ፍኖት- የጋዜጠኛ ሰርክዓለም ፋሲል ንብረቶች እስከአሁን አልተመለሱም
ፍኖት- የጋዜጠኛ ሰርክዓለም ፋሲል ንብረቶች እስከአሁን አልተመለሱም
ባለፈው መስከረም 3 ቀን 2004 ዓ.ም በ “ሽብር” ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በዕለቱ ሲያሽከረክሯት የነበረች የቤት መኪና እና መተዳደሪያቸው የሆነውን የቤት ኪራይ ገንዘብ እንዲመለስላቸው ጋዜጠኛ ሰርክዓለም ፋሲል ቢጠይቁም እስከአሁን እንዳልተመለሰላቸው ገለፁ፡፡
ወ/ሮ ሰርክዓለም ንብረቶቹ በተያዙበት ማዕከላዊ እስር ቤት ሄደው የመኪናውን ሊብሬ በእሳቸው ስም እንደሆነ ለማስረጃነት ቢያቀርቡም “ከአንቺ እጅ አልያዝንም” የሚል መልስ እንደተሰጣቸውና መተዳደሪያቸው የሆነው የቤት ኪራይ ገንዘብንም ሲጠይቁ “ሁሉንም ከአንቺ ስላልወሰድን አጣርተን ስንጨርስ ደውለን እንጠራሽና ትወስጃለሽ” ብለው እንደመለሷቸው በተለይ ለዝግጅት ክፍሉ ገልጸዋል፡፡
ሕወሃት ኢሕአዴግ ኢቲቪን፣ ራዲዮዉን በሙሉ ሕገ ወጥ በሆነ መንገድ አፍኖ ይዟል። የአንድነት ፓርቲ በፍኖት ጋዜጣ ሕዝቡን ለመድረስ፣ ለማስተማር እየሞከረ ነዉ። ጋዜጣዉን በብዛት ለማሳተም፣ በአገሪቷ ክፍሎች በስፋት ለማሰራጨት የገንዘብ አቅም ይጠይቃል።፡ለዚህ ኢትዮጵያዊ አላማ የድርሻዎትን ይወጡ ዘንድ አገራዊ ጥሪ እናቀርባለን። በገንዘብዎት አገር ቤት የሚደረገዉን ትግል ይርዱ።