‹‹ህዝቡ ሠላማዊ ለውጥ ይፈልጋል፤ ጊዜው የለውጥ ነው››
እስክንድር ነጋ
በዚህ ሳምንት የማካፍላችኹ ዛሬ ማክሰኞ አዲስ አበባ ውስጥ ከሚታተመው ፍኖተ -ነፃነት ጋዜጣ ጋር ያደረግኹትን ቃለምልልስ ነው። ሙሉ ቃለ ምልልሱን ለማንበብ: www.andinet.com ኢህአዴግ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ጅምር መኖሩን በተደጋጋሚ ይገልጻል ። ፖለቲካውም፣ ኢኮኖሚውም፣ ማህበራዊ ጉዳይ ጅምር አለ፡፡ የዴሞክራሲ ሥርዓት በአጭር ጊዜ የሚገነባ አይደለም፡፡ ፈረንጆች 200 ዓመት ፈጅቶባቸዋል ይላል፡፡ ይህንን አስተሳሰብ አንደት ይመለከቱታል?