የአለማችን ጠንካራው የሰብአዊ መብቶች ተሟጋች የሆነው ሂውማን ራይተስ ወች ለእንግሊዙ የውጭ የልማት ትብብር ሚኒስትር አንዲሪው ሚቼል በጻፈው ደብዳቤ፣ ባለስልጣኑ ለኢትዮጵያ የሚሰጠው የውጭ እርዳታ ኢትዮጵያውያንን ለመጨቆኛነት መዋሉን ማረጋገጥ አልቻልም በማለት ለቢቢሲ የሰጡት ቃል ተአማኒነት የሌለውና ህዝብን ሆን ብሎ ለማደናገር የቀረበ ነው በማለት ወቅሷል። ሂውማን ራይትስ ወች ለኢትዮጵያ የሚሰጠው እርዳታ ለተገቢው ህዝብ ከሚደርስ ይልቅ የመለስ መንግስት የፖለቲካ […]

የአባይ ግድብ የህዝብ አደራጅ ኮሚቴ ተብሎ የተቋቋመው ድርጅት ሀላፊ የሆነው በረከት ስምኦን ለብሉምበርግ እንደተናገረው ፣ የመንግስት ሰራተኛው ከደሞዙ እየቀነሰ የአባይን ግድብ ቦንድ እንዲገዛ መታዘዙ የሚያዛልቅ አልሆነም በማለት ቀደም ሲል ከፍተኛ የህዝብ መነቃቃት ታይቶበታል ተብሎ በወያኔና ተባባሪዎቹ ሚዲያ ሲራገብ የነበረውን ባዶ ፕሮፖጋንዳ አጋለጠ። ላለፉት በርካታ ወራት ጠዋትና ማታ ህዝብ በነቂስ ወጥቶ ለግድቡ ማሰሪያ ገንዘብ እያዋጣ ነው […]

በምዕራባዊያን የገንዘብና የፖለቲካ ድጋፍ ህዝባችንን አፍኖና ረግጦ እየገዛ ያለው የዘረኛው መለስ ዜናዊ አገዛዝ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዜጎቻችን ላይ አጠናክሮ የቀጠለውን እስር በማውገዝ ቁጥራቸው በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን በትናንትናው ዕለት በአሜሪካን ስቴት ዲፓርትሜንት ፊት ለፊት ተገኝተው ደማቅ ሰላማዊ ሰልፍ ማካሄዳቸውን ሪፖርተራችን ከሥፍራው በላከልን ዜና ገለጸ። ሞት ለወያኔ-፤ ሞት ለጎጠኞች ፤ ሞት ለሽብርተኛው መለስ ዜናዊ፤ መለስ ዜናዊ […]

ዘረኛውና አምባገነኑ የወያኔ አገዛዝ በተለይም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ንጹሃን ዜጎችን ሽብርተኞች ናችሁ በማለት የጀመረው የጅምላ እስራት፣ የአምባገነኑ ስርአት ማብቂያ ዋዜማ መሆኑን የሚያመለክት ሲሆን አገዛዙ እየፈጸመ ያለው ድርጊት ደግሞ የራሱን መቀበሪያ ጉድጉአድ እየቆፈረ እንደሆነ የሚያረጋግጥ ነው በማለት በርካታ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ለዘጋቢያችን ገለጹ:: እንደዘጋቢያችን ሪፖርትና በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ ክፍለ ከተሞች በመዘዋወርም ያነጋገራቸው በርካታ የአዲስ […]

ዘረኛው የወያኔ አገዛዝ በወገኖቻችን ላይ የጀመረውን የእሥር ዘመቻ ለማስቆምና ሽብርተኝነትን በመከላከል ሥም በአገዛዙ እየተካሄደ ያለውን መንግሥታዊ ሽብር ለአለም አቀፉ ህብረተሰብ ለማሳወቅ ኢትዮጵያዊያኑ በየሚኖሩበት የምዕራብ አገሮች ከፍተኛ የሆነ እንቅስቃሴ እያካሄዱ መሆኑን ወደ ዝግጅት ክፍላችን እየደረሱ ያሉ መረጃዎች አመለከቱ። ባለፈው ሰኞ በአሜሪካን አገር ስቴት ዲፓርትመንት ፊት ለፊት የተጀመረው የኢትዮጵያዊያን ተቃውሞ፤ በነገው ዕለት መስከረም 19 ወይም እንደ ፈረንጆቹ […]

ዘረኛው የወያኔ አገዛዝ በድህረ ምርጫ 97 የቅንጅት መሪዎችን፤ ጋዜጠኞችንና የስብአዊ መብት ተሟጋቾችን እስር ቤት ባጎረበት ወቅት፤ ዳግም ለወያኔ እስር በተዳረገው ባለቤቷ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ጋር እስር ቤት እየማቀቀች የተገላገለቺው ህጻን ልጇ እንደ አባቱ የነጻነት ታጋይ እንዲሆን ምኞቷ መሆኑን ጋዜጠኛ ስርካለም ፋሲል አዲስ ጉዳይ በተባለ መጽሄት ላይ ባሳተመቺው ጽሁፍ መግለጿን ለማወቅ ተችሎአል። ጋዘጠኛ ስርካለም በአመዛኙ ስለ […]

ስለሉሉ የማያውቅ እንደማይኖር ተስፋ አለኝ፡፡ ሉሉ የአፄ ኃይለ ሥላሤ ድንክ ውሻ ናት ወይም ነበረች – አፈሩ ይቅለላት ነፍሷም በየማነ ብፁዓን አክልብት ይቀመጥና፡፡ ያቺ ድንክዬ የጠቅል ውሻ ታሪከኛ ነበረች አሉ፤ ተራ ውሻ አልነበረችም፡፡ ሥልጣንና ማዕረጓ ራሱ ከንጉሡ በታች ከመኳንንትና መሣፍን በላይ እንደነበር በወቅቱ ለንጉሡ ቅርበት የነበራቸው አረጋዊ ዜጎች ያስታውሳሉ፡፡ የማንንም እግር እየሄደች ብትዘነጥል ከመብቶቿ አነስተኛው ነበር፡፡ […]

– ‹‹አውሮፕላኑ ከመውደቁ በፊት ቡርቱካናማ ፍንዳታ ተመልክተናል›› የራፊቅ ሃሪሪ ኤርፖርት የበረራ ተቆጣጣሪዎች-    የሊባኖስ ባለሥልጣናት የተጠየቁዋ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ ተወስኖ ሲካሄድ የቆየው የወርቅ ግብይት፣ በተመረጡ አራት የክልል ከተሞች እንዲካሄድ በተላለፈው መመርያ…

በአዲሷ ደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያን ባህል ለማስተዋወቅ በመጓዝ ላይ የነበሩት በብዛት የሕወሓት ታዋቂ ታጋዮች የሚገኙበት የአርቲስቶች ቡድን በገጠመው የተሽ

በተለያዩ የኦሮሚያ ፍርድ ቤቶች ላይ ከሕግ አግባብ ውጭ ውሳኔ እንደተወሰነባቸው በመግለጽ ቅሬታ ባቀረቡ 246 ባለጉዳዮች ምክንያት፣ በሥነ ምግባር ጉድለት በ

ፍኖት- የጋዜጠኛ ሰርክዓለም ፋሲል ንብረቶች እስከአሁን አልተመለሱም
ባለፈው መስከረም 3 ቀን 2004 ዓ.ም በ “ሽብር” ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በዕለቱ ሲያሽከረክሯት የነበረች የቤት መኪና እና መተዳደሪያቸው የሆነውን የቤት ኪራይ ገንዘብ እንዲመለስላቸው ጋዜጠኛ ሰርክዓለም ፋሲል ቢጠይቁም እስከአሁን እንዳልተመለሰላቸው ገለፁ፡፡
ወ/ሮ ሰርክዓለም ንብረቶቹ በተያዙበት ማዕከላዊ እስር ቤት ሄደው የመኪናውን ሊብሬ በእሳቸው ስም እንደሆነ ለማስረጃነት ቢያቀርቡም “ከአንቺ […]

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)
UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY(UDJ)
ቁጥር፡-አንድነት /437/2ዐዐ4
ቀን 15/01/2004 ዓም
ግልጽ ደብዳቤ
ለኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ
አዲስ አበባ
ጉዳዩ፡- በሽብርተኝነት ስም የታሰሩ አባሎቻችንና ሌሎች ዜጎች ሕገ-መንግሥታዊ መብታቸው እንዲከበርላቸው ስለመጠየቅ፣
በኢትዮጵያ ሕዝብ ዘንድ በግልጽ እንደሚታወቀው አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) በሕገ-መንግሥቱ በተደነገገው የመደራጀት መብት መሠረት ሕጋዊና ሠላማዊ በሆነ መንገድ ለዜጎች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች እውን […]

አቶ ኦልባና ሌሊሳ በምዕራብ ሸዋ ጨሊ ወረዳ በ1966 ዓ.ም ተወለዱ፡፡ የመጀመሪያና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውንም በተወለዱበት አካባቢ አጠናቀው ወደ መንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋም በመግባት በግብርና ዲፕሎማ አግኝተዋል፡፡ ከዚያም በመንግሥት ግብርና ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ውስጥ በሚተዳደር መስሪያ ቤት ተቀጥረው ለዓመታት አገልግለዋል፡፡ በማታው መርሐ ግብር በአምቦ ዩኒቨርስቲ የትምህርት ደረጃቸውን ለማሻሻል እየተማሩ እንደነበርና በተደረገባቸው የፖለቲካ ጫና ምክንያት ሥራቸውን በፈቃዳቸው […]

ወ/ት ሊዲያ ዘሪሁን ትባላለች፡፡ በእስር ላይ የሚገኙት የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ /ኢብአፓ/ ፕሬዝደንት የአቶ ዘሪሁን ገ/እግዚአብሔር ልጅ ናት፡፡ በአባቷ ዙሪያ ባልደረባችን ብዙአየሁ ወንድሙ አነጋርሯታል፡፡ መልካም ቆይታ፡፡
አባትሽ አቶ ዘሪሁን ገ/እግዚአብሔር በእስር ላይ እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡ በመጀመሪያ አቶ ዘሪሁን የት ተወለዱ?
ወ/ት ሊዲያ- ዘርዬ የተወለደው እዚሁ አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ሥፍራው መርከቶ የሚባል አካባቢ ነው፡፡
ስለ ትምህርታቸው አጠቃላይ ሁኔታ ብትገልጪልኝ […]

ሽብርተኝነት ከ20ኛው ክፍለ ዘመን ሁለተኛው አጋማሽ ጀምሮ እየጎላ የመጣ አደገኛ ክስተት ነው፡፡ አደገኛነቱ በግልጽ የታየው እ.ኤ.አ መስከረም 11 ቀን 2001 ዓ.ም በኒውዮርክ ከተማ የንግድ ማዕከል ላይ በደረሰው ጥቃት ነው፡፡ በዚህ ጥቃት በሺዎች የሚቆጠር ህይወት ጠፍቷል፡፡ በቢሊዮን ዶላር የሚገመት ንብረት ወድሟል፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ በዓለም ሕዝብ ላይ ይህ ነው የማይባል ድንጋጤና የመንፈስ ጭንቀት ፈጥሯል፡፡
ተንታኞች ሽብርተኝነትን በተለያየ […]