የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ፣ ከካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ጋር ያለን ልዩነት “ጠባብ ነው” ማለታቸው እያነጋገረ ነው፡፡ፓትርያርኩ ይህን የተናገሩት ባለፈው ሳምንት በዓዲግራት ሀገረ ስብከት ተገኝተው የደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያንን በመረቁበት ወቅት ሲሆን በሥነ ሥርዓቱ ላይ የትግራይ ክልል …

ፓትርያርኩ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ከካቶሊክ ጋር ያለን ሃይማኖታዊ ልዩነት “ጠባብ ነው” ማለታቸው እያነጋገረ ነው Read more »

 ሰሞኑን ቢቢሲ በሰሜን ኢትዮጵያ ወሎ አካባቢ ተገኝቶ ድርቁ ባስከተለው ረሃብ ላይ ያቀረበው ዶክመንተሪ፤ በተለያዩ አለማቀፍ ሚዲያዎች አነጋጋሪ ሆኖ የሰነበተ ሲሆን መንግስት በድርቁ የሰው ህይወት አልፏል የሚባለውን አልቀበልም ብሏል፡፡ በ1977 ዓ.ም የተከሰተው አስከፊ ድርቅ የብዙዎችን ህይወት በቀጠፈበት ወሎ ቆቦ አካባቢ የቢቢሲው …

ቢቢሲ በኢትዮጵያ ድርቅ ባስከተለው ረሃብ ላይ ያቀረበው ዘገባ አነጋጋሪ ሆኗል Read more »

የፕላስቲክ ቱቦዎችንና መገጣጠሚያ ማሽነሪዎችን ለማስመጣትና በአገር ውስጥ ለመገጣጠም ከኢትዮጵያውያን ጋር ባለድርሻ በመሆን ያቋቋሙትን ኩባንያ መጠቀሚያ በማድረግ፣ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ኤልሲ ከፍተው ካገኙት የውጭ ምንዛሪ ውስጥ ከ62.2 ሚሊዮን ብር በላይ በውጭ ባንክ በመደበቅ የተጠረጠሩ ሁለት የውጭ ዜጐች ተከሰሱ፡፡

 

የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ክስ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ክስ የመሠረተባቸው ተጠርጣሪ ተከሳሾች፣ በትውልድ አሜሪካዊና በዜግነት ደቡብ አፍሪካዊ መሆናቸው የተገለጸው ሚስተር ማይክል ማትሰንርና እንዲሁም ግብፃዊ መሆናቸው የተገለጸው ሚስተር አይመን አብድል ሞተልብ ሙሳ ኢሳ መሆናቸው በክሱ ተገልጿል፡፡

ግለሰቦቹ የተከሰሱት በከባድ የማታለል ወንጀልና በሕገወጥ መንገድ የተገኘን ገንዘብ ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብ ወንጀል መሆኑንም ክሱ ይጠቁማል፡፡

ተከሳሾቹ ድርጊቱን እንዴት እንደፈጸሙት ዓቃቤ ሕግ በክሱ እንደገለጸው፣ ኢትዮጵያውያንና ግብፃዊው ሚስተር አይመን በጋራ ባቋቋሙት ስታር ፓይፕና ፊቲንግስ ኩባንያ ውስጥ፣ ሚስተር ማትሰን ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው ይቀጠራሉ፡፡ ሚስተር አይመን ለብቻቸው ያቋቋሙት ጎልደን ትሬዲንግ ከሚባለው ኩባንያ በተጨማሪ ከሚስተር ማትሰን ጋር በጋራ ያቋቋሙት በዱባይ የሚገኝ ዋሶ ቴክኖሎጂ ግሩፕ የሚባል ኩባንያ አላቸው፡፡ በመሆኑም ተከሳሾቹ ከህንድና ከቻይና ወደ አገር ውስጥ እንደሚያስገቡ የገለጹትን የፕላስቲክ ቱቦና መገጣጠሚያ ማሽነሪዎችን፣ በኢትዮጵያ ንግድ መርከብ ለማጓጓዝ የተለያየ መጠን ያለው ዶላር ለማስጫኛ በመክፈል ዕቃዎቹን እንዳስገቡ መግለጻቸውን ክሱ ያስረዳል፡፡ 

ተከሳሾቹ ከቻይናና ከህንድ ከ2004 ዓ.ም. እስከ 2005 ዓ.ም. ድረስ በኢትዮጵያ ንግድ መርከብ እያስጫኑ ዕቃውን ሲያስገቡ፣ ለማስጫኛ ያልተከፈለውን የገንዘብ መጠን፣ በሐሰተኛ የማስጫኛ ደረሰኝና የንግድ ሽያጭ ደረሰኝና በሐሰተኛ ማኅተም ተጠቅመው ወንጀሉን እንደፈጸሙ የዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡

ተከሳሾቹ በቻይና የኢትዮጵያ ንግድ መርከብ ወኪል የሆነው ‹‹የቻይና የውቅያኖስ አጓጓዥ ኤጀንሲ ሻንጋይ›› የሚል ሐሰተኛ የጭነት ደረሰኝ በማዘጋጀት፣ ‹‹የመጫኛ መነሻ ወደብ ሻንጋይ ቻይና፣ ጭነት ማራገፊያ ጂቡቲ የባህር ወደብ፣ መድረሻ ሞጆ ደረቅ ወደብና አጓጓዥ የኢትዮጵያ ንግድ መርከብ›› የሚል ሐሰተኛ ሰነድ አዘጋጅተው የተለያየ መጠን ያለው ዶላር እንደተከፈለ በማስመሰል፣ ጠቅላላ ድምሩ 62,278,179 ብር ዱባይ ሚስተር ማይክልና ሚስተር አይመን በጋራ በዱባይ ማሽሩክ ባንክ በከፈቱት ‹‹ዋሶ ቴክኖሎጂ ግሩፕ›› ተብሎ በሚጠራው ድርጅታቸው አካውንት ውስጥ እንዲገባ ማድረጋቸውን ክሱ ያስረዳል፡፡

ተከሳሾቹ የተጠቀሰውን ያህል ገንዘብ ዱባይ በሚገኘው የድርጅታቸው አካውንት ማሽሩክ ባንክ ያስገቡት፣ ለምሳሌ ዕቃውን ያስጫኑት በ19,000 ዶላር ከሆነ ኤልሲ ከፍተው የውጭ ምንዛሪ ከጠየቁት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቃሊቲ ቅርንጫፍ በሚያቀርቡት ሐሰተኛ ሰነድ 40,000 ዶላር እየተቀበሉ፣ ልዩነቱን ለግላቸው ማድረጋቸውን ክሱ ያስረዳል፡፡ 

ቻይናና ህንድ ውስጥ ላለው ስታር ፓይፕና ፊቲንግስ ፋብሪካ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ሲላክ ‹‹የተመረተበት አገር ቻይና፣ ለማሽነሪው ለአንዱ ብቻ የተከፈለ 385,370 ዶላር›› በማለትና ትክክለኛ ምርት ለማስመሰል ‹‹በስቴት ኦፍ ቴክሳስ ንግድ ምክር ቤት የተረጋገጠ›› የሚል ሐሰተኛ ሰነድ ማኅተም ተደርጐበት እንደቀረበ ክሱ ይገልጻል፡፡

በስቴት ኦፍ ቴክሳስ ንግድ ምክር ቤት በተመዘገበው የቻይና ኩባንያ የተመረተ እውነተኛ ምርት ለማስመሰል፣ ተከሳሾቹ ዋሶ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ፕሮፎርማ ሰብስቦ እንዳረጋገጠ የሚያሳይ የንግድ ደረሰኝ በማቅረብ፣ እውነተኛ አስመስለው በሐሰተኛ ሰነድ እየተገለገሉ፣ ከዘጠኝ ጊዜያት በላይ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የውጭ ምንዛሪ በመውሰድ የተጠቀሰውን ገንዘብ ዱባይ ወደሚገኘው አካውንታቸው ለማሸሽ መቻላቸውን ክሱ ያብራራል፡፡

ተከሳሾቹ ‹‹ለኢትዮጵያ ንግድ መርከብ በቻይና ውቅያኖስ ጉዞ ኤጀንሲ የተከፈለ የውጭ ምንዛሪ›› በማለት በሐሰት ባዘጋጁት የተለያየ ሰነድ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ያወጡትን የውጭ ምንዛሪ፣ ወደ ዱባይ ማሽሩክ ባንክ በመላክ ከባድ የማታለል ወንጀል መፈጸማቸውን የዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡

ሚስተር ማትሰን በቁጥጥር ሥር ሲሆን፣ በዋስትናው ላይ ብይን ለመስጠትና የክሱን ሒደት ለማስቀጠል ለኅዳር 8 ቀን 2008 ዓ.ም. ተቀጥሯል፡፡ ሚስተር አይመን ሊገኙ ባለመቻላቸው በጋዜጣ ጥሪ እንዲደረግላቸው ትዕዛዝ ተሰጥቶ ለመጠባበቅ ለታኅሳስ 6 ቀን 2008 ዓ.ም. ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡

ከሁለቱ የውጭ ዜጎች ጋር ክስ የተመሠረተባቸውና በ100,000 ብር ዋስ በውጭ ሆነው ክሳቸውን እንዲከታተሉ ትዕዛዝ የተሰጠባቸው ደግሞ አቶ ወሰንዓለም ገብረ እግዚአብሔር ይባላሉ፡፡

አቶ ወሰንዓለም የተጠረጠሩት ሚስተር ማትሰን የስታር ፓይፕና ፊቲንግስ ሥራ አስኪያጅ ሆነው ሳሉ፣ ከድርጅቱ መተዳደሪያ ደንብ ውጪ ድርጅቱ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቃሊቲ ቅርንጫፍ ካስቀመጠው ገንዘብ ውስጥ፣ ሦስት ሚሊዮን ብር ‹‹ለሚመለከተው ሁሉ›› ተብሎ በተሰጣቸው ውክልና በድርጅቱ ስም በማውጣታቸው መሆኑን ክሱ ያብራራል፡፡ በዋና ወንጀል አድራጊነት በፈጸሙት በሌላ ሰው ጥቅም ላይ የሥራ አመራር ጉዳት ማድረስ ወንጀል መከሰሳቸውን የዓቃቤ ሕግ ክስ ያብራራል፡፡     

 

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባባሪያ ቢሮ (OCHA) የአስቸኳይ መልስ ፋንድ ክፍል ሰርፍ (CERF) ለኢትዮጵያ ከገጠሙት ሁሉ የከፋ በሆነ ድርቅ ለተጎዱ ማህበረሰቦች የአስራ ሰባት ሚሊዮን ዶላር አስቸኩዋይ ርዳታ ትናንትና ሰጠ።

የወተቱ እንቆቅልሽ

አቶ ደረጀ ዳዲ በሰንዳፋ ከተማ ወተት አምራች ነው፡፡ የራሱን ብቻም ሳይሆን ከአካባቢው ገበሬዎች እየሰበሰበ አዲስ አበባ አምጥቶ ለአከፋፋዮች ያስረክባል፡፡ በቀን እስከ 800 ሊትር ወተት ያቀርብ የነበረ ቢሆንም፣ በቅርቡ የዓለም አቀፍ

የእንስሳት ምርምር ኢንስቲትዩት (IRLI) ጥናትን በመጥቀስ በአዲስ አበባና በአዲስ አበባ ዙሪያ ከሚገኙ ከተሞች በተሰበሰቡ ወተቶች ውስጥ አፍላቶክሲን የተሰኘ ኬሚካል መገኘት በመገናኛ ብዙኃን በመዘገቡ ምክንያት፣ ትልቅ ኪሳራ እንደደረሰበት አቶ ደረጀ ለሪፖርተር ገልጿል፡፡ በዚህም በአሁኑ ወቅት በቀን ከ300 ሊትር በላይ ማቅረብ አልቻለም፡፡ በወተት ውስጥ ለአፍላቶክሲን መገኘት ምክንያት የሆነው የሻገተ ፋጉሎ መሆኑ በጥናቱ ቢጠቀስም፣ ሪፖርተር በተለያዩ የሰንዳፋ ከተማ ወረዳዎች ተዘዋውሮ ያነጋገራቸው ወተት አምራቾች ፋጉሎን ለመኖነት መጠቀም ካቆሙ ዓመታት መቆጠራቸውን ገልጸዋል፡፡ ከኑግ ዘይት ሲጨመቅ ተረፈ ምርት የሆነው ፋጉሎ ዋጋ በኩንታል 800 ብር መሆኑም፣ ከዋጋ አንፃር ተመራጭ እንደማያደርገውም ያስረዳሉ፡፡ በበረህ ወረዳ ከዳቤ ቀበሌ ወተት አምራች የሆነው አቶ ይገዙ አሰፋም የአፍላቶክሲን መገኘት ዜና በእጅጉ ገቢያቸውን እንደጐዳው ገልጿል፡፡

ባለፈው ሳምንት ተቀባዮች ሙሉ በሙሉ ወተት እንዳልተረከቡት ይናገራል፡፡ እሱም በአካባቢው ፋጉሎን ለእንስሳት መኖ ጥቅም ላይ እንደማይውል፣ ይልቁንም ቢሾፍቱ ከተማ ከሚገኝ ዓለማ ካውዳይስ የእንስሳት መኖ ከተሰኘ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር የተመጣጠነ መኖ እየገዙ እንደሚጠቀሙ አስረድቷል፡፡ በበረህ ወረዳ ግራር ቀበሌ ኗሪና ለሰንዳፋ አካባቢ የእንስሳት መኖ አቅራቢና ወተት አምራች የሆነው አቶ ተሾመ መንግሥቱም፣ በአካባቢው ፋጉሎን ለመኖነት እንደማይጠቀሙ ይናገራል፡፡ እሱም በቀን እስከ 160 ሊትር ወተት ያቀርብ የነበረ ቢሆንም፣ ባለፈው ሳምንት ምንም ተረካቢ አለማግኘቱን ገልጿል፡፡ በወተት ንግዳቸው ላይ እንደዚህ ያለ ኪሳራ ያስከተለው መረጃ ትክክል አለመሆኑ በተደጋጋሚ በመገናኛ ብዙኃን ቢገለጽም፣ ብዙም የተቀየረ ነገር እንደሌለ አምራቾቹ ሪፖርተር ባነጋገራቸው ወቅት ገልጸዋል፡፡

ምርምሩ የተካሄደው ከአዲስ አበባ፣ ከቢሾፍቱ፣ ከሰበታ፣ ከሰንዳፋና ከሱልልታ ከተማ በተወሰዱ የወተት ናሙናዎች ላይ ሲሆን፣ አፍላቶክሲን በወተት ናሙናዎቹ ውስጥ (0.41 ማይክሮ ግራም በሊትር) መገኘት ዜና በኋላ ለወትሮ የወተት ገበያ ግርግር በነበረበት ሰንዳፋ ከተማ፣ ገበያው እረጭ ማለቱን ሪፖርተር በከተማው ተዘዋውሮ ካነጋገራቸው አምራቾች ማረጋገጥ ችሏል፡፡ አምራቾቹ ወጣ የተባለው ምርምር ገበሬውን ክፉኛ የጐዳ፣ በአገር ሀብት ላይም ከፍተኛ አሉታዊ ተፅዕኖ ያሳደረ በመሆኑ ነገሮች ወደነበሩበት ይመለሱ ዘንድ መንግሥትና የሚመለከታቸው ሁሉ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ ጥናቱን በሚመለከት የመንግሥትንና ጥናቱን የሠራው የዓለም አቀፍ የእንስሳት ምርምር ኢንስቲትዩት አስተያየትን፣ እንዲሁም መንግሥት የወሰዳቸውን ዕርምጃዎች በሚመለከት የተጠናቀረው ዘገባ በማኀበራዊ ገጽ ላይ ይመልከቱ፡፡ (በዘገባው ሚሊ ግራም ተብለው የተቀመጡት መለኪያዎች ማይክሮ ግራም ተብለው እንዲነበቡ የዝግጅት ክፍሉ ያሳስባል)   

 

አርሶ አደሩን በመግደል የተጠረጠረው ፖሊስ መሰወሩ ተጠቆመ

‹‹መያዣ አውጥተን እያፈላለግነው ነው›› ፖሊስ

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሰያን ደብር ቀበሌ ገበሬ ማኅበር ውስጥ፣ በአካባቢው የተመደበ ፖሊስ አርሶ አደሩን ገድሎ መሰወሩን የአካባቢው ነዋሪዎች ለሪፖርተር ገለጹ፡፡

ሟች አርሶ አደር ጌቱ ዘውገ የሚባል የ27 ዓመት ወጣት መሆኑን የገለጹት የአካባቢው ነዋሪዎች፣ ለመሞቱ ምክንያቱ የሆነው ጥቅምት 20 ቀን 2008 ዓ.ም. ከአንድ ሌላ አርሶ አደር ጋር በተፈጠረ አለመግባባት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የተጋጩበት ምክንያት ባይታወቅም ሟች አቶ ጌቱ ከአንድ የአካባቢው ሰው ጋር ሲጣላ የአካባቢው ነዋሪዎች ገላግለዋቸው ወደየቤታቸው የሄዱ ቢሆንም፣ በአካባቢው ግጭት እንደነበር ሪፖርት የደረሰው ተጠርጣሪ ምክትል ሳጅን ግርማ ብርሃኑ፣ ወደ  ሟች ቤት መምጣቱን ነዋሪዎቹ ገልጸዋል፡፡ ተጠርጣሪው ምክትል ሳጅን ግርማ ሟችን ይጠራና ወደ ፖሊስ ጣቢያ ይዞት ለመሄድ በመነጋገር ላይ እያሉ ሌሎች ሁለት ፖሊሶች ይደርሳሉ፡፡ አንዱ ፖሊስ ሟች ላይ ድብደባ እየፈጸመበት እያለ፣ ምክትል ሳጅኑ በያዘው ክላሽኒኮቭ ጠመንጃ ተኩሶ እንደገደለው የአካባቢው ነዋሪዎች አስረድተዋል፡፡

በወቅቱ በተፈጠረው ግርግር ተጠርጣሪውን ማንም ሊይዘው እንዳልቻለና ወደ ላይ እየተኮሰ ከአካባቢው መሰወሩን የገለጹት ነዋሪዎቹ፣ በመተባበር በሟች ላይ ድብደባ የፈጸመበት ሌላው ፖሊስ መያዝና በሕግ መጠየቅ ሲገባው፣ ከአካባቢው ዞር ተደርጎ ሌላ ቀበሌ ገበሬ ማኅበር መመደቡ የአካባቢውን ነዋሪዎች እንዳስቆጣ ተናግረዋል፡፡ ሟች በቅርቡ ትዳር የያዘ መሆኑንና ቤተሰቡን እንደሚረዳ፣ በአካባቢው ተወዳጅ ወጣት አርሶ አደር እንደነበር የሚናገሩት ነዋሪዎቹ፣ በቤተሰቦቹ ፊት በጠራራ ፀሐይ ገድሎት የተሰወረውን የፖሊስ ባልደረባ የክልሉና የፌዴራል መንግሥት ለሕግ እንዲያቀርቡት ጠይቀዋል፡፡

በአርሶ አደሩ ላይ ተፈጽሟል ስለተባለው የግድያ ወንጀል ማብራርያ እንዲሰጡ ሪፖርተር ያነጋገራቸው በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደነባ ወረዳ ፖሊስ መምርያ ኃላፊ ኢንስፔክተር መስፍን ደጉ ግድያው መፈጸሙን አረጋግጠዋል፡፡ ወንጀሉ እንደተፈጸመና ተጠርጣሪው ምክትል ሳጅን ግርማ ብርሃኑ ግን እንዳልተያዘ የገለጹት የመምርያ ኃላፊው፣ ፖሊስ ምርመራውን ጨርሶ መያዣ በማውጣት ተጠርጣሪውን ለመያዝ እየሠራ መሆኑንና ከኅብረተሰቡ ጋር ተባብረው በቅርቡ በቁጥጥር ሥር እንደሚያውሉት ተናግረዋል፡፡

ግድያው የተፈጸመው በሁለት ግለሰቦች መካከል በተነሳ ፀብ ምክንያት መሆኑን በተደረገው ምርመራ መረጋገጡን የገለጹት ኢንስፔክተሩ፣ ሟች ለሕግ አልገዛም በማለት በፖሊሶች ላይ ዕርምጃ ሊወስድ ሲል ግድያው ሊፈጸም እንደቻለ መረጃ ማግኘታቸውንም ጠቁመዋል፡፡

የአካባቢው ፖሊስና ነዋሪዎች ተስማምተውና ተከባብረው እንደሚኖሩ የገለጹት የመምርያ ኃላፊው፣ አንዳንድ ጊዜ ሳይታሰብ ወንጀል የሚፈጸም በመሆኑ ፈጻሚውን በሕግ ፊት ማቅረብ ግድ ስለሆነ፣ የተቻለውን ሁሉ በማድረግ ተጠርጣሪውን ይዞ ለማቅረብ አስፈላጊው ጥረት እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ 

 

በ50 ሺሕ ብር ዋስ ይፈቱ የተባሉት መምህር ግርማ ይግባኝ ተጠየቀባቸው

በተጠረጠሩበት ሐሰተኛ ሰነድ መጠቀም ወንጀል ተጨማሪ ጊዜ ተጠየቀባቸው

የእሳቸው ተከታይና የሚሏቸውን ነገር ሁሉ ያደርጉ የነበሩን ግለሰብ ቤት በማሸጥና ገንዘቡንም እንዲፀለይበት በማለት ወስደዋል ተብለው ተጠርጥረው የታሰሩት መምህር ግርማ ወንድሙ፣ በ50,000 ብር ዋስ እንዲለቀቁ ፍርድ ቤት በሰጠው ትዕዛዝ ላይ ፖሊስ ይግባኝ ማለቱ ታወቀ፡፡ 

የፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ወንጀል ችሎት ለመምህር ግርማ የፈቀደውን የ50,000 ብር ዋስትና የተቃወመው ፖሊስ፣ ቅሬታውን ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ወንጀል ችሎት አቅርቧል፡፡ ፖሊስ ባቀረበው መከራከሪያ ነጥብ ላይ ብይን ለመስጠት ፍርድ ቤቱ ለኅዳር 13 ቀን 2008 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ 

ተጠርጣሪው ሐሰተኛ ሰነድ መጠቀማቸውን ገልጾ ፖሊስ ባቀረበው ክስ ምክንያት መምህር ግርማ ኅዳር 3 ቀን 2008 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ቀርበው የነበረ ሲሆን፣ እሳቸው ከቤተክህነት እንደተሰጣቸው የገለጹት ሰነድ በፎረንሲክ ተመርምሮ ሐሰተኛ መሆኑን እንዳረጋገጠ ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡ ሌላ ተጨማሪ የሚመረመር ሰነድ እንዳለውና ተጨማሪ ሰነድ ሰጥተዋል የተባሉት የቤተ ክርስቲያን አባት በአገር ውስጥ አለመኖራቸውን በማስታወቅ፣ ተጨማሪ 14 ቀናት እንዲሰጠው ጠይቋል፡፡ 

የመምህር ግርማ ጠበቆች ፖሊስ ያቀረበውን ማመልከቻና ተጨማሪ ቀናት በመቃወም፣ ደንበኛቸው በዋስ ተለቀው ጉዳያቸውን በውጭ ሆነው እንዲከታተሉ ጠይቀዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ የጠበቆቹን ማመልከቻ በማለፍ የሰባት ቀናት ተጨማሪ ጊዜ ለፖሊስ ፈቅዷል፡፡ 

 

“ሃብት ያለው ሰው አይታሰርም። ተፈርዶባቸው እስር ቤት ያሉ ባለ ሃብት መንገድ ላይ ሲሄዱ ሌላ ሰው ገጭተው ሌላ ክስ ተመሠረተባቸው። አቃቤ ሕግ ምሥክር ማስፈራራት የሃሰት መረጃ ማስጠናት። በጥናቱ ካገኘናቸው ውስጥ ናቸው።” አቶ ተካ ገብረ የሱስ፤ የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዲሬክተር።

ከልክ ያለፈ ላብ (ሃይፐርሃይድሮሲስ) (በዶ/ር ሆነሊያት ኤፍሬም ቱፈር) ከልክ ያለፈ ላብ ከእጅ፣ከእግር፣ከብብት እና ፊት አካባቢ በመመንጨት ሙሉ ሰውነትን በላብ እንዲዘፈቅ ያደርጋል። በዚህ ችግር የሚጠቁ ሰዎች መጠነኛ የሚባል የእለት ተእለት እንቅስቃሴ ለማድረግ እስኪቸገሩ ድረስ በከባድ ላብ ይዘፈቃሉ። ከዚያም ባለፈ ለማህበራዊ ችግሮችና …

ከልክ ያለፈ ላብ (ሃይፐርሃይድሮሲስ) (በዶ/ር ሆነሊያት ኤፍሬም ቱፈር) Read more »

በደርግ ‹‹ክፉ ቀን›› ለሰብዐዊ ዕርዳታ የሚውል እህል አሜሪካና ራሺያ ይልኩልን ነበር፡፡ በኢቲቪ፣ በሬዲዮና አዲስ ዘመን… መጠኑ የሚነገረን የአሜሪካው በሜትሪክ ቶን ሲሆን የራሺያው በኩንታል ነበር፡፡የአሜሪካውን አሳንሶ፣ የራሺያውን አብዝቶ የማሳየት ፕሮፖጋንዳ፡፡አሁንም ከሰሞኑ ከቻይና 163 ሚሊዮን ብር ፣ ከአሜሪካ 97 ሚሊዮን ዶላር፣ ከተባበሩት …

በዚህ ‹‹ክፉ ቀን›› ታሪክ ራሱን በመድገም የደርግን ዘመን አስታወሰኝ Read more »

Minilik Salsawi – አንድ – ለፓሪሱ ጥቃት አስለቃሽ የተቀጠሩ ይመስል የወያኔ ካድሬዎች ሙሾውን ተያይዘውታል::የኢትዮጵያ ረሃብ ሕዝብን እየገደለ እያሳደደ ባለበት በዚህ አደገኛ ጊዜ ላይ የድርጊት መረሃ ግብሮች ሁሉ ሕዝብን ለማዳን መረባረብ በሚጠበቅበት ወቅት የፓሪሱን ጥቃት እንደ አጀንዳ ይዞ ማራገብ አገዛዙ ምን …

ለራስዋ ያላወቀች ለቅዱስ ገብርኤል መድሃኒት ጠየቀች::የፓሪሱን ጥቃት የረሃቡን ጉድ ለመሸፈን አጀንዳ ማድረግ ዝቅጠት ነው:: Read more »

በትላንትናው እለት በገለፅነው መሰረት በሀገራችን በተከሰተው ቀውስ (ድርቅ/ርሃብ) ዙሪያ ‹‹ያገባኛል!›› የምንል ዜጎች በበጎፈቃደኝነት ኮሚቴ አቋቁመናል፡፡ ዛሬ ባደረግነው አስቸኳይ ስብሰባ የተገኙ 13 ሰዎች የሚከተለውን ውሳኔ አሳልፈዋል፡፡ 1. ሁላችንም እንደዜጋ ከራሳችን በመጀመር ሚናችንን መወጣት ይኖርብናል፡፡ በዚህም መሰረት ከእያንዳንዳችን በነፍስ ወከፍ በትንሹ ከ100 …

‹‹ቤዛ እንሁን!›› ወገን ተርቧል፤ እንድረስለት! የበጎ ፈቃደኝነት ኮሚቴ ተቋቋመ:: Read more »

ቃር የምንለው ወይንም በህክምና አጠራሩ ሃርትበርን (Heartburn) በመባል የሚታወቀው የህመም አይነት ሲሆን አብዛኞችን የሚያጠቃ እና እጅግ የተለመደም ችግር ነው። በደረት አካባቢ የማቃጠል ስሜት መሰማት በአብዛኛው ከምግብ በኃላ እና እንቅልፍ ስንተኛ የሚብስ ነው። ይህም የሚከሰተው የጨጓራ ውስጥ አሲድ ወደ ላይኛው የምግብ …

ቃር (Heartburn) (በዶ/ር ሆነሊያት ኤፍሬም ቱፈር) Read more »

“ሬድ ቡል”ን የመሳሰሉ ሃይል ሰጪ መጠጦች በተለይ ከአልኮል መጠጥ ጋር ተደባልቀው ሲጠጡ የጤና ችግር ሊያስከትሉ እንደሚችል የዓለም ጤና ድርጅት ተመራማሪዎች አስጠነቀቁ፡፡በአውሮፓ የተደረገ ጥናት እንዳረጋገጠው፣ ከ70 በመቶ በላይ የሚሆኑ እድሜያቸው ከ18-29 ዓመት የሚደርሱ ወጣቶች፣ እንደ “ሬድ ቡል” ያሉ ሃይል ሰጪ መጠጦችን …

ሃይል ሰጪ መጠጦች በተለይ ከአልኮል መጠጥ ጋር ተደባልቀው ሲጠጡ የጤና ችግር ያስከትላሉ ተባለ Read more »

    በቅርቡ የተቋቋመው የኩላሊት እጥበት ማዕከል፣ ለኩላሊት ሕመምተኞች የእጥበት ህክምና ለመስጠት በኤስ ኤም ኤስ እያሰባሰበ ያለው ገንዘብ፣ “ለታለመለት ዓላማ አልዋለም”፤ መባሉ እያወዛገበ ነው፡፡ ባለፈው አርብ ጥቅምት 26 ሬዲዮ ፋና ባስተላለፈው ዘገባ፣ ማዕከሉ ለኩላሊት ህመምተኞች የእጥበት አገልግሎት ለመስጠት ከህዝብ ከሚሰበሰበው የበጐ አድራጐት ገቢ፣ ኮሚሽን እየከፈለ መሆኑን ጠቅሶ ድርጊቱ ህገወጥ ነው ብሏል፡፡ 524 ሺህ ብር ኮሚሽን ተቀብያለሁ ያሉ ግለሰብም በዋቢነት ማቅረቧ ታውቋል፡፡ የማዕከሉ የቦርድ አባልና የገቢ አሰባሳቢ ኦፊሰር ደራሲና ዳይሬክተር አንተነህ ሃይሌ በበኩሉ፤ “የኩላሊት እጥበት ማዕከሉ በSMS ከህዝብ ከሰበሰበው 7 ሚሊዮን ብር ውስጥ 4 ሚሊዮን ብር ተመዝብሯል የሚል ዘገባ በሬዲዮ ፋና መሰራጨቱን ጠቁሞ፤ 7 ሚ. ብር የሚለውን ከየት አምጥቶ እንዳወራ አናውቅም ብሏል፡፡ “የፋና ሃሰተኛ ዘገባ የህዝቡን በጐነት የሚረብሽና የህሙማንን ህልም የሚያጨልም ነው፤” ሲልም ተችቷል፡፡“የፋና ዘገባ እውነትን ማዕከል ያደረገ አይደለም፤” ያሉት የማዕከሉ የቦርድ ሰብሳቢ ኢንጂነር ሳሙኤል ይርጋ፤ “ለሚሠራው ሥራ የሚከፈል ኮሚሽን የለም” ሲሉ አስተባብለዋል፡፡ማዕከሉ ከገራዶ ፊልም ፕሮዳክሽን ጋር ስለፈጸመው የሥራ ውል የተጠየቁት ሰብሳቢው፣ “ማዕከሉ ሥራ ሲጀምር ምንም ገንዘብና የሰው ሃይል ስላልነበረው የኤስኤምኤሱን አጠቃላይ ሥራ እንዲያከናውንና ለእድለኞች ሽልማት ከገቢው ከ10 በመቶ ያልበለጠ ሒሳብ እንዲወራረድለት ውል ፈጽመናል” ብለዋል፡፡ እያንዳንዱም ወጪ በደረሰኝ እንደሚገባና እንደሚወጣ ከቀሪው ጋር የሚያሳይ የባንክ ስቴትመንት እንዳለ ገልፀዋል፡፡ ሬዲዮ ፋና ያለ መረጃ ያሰራጨውን ዜና በተመለከተ፣ ይቅርታ እንዲጠይቀን ደብዳቤ አስገብተናል – ብለዋል ሰብሳቢው፡፡

ፓትርያርኩ ከካቶሊክ ጋር ያለን ሃይማኖታዊ ልዩነት “ጠባብ ነው” ማለታቸው እያነጋገረ ነው

    የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ፣ ከካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ጋር ያለን ልዩነት “ጠባብ ነው” ማለታቸው እያነጋገረ ነው፡፡ፓትርያርኩ ይህን የተናገሩት ባለፈው ሳምንት በዓዲግራት ሀገረ ስብከት ተገኝተው የደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያንን በመረቁበት ወቅት ሲሆን በሥነ ሥርዓቱ ላይ የትግራይ ክልል ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ተስፋ ሥላሴ መገኘታቸውን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ድረ ገጽ ዘግቧል፡፡
ፓትርያርኩ አቡነ ማትያስ፣ “ከካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ጋር  ያለንን ጠባብ የሃይማኖት ልዩነት ጠብቀን፣ በዜግነታችንና በክርስቶስ ልጅነታችን በዋና ዋና የልማት ሥራዎች ዙሪያ በጋራ በመሥራት፣ ለክርስቶስም ለሰው ልጅም ደስታን የሚሰጥ አገልግሎት ማበርከት  ይጠበቅብናል፤” ብለዋል – ድረ ገጹ እንደዘገበው፡፡ይሁንና የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንና የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ያላቸው የእምነትና የሥርዓት አስተምህሮ ልዩነት መሠረታዊ መሆኑን የጠቀሱ አስተያየት ሰጪዎች፣ ፓትርያርኩ ሃይማኖታዊ ልዩነቱ ጠባብ እንደሆነ ተናግረዋል ተብሎ በሰፈረው ዘገባ ግር መሰኘታቸውን ጠቁመዋል፡፡

   በስፔናዊው ሚጌል ሊያንሶ ተፅፎ የተዘጋጀውና ከ60 በላይ በሚሆኑ ዓለም አቀፍ የፊልም ፌስቲቫሎች ላይ ተሳትፎ፣ 10 ሽልማቶችን ያሸነፈው “Crumbs” (ስብርባሪ) የተሰኘው ሳይንሳዊ ልብወለድ ፊልም፤ ትላንት ምሽት በአቤል ሲኒማ ተመረቀ፡፡ ከዓለም ጦርነቶች ፍፃሜ በኋላ ምን ሊፈጠር እንደሚችል በሚያመለክተው በዚህ ፊልም ላይ ዳንኤል ታደሰ (ጋጋኖ) በመሪ ተዋናይነት የተጫወተ ሲሆን ባሳየው የትወና ብቃትም አድናቆት ተችሮታል ተብሏል፡፡ ለትወናው አምስት ሺህ ዩሮ (125ሺ ብር) እንደተከፈለው ጋጋኖ ለአዲስ አድማስ ተናግሯል፡፡ ፊልሙ በአውሮፓና በአሜሪካ በተለያዩ ከተሞች ለእይታ ቀርቦ አድናቆትን ያተረፈ ሲሆን ከ60 በላይ ዓለም አቀፍ ፊልም ፌስቲቫሎች ላይ ተሳትፎ፣ ከ10 በላይ ሽልማቶችን ማግኘቱን የፊልሙ ፕሮዲዩሰር አርቲስት ዮሐንስ ፈለቀ ገልጿል፡፡ “ክረምብስ” ፊልምን፣ ለመስራት 200ሺ ዶላር እንደፈጀ ተናግሯል፡፡   

የአይሲስ ደጋፊዎች በማህበራዊ ድህረገጾች በተለይ በትዊተር የፓሪሱ ጥቃት በመድረሱ ደስታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ::#ParisIsBurning,እና #باريس_تشتعل.,(ሲተረጎም: “Paris Burns”.)በሚሉ ሃሽታጎች በመጠቀም በፓሪስ እና በነዋሪዎቿ ላይ በደረሰው አደጋ የተሰማቸውን ደስታ በመግለጽ ለአይሲስ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል::ሲል ኒውስዊክ ጽፏል:: ዝርዝር ሃተታ እዚህ ይመልከቱት

የፓሪስ ከተማ ፍንዳታዎች አለምን አስቆጥቷል አስደንግጧል::እስካሁን 158 ሰዎች ሞተዋል::በአጥፍቶ ጠፊዎች የቦምብ ጥቃት እና በታጠቁ ሃይሎች የደረሰው ግድያ ፓሪስን አናውጧታታል::የፈረንሳይ ፕሬዚዳት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሲያውጁ የፈረንሳይ ድንበሮች ሙሉ በሙሉ ተዘግተዋል:: በስታድ ደ ፍራንስ ስታዲየም አቅራቢያ በተዘጋጀ የሙዚቃ ኮንሰርት በተፈጸመ ሽብር ነው …

በፈረንሳይ ፓሪስ የአጥፍቶ ጠፊዎች እና የታጣቂዎች ጥቃት ከባድ ጉዳት አደረሰ:: Read more »

መንግስት በስልጤ ዞን እየፈፀመ ያለው የሂጃብ ገፈፈ በመቃወም በዛሬው እለት በሻሸመኔ ከተማ ተቃውሞ ተካሄደ። በዛሬው እለት በነበረው ተቃውሞ የመንግስትን በሃይማኖት ጣልቃ ገብነትና የሂጃብ ገፈፋ ተቃውመዋል። ዝርዝሩን በምሽት ዝግጅታችን ቢቢኤን ይዞ የሚቀርብ ይሆናል። ድምፃችን ይሰማ እየተደረጉ ያሉ የሂጃብ ገፈፋና ብሄራዊ ጭቆናንን …

በስልጤ ዞን እየፈፀመ ያለው የሂጃብ ገፈፈ በመቃወም በዛሬው እለት በሻሸመኔ ከተማ ተቃውሞ ተካሄደ። Read more »

‹‹ርሃቡን ያመጣው የኢህአዴግ የስልጣን ስስት ነው!›› • ‹‹ለመፍትሄው መረባረብ አለብን›› ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ለነገረ ኢትዮጵያ የሰጡት አስተያየት ‹‹የርሃቡ የቅርብ ጊዜ ምክንያቱ የዝናብ እጥረት ነው፡፡ የዝናብ እጥረት ድርቅን እስከተለ፡፡ ርሃቡን ያመጣው ግን የኢህአዴግ የስልጣን ስስት ነው፡፡ የኢህአዴግ የስልጣን ስስት ለረዥም ጊዜ፣ …

‹‹ርሃቡን ያመጣው የኢህአዴግ የስልጣን ስስት ነው!›› ኢ/ር ይልቃል ጌትነት Read more »

አቦ አታድርቁና! ስንቱን ነገር ፈትፍተን አጉርሰናችሁ እንችለዋለን?! ‘ድርቁን ፖለቲሳይዝ አታድርጉት’ ከመባባል በፊት ቁጥር ቅነሳውን ምን አመጣው? ያው ፖለቲሳይዝድ የሆነ ነገር ስለሆነ አይደል? ድርቅ (drought) የዝናብ መቅረት እንጂ የምግብ መጥፋት (famine) አይደለም። በትክክለኛ ትርጓሜው ሲታይም፥ መንግስት ሕዝብን እንዲያገለግል የሚሾም፣ አስተናባሪ እንጂ …

‘ድርቁን ፖለቲሳይዝ አታድርጉት’ ከመባባል በፊት ቁጥር ቅነሳውን ምን አመጣው? Yohanes Molla Read more »

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በያዝነው አመት አጋማሽ 15 ሚሊዮን ህዝብ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልገው በሪፖርቱ አመልክቷል፡፡ መንግስት በበኩሉ 8.2 ሚሊዮን ህዝብ እንደተራበ አምኗል፡፡ ሰሞኑን ቢቢሲ በሰራው ዘገባ በርሃቡ ምክንያት በየቀኑ 2 ህፃናት እየሞቱ እንደሆነ ገልፆአል፡፡ ለተራቡት ዜጎች እርዳታ ባለመድረሱ በርካቶች ወደ …

ለተራቡት ዜጎች እርዳታ ባለመድረሱ በርካቶች ወደ ከተሞች እየተሰደዱ ነው፡፡ Read more »

ኀዳር ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ለስድስት ከፍተኛ ጡረተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ለእያንዳንዳቸው በ25 ሚሊየን ብር ወጪ በስጦታ የሚለገሳቸው የመኖሪያ ቤት እየተገነባ መሆኑ ሰሞኑን በመገናኛ ብዙሃን ይፋ ከሆነ በሁዋላ በአዲስ አበባ ከተማ ከፍተኛ የመነጋገሪያ አጀንዳ ሆኗል፡፡ በተለይ በረሃብ ምክንያት ከ 15 ሚሊየን ያላነሱ ወገኖችን ችግር ላይ በወደቁበት፣ በከተሞች አካባቢ ከፍተኛ ኑሮ ውድነትና የስራ …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ነፃነት ዘለቀ

ውድ አንባቢያን ዛሬ ትንሽ ለየት ባለ ሁኔታ የልብ የልባችንን ነው የምንጫወተው። መደባበቅ ብሎ ነገር አይኖርም። ለምኑ ብለን? ለየትኛው ጊዜስ ብለን እንወሻሽ? “በገና ጨዋታ አይቆጡም ጌታ” – መተዛዘብን ለዛሬ እንርሳት።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Ethiopian Electric Power Corporation. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽንጓድ ካፍትሌ ከአርባምንጭ

የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የደርግ ሥርዓት መገርሰሱን በማስመልከት ያስተላለፉትን መልዕክት ሰምቼ ነበር። መልዕክቱ ባጭሩ እንዲህ የሚል ነበር። “የድህነት ዘበኛ የነበረው ሥርዓት ስለተወገደ ከዚህ በኋላ ጦርነታችሁ ከዘበኛው ጋር ሳይሆን ቀጥታ ከጠላቱ (ድህነት) ጋር ነው።” በእርግጥ ደርግ ሥልጣን ላይ በነበረበት ጊዜ ”ሁሉም ነገር ወደ ጦር ግንባር!” እያለ ሕዝቡ በድህነት እንዲማቅቅ አድርጓል። ከዚህ የተነሳ የሥርዓቱ መውደቅ ብዙዎችን በደስታ አስፈንጥዟል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ወለላዬ ከስዊድን

አቶ ዘለሌ ፀጋ ስላሴ ዝግጅቱን በንግግር ሲከፍቱቅዳሜ ጥቅምት 20 ቀን 2008 ዓ.ም. (ኦክቶበር 31 ቀን 2015 እ.ኤ.አ.) በስዊድን ዋና ከተማ በስቶክሆልም ለአርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ መርጃ የሚሆን የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ተደረገ። በዝግጅቱ ላይ በርካታ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ተገኝተዋል። በቦታው ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት አቶ አበበ ቦጋለ የውጪ እንቢተኝነት ሊቀመንበር እና አቶ ቸኮል ጌታነህ የንቅናቄው ከፍተኛ አመራር ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ኀዳር ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኢትዮጵያ አየር መንገድ ረዳት አብራሪ የነበረውና በድርጅቱ ውስጥ ያለው ዘረኝነትና አድሎዋዊ አሰራር ስራዬን በነጻነት ለመስራት አላስቻለኝም በሚል ምክንያት ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየርመንገድ የሆነውን ከአዲስ አበባ ተነስቶ በካርቱም በኩል አቋርጦ ወደ ጣሊያን ይበር የነበረን ቦይንግ 767-300 አውሮፕላን በመጥለፍ ስዊዘርላንድ ጄኔቫ ካሰረፈ በሁዋላ ጉዳዩን ሲከታተለው የነበረው ፍርድ ቤት ክሱ …

በአውሮፓ ውስጥ ኤርትራዊ ስደተኞች ነን ብለው ከተመዘገቡ ውስጥ እስከ 40 በመቶ የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን ናቸው ተባለ:: በኢትዮጵያ የኦስትሪያ አምባሳደር አንድሬስ ሜላን እንደተናገሩት ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ሳኡድ አረቢያን ደቡብ አፍሪካን እና አውሮፓን አጥለቅልቀውታል::አውሮፓ ውስጥ በተደረገ ማጣራት ከ30 እስከ 40 ፐርሰንት የሚሆኑት በኤርትራዊነት ስም …

በአውሮፓ ውስጥ ኤርትራዊ ስደተኞች ነን ብለው ከተመዘገቡ ውስጥ እስከ 40 በመቶ የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን ናቸው ተባለ:: Read more »

በሀገራችን ያለው ድርቅ ክብደት ከ1977ጋር የሚመሳሰል እንደሆነ የመንግሰት ሹም ከሸገር ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ምልልስ አረጋግጠዋል፡፡ ልዩነቱ ግን አሁን መንግሰት ይህን ለመቋቋም የሚያስችል አቅም አለን የሚልው ጉዳይ ነው፡፡ ይህ አቅም ግን መሬት ላይ ወርዶ ስናየ ወኔ ብቻ ይመስላል፡፡ ከፕሮፓጋንዳ ያለፈ የፈረንጆቹን ደጅ እንዳይጠኑ የሚያደርጋቸው አይደለም፡፡ “ደርግ” በ1977 የነበረፈውን ድርቅ ለዓለም ይፋ አድርጎ የነበረ ሲሆን የዚያን ጊዜ […]

The post ፕሮፓጋንዳው ስብዓዊነት ይኑረው!!! ሰው እየሞተ ነው!! ቁጥሩን ቤቱ ይቁጠረው!!! ግርማ ሰይፉ appeared first on ሳተናው .

ጥቅምት ፴ (ሠላሳ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከቅማንት ብሄረሰብ ጥያቄ ጋር በተያያዘ በአርሶ አደሩና በክልሉ ልዩ ሃይል መካከል ከማውራ 15 ኪሜ ርቃ በምትገኘዋ ሮቢት አካባቢ እንዲሁም በላይ አርማጭሆ ዋና ከተማ ትክል ድንጋይ ከፍተኛ ውጥረት ነግሶአል። እስከትናንት ድረስ በአርሰዶ አደሩና በልዩ ሃይል መካከል በተደረገ የተኩስ ለውጥጥ ከ100 በላይ የልዩ ሃይል አባላት ሲገደሉ፣ ከ36 ያላነሱ ንጹሃን …

ጥቅምት ፴ (ሠላሳ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአማራ ክልል ምስራቃዊ አካባቢዎች በዝናብ እጥረት ለረሃብ የተጋለጡ አርሶአደሮች በዚህ ችግር ላይ እያለን በአካባቢው አመራሮች ግብር እንድንከፍል በመገደዳችን ከፍተኛ ችግር ላይ ነን በማለት ተናገሩ፡፡ በድርቁ የተጎዱት አካባቢ የሚኖሩ የመንግስት ሠራተኞች በተለይ ለኢሳት ሲናገሩ ‹‹ የዝናቡ እጥረት እንዳለ ሆኖ መንግስት ለአርሶ አደሮች ግብአት አላቀረበም፡፡አርሶ አደሩ በዚህ ዓመት የሚቀምሰው …

ጥቅምት ፴ (ሠላሳ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ኦሞ ዞን በጂንካ ከተማ አርኪሻ ቀበሌ ኬላ መንደር ነዋሪዎች ቤቶቻቸዉ በዶዘር እንዲፈርስ በመደረጉ ለጎዳና ተዳዳሪነት መዳረጋቸዉንና በእሪታና ለቅሶ መንገድ በመዝጋት ጥቅምት 25፣ 2008 ከሰዓት በኃላ በማሰማታቸዉ ልዩ ኃይልና ፖሊስ ለመበተን ሲሞክሩ ቦታ እየቀያየሩ ተቃውሞአቸውን እስከ ምሽት ሲያሰሙ ቆይተዋል። ጥቅምት 27ትም እንዲሁ ቤት ማፍረሱም ተቃዉሞዉም ቀጥሎ የዋለ …

ኀዳር ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ዛሬ ህዳር 2፣ 2008 ዓም ከጎንደር ወደ መተማ ሲጓዙ ከነበሩ ኦራል መኪኖች መካከል አንደኛው ግንድ መጣያ ቀበሌ ልዩ ስሙ ባለእግዚብሄር ቦታ ላይ ሲደርስ ባጋጠመው የቴክኒክ መበላሸት የተነሳ በመገልበጡ በሸራ ተሸፍነው ሲጓዝ ከነበሩት ወታደሮች መካካል 20 የሚሆኑት ወዲያውኑ ሲሞቱ፣ በርካታ ቁጥር ያላቸው ወታደሮች ቆስለው ወደ ጎንደር ሆስታል …

ኀዳር ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በደቡብ ክልል ሰገን ዞን ኮንሶ ወረዳ የሚገኙ ነዋሪዎች በዞን ደረጃ ራሳቸውን ለማስተዳደር እንዲፈቅድላቸው ጥያቄ በማቅረባቸው ብቻ የብሔረሰቡን አባላት ማሳደድ፣ ማሰር፣ መደብደብ ዘመቻው የቀጠለ ሲሆን፣በአካባቢው ያለው ውጥረት ተባብሷል፡፡ የደቡብ ክልል መንግስት የኮንሶን ጥያቄ በአግባቡ ከመመለስ ይልቅ ጥያቄውን በኃይል ወደማፈን በመሸጋገሩ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ብቻ ከጉዳዩ ጋር እጃቸው …

በማታለል ወንጀል የተጠረጠሩት መምህር ግርማ ዋስትና ቢፈቀድላቸውም አልተፈቱም

በየካ ክፍለ ከተማ ኮተቤ በተለምዶ ወሰን ግሮሰሪ በመባል በሚታወቀው አካባቢ፣ የሚኖሩ ግለሰብን መኖሪያ ቤት በማሸጥና ገንዘባቸውንም ‹‹ፀሎት ይደረግበት›› በማለት አታለው ወስደዋል ተብለው ተጠርጥረው የታሰሩት [መምህር] ግርማ

ወንድሙ፣ ጥቅምት 30 ቀን 2008 ዓ.ም. በ50 ሺሕ ብር እንዲፈቱ የተፈቀደላቸው ቢሆንም፣ በተጠረጠሩበት ሌላ ወንጀል አልተፈቱም፡፡ 

ግለሰቡን በቁጥጥር ሥር አድርጐ በመመርመር ላይ የሚገኘው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን መርማሪ ቡድን፣ ጥቅምት 25 ቀን 2008 ዓ.ም. ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ወንጀል ችሎት ባቀረበው የምርመራ ሥራው፣ ተጠርጣሪው ፈቃድ ማግኘት ከሚገባቸው ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን (ቤተ ክህነት) ፈቃድ ሳያገኙ፣ በሐሰተኛ ሰነድ (ፎርጅድ) ሲገለገሉ እንደነበር አስረድቷል፡፡ 

በመሆኑም ቀሪ ምርመራ እንደሚቀረው ገልጾ፣ ከጠየቀው 14 ቀናት ተጨማሪ ጊዜ ፍርድ ቤቱ ሰባት ቀናትን ፈቅዶለታል፡፡ በመሆኑም [መምህር] ግርማ፣ ከቤት ሽያጭና ከሲም ካርድ ጋር በተያያዘ በቀረበባቸው ወንጀል በ50 ሺሕ ብር ዋስትና እንዲለቀቁ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ቢሰጥም፣ በሐሰተኛ ሰነድ የተጠየቀባቸው የሰባት ቀናት ጊዜ የሚያልቀው ኅዳር 2 ቀን 2008 ዓ.ም. በመሆኑ በማረፊያ ቤት ለመቆየት ተገደዋል፡፡ 

 

ላለፈዉ ስድስት ወራት የህዳሴ ግድብ በመባል የሚታወቀዉ እንዲያጠኑ የፈረንሣዩ «ቢአርኤል» እና የኔዝርላንዱ «ዴልታሬስ» የአማካሪ ኩባኒያዎች መሃል የተፈጠረዉን ኣለመግባባት ካልተፈታ ከሌሎች አመራጮች ዳግም ጨረታ ማዉጣት እንደሚጠበቅባቸዉ በዉሃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር ከፍተኛ ባለሙያ ለዶቼ ቬሌ ተናግሮዋል።

ኀዳር ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በከተማው ከሚገኙና በአብዛኛው የገዢው ፓርቲ ዋነኛ ደጋፊ ባለሃብቶች ተብለው ከሚታወቁት መካከል 14 ቱ በአራጣ ማበደር ወንጀል ተከሰው ከሶስት ቀናት በፊት ታስረዋል። ከተያዙት ባለሃብቶች መካከል አቶ ስማቸው፣ አቶ ዘገየ መላኩ፣ ዶ/ር በቀለ፣ ሞላ ጌታሁን፣ አውዱ፣ ኪዳኔ ካህሳይ፣ አበበ ደመቀ፣ አቶ እስራ፣ ፖለስ ጌታው አበሬ፣ እንዲሁም አቶ ካሳሁን …

በርሃብ ለተጠቁት ዘመቻ ሊደረግ ነው በርሃብ ለተጠቁት ኢትዮጵያውያን ለሁለት ቀን የሚቆይ የማህበራዊ ድረ ገፅ ዘመቻ ሊደረግ ነው፡፡ ዘመቻው አርብ ህዳር 3/2008፣ እና ቅዳሜ ህዳር 4/2008 እንደሚደረግም ታውቋል፡፡ ዘመቻውም በእንግሊዘኛ ‪#‎EthiopiaFamine‬ እንዲሁም በአማርኛ ‪#‎ክፉ_ቀን‬ በሚል መለያ (ሀሽ ታግ) ይደረጋል፡፡ በመጀመሪያው ቀን …

በርሃብ ለተጠቁት ኢትዮጵያውያን ለሁለት ቀን የሚቆይ የማህበራዊ ድረ ገፅ ዘመቻ ሊደረግ ነው፡፡ Read more »

በማህበር ተደራጅተው፣ በራሳቸው ቤት የሰሯቸውና የብረታብረት፣ የእንጨት ስራ፣ ጋራዥ፣ ቁርስና ሻሂ፣ የተለያዩ ሸቀጦች የሚሰራባቸው ቤቶች በሃይል እየፈረሱ ነው። በነዚህ ቤቶች ሲሰሩ የነበሩ ወጣቶችና ቤተሰቦች ያለ ካሳ፣ ያለ ቅያሪ መስርያ ቦታ እንዲያፈርሱ እየተገደዱ ነው። ቤታቸው የፈረሰባቸው ወጣቶች ስራ ኣጥተው ለስደት እንዲሄዱ …

በእንቅርት ላይ ጀሮ ደገፍ : በማይጨው ከተማ ከ105 በላይ ቤቶች ለከተማ ውበት በሚል ሰበብ እየፈረሱ ነው። Read more »

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሐዋሳ ቅርንጫፍ የደንበኞች አገልግሎት ሥራ አስኪያጅና የደንበኞች አገልግሎት መኮንን፣ በሥልጣን ያላግባብ የመገልገል የሙስና ወንጀል ክስ ጥቅምት 29 ቀን 2007 ዓ.ም. ተመሠረተባቸው፡፡ 

የፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ዓቃቤ ሕግ ክስ የመሠረተባቸው ሶስና ሀዲስ ገበየሁ (የደንበኞች አገልግሎት መኮንን)፣ አቶ ጌታቸው ዋቅሹም (የደንበኞች አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ ናቸው፡፡ በተጨማሪም በደቡብ ክልል መንግሥት ኦዲት ቢሮ የመዝገብ ቤት ሠራተኛ አቶ ፀጋዬ ግርማ ሲሆኑ፣ ክሱ የቀረበው ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት ነው፡፡

ተጠርጣሪዎቹ በጥቅም ተመሳጥረውና ሥልጣናቸውን ያላግባብ በመገልገል፣ የባንኩ ባልደረባ የሆኑት ወ/ሮ አለፊያ ከድር ለቤት መግዢያ ባንኩ የፈቀደላቸውን 320,000 ብር ለግል ጥቅም ማዋላቸውን የዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡ 

ተከሳሾቹ ባንኩ ለግለሰቧ የፈቀደውን ገንዘብ ቤቱን የሸጡላቸው ወ/ሮ ፅጌረዳ ሰይፉ አካውንት ማስገባት ሲገባቸው፣ በሁለተኛ ተከሳሽ ፀጋዬ ግርማ አካውንት ውስጥ በማስገባትና በተለያዩ ጊዜያት እያወጡ መጠቀማቸውም በክሱ ተገልጿል፡፡

የደንበኞች አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ አቶ ጌታቸው ዋቅሹም፣ ገንዘቡ ለወ/ሮ ፅጌረዳ ሰይፉ ገቢ መደረጉን ሳያረጋግጡ በማፅደቃቸው፣ ከባድ ጉዳት በማድረስና ኃላፊነታቸውን ባለመወጣት ወንጀል ተከሰዋል፡፡ አቶ ጌታቸው የተጠረጠሩበት ወንጀል ዋስትና እንደማያስከለክል ተገልጾ፣ በ3,000 ብር ዋስ እንዲለቀቁ ፍርድ ቤቱ በማዘዝ ለኅዳር 21 ቀን 2008 ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡