የድህነት ዘበኛ
ጓድ ካፍትሌ ከአርባምንጭ
የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የደርግ ሥርዓት መገርሰሱን በማስመልከት ያስተላለፉትን መልዕክት ሰምቼ ነበር። መልዕክቱ ባጭሩ እንዲህ የሚል ነበር። “የድህነት ዘበኛ የነበረው ሥርዓት ስለተወገደ ከዚህ በኋላ ጦርነታችሁ ከዘበኛው ጋር ሳይሆን ቀጥታ ከጠላቱ (ድህነት) ጋር ነው።” በእርግጥ ደርግ ሥልጣን ላይ በነበረበት ጊዜ ”ሁሉም ነገር ወደ ጦር ግንባር!” እያለ ሕዝቡ በድህነት እንዲማቅቅ አድርጓል። ከዚህ የተነሳ የሥርዓቱ መውደቅ ብዙዎችን በደስታ አስፈንጥዟል።