኑን የሲዳማ ቡና አቅራቢዎች ማኅበር አስታወቀ፡፡

ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ሰሞኑን የኡጋንዳ የሦስት ቀናት ጉብኝታቸውን አጠናቀው በሚመለሱበት ወቅት ቆይታቸውን በተመለከተ ከፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ጋር በመሆን በሰጡት መግለጫ፣ ከጋዜጠኞች የቀረበላቸው ቀዳሚው ጥያቄ ከአልሸባብ ጋር ያላቸውን ቁርኝት በተመለከተ ማብራርያ እንዲሰጡ ነበር፡፡

ከመጀመሪያዋ የብርሃን ብልጭታ ጀምሮ ጊዜ እንደ ጅረት ይተማል፡፡ የጊዜ ጅረት መጠኑ አይሞላም፣ አይጎድልም፣ ሁልጊዜም አንድ ነው፡፡ የማይደርቅ ጅረት ነው፡፡ ትውልድም ከሰው ልጅ የህላዌ ጅማሮ አንስቶ በጊዜ ስጋጃ ላይ ይነጉዳል፡፡ የትውልድ ጅረት ግን አቀበትና ቁልቁለት፣ የበጋ እና የፀሐይ ወራት አሉት፡፡ የትውልዱ …

የጭቆና ሰንበሮች በአንዱዓለም አራጌ Read more »

እንደምን ሰነበታችሁ ውድ አንባቢያን፡፡ የሰሞኑ የሀገራችን የፖለቲካ ንፋስ እንዴት ይዟችኋል? እኔማ አንዱን ስሰማው እያደነገዘኝ ሌላውን ስሰማው ደግሞ እያደነዘዘኝ ፈዝዤላችኋለሁ፡፡ ለደግ ያድርግልህ በሉኝ፡፡ አሳሳቢ ሁኔታ ውስጥ የምንገኝ ይመስለኛል፡፡ አንዱ ከአንዱ መማርና ካለፈ ታሪክ ዕውቀትን ገብይቶ የወደፊቱን ለማስተካከል መሞከር ዕርም የተባለበት ጊዜ …

አርአያነታቸው የሚያኮራ ፍጡራን በይነጋል በላቸው Read more »

ልጅ ተክሌ (ኦታዋ)ብሄርንና ሀይማኖትን መሰረት ያደረገ ክርክር አስቸጋሪ ነው። ሀይማኖት ይብሳል። በንጽጽር፡ ከሀይማኖት ደግሞ ብሄር ለክርክር ይቀላል።