“ክ/ከተማው ቦታው አይነካባችኹም ብሎ አዘናግቶናል፤ ለሌላ ዓላማ መዋሉ አሳዝኖናል” /ምእመናን/ “ለሌላ ዓላማ ሳይውል አጥቢያዎቹ በዕቅዳቸው እንዲያለሙት አመራር ይሰጥላቸው” /ቅ/ሲኖዶስ/ “ልማቱ በዓለ ጥምቀቱን ታሳቢ ያደረገ ነው፤ ቦታው በታቦት ማደርያነቱ ይቀጥላል” /ክ/ከተማው/ (አዲስ አድማስ፤ ናፍቆት ዮሴፍ፤ ቅዳሜ ጥቅምት ፳፯ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም.) ላለፉት 52 ዓመታት በበዓለ ጥምቀት ማክበርያነት እና በታቦት ማደርያነት ሲያገለግል የነበረው የባሕረ ጥምቀት ቦታ ለሌላ …

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝን እንዳንጠይቅ ተከለከልን ሲሉ ቤተሰቦቹ አመለከቱ

የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ችግራቸውን እንዲፈታላቸው ጠይቀዋል

       በእስር ላይ የሚገኘውን ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ላለፉት 20 ቀናት መጠየቅና ማግኘት እንዳልቻሉ የጠቆሙት ቤተሰቦቹ፤ የጤንነቱ ጉዳይ እንዳሳሰባቸው በመግለፅ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ለችግራቸው እልባት እንዲሰጣቸው በደብዳቤ አመለከቱ፡፡
የጋዜጠኛው ቤተሰቦች በደብዳቤያቸው እንደገለፁት፤ ከጥቅምት 7 ቀን 2008 ዓ.ም ጀምሮ  ምክንያቱን ባላወቁት ሁኔታ ተመስገን በሚገኝበት ዝዋይ ማረሚያ ቤት ቤተሰብም ሆነ ወዳጅ ዘመድ እንዳይጠይቀው መከልከሉ መላው ቤተሰቡን ስጋት ላይ ጥሎታል፡፡
የጤናው ጉዳይ በእጅጉ ያሳስበናል ያሉት ቤተሰቦቹ፤ በተለይ ቀደም ብሎ የነበረበት ህመም ተባብሶ የግራ ጆሮው መስማት እስከመቸገር እንዳደረሰውና የወገብ ህመሙ እረፍት ነስቶ አላስተኛ እያለው መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
በተደጋጋሚ ወደ ዝዋይ ማረሚያ ቤት ቢመላለስም ተመስገንን ማግኘት እንዳልቻለ የሚናገረው የተመስገን ታናሽ ወንድም ታሪኩ ደሳለኝ፤ የማረሚያ ቤቱ ጥበቃዎች “ለምን መጠየቅ ተከለከልን?” ስንላቸው፤ “የበላይ ትዕዛዝ ነው” ይሉናል፤ ብሏል፡፡ በዚህም የተነሳ ተመስገንን ላለፉት 20 ቀናት እንዳላዩትና ቤተሰቡንም ለጭንቀት እንደዳረገ ይገልፃል፡፡
“የቤተሰባችን አባል በሆነው ተመስገን ላይ በተለየ ሁኔታ ተደጋጋሚ የህግ ጥሰት እየደረሰ ነው” ያሉት ቤተሰቦቹ፤ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ከዚህ ቀደም እንዳደረገው ጣልቃ በመግባት ችግሩን እንዲፈታላቸው ጠይቀዋል፡፡
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ቀድሞ ይሠራበት በነበረው “ፍትህ” ጋዜጣ ላይ በወጡ ጽሑፎች ምክንያት፣ ተከሶ የ3 አመት እስራት ተፈርዶበት፣ ማረሚያ ቤት እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ 

ቴክኖ ሞባይል ላለፉት 3 ወራት አላመረተም

    በሀገሪቱ በተከሰተው የውጭ ምንዛሪ እጥረት የሀገር ውስጥ ኩባንያዎች ምርት ማምረት እስከማቆም የደረሱ ሲሆን በአስመጪና ላኪነት የንግድ ስራ ላይ የተሠማሩ ነጋዴዎችም መቸገራቸውን ገልፀዋል፡፡
ከ900 በላይ ሠራተኞችን ይዞ ተንቀሳቃሽ ስልኮችን በማምረት ሥራ ላይ የተሠማራው የቴክኖ ሞባይል አምራቹ ዊጉዩ ኩባንያ፤ በውጭ ምንዛሪ እጥረቱ የተነሳ ላለፉት 3 ወራት ምርት ማምረት ማቆሙን አስታውቋል፡፡
ኩባንያው የውጭ ምንዛሪ ከባንክ ቢጠይቅም “ትንሽ ጊዜ ታገሱ” የሚል መልስ እንደተሰጠው የቴክኖ የአስተዳደር ክፍል ሃላፊ አቶ ገነነ አዘነ ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡
ሃላፊው እንዳሉት፤ ኩባንያው ጠንካራ የገንዘብ አቅም ያለው በመሆኑ ለኪሣራ ባይዳረግም ስራ ባቆመባቸው ወራት በመቶ ሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ አጥቷል፡፡
“ችግራችንን ለመንግስት አሳውቀናል፤  በቅርብ ጊዜ ችግሩ ይፈታል የሚል ተስፋ አለን” ብለዋል፤ ሃላፊው፡፡
ኩባንያው በቀን ከ10ሺህ በላይ ተንቀሳቃሽ ስልኮችን አምርቶ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገራት ያቀርብ እንደነበርና በአሁን ሰአት በምንዛሪ እጥረቱ የተነሣ ሙሉ ለሙሉ ምርት ማቆሙን ጠቁመው፣ ያጋጠማቸው ችግር ጠንከር ያለ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
በተመሳሳይ በጉዳዩ ላይ ያነጋገርናቸው በአስመጪነትና ላኪነት ስራ ላይ የተሠማሩ ነጋዴ በበኩላቸው፤ የዶላር እጥረቱ ከአንድ አመት በላይ እንደሆነው፤ ነገር ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እጥረቱ እየተባባሰ እንደመጣና በንግድ ስራቸው ላይ ከፍተኛ ፈተና እንደጋረጠባቸው ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡   
“ከ5ሺ ዶላር ጀምሮ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት ለባንክ ፕሮፎርማ ካስገባን በኋላ እድል ከቀናን ከ3 እና 4 ወር በኋላ ነው የምናገኘው” የሚሉት ባለሃብቱ፤ በችግሩ የተነሳ ሠራተኛ በትነው ስራ ፈተው እስከመቀመጥ መድረሣቸውን ገልፀዋል፡፡
የብረታ ብረት ኢንዱስትሪ ስራ አስኪያጅ የሆኑ ግለሰብም ፋብሪካቸው በውጭ ምንዛሪ እጥረት የተነሳ ከውጭ ጥሬ እቃ ማስገባት መቸገሩን ጠቅሰው ባለፉት 4 ወራት ኢንዱስትሪያቸው ለከፍተኛ ኪሣራ እየተዳረገ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ “መንግስት በተደጋጋሚ ችግሩ በአጭር ጊዜ ይቀረፋል” የሚል ምላሽ ሲሰጠን ቆይቷል ያሉት ስራ አስኪያጁ፤ ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ግን ችግሩ ይበልጥ እየተባባሰ መጥቷል ብለዋል፡፡
በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ውስጥ ችግሩ ካልተቃለለላቸው ሠራተኛ እስከመቀነስ የሚደርስ እርምጃ ሊወስዱ እንደሚችሉ የጠቀሱት ስራ አስኪያጁ፤ በቅርብ የሚያውቋቸው ፋብሪካዎችም ተመሳሳይ እርምጃ መውሰዳቸውን እንደታዘቡ ለአዲስ አድማስ አስረድተዋል፡፡ በአስመጪነትና ላኪነት የንግድ ስራ ላይ የተሠማሩ ሌላው አስተያየት ሰጪ፤ የዶላር እጥረቱ ስራቸውን ሙሉ ለሙሉ እንዳስተጓጐለባቸው ጠቁመው፤ መንግስት በአጭር ጊዜ ውስጥ እልባት ካላበጀለት የስራ ዘርፋቸውን ለመቀየር እንደሚገደዱ ተናግረዋል፡፡
“የምንዛሬ ጥያቄ ስናቀርብ በአሁን ሰአት መንግስት ከውጭ ስንዴ እያስገባ ስለሆነ ትንሽ ታገሱ የሚል ቀጥተኛ ያልሆነ የቃል መልስ እየተሰጠን ነው ብለዋል – ባለሀብቶቹ፡፡
ጉዳዩን በተመለከተ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ሃጂ ኢብሣ ተጠይቀው ሲመልሱ፤ “ይሄ የኛም
ጥያቄ ነው ትክክለኛ ምላሽ የሚገኘው ከብሔራዊ ባንክ ነው” የሚል ምላሽ የሰጡን ሲሆን የብሔራዊ ባንክ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ መስፍን ደምሴ ጋር ደውለን መረጃ ለማግኘት ብንሞክርም በደብዳቤ መጠየቅ እንዳለብን ተገልፆልናል፡፡  

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) ከደቡብ አፍሪካ ደርባን የአይን እማኞችን ጠቅሶ የአሜሪካ ድምጽ እንግሊዘኛው ድህረገጽ እንዳለው ባለፈው ሳምንት ብቻ ስድስት ኢትዮጵያውያን የውጪ ዜጎች ይውጡልን በሚሉ ደቡብ አፍሪካውያን መገደላቸው ታውቋል::ዮናስ ፍቅሩ ይባላል በደርባን ኢትዮጵያዊ ነጋዴ ሲሆን ስድስቱንም ሟጮች ያውቃቸዋል::ሁሉም በ20ዎቹ እድሜ ክልል …

በደቡብ አፍሪካ ስድስት ኢትዮጵያውያን ተገደሉ::ደቡብ አፍሪካውያን ለውጪ ዜጎች ያላቸው ጥላቻቸው አገርሽቶባቸዋል::‪ Read more »

በዚህ ሳምንት በማዕከል የሚደረገው ለውጥ ይፋ ይሆናል

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለክፍላተ ከተማና ለወረዳዎች 1,600 አመራሮችን ሾመ፡፡ ለተሿሚዎቹ ባለፈው ሳምንት ለሦስት ቀናት የቆየ የፖሊሲ ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡ 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሙስናና በብልሹ አሠራር ገምግሞ ካሰናበታቸው አመራሮች በተጨማሪ፣ ከዲፕሎማ በታች የትምህርት ደረጃ ያላቸውን አመራሮች አንስቷል፡፡ በእነዚህ ተሿሚዎች ምትክ ለአሥሩ ክፍላተ ከተሞችና ለ116 ወረዳዎች የተሾሙት 1,600 አመራሮች ከመጀመሪያ ዲግሪና ከዚያ በላይ የትምህርት ደረጃ ያላቸው ናቸው ተብሏል፡፡ 

እነዚህ ተሿሚዎች አዳዲስና ከዚህ ቀደም በአስተዳደር መሥሪያ ቤቶች በተለያዩ ደረጃዎች ሲያገለግሉ የቆዩ ናቸው፡፡ ለእነዚህ ተሿሚዎች ባለፈው ሳምንት ከማክሰኞ ጥቅምት 16 ቀን 2008 ዓ.ም. ጀምሮ ለሦስት ቀናት የቆየ የፖሊሲ ማብራሪያ እንደተሰጣቸው ታውቋል፡፡ 

የፖሊስ ማብራሪያውን የሰጡት የአዲስ አበባ አቅም ግንባታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ይስሐቅ ግርማይና የአዲስ አበባ ኢሕአዴግ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተወልደ ገብረ ፃድቃን ናቸው፡፡ 

በፖሊሲ ማብራሪያው እነዚህ ተሿሚዎች በከተማው መልካም አስተዳደር ማስፈን፣ የፀረ ሙስና ትግል በብቃት ማካሄድ እንዳለባቸውና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ተግባራዊ ለማድረግ ያቀደውን የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ለማሳካት መሥራት እንደሚኖርባቸው፣ በፖሊሲ ማብራሪያው ማሳሰቢያ እንደተሰጣቸው ከአቅም ግንባታ ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

በተለይ አቶ ይስሐቅ በሥልጠና ወቅት እንደተናገሩት፣ ከዲፕሎማ በታች የትምህርት ደረጃ ያላቸው ከኃላፊነት የተነሱ አመራሮች በቀጣይ ትምህርታቸውን የሚቀጥሉበት አሠራር ይፈጠራል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የተነሱት የቀድሞ አመራሮች በጥቃቅንና በአነስተኛ ማኅበራት ተደራጅተው የተለያዩ ሥራዎችን እንዲያካሂዱ ይደረጋል ሲሉ አቶ ይስሐቅ በሥልጠናው ወቅት መግለጻቸው ታውቋል፡፡ 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በክፍላተ ከተሞችና በወረዳዎች ሲያካሂድ የቆየውን ሹም ሽር በማጠናቀቅ፣ ትኩረቱን በማዕከል ደረጃ በሚያካሂደው ለውጥ ላይ አድርጓል፡፡ በዚህ ሳምንት መጨረሻ በማዕከል ደረጃ የሚያካሂደውን የመዋቅርና የባለሥልጣናት ሹም ሽር ይፋ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡      

 

ጥቅምት 20 ለ21 አጥቢያ 2008 ዓ.ም. የልጃቸውን ጓደኛ በሽጉጥ ተኩሰው በመግደል የተጠረጠሩ ሐኪም፣ ከነመሣሪያቸው በቁጥጥር ሥር ውለው እየተመረመሩ መሆኑ ታወቀ፡፡

በየካ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 13/14 ልዩ ሥፍራው ማጂክ ካርፔት በሚባለው ትምህር ቤት አካባቢ የተገደለው ወጣት ቴዎድሮስ ሲሳይ ይባላል፡፡

ቴዎድሮስ ከጓደኞቹ ጋር በመሆን በዕለቱ የማንቸስተር ዩናይትድ ግጥሚያ ሲመለከቱ አምሽተው በዚያው ሲዝናኑ ያመሻሉ፡፡ ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት አካባቢ ሟች ቴዎድሮስና ጓደኞቹ በግድያ ወደተጠረጠሩት ዶ/ር ተስፋዬ ያዕቆብ (በሰላም ከፍተኛ የጥርስ ክሊኒክ የጥርስ ሐኪም ናቸው ተብሏል) ቤት መሄዳቸውን ሪፖርተር ያነጋገራቸው የዓይን እማኞች ገልጸዋል፡፡

የተጠርጣሪው ልጅ መጠጥ ሲቀምስ የመጮህና የመበጥበጥ ባህሪ እንዳለበት የሚናገሩት የዓይን እማኞች፣ ጓደኞቹን ይዞ ቤቱ እንደደረሰ ባህሪው በመነሳቱ ሟችና ሌሎች ሁለት ጓደኞቹ ከግቢ ወጥተው በመሄድ ላይ እያሉ ተጠርጣሪው ሽጉጥ ይዘው መውጣታቸውን ተናግረዋል፡፡ አንደኛው ወጣት ኳስ ሲያዩ ማምሸታቸውን በማስረዳት ላይ እያለ ተጠርጣሪው ወደ ሟች ተጠግተው በመተኮስ እንደገደሉት የዓይን እማኞች ተናግረዋል፡፡

የሟች ጓደኞች ተጠርጣሪው ሐኪም ሆን ብለው እንደገደሉት የገለጹ ቢሆንም፣ ተጠርጣሪው ግን ባርቆባቸው እንደሆነ ለፍርድ ቤት ማስረዳታቸውን ሪፖርተር ከፖሊስ ያገኘው መረጃ ያስረዳል፡፡

ተጠርጣሪውን ሐኪም በቁጥጥር ሥር አድርጎ በመመርመር ላይ የሚገኘው ፖሊስ፣ ፍርድ ቤት አቅርቦ ጊዜ ቀጠሮ ጠይቆባቸዋል፡፡ ሟች ቴዎድሮስ ሲሳይ በሳሪስ አቦዬ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን ጥቅምት 22 ቀን 2008 ዓ.ም. ከቀኑ ስምንት ሰዓት የቀብር ሥርዓቱ መፈጸሙም ታውቋል፡፡

 

በማላዊ ታስረው የነበሩት ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞች የእስር ጊዜያቸውን ጨርሰውም እዚያው እስር ቤት እስከዛሬ ይገኛሉ። ከነዚህ ውስጥ ወደ 200 የሚሆኑ ወደ ሃገራቸው ሲመለሱ፣ እስካሁን እስር ቤት ስለሚገኙት ፍልሰተኞች ጉዳይ የት ደርሷል?

የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን የመርካቶ ቁጥር ሁለት ቅርንጫፍ ከፍተኛ ኦዲተርና ሦስት ኦፊሰሮች ጉቦ በመቀበል ከባድ የሙስና ወንጀል ጥቅምት 22 ቀን 2008 ዓ.ም. ተከሰሱ፡፡

ተከሳሾቹ የግል ተበዳይ አቶ ዮሐንስ ጥጋቡ የተባሉትን በጨርቃ ጨርቅ ንግድ የተሰማሩ ነጋዴ፣ ‹‹ግዢና ሽያጭ አልተጣጣመም፣ በቆጠራ የሚፈጠረውን ጉድለት ባላንስ እናደርግልዎታለን፤›› በማለት ሁለት ሚሊዮን ብር ጉቦ መጠየቃቸውን፣ የፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የመሠረተው ክስ ያስረዳል፡፡

የጉቦ መቀበል ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ የተመሠረተባቸው የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ሠራተኞች አቶ መሠረት ታደሰ የተባባሪዎች ምልመላና ሥልጠና ኦፊሰር፣ አቶ አበበ ደቦ ቡልቱሜ የኢንቬስትጌሺን ከፍተኛ ኦዲተር፣ አቶ አያና ጋሩማ የኢንተለጀንስ አሰባሰብ ጀማሪ ኦፊሰር፣ አቶ ሀብታሙ ታደሰ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አምቦ ቅርንጫፍ ኦፊሰርና አቶ አብዲሳ ደቦ ቡልቱሜ የባንኩ የሰው ኃይል አስተዳዳር ባለሙያ ናቸው፡፡

ተከሳሾቹ ከላይ የተጠቀሰውን ሁለት ሚሊዮን ብር ጉቦ የጠየቋቸው አቶ ዮሐንስ ባለመስማማታቸው፣ አንደኛ ተከሳሽ አቶ መሠረት አደራዳሪ መስሎ ነጋዴውን በመቅረብ፣ ‹‹ኦዲተሮቹ ብዙ ገንዘብ መቀበል ስለለመዱ አንተ ሁለት መቶ ሺሕ ብር ብትሰጣቸው ምንም አይደለም፤›› ቢላቸውም ተበዳዩ አለመስማማታቸውን ክሱ ይጠቁማል፡፡ 

የነጋዴውን አለመስማማት የተረዱት ተከሳሾች ያላቸውን ዕቃ ብዛት በጽሑፍ እንዲያቀርቡ ጠይቀዋቸው እንደሰጧቸው የሚገልጸው የዓቃቤ ሕግ ክስ፣ በዝርዝር የሰጡት ዕቃ ጉድለት እንደሚያመጣና ጠቅላላ የዕቃውን ብዛት እንዳልሰጧቸው ሲገልጹላቸው፣ ተበዳዩም ካልተቆጠረ እንደማይታወቅ በመግለጽ እንደተከራከሯቸው ክሱ ያስረዳል፡፡

የግል ተበዳዩን በተለያየ መንገድ ስላስጨነቋቸው ግንቦት 15 ቀን 2007 ዓ.ም. ለአንደኛ ተከሳሽ አራት መቶ ሺሕ ብር መስጠታቸውን፣ በድጋሚ በተለያዩ ቀናት በድምሩ ሁለት መቶ ሺሕ ብር መስጠታቸውን ክሱ ይገልጻል፡፡ ተከሳሾቹ ሰነዱን ሲመረምሩ ተበዳዩ 12 ሚሊዮን ብር የሚደርስ ከፍተኛ ዕዳ እንደሚመጣባቸው ማወቃቸውን በመንገር፣ ተበዳዩን በማስጨነቅ አራት መቶ ሺሕ ብር እንዲሰጧቸው ማድረጋቸውን፣ በአጠቃላይ በተለያዩ ቦታዎች በመቅጠር ተከሳሾች ከተበዳይ 1.2 ሚሊዮን ብር መቀበላቸውን ክሱ ያስረዳል፡፡

አቶ መሠረት የተባለው ተከሳሽ ጉቦ በመቀበል ያገኘውን ገንዘብ ለመሰወርና ለመደበቅ፣ አምቦ ከተማ ለሚኖረውና ለአራተኛ ተከሳሽ ወንድሙ አቶ ሀብታሙ አምስት መቶ ሺሕ ብር መስጠቱ በክሱ ተጠቅሷል፡፡ አቶ ሀብታሙ የገንዘቡ አመጣጥ ሕገወጥ መሆኑን እያወቀ፣ አምቦ ከተማ ቀበሌ 02 ውስጥ ስፋቱ 200 ካሬ ሜትር ቦታ በ140 ሺሕ ብር በእናቱ ስም እንደገዛለት፣ 100 ሺሕ ብር ደግሞ ለሌላ ግለሰብ እንዲያስቀምጥለት መስጠቱን ክሱ ያብራራል፡፡ አቶ አበበ ደግሞ ለአቶ አብዲሳ 287,900 ብር ሲሰጠው ገንዘቡን መሬት ውስጥ መቅበሩን፣ አቶ አያና የተባለው ሦስተኛ ተከሳሽ ደግሞ በአምቦ ከተማ 400 ካሬ ሜትር መሬት በ80 ሺሕ ብር በመግዛት በሕገወጥ መንገድ የተገኘን ገንዘብ ሕጋዊ ለማሰመሰል መሥራታቸውን ክሱ ያብራራል፡፡

በአጠቃላይ ተከሳሾቹ ፈጽመዋል በተባለው ጉቦ መቀበል ከባድ የሙስና ወንጀልና በወንጀል የተገኘን ገንዘብ ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብ የሙስና ወንጀል የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ክስ መሥርቶባቸዋል፡፡

     

 

ጥቅምት ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባለፈው ሳምንት መስተዳድሩ የባጃጅ አሽከርካሪዎችን በተመለከተ ያወጣውን ህግ የተቃወሙ አሽከርካሪዎች የ3 ቀናት የስራ ማቆም አድማ ካደረጉ በሁዋላ፣ የተወሰኑ አሽከርካሪዎች ተይዘው ከፍተኛ ድብደባ እንደተፈጸመባቸው ለኢሳት ተናግረዋል። ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ አሽከርከሪዎች እንደሚሉት ፣ ወደ እስር ቤት ከተወሰዱ በሁዋላ ጨማቸውን አውልቀው፣ እጆቻቸው በሲባጎ ገመድ ወደ ሁዋላ ታሰሮ የወስጥ እግራቸውን …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

የተመድ ፀጥታ ጥበቃ ም/ቤት በኤርትራ ላይ በጎርጎሪዮሳዊው 2009 ዓም የጣለውን የጦር መሪያ ማዕቀብ ባለፈው ሳምንት እስከ እስከ ኅዳር፣2016 ዓም አራዘመ። ምክር ቤቱ የወሰደው ይህ ውሳኔ የአውሮጳ ኅብረት በስደተኞች ጎርፍ የገጠመውን ቀውስ የስደተኞች መፍለቂያ ከሆኑት ኤርትራን ከመሳሰሉ ሃገራት ጋር ባንድነት መፍትሔ ለመሻት በያዘበት ወቅት ነው።

ዶክተር አክሊሉ ሀብቴ አቋማቸውን በየጊዜው በመቀያየር፡ የዋሽንገትን ዲሲ ቅድስት ማርያምን ወደ አቡነ ማትያስ ጉያ ለመክተት ከፈለጉት ሰዎች ጋራ መስማማታቸው ሰውን ግራ አጋባው። ሙሉውን ለማንበብ የሚቀጥለውን ሰንሰለት በመጫን ይመልከቱ። የዶክተር አክሊሉ አቋም የዶክተር አክሊሉ ሐብቴ አቋም ሰውን ግራ አጋባው ጥቅምት 15 ቀን 2008 …

የዶክተር አክሊሉ ሐብቴ አቋም ሰውን ግራ አጋባው – ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ Read more »

(በብአዴን/ኢህዴን 35ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ምክንያት በማድረግ የጻፍኩት) የህወሓት ፈተና – ‹‹የታገልኩት፣ የቆሰልኩት፣ የሞትኩትም እኔ ብቻ ነኝ እና የታሪኩ ባለቤትም የትግሉ ውጤት ይበልጥ ተጠቃሚም መኾን ያለብኝ እኔ ነኝ››። ይህ ትርክት ጫፍ ሄዶ ሄዶ ኢዲሞክራሲያዊነት እና ጠባብነት የወለደው ኾኖ ወደ ትምክህተኝነት ሊያድግ ይችላል። ኣብዛኞቹ የዚህ ፈተና ሰለባ የኾኑ የድርጅቱ ኣባሎች ብ1993ቱ የድርጅቱ የውስጥ ትግል የተሸኙ ሲኾን የነሱ ደጋፊዎች እዚሁ የማሕበረሰብ ሚዲያ ላይ የሚያሳዩት ትምክህት አሁንም አለ። ድርጅቱ የዚህ አይነቱ አዝማሚያ ዋናው ፈተናው ሲኾን በቀጣይ የቀሩ ትርፍራፊ የማጽዳት ስራዉን አጠናክሮ የማካሄድ ሓላፊነት አለበት። ይህንን ፈተና ተቋቁሞ እኩልነት በመቀበል የታገልነው በጋራ እና ለጋራ ጥቅም ነው በማለት እዚህ ለበቃ አብዛኛው አባሉን በዚህ አስተሳሰብ ዙሪያ ማሰለፍ ከቻለ ህወሓት ውጤታማ ይኾናል። ብአዴን፦ ያለፉ ስርዓቶች፣ በተለይ የአጼኣዊው የዘውድ ስርዓት፣ ናፍቆት። ይህ በእኩልነት ያለማመን የአንዳንድ የብአዴን ትልቁ ፈተና ነው። የጥንት ታሪኮች የአንድ ብሔር ይኾኑ ዘንድ የመመኘት ከዚህ በዘለለም የትምክህት ሃይሉ የሚያራምደው በአለፉት ስርአቶች የተፈጸሙ በደሎች የመካድ አዝማሚያ። ብአዴን የዚህ አይነቶቹ አባላት ሽኝቶ ብቻ ሳይኾን የተፈጠረው አዲስ የኢትዮጵያዊነት የእኩልነት ትርጉም አልጥም ብሏቸው ወደ ድሮ አመለካከታቸው በመኮብለል ብዙ አባላቶቹ እና አመራሮች ሳይቀር ከመስመሩ ወጥተዋል። አንዳንዶቹ ወደ ትክክለኛ ቀለማቸው በመሄድ ፓርቲዎች አቋቁመው ብአዴንን ዞረው ታግለዉታል። ይህንን ፈተና ተቋቁሞ የጋራ ሀገር ነው ያለን የልፉት ስርዕእቶች ሁላችንንም በድለዋል። እነዚህ ስርዓቶች ላይመለሱ በተባበረ ክንድ ተወግደዋል። ስርዓቶቹን ለማስወገድ የአማራ ብሔር ተወላጆችም አኩሪ ተጋድሎ መፈጸማቸውን ማስተማር […]

አትሌት ከላሊ ንጉሴ አብርሃ

ከላሊ ንጉሴ ይባላል፡፡ የረዥም ርቀት እና ማራቶን ሯጭ ሲሆን አሁን የሚገኘው በስደት ቶሮንቶ፣ ካናዳ ውስጥ ነው፡፡ ኢትዮጵያ በነበረበት ወቅት ከአትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና ተያያዥ ጉዳዮች ጋር ያሳለፈውን የህይወት ተሞክሮ በማስመልከት ከኢትዮጵ ዛሬ ጋር አጭር ቆይታ አድርጓል፤ እንደሚከተለው ይቀርባል፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ማጣርያ ግጥሚያ ለመሳተፍ ወደ ቦትስዋና በቅርብ ለሄዱት 10 የኤርትራ ብሔራዊ የእግር ኳስ ተጫዋቾች የፖለቲካ ጥገኝነት የቦትስዋና መንግስት ፈቅዶላቸው እንደነበር ይታወሳል። ስፖርተኞቹ ጥቅምት 2 ቀን 2008 ዓ.ም. ከቦትስዋና ቡድን ጋር ከተጫወቱ በውኃላ ነው ወደ ሃገራቸው በሚወስዳቸው አውሮፕላን ላይ አንሳፈርም በማለት በቦትስዋና ጥገነት የጠየቁት።

ጥቅምት ፳፭ (ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት የፖሊስ ምንጮች እንደገለጹት አንድ የአየር ጤና የፖሊስ ባልደረባ በህክምና እጦት መሞቱን ተከትሎ፣ የክፍለከተማው ፖሊሶች ስራ በማቆም ተቃውሞአቸውን ከገለጹ በሁዋላ፣ በተለያዩ ክፍለ ከተሞች ፖሊሶች መልቀቂያ አስገብተዋል። የመቀሌ ከተማ ተወላጅ የሆነው ኦፊሰር የማነ በኩላሊት ህመም ሲሰቃይ ከቆዬ በሁዋላ፣ በፖሊስ ሆስፒታል ተገቢውን ህክምና ባለማግኘቱ፣ በግል ለመታከም 16 ሺ …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

በውጭ ከሚኖሩ ዜጎች፣ ወደ ኢትዮጵያና ኬንያ የሚላከው ገንዘብ መጠን እያደገ በመሄድ ላይ መሆኑ ተገለፀ። በዚህ መንገድ ወደ ሁለቱ ሃገራት የሚገባው የውጭ ምንዛሬ ከሰሃራ በስተደቡብ ከሚገኙ የአፍሪቃ ሃገራት ጋር በንፅፅር ሲታይ ከፍተኛ መሆኑን የዓለም ባንክ አስታውቋል።

መንግስት በርሃብ ለተጠቁት ዜጎች እርዳታ እየሰጠ እንዳልሆነ ታወቀ • በርሃብ የተጠቁት ዜጎች ቀያቸውን ለቀው እየተሰደዱ ነው • ‹‹ሰው በርሃብ እያለቀ ነው›› • ‹‹የሚላስ የሚቀመስ የለም፡፡ ቤተሰባችን ፈርሷል›› • ‹‹እርዳታ ቢሰጥማ ከዚህ ድረስ አንመጣም ነበር፡፡›› መንግስት በርሃብ ለተጎዱት ዜጎች እርዳታ እየሰጠ …

መንግስት በርሃብ ለተጠቁት ዜጎች እርዳታ እየሰጠ እንዳልሆነ ታወቀ • በርሃብ የተጠቁት ዜጎች ቀያቸውን ለቀው እየተሰደዱ ነው Read more »

ክብደትን መቀነስ የልብ በሽታን ለማስወገድ ትክክለኛውመንገድ ነው፡፡ ከፍተኛ የሰውነት ክብደት የደም ቅዳ ሴሎቻችን እንዲጠቡ ያደርጋቸዋል፡፡ በዚህ ሳቢያም የኮሌስትሮል ዝቃጮች እንዲሰበሰቡና እጢ እንዲፈጠር ያደርጋል፡፡ ይህ ደግሞ አደገኛ የልብ ህመም እንዲከሰትብዎ ምክንያት ይሆናል፡፡ ክብደትዎን በመቀነስ በተለይም የሆድ አካባቢ ቦርጭዎን በማጥፋት የደም ቅዳ …

የልብ በሽታን ለመከላከል … ክብደትዎን ይቀንሱ Read more »

“እኔ በቁሜ ብሸለምም ሽልማቱ ለሌሉት ባልደረቦቼም ነው” (አርቲስት ዙፋን) “ቆንጆ ቆንጆ ሴቶች ፈልጉ” ተብሎ ነው፤ተመርጬ የተቀጠርኩት · ተወዛዋዥነት ለዘመናት ተንቆ የኖረ ሙያ ነው ትላለች የ50 ዓመት የኪነ ጥበብ ጉዞሽ እንደሚዘከር ቀደም ብሎ መረጃ ነበረሽ? በሰማሽ ወቅት ምን አልሽ? የአንጋፋ አርቲስቶችን …

የ50 ዓመታት የከያኒ ህይወት- ከኮረዳነት እስከ እማወራነት! Read more »

  Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – በተለያዩ መስሪያ ቤቶች የተለያዩ አይነት የሙስና ወንጀሎች ሲሰሩ በጉምሩክ እና ገቢዎች መስሪያ ቤትን የሙስና ወንጀል የለም ብሎ ባይካድም ከጥቅማቸው ይልቅ የሕዝብ አደራ አንበላም የሚሉ ሰራተኞች ለሕወሓት ስውር እጆች አንታዘዝም በማለታቸው በሙስና ስም ጥቃት እየደረሰብን …

ለሕወሓት ስውር እጆች ታዛዥ ስላልሆንን እየተጠቃን ነው ሲሉ የጉምሩክ ሰራተኞች ይናገራሉ:: ‪ Read more »

ተወዳጅ የማህበራዊ ሚዲያ የሆነው ፌስቡክ አገልግሎቶቹን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያዘመነ እና አዳዲስ መተግበሪያዎችን እያስተዋወቀ ይገኛል። በቅርቡ አዲስ የቪዲዮ ማጫወቻ አገልግሎት ማስታወቁም ይታወሳል። ታዲያ ፌስቡክ ገፃችን ላይ የሚመጡ እና የወደድናቸውን ቪዲዮዎችን ቀለል ባለ መንገድ እንዴት አውርደን ለራሳችን መያዝ እንችላለን የሚለውን እንመከለታለን። …

ፌስቡክ ገፃችን ላይ የሚመጡ እና የወደድናቸውን ቪዲዮዎችን ቀለል ባለ መንገድ እንዴት አውርደን ለራሳችን መያዝ እንችላለን ? Read more »

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወሳኝነታቸውን ያሳዩበት መድረክ

በኢትዮጵያ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍ እስከዛሬ ሲደረጉ ከነበሩ ከንግግር ያልዘለሉ የቁርጠኝነት ማሳያዎች አንድ እርከን የዘለለ እንደሆነ የተነገረለት በጥናት ላይ የተመሠረተ ውይይት፣ በቅርቡ በመንግሥት ከፍተኛው አስፈጻሚ አካል ተካሂዷል፡፡

ይህ ለሕዝብ ከወትሮው በተለየ በከፍተኛ ባለሥልጣናት መካከል ወቀሳና ተጠያቂነትን ያስነሳው ውይይት፣ መነሻ ምክንያቱ ታች መሬት ተወርዶ በመልካም አስተዳደር ችግሮች ላይ የዳሰሳ ጥናት መካሄዱ ነው፡፡ የጥናቱ አቅራቢዎች በውይይቱ ወቅት የችግሩን ስፋትና መጠን ሲያስረዱ፣ ለወትሮው የሐሳብ ልዩነቶቻቸውን ከመጋረጃ በስተጀርባ በመጨረስ ለሕዝብ አንድ ሆነው በመቅረብ የሚታወቁት የኢሕአዴግ ቱባ ባለሥልጣናት፣ በአደባባይ ልዩነቶቻቸውን በግልጽ ያወጡበት ውይይት እንደነበር ታይቷል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የአገሪቱ ቁንጮ ባለሥልጣን ሆነው ከመጡበት ጊዜ  ጀምሮ፣ በግልጽ የሥልጣን ባለቤትና የገዥው ፓርቲ አቅጣጫ የመወሰን ሥልጣን እንዳላቸው ያሳዩበትም ነበር፡፡ በተለይ በመሬት፣ በኢንቨስትመንት፣ በፍትሕና በተለያዩ መስኮች በጥናቱ የቀረበው አሳሳቢ ሥጋት ካልተወገደ አደገኛነቱንም በማስጠንቀቅ አውስተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አፅንኦት በመስጠት ለአገሪቱም ሆነ ለሕዝቡ አደገኛ የሆነውን የመልካም አስተዳደር ችግር መታገል የሕዝብ አመኔታን እንደሚያስገኝ አስታውቀው፣ የመንግሥት ባለሥልጣናትም በውስጣቸው መደንገጥ እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡ ከውይይቱ በኋላ ባለሥልጣናት በብሔር፣ በዝምድና፣ በጥቅማ ጥቅምና በመሳሰሉት ከተሳሰሯቸው ኔትወርኮቻቸው እንዲላቀቁም አስጠንቅቀዋል፡፡ ዝርዝሩን ለመመልከት እዚህ ላይ ይጫኑ ወይም በ ፖለቲካ ገጽ ይመልከቱ፡፡

 

ጥቅምት ፳፬ (ሃያ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአንድነት መግባባትና መተባበር ሊቀመንበር የሆኑት የአቶ ፈንታሁን ብርሃኑ የ13 አመት ሴት ልጅ በአንድ ወጣት በስለት በአሰቃቂ ሁኔታ ስትገደል፣ ሌላው የሰማያዊ ፓርቲ የምክር ቤት አባል አቶ አበራ ሃይለማርያምም በዚሁ ወጣት ተገድለዋል። አቶ ፋንታሁን ለኢሳት እንደተናገሩት ጎረቤታቸው የሆኑት አቶ አበራ የተገደሉት ምናልባትም ጩኸት ሰምተው ልጃቸውን ለመታደግ በመሞከራቸው ሳይሆን …

ጥቅምት ፳፬ (ሃያ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ታይዋን በሚባለው አካባቢ ይሰሩ የነበሩ ነጋዴዎች፣ ሆን ተብሎ በተቀሰቀሰ እሳት ድርጅታቸው እስከ ሙሉ ንብረታቸው እንደወደመባቸው ለኢሳት ተናግረዋል። ድርጊቱ ከሌሊቱ 11 ሰአት ላይ የተፈጸመ ሲሆን፣ መንግስት በአካባቢው ለሚያሰራው መንገድ ድርጅቶችን በማቃጠል ካሳ እንዳይከፍል ለማድረግ ነው በማለት ነዋሪዎች ተናግረዋል። በቃጠሎው ከ15 በላይ የንግድ ድርጅቶች የወደሙ ሲሆን፣ ፖሊሶች ህዝቡ …

በፌዴሬሽኑ ተልካሻ አሰራር ስህተት የሴቶች ብሄራዊ ቡድን ከአፍሪካ ዋንጫ ታገደ ፌዴሬሽኑ በሚሰራው ተደጋጋሚ ስህተት ትምህርት የሚሰጥ እርምጃ መወሰድ አለበት !!! በፌዴሬሽኑ ተልካሻ አሰራር ምክንያት የኢትዮጵያ ሴቶች ቡድን ከአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያውጭ ሆነ በወንዶች ብሄራዊ ብድን ቢጫ ካርድ ትምህርት ያልወሰደው የኢትዮጵያ የእግር …

በፌዴሬሽኑ ተልካሻ አሰራር ስህተት የሴቶች ብሄራዊ ቡድን ከአፍሪካ ዋንጫ ታገደ Read more »

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

የጀርመኑ ኮሜርስ፤የዩናይትድ ስቴትሱ ሲቲ እና የኬንያው ንግድ ባንኮች በአዲስ አበባ ቢሮ የመክፈት እቅድ ሰንቀዋል። በኢትዮጵያ ቢሮዎቻቸውን የከፈቱት የውጭ ኩባንያዎች ግን በዘርፉ ያለምንም ገደብ የመስራት ፈቃድ የላቸውም።

ኢትዮጵያ ውስጥ ከህገ መንግስቱ ጀምሮ አዋጅና በሌሎችም የዜጎችን መብት የሚደነግጉ በርካታ መሰረቶች ቢኖሩም ለይስሙላ ህጋዊ ሥርዓት እንዳለ ከማስመሰልም አልፎ ለአገዛዙ ማጥቂያና መግዢያ ከመሆን ባለፈ የዜጎችን መብት እያስከበሩ አይደለም፡፡ ባለፉት 6 ወራት እንኳን ህግ እንደተቀበረች፣ በዚሁ አገዛዙ ውስጥ ተፅዕኖ ያለው የፍርድ …

ከነካባው የተቀበረውን የፍትህ ሥርዓት ነፃ ለማውጣት ትግላችን አጠናክረን እንቀጥላለን! (ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ) Read more »

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር የሆኑት ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት የእጅ ስልክ ባልታወቁ ሰዎች እጅ የገባ ሲሆን ኢንጂነር ይልቃል በሃገር ውስጥ እና በውጪ ሃገር ላሉ አባሎቻቸው እና ደጋፊዎቻቸው የሚቀጥለውን ማሳሰቢያ አስተላልፈዋል:: ማሳሰቢያ :- የእጅ ስልክ (ሞባይሌ) ባልታወቁ ሰዎች እጅ ስለገባ ከዛሬ ጥቅምት 24/2008 …

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል የእጅ ስልክ ባልታወቁ ሰዎች እጅ ገባ:: Read more »

የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት የነበሩት ሊቀ ትጉሃን አስታጥቄ አባተ፣ በማታለል ወንጀል ተጠርጥረው ክስ ተመሠረተባቸው፡፡ ክሱ ቀደም ብሎ በ1998 ዓ.ም. ተመሥርቶባቸው የነበረ ቢሆንም፣ እንዲቋረጥ ተደርጎ ከቆየ በኋላ የፍትሕ ሚኒስትር ዴኤታ በነበሩት አቶ ልዑል ወልዱ (አሁን የትግራይ  ክልል ፍትሕ ቢሮ …

የቀድሞ የአርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት ‹‹አርበኛ ሳይሆኑ አርበኛ ነኝ›› በማለት በማታለል ወንጀል ተጠርጥረው ተከሰሱ Read more »

ወያኔ ምክረ ሃሳብ ይበለው እንጂ የፖሊሲ ማሻሻያ የቀለበው ቀጥታ መሆኑ ታውቋል:: -በግል ባንኮች ላይ የተጣለው የቦንድ ግዥ እንዲነሳ ጠይቋል -የታክስ ነፃ መብቶች እንዳይሰጡ ብሏል -የብር የመግዛት አቅም መቀነስ አለበት ብሏል የዓለም ገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ሁኔታ ከገመገመ በኋላ፣ …

የዓለም ገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ለወያኔ አዲስ የፖሊሲ ማሻሻያ አቀረበ:: Read more »

  Minilik Salsawi – ስካቢስ የተሰኘ ወረርሽኝ በምሥራቅ ጎጃም፣ በሰሜን ጎንደር፣ በደቡብ ወሎና በዋግ ህምራ ዞኖች በሚገኙ 20 ወረዳዎች ላይ መከሰቱን የተባበርት መንግስታት ድርጅት ያስታወቀ ሲሆን ከፍተኛ የሰብኣዊ ቀውስ ያስከተለውን የድርቁን ሁኔታ ሽላ በማለት አጣብቂኞቻቸውን ለማላላት ደፋ ቀና የሚሉት ባለስልጣናት …

ወገን በወረርሽኝ በሽታ እያለቀ ነው:: የድርቁ ሁኔታ ከመባባሱ አልፎ ከንጽህና ጋር የተያያዙ እና ውሃ ወለድ በሽታዎች ተስፋፍተዋል:: ‪ Read more »

ጥቅምት 20 ለ21 አጥቢያ 2008 ዓ.ም. የልጃቸውን ጓደኛ በሽጉጥ ተኩሰው በመግደል የተጠረጠሩ ሐኪም፣ ከነመሣሪያቸው በቁጥጥር ሥር ውለው እየተመረመሩ መሆኑ ታወቀ፡፡በየካ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 13/14 ልዩ ሥፍራው ማጂክ ካርፔት በሚባለው ትምህር ቤት አካባቢ የተገደለው ወጣት ቴዎድሮስ ሲሳይ ይባላል፡፡ ቴዎድሮስ ከጓደኞቹ ጋር …

የልጃቸውን ጓደኛ በመግደል የተጠረጠሩት በሰላም ከፍተኛ የጥርስ ክሊኒክ የጥርስ ሐኪም ታሰሩ Read more »

አቃቢ ሕጎች ሆን ብለው ተገበዉን ሕግ ጠቅሰው አይከሱም :: ምስክሮች ማስጠናት፣ በግድ “ይሄን መስከር ተብሎ ማስፈራራት፣ ካልመሰከርክ እዚህ ትከርማታለህ፣ አንተም ትታሰራልህ” የማለት ነገር አለ:: ከፍተኛ አመራር ጣልቃ ገብነት አለ። ይሄን ፋይል ዝጋ፣ ምርመራም ከተጀመረ አቁም፤ እንባላለን፣ የሚል ራሳቸው ባለሞያዎቹ የሚያነሱት …

VIDEO : አቃቢ ሕጎች ሕግ ጠቅሰው አይከሱም ምስክሮች ማስጠናት፣ በግድ “ይሄን መስከር ተብሎ ማስፈራራት፣ ካልመሰከርክ እዚህ ትከርማታለህ፣ አንተም ትታሰራልህ” የማለት ነገር አለ: Read more »

አቶ <ክቡር ጠቅላይ ሚንስቴር> ሃይለማርያም ደሳለኝ ፣ ጠቅላይ ሚንስቴር ፣ ጠቅላይ ሚንስቴር የሚሸት ነገር ተናገሩ ፣ ልል አልኩና ፣ እስኪ ከመቸኮል ፣ ምን አዲስ ነገር ተናገሩ ? ህዝቡ የማያውቀውን ፣ ወይም ህዝቡ ያጣውን እና ከመሪው መስማት የሚሻውን ምን አዲስ ነገር …

የሃይለማርይም እንባ እና የኔ አጭር ዘገባ ( ሄኖክ የሺጥላ ) Read more »

የ54 አመቱ አሪክ የተባለ እስራኤላዊ መንገደኛ ከቻድ ወደ አዲስ አበባ በሚሄደው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ላይ እያለ በአንድ ሱዳናዊ ተሳፋሪ የግድያ ሙከራ ተደረገበት። ሱዳናዊ አህመድ መሃመድ የተባለው አጥቂ በቁጥጥር ስር ውሎ ዛሬ በአዲስ አበባ ለፍርድ ቀርቧል:: [youtube http://www.youtube.com/watch?v=4CT4hOXtlpk]   An …

እስራኤላዊ መንገደኛ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ላይ እያለ በሱዳናዊ ተሳፋሪ የግድያ ሙከራ ተደረገበት ። Read more »

የኦፌኮ/መድረክ ከፍተኛ አመራር ዶክተር ሞጋ ፉሪሳ ስለኢትዮጵያዊነት ስለጎሳ ፖለቲካ እና ወቅታዊ ሁኔታዎች ይናገራሉ:: http://www.1ethiopia.net/v/esat-yesamintu-engida-interview-with-dr-moga-frissa-about-current-and-ethnic-politics  

በአማራ ክልላዊ መንግሥት በድርቅ በተጠቁ በተለያዩ ዞኖች የተከለሉ ውኃ ምንጮች ውስንነት፣ ከንፅህና ጋር ለተያያዙ በሽታዎች መፈጠር ምክንያት መሆኑ ተገለጸ፡፡ 

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት በዚህ ሳምንት በወጣው ሪፖርት፣ ‹‹ስካቢስ›› የተሰኘ ወረርሽኝ በምሥራቅ ጎጃም፣ በሰሜን ጎንደር፣ በደቡብ ወሎና በዋግ ህምራ ዞኖች በሚገኙ 20 ወረዳዎች መከሰቱን አስታውቋል፡፡ በዋግ ህምራ ዞን ብቻ 88,905 ግለሰቦች በወረርሽኙ መያዛቸው ታውቋል፡፡ የጤና ጥበቃ  ሚኒስቴር በበሽታው ለተጠቁ ሥፍራዎች መድኃኒቶችን በመላክ ላይ መሆኑን የገለጸው ጽሕፈት ቤቱ፣ የችግሩ መጠን ከፍተኛ በመሆኑ የተለያዩ ዘርፎችን ትብብር የሚጠይቅ እንደሆነ ጠቁሟል፡፡ 

በሽታው ተዛማች በመሆኑ ወረርሽኙን ለመቆጣጠር የተጀመረው ጥረት በአፋጣኝ ተስፋፍቶ መቀጠል እንደሚኖርበት የገለጸው ጽሕፈት ቤቱ፣ ወረርሽኙ የተከሰተው ከድርቁ ጋር ተያይዞ እንደሆነ በሪፖርቱ አስፍሯል፡፡ 

ካለፈው ጥር ወር ጀምሮ በምግብ እጥረት የተጎዱ ሕፃናት ቁጥር እየጨመረ መጥቷል፡፡ ዕድሜያቸው ከአምስት ዓመት በታች የሆኑ የምግብ ፕሮግራም የሚያስፈልጋቸው ሕፃናት ቁጥር ከሌላው ጊዜ በ20 በመቶ መጨመሩን፣ የተጎጂዎቹ ቁጥር በየወሩ እየጨመረ መሄዱን ጽሕፈት ቤቱ በሪፖርቱ አመልክቷል፡፡

በመስከረም ወር የተመዘገቡ በምግብ ዕጦት የተጎዱ ሕፃናት ቁጥር 35,216 የነበረ ሲሆን፣ በነሐሴ ወር ከተመዘገቡት 43,391 ሕፃናት የ19 በመቶ ቅናሽ ያሳየ ቢሆንም፣ በአገር አቀፍ ደረጃ በመስከረም ወር የተመዘገበው በምግብ ዕጦት የተጎዱ ሕፃናት ቁጥር ከሌላው ማንኛውም ዓመት የ20 በመቶ ብልጫ አለው፡፡ 

ከፍተኛው ቁጥር የተመዘገበው በአማራ ክልል እንደሆነ የገለጸው ጽሕፈት ቤቱ፣ በየወሩ በክልሉ 6,489 በምግብ ዕጦት የተጎዱ ሕፃናት ወደ ምግብ ፕሮግራም እንደሚገቡ ጠቁሟል፡፡ 

በኤልኒኖ ምክንያት በተፈጠረው አየር መዛባት የተከሰተው ድርቅ እየተባባሰ መምጣቱን ጠቅሶ፣ እየጨመረ የመጣውን የምግብ ዕርዳታ ፍላጎት መጠን ለማሟላት የኢትዮጵያ መንግሥት ተደጋጋሚ ጥሪ ቢያቀርብም አጥጋቢ ምላሽ አለመገኘቱን አስታውቋል፡፡ እ.ኤ.አ. የ2015 እና የ2016 የአስቸኳይ ጊዜ ዕርዳታ ፍላጎት ማሟላት የሚያስችል የገንዘብ ምንጭ አለመኖሩ አሳሳቢ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ እ.ኤ.አ. ለ2016 የሚያስፈልገው ዕርዳታ በአስቸኳይ መገኘት እንዳለበት የገለጸው ጽሕፈት ቤቱ፣ ዕርዳታውን አጓጉዞ ከሚፈለገው ሥፍራ ለማድረስ ከሦስት እስከ አምስት ወራት ቀድሞ መዘጋጀት እንደሚኖርበት ጠቁሟል፡፡ 

መንግሥት ከለጋሾች የሚፈለገውን ያህል የገንዘብ ድጋፍ ባለማግኘቱ ሁኔታዎች በከፉበት አካባቢ በራሱ ወጪ ዕለታዊ ዕርዳታዎች በማድረግ ላይ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ 

ከመንግሥት የመጠባበቂያ ምግብ ክምችት 50,000 ሜትሪክ ቶን ስንዴና 300 ሜትሪክ ቶን የምግብ ዘይት በመከፋፈል ላይ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ የከብቶች መኖ በመታደል ላይ መሆኑን፣ የውኃ ጉድጓዶች ጥገና ሥራ እየተከናወነ እንደሆነና የውኃ ማጣሪያ ኬሚካሎች በመሠራጨት ላይ መሆናቸው ተገልጿል፡፡ 

በአሁኑ ወቅት በተፈጠረው ድርቅ ምክንያት 8.2 ሚሊዮን ዜጎች የአስቸኳይ ጊዜ ዕርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሲሆን፣ የዕርዳታ አቅርቦቱ ካልተፋጠነና የአየር ፀባዩ ካልተለወጠ የተረጂዎች ቁጥር በሁለት ወራት ውስጥ 15 ሚሊዮን ሊደርስ እንደሚችል ተገምቷል፡፡ 

 

በሽብር ድርጊት ወንጀል ክስ ተመሥርቶባቸው ዓቃቤ ሕግ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን ካቀረበባቸው በኋላ መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነፃ የተሰናበቱት የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች፣

ዓቃቤ ሕግ ያቀረበባቸው ይግባኝ ተመርምሮ እንደሚያስቀርብና እንደማያስቀርብ ለመንገር በድጋሚ ተቀጠሩ

የሥር ፍርድ ቤት ውሳኔን በመቃወም የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ያቀረበውን ይግባኝ ተከትሎ ውሳኔው እንዳይፈጸም ዕግድ የሰጠው የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ ጥቅምት 22 ቀን 2008 ዓ.ም. የውሳኔ መዝገቡን መርምሮ ዓቃቤ ሕግ ባቀረበው የይግባኝ አቤቱታ ላይ ‹‹ያስቀርባል ወይም አያስቀርብም›› ብሎ ብይን ለመስጠት ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረ ቢሆንም፣ ዓቃቤ ሕግ የተቃወመው የሥር ፍርድ ቤት የውሳኔ መዝገብ እንዳልቀረበለት ገልጿል፡፡ በመሆኑም ውሳኔውና ዝርዝር ማስረጃዎቹ ተያይዘው እንዲቀርቡለት ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ 

በዕለቱ ይግባኝ የተጠየቀባቸው የአንድነት አመራር የነበሩት አቶ ሀብታሙ አያሌውና አቶ ዳንኤል ሺበሺ፣ የአረና ፓርቲ አመራር የነበሩት አቶ አብረሃ ደስታና የሰማያዊ ፓርቲ አመራር የነበሩት አቶ የሺዋስ አሰፋ፣ እንዲሁም አብረዋቸው ይግባኝ የተባለባቸው አቶ አብረሃም ሰለሞን በችሎት አልተገኙም፡፡ ፍርድ ቤቱ በችሎት በሰጠው ትዕዛዝ መዝገቡን መርምሮ ብይን ለመስጠት ለጥቅምት 29 ቀን 2008 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ 

 

አፌን መረረኝ፤ ጠረን አመጣብኝ፤ የተለያዩ ሰዎች ሲናገሩት የሚደመጥ ችግር ነዉ። የአፍ ምሬት ከምን ይመጣል? ዉስጥ ደዌ ከፍተኛ ሃኪም ዶክተር ቶሌራ ወልደየስ፤ አፍን ሊያመርሩ የሚችሉ የተለያዩ ምክንያቶች ሊሆኑ እንደሚችሉ ነዉ በዝርዝር ያብራሩት። ዶክተር ቶሌራ የተለያዩ በሽታዎችም አፍ ላይ ምሬት እንዲሰማን ሊያደርጉ …

የአፍ ምሬትና ጠረን መንስኤዎቹ Read more »