ዲባቶ አረጋዊ በርሄ ከኦታዋ ኢትዮጵያዊያን ጋር መከረ

ስብሰባው በካሜራ እንዲቀረጽ ተፈቅዷል

ለተቃዋሚ ሀይሎች ኅብረት ምስረታ ከግንቦት ሰባትና ሌሎች ተቃዋሚ ሀይሎች ጋር እየሰራን ነው” 

Ethiopia Zare (ሰኞ ነሐሴ 14 ቀን 2003 ዓ.ም August 14 2011) ቀውሱ ያለው አሮጌው ስርአት እየወደቀ፡ አዲሱ ስርአት ግን አልወለድ ማለቱ ላይ ነውበሚለው የኢጣሊያዊው ፈላስፋና ፖለቲከኛ የሁለተኛ ዓለም ጦርነት ዋዜማ ንግግር ጥቅስ መልእክቱን አጽንኦት የሰጠው፡ የኢትዮጵያን የህዝብ ፍሰትና ፍልሰት ታሪክ አንስቶ፡ በዘመናዊ ታሪኳ ኢትዮጵያ የገባችበትን ቀውስ ጠቅሶ፡ በዋንኛነት አሁን ኢትዮጵያ ያጋጠማትን አደጋ ያብራራው የቀድሞ የህወሀት መስራች፡ የታንድ (የትግራይ ትብብር ለብሄራዊ ዴሞክራሲ) መሪ ዲባቶ አረጋዊ በርሄ፡ በኦታዋ ከሚገኙ አያሌ አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊአን ጋር ገንቢ ውይይት አድርጓል።