በዛሬው አለት ሉሲ (ድንቅነሽ) በኣፋር ክልል በ፲፱፮፮ ኣመተምህረት የተገኘችበት ኣርባ ኣንደኛ ፵፩ ኣመቷ ነው።
በዛሬው አለት ሉሲ (ድንቅነሽ) በኣፋር ክልል በ፲፱፮፮ ኣመተምህረት የተገኘችበት ኣርባ ኣንደኛ ፵፩ ኣመቷ ነው። http://mereja.com/forum/viewtopic.php?f=2&t=107047
በዛሬው አለት ሉሲ (ድንቅነሽ) በኣፋር ክልል በ፲፱፮፮ ኣመተምህረት የተገኘችበት ኣርባ ኣንደኛ ፵፩ ኣመቷ ነው። http://mereja.com/forum/viewtopic.php?f=2&t=107047
News Ethiopia Wetatoch Dimts 99 23.11. 2015 መረጃ ሙሉ ያደርጋል ለዚህ ደግሞ የኢትዮጵያ ወጣቶች ድምፅ ሳምንታዊ ዜናዎችን እንዲሁም የስፖርት ዘገባዎች መጣጥፎችን ለስለስ ካሉ ሙዚቃዎች ጋር ይዘንላችሁ ቀርበናል አብራችሁን ሁኑ [youtube http://www.youtube.com/watch?v=xYH0l834N44]
–በጦርነቱ ቁጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች መሞታቸውና ንብረት መውደሙ ተገልጿል
በደቡብ ክልል ሸካ ዞን ይዞታቸው ለኢንቨስተር በመሰጠቱ ምክንያት ምትክ ቦታ እንዲሰጣቸው ጥያቄ በማቅረባቸው ‹‹ለሕግ ተገዢ አይደሉም›› በማለትና በሽፍታነት በመፈረጅ፣ በሸኮዎች ላይ ዕርምጃ ለመውሰድ ሸካዎችን በማስታጠቅና
የእርስ በርስ ጦርነት በማነሳሳት የተጠረጠሩ፣ የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪን ጨምሮ 12 ተሿሚዎች ክስ ተመሠረተባቸው፡፡
የደቡብ ክልል መንግሥት ፍትሕ ቢሮ ዓቃቤ ሕግ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ተዘዋዋሪ አንደኛ ወንጀል ችሎት ኅዳር 9 ቀን 2008 ዓ.ም. ያቀረበው ክስ እንደሚያስረዳው፣ የሸኮ ብሔር ተወላጆችና የየኪ ወረዳ ፃኑ ቀበሌ ጉፍታ ንዑስ መንደር ነዋሪዎች ይዞታ ለኢንቨስተር ተሰጥቷል፡፡ ነዋሪዎቹ ለረዥም ዓመታት ምትክ ቦታና የንብረት ግምት እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡ ጥያቄያቸውን በመቀበል ምላሽ መስጠት ያልፈለጉት የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አዝመራ አንደሞና የሥራ ባልደረቦቻቸው፣ ‹‹ለሕግ ተገዢ አይደሉም›› በማለትና በወንጀለኛነትና በሽፍታነት በመወንጀል፣ በዞኑ ፖሊሶች ተይዘው እንዲታሰሩ ማድረጋቸውን ዓቃቤ ሕግ በክሱ ዘርዝሮ አቅርቧል፡፡
ሕጋዊ መብታቸውን በመጠየቃቸው ወንጀለኞች የሚል ስያሜ በመስጠት ነዋሪዎቹን በመተባበር በማሰርና የእርስ በርስ ጦርነት እንዲነሳ ያደረጉት ተጠርጣሪዎች የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አዝመራ አንደሞ፣ በዞኑ የደኢሕዴን ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አልማው ዘውዴ፣ የየኪ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ወርቁ ሻረው፣ የየኪ ወረዳ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አምሳሉ ከሴቶ፣ የቴፒ ከተማ ከንቲባ አቶ ሻሎ አድሎና ሌሎችንም ተጠርጣሪዎች ዓቃቤ ሕግ በክሱ ዘርዝሯል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ ከ30 በላይ የፖሊስ አባላትን መሣሪያ በማስታጠቅ፣ ሚያዝያ 20 ቀን 2006 ዓ.ም. ወደ ፃኑ ቀበሌ ጉፍታ ንዑስ መንደር በመሄድ የሸኮ ብሔር ተወላጆችን ከበው መያዛቸውን የሚገልጸው የዓቃቤ ሕግ ክስ፣ ያልተያዙት የአካባቢው ነዋሪዎች በሁኔታው በመደናገጥና በመረበሽ ንብረታቸውንና ቤታቸውን ጥለው አጎራባች ወደሆነው ጋምቤላ ክልል ዶንቻዬ ቀበሌ መሰደዳቸውንም ያስረዳል፡፡
የሸኮ ነዋሪዎች ቀዬአቸውን ትተው ሲሰደዱ ተጠርጣሪዎቹ ‹‹አካባቢውን ተቆጣጥረነዋል›› በማለት አካባቢው ላይ ባንዲራ መትከላቸውንና ተመልሰው ሲመጡ ዕርምጃ ለመውሰድ የሚያስችላቸውን ንዑስ የፖሊስ ጣቢያ መክፈታቸውም ተገልጿል፡፡ በአካባቢው ምሽጎችን ቆፍረው ለውጊያ ቅድመ ዝግጅት ማድረጋቸውን ዓቃቤ ሕግ በክሱ አካቷል፡፡
ድንገት በተፈጠረባቸው ወረራ ወደ አጎራባች ክልል የተሰደዱት ሸኮዎች ወደ ቀያቸው እንዳይመለሱ ሕገወጥ ድብደባና እስር በተጠርጣሪዎቹ ሲፈጸምባቸው ቆይቶ፣ ድርጊቱ ወደ እርስ በርስ ግጭት ተቀይሮ በሸኮዎችና በሸካ ብሔረሰቦች መካከል ጦርነት እንዲፈጠር ማድረጋቸውንም የዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡
በሸኮዎችና በሸካ ተወላጆች መካከል በተደረገ የእርስ በርስ ጦርነት ስማቸው የታወቁ ስድስት ሰዎች መሞታቸውን ማረጋገጡን ዓቃቤ ሕግ በክሱ ገልጿል፡፡ በተጨማሪም ስማቸውን ማወቅና መለየት ያልተቻለ በርካታ ሰዎች መሞታቸውን ባቀረበው ክስ ላይም ገልጿል፡፡ ከሰባት የሚበልጡ ነዋሪዎችም ከፍተኛ የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸውና የገቡበት እንዳልታወቀም አክሏል፡፡ ጦርነቱ ከእነሱ አልፎ ወደ አጎራባች ቀበሌዎች እንዲስፋፋና በዞኑ የፀጥታ ችግር እንዲሰፍን ምክንያት መሆናቸውንም ዓቃቤ ሕግ በክሱ አስረድቷል፡፡
ተከሳሾቹ ‹‹ወደዳችሁም ጠላችሁም የዞኑና የወረዳው ቁልፍ ያለው በእኛ እጅ ነው›› በማለት በሁለቱ ብሔረሰቦች መካከል የተነሳው ግጭት ወደ ቴፒ ከተማ አስፋፍተዋል፡፡ በግንቦት ወር 2007 ዓ.ም. የቴፒ ከተማ ፖሊስ አባላት የሆኑ አምስት ፖሊሶች ወደ ጫካ ገብተው በነበሩ የሸኮ ተወላጆች እንዲገደሉ ማድረጋቸውንና ግጭቱ እስካሁን እንዲቀጥል ማድረጋቸውን ክሱ ያስረዳል፡፡ ተከሳሾቹ የአካባቢው ነዋሪዎች ከቀዬአቸው እንዲፈናቀሉ ማድረጋቸውን፣ በሕዝብ ደኅንነትና ኑሮ ላይ ከፍተኛ ቀውስ ማስከተላቸውንና የእርስ በርስ ጦርነት የማነሳሳት ወንጀል መፈጸማቸውን ዓቃቤ ሕግ አብራርቷል፡፡
ተከሳሾቹ በተሰጣቸው ሥልጣንና ኃላፊነት ሕግና ሥርዓትን ተከትለው ኅብረተሰቡን ማገልገል ሲገባቸው፣ ሥልጣናቸውን ተገን በማድረግ ሆን ብለውና አስበው በሕገወጥ ተግባራት በመሰማራት በሕዝብና በመንግሥት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሳቸውን ዓቃቤ ሕግ በክሱ አብራርቶ ለፍርድ ቤቱ አቅርቧል፡፡ ፍርድ ቤቱ የተከሳሾቹን ጉዳይ የሚያየው በተዘዋዋሪ ችሎት ቢሆንም፣ የሚቀጥለው ችሎት መቼ እንደሚሰየም አልታወቀም፡፡

የኢትዮጵያ የመድኃኒት፣ የምግብና የጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለሥልጣን እ.ኤ.አ. ኖቬምበር 1 ቀን 2015 ባሠራጨው ሰርኩላር፣ ኮዴይን የተባለው የሕመም ማስታገሻ ላልተወሰነ ጊዜ ኢትዮጵያ ውስጥ ጥቅም ላይ እንዳይውል አግዷል፡፡
ባለሥልጣኑ ለክልሎችም ሆነ ለፌዴራል መንግሥት የጤና ቢሮዎች በላከው ደብዳቤ እንደገለጸው፣ ኮዴይን የተባለው መድኃኒት ለኢትዮጵያውያን የዘረ መል አወቃቀር (Genetic Makeup) የማይስማማ መሆኑንና ጥቅም ላይ ከዋለም እስከ ሞት ሊያደርስ እንደሚችል በጥናት መረጋገጡን አስታውቋል፡፡
ባለሥልጣኑ ዕገዳውን ያደረገው የአሜሪካ የምግብና የመድኃኒት አስተዳደር በኢትዮጵያና በሌሎች አገሮች ላይ አተኩሮ ባከናወነው ጥናት፣ ኮዴይን የተባለው የሕመም ማስታገሻ እስከ ሞት የሚያደርስ መሆኑን በማሳወቁ ነው፡፡
የተሠራው ጥናት እንዳመለከተው በዘረ መል አወቃቀር ምክንያት አንዳንድ ሰዎች ኮዴይን ሲወስዱ ወደ ሞርፊን እንደሚቀየር፣ በዚህም ምክንያት በደም ውስጥ የሚገኘውን የሞርፊን መጠን በከፍተኛ ሁኔታ በመጨመር ለመተንፈስ ችግር ብሎም ለሞት እንደሚያደርስ ተገልጿል፡፡
በመሆኑም ማንኛውም የጤና ባለሙያና የጤና ተቋም ኮዴይን የተባለውን የሕመም ማስታገሻ በየትኛውም ዕድሜ ለሚገኙ ታካሚዎች በሕመም ማስታገሻነት ወይም ለብርድና ለሳል ሕመሞች እንዳያዙ ደብዳቤው የደረሳቸው የጤና ቢሮዎች፣ በሥራቸው ለሚተዳደሩ የጤና አገልግሎት ተቋማት እንዲያስተላልፉ አዟል፡፡ ዕገዳው የተደረገው ላልተወሰነ ጊዜ እንደሆነ ቢገልጽም፣ ላልተወሰነ የተባለበት ጊዜ ምክንያቱ ምን እንደሆነ ደብዳቤው አይገልጸም፡፡
ጉዳዩን በተመለከተ የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ተንቀሳቃሽ ስልክ ላይ በተደጋጋሚ ቢደወልም ጥሪውን አልመለሱም፡፡ የአሜሪካ የምግብና የመድኃኒት አስተዳደር ጥናት እንደሚያመለክተው፣ ምርመራ ከተካሄደባቸው 122 ኢትዮጵያውያን መካከል 29 በመቶ የሚሆኑት ወይም 35 ኢትዮጵያውያን የዘረ መል አወቃቀር ኮዴይን በከፍተኛ ፍጥነት ወደ ሞርፊን የሚቀይር ኢንዛይም አላቸው፡፡
ይህ የጥናት ውጤት ከተገለጸ ስድስት ወራት ቢሆነውም የኢትዮጵያ የመድኃኒት፣ የምግብና የጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለሥልጣን ውሳኔ ሳይወስድ እስከተጠቀሰው ቀን ቆይቷል፡፡ በተመሳሳይ ጥናት የአዲስ አበባ የወተት አቅርቦት ለካንሰር የሚዳርግ አፍላቶክሲን የተባለ ውህድ እንዳለው ከተገለጸ ከስድስት ወራት በኋላ መረጃው በተለያዩ የማኅበራዊ ድረ ገጾች ሲለቀቅ፣ ባለሥልጣኑ የራሱን ተጨማሪ ጥናት እያከናወነ መሆኑን ሰሞኑን ለመገናኛ ብዙኃን መግለጹ አይዘነጋም፡፡
“የኢትዮጵያ ወታደሮች የኬንያን ድንበር ዘልቀው ሦስት የኬንያ ፖሊሶችን ገደሉ” ሲሉ የኬንያ ጋዜጦች ፅፈዋል፤ የሃገሪቱ ፖሊስ ግን ሰዎቹን የገደሉት የኢትዮጵያ ታጣቂ አማፂያን እንጂ የመንግሥቱ ወታደሮች አይደሉም ይላል፡፡
ኅዳር 8 ቀን 2008 ዓ.ም. ረቡዕ ለሐሙስ አጥቢያ ከጓንግዙ ቻይና ወደ አዲስ አበባ በመብረር ላይ የነበረ ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነ ቦይንግ 777 አውሮፕላን ውስጥ የተሳፈረ መንገደኛ፣ በስካር መንፈስ ሁከት በመፍጠሩ በመንገደኞች ርብርብ በቁጥጥር ሥር ዋለ፡፡
የበረራ ቁጥር ኢቲ607 ከ300 በላይ መንገደኞች አሳፍሮ ከጓንግዙ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት የተነሳው ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት ነበር፡፡ አንድ ሰዓት ተኩል ከበረረ በኋላ በበረራ አስተናጋጆች አማካይነት ለመንገደኞች እራት ቀርቦ ካበቃ በኋላ፣ አብዛኛዎቹ መንገደኞች አሸልበው ነበር፡፡
በአውሮፕላኑ የተሳፈሩ መንገደኞች ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ከእንቅልፋቸው የነቁት በሰሙት ጩኸት ምክንያት ነበር፡፡ በኢኮኖሚ ክፍል የነበሩ የበረራ አስተናጋጆች እየተጯጯሁ ወደ ቢዝነስ ክፍል ሲሮጡ መመልከታቸውን መንገደኞች ተናግረዋል፡፡ ከእንቅልፋቸው ተደናግጠው የተነሱ የተወሰኑ መንገደኞች የበረራ አስተናጋጆቹን ተከትለው ሮጠዋል፡፡
‹‹የበረራ አስተናጋጆቹ ሊገለን ነው›› እያሉ እየሮጡ ወደ ቢዝነስ ክፍል መምጣታቸውን የገለጹት ተሳፋሪዎች፣ ዕድሜው በ30ዎቹ መጨረሻ የሚገመት ናይጄሪያዊ መንገደኛ በስካር መንፈስ ተገፋፍቶ የበረራ አስተናጋጆችን ለመደብደብ ሲያባርር መመልከታቸውን ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
በዚህን ወቅት በቢዝነስ ክፍል ውስጥ የተሳፈሩ አንድ ኢትዮጵያዊ ባለሀብት፣ በቢዝነስ ክፍል መግቢያ ላይ ጠብቀው ከሁከት ቀስቃሹ ናይጄሪያዊ ጋር ግብግብ ፈጥረዋል፡፡ ናይጄሪያዊው ግዙፍ ቢሆንም ኢትዮጵያዊው ባለሀብት እንደምንም ብለው መተናነቃቸውን ገልጸው፣ ሌሎች ናይጄሪያዊያን መንገደኞች ባደረጉላቸው እገዛ ግለሰቡን ከወለል ላይ ሊጥሉት ችለዋል፡፡ መንገደኞቹ ነውጠኛውን ተሳፋሪ በደረቱ በማስተኛት እጁን የኋሊት አስረውታል፡፡ ግለሰቡ መጠጥ መጠጥ ይሸት እንደነበር መንገደኞች ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለሪፖርተር በላከው ማብራሪያ፣ ግለሰቡ በአውሮፕላኑ ውስጥ የአልኮል መጠጥ እንዳልቀረበለት ገልጿል፡፡ ለመንገደኛው የቀረበለት ለስላሳ መጠጥና ምግብ ብቻ እንደሆነ የጠቆመው አየር መንገዱ ግለሰቡ ግን ሰክሮ እንደነበር ይታመናል ብሏል፡፡
ሪፖርተር ያነጋገራቸው መንገደኞች ግለሰቡ አውሮፕላኑን ከመሳፈሩ በፊት፣ የአልኮል መጠጥ በብዛት ሳይወስድ እንዳልቀረ ግምታቸውን ተናግረዋል፡፡
የአውሮፕላኑ ሠራተኞች ነውጠኛው ግለሰብ በሌሎች ተሳፋሪዎችና በአውሮፕላኑ ላይ ጉዳት ሳያደርስ፣ ከሌሎች ተሳፋሪዎች ጋር በመተባበር ሁኔታውን መቆጣጠራቸውን አየር መንገዱ አስታውቋል፡፡
ግለሰቡ በቁጥጥር ሥር ከዋለ በኋላ አውሮፕላኑ ለሰባት ሰዓታት ያህል በመብረር ከንጋቱ 12 ሰዓት ላይ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት በሰላም አርፏል፡፡ መንገደኞቹና የአውሮፕላኑ ሠራተኞች ግለሰቡን ለኤርፖርት ደኅንነት ሠራተኞች አስረክበዋል፡፡ ግለሰቡ ለፌደራል ፖሊስ ተላልፎ ከተሰጠ በኋላ፣ ፖሊስ ምርመራ እያካሄደበት መሆኑ ታውቋል፡፡
ከግለሰቡ ጋር ግብግብ የፈጠሩት ተሳፋሪዎች ለወደፊቱ ተመሳሳይ ድርጊት እንዳይፈጠር በግለሰቡ ላይ ጠንከር ያለ ቅጣት ሊጣል እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ ‹‹የፖሊስን ሪፖርት ተመልክተን በቀጣይ መደረግ ስላለበት ጉዳይ እንመክራለን፤›› ያለው አየር መንገዱ፣ የፖሊስ ምርመራ ከተጠናቀቀ በኋላ በግለሰቡ ላይ የወንጀል ክስ ይመሠረታል የሚል እምነት እንዳለው አስታውቋል፡፡
ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።
ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና
ኀዳር ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በወሎ፣ቆቦና ዋግ ህምራ አካባቢ የሚኖሩ አርሶ አደሮች የዘንድሮው ድርቅ ከ1977ቱ ያልተለየ ነው በማለት ለኢሳት ተናገሩ፡፡ ተጎጂዎች በድርቁ በርካታ ሃብት ንብረታቸውን በመጨረሳቸው ባዶ እጃቸውን እንደቀሩ ይናገራሉ፡፡የገዢው መንግስት ሚዲያዎች በድርቁ የሞተ ሰው የለም በማለት ለማስተባበል ቢሞክሩም ተጎጅዎቹ ‹‹ ከሃብታችን ባሻገር ልጆቻችን እየተነጠቅን ነው፡፡ ›› በማለት በተጨባጭ ያለውን የወቅቱን …
ኀዳር ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ድርጊቱ የተፈጸመው ባለፈው መስከረም ወር ሲሆን የቀብሩ ስነስርዓት የተፈጸመው ግን ባሳለፍነው ሳንምት ነው። በመተከል ዞን በዳንጉር ወረዳ 12 የአማራ ተወላጆች ለቀን ስራ ተብለው ከተወሰዱ በሁዋላ በወረዳው አስተዳደሪ ትእዛዝ ኮከል ቀበሌ ላይ አሰቃቂ በሆነ ሁኔታ ተረሽነዋል።አስከሬናቸው ተቆራርጦ በጆንያ ተጠቅሎ መገኘቱንና የቀብር ስነስርዓታቸውም መፈጸሙን ምንጮች ገልጸዋል። የተገደሉት ነዋሪዎች …
የአገራችንን ስምና ዝና በማጉደፍ የታወቁት ረሃብና ጠኔ ዘንድሮም ጓዛቸውን ጠቅለው ይዘው አገራችንን እየጎበኙ ነው። ባሁኑ ወቅት 8.2 ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ በረሃብ አለንጋ እየተገረፈ ሲሆን ከጥቂት ጊዜ በኋላ ይህ ቁጥር ወደ አስራ አምስት ሚሊዮን ያድጋል የሚል አስተያየት ጉዳዩን ከሚያውቁ ባለሙያዎች እየተነገረ …
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) የኣንድ ኣገር ኣገዛዝ ትክክለኛ ኣስተዳደር የሚተገብር ከሆነ አጅግ የበለጸገ አና የሰለጠነ ትውልድ ያፈራል። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያ ውስጥ ኣይሰራም። ባለፉት 25 ኣመታቶች ስልጣኑን ኣንቆ ኣለቅ ያለው ወያኔ የሰለጠኑ ዜጎችን ከማፍራት ይልቅ የሚሰደዱ ዜጎችን በማፍራት በኣለም ኣቀፍ ደረጃ …
ላለፉት 25 ኣመታት የሰለጠኑ ሳይሆን የተሰደዱ ዜጎችን ያፈራ የወያኔ ኣገዛዝ ፈተና ውስጥ ነኝ አያለ ነው። Read more »
1. ይህ ስብስብ በሕግ አይን እንዴት ይታያል? የተለያዩ ሰዎች ‹‹ይህ ጊዜያዊ ስብስብ የመንግስት እውቅናና ፈቃድ አለው ወይ?›› ሲሉ መጠየቃቸው ይታወሳል፡፡ ይህንኑ በተመለከተ የተለያዩ የዚህ ስብስብ ዓላማ ተጋሪ የሆኑ የሕግ ባለሙያዎች እንደገለፁልንና በወንጀለኛ መቅጫ ሕግ አንቀፅ 862 በግልፅ እንደተመለከተው፤ የሰብአዊ እርዳታን …
የኪንታሮት ህመም በታችኛ የትልቁ አንጀትና ፊንጥጣ አካበቢ ያሉ የደም መልስ( veins) የደም ቧንቧዎች በሚያብጡበትና በሚቆጡበት ወቅት የሚከሰት የህመም አይነት ነዉ፡፡ የኪንታሮት ህመም ሰገራ በሚወጡበት ወቅት ሲያምጡ፣ ወይም በፊንጥጣና በታችኛዉ የትልቁ አንጀት አካበቢ ባሉ የደም ስሮች ላይ እንደ እርግዝናና ሌሎች ጭነትን …
-በጦርነቱ ቁጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች መሞታቸውና ንብረት መውደሙ ተገልጿል በደቡብ ክልል ሸካ ዞን ይዞታቸው ለኢንቨስተር በመሰጠቱ ምክንያት ምትክ ቦታ እንዲሰጣቸው ጥያቄ በማቅረባቸው ‹‹ለሕግ ተገዢ አይደሉም›› በማለትና በሽፍታነት በመፈረጅ፣ በሸኮዎች ላይ ዕርምጃ ለመውሰድ ሸካዎችን በማስታጠቅና የእርስ በርስ ጦርነት በማነሳሳት የተጠረጠሩ፣ የሸካ ዞን …
የወያኔ የጎሳ ፖለቲካ ውጤት :- የእርስ በርስ ጦርነት በማስነሳት የተጠረጠሩት የሸካ ዞን አስተዳዳሪና ሌሎች ሹማምንት ተከሰሱ Read more »
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የግብርና ኢኮኖሚ እምብርት ከሆኑ ከተሞች አንዷ በሆነችው ቴፒ ከተማ፣ በፀጥታ መደፍረስ ሳቢያ ውጥረት ነግሷል፡፡ ቴፒ ከተማና ዙሪያዋ በፌዴራል ፖሊስ ጭምር ጥበቃ ቢደረግላቸውም፣ የሽፍታ ኃይል በመኖሩ ከሥጋት መላቀቅ እንዳልቻሉ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የከተማው ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡ ለተፈጠረው የፀጥታ ችግር …
ባለፉት ፪፭ ኣመታት ወያኔ የሰለጠነ የሰው ሃይል ኣላፈራም።የሠለጠነ የሰው ኃይል እጥረት ለኢንዱስትሪያላይዤሽን ዕቅዴ ዋነኛ ፈተና ነው ኣለ።ላለፉት ሁለት አሥርት ዓመታት የጠቅላይ ሚኒስትር የኢኮኖሚ ልዩ አማካሪ በመሆን እያገለገሉ የሚገኙት አቶ ነዋይ ገብረ አብ፣ የቀጣዮቹ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዶች ዋነኛ ፈተና የሚሆነው የሠለጠነ …
ባለፉት 25 ኣመታት ወያኔ የሰለጠነ የሰው ሃይል ኣላፈራም።የሠለጠነ የሰው ኃይል እጥረት ለኢንዱስትሪያላይዤሽን ዕቅዴ ዋነኛ ፈተና ነው ኣለ። Read more »
ብዙዎችን በተለይ በወሎ ኮረምና ደቡብ ትግራይ ለሕልፈት ባበቃው የ1977 ዓ.ም. ረሃብ ለዕርዳታ ፈላጊዎች እህል በማድረስ ረገድ ትልቁ ችግር ትራንስፖርት ነበር፡፡ ለተጐጂዎች የሚሆን የዕርዳታ እህል በአሰብ ወደብ ወደ አገር ውስጥ ከገባ በኋላ፣ ድርቅ ወደነበረባቸው ቦታዎች ለማድረስ መንገድ አለመኖሩ በእጅጉ ፈታኝ እንደነበር …
በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል የቀጠለዉ ቁርቁስና፣ ፖለቲካዊ ዉዝግብ አሁን ደግሞ በስፖርቱ ላይ ጫናዉን ያሳረፈ መስሏል። ኢትዮጵያ ከሕዳር 11 ጀምሮ ለ 15 ቀናት በምታስተናግደዉ የምሥራቅና መካከለኛው አፍሪካ ሀገሮች «ሴካፋ» የእግር ኳስ ሻምፒዮናን ኤርትራ እንዳትካፈል ኢትዮጵያ አግዳለች ሲል አሶሺየትድ ፕረስ ያወጣዉን ዘገባ ተከትሎ፤
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – የስለላ እና ደህንነት አባሎቹ እየተሙለጨለጩበት ከባድ ትንቅንቅ ውስጥ ያለው እና ባለፈው ወር በግምገማ በተደጋጋሚ ሲታመስ የነበረው የወያኔ ደህንነት ቢሮ በአባላቶቹ ላይ አዲስ የአሰራር ስልት ሊዘረጋ መሆኑ ታውቋል::ባለፈው በተደረገው ግምገማ የተባረርት እንዲሁም ከደረጃቸው ዝቅ ያሉ እና …
ወንዶች ሆይ ቀኑ ከፍቷልና መቀመጫችሁን ጠብቁ /እውነተኛ ገጠመኝ/ ከቦሌ ወደ ሳሪስ በሚወስደዉ መንገድ ላይ ከመሼ ታክሲ እየጠበኩ ነበር፡፡ ስዓቴን ስመለከት ሁለት ሰዓት ተኩል ይላል፡፡ የተከራየሁበት ግቢ በር ሦስት ሰዓት ላይ ተቆልፎ ስለሚዘጋ በሠላሳ ደቂቃ ውስጥ መድረስ አለብኝ፡፡ በጭንቀት በቆምኩበት በዚህ …
ወንዶች ሆይ ቀኑ ከፍቷልና መቀመጫችሁን ጠብቁ /እውነተኛ ገጠመኝ/ – ዘሐዲስ አየለ አበራ Read more »
Minilik Salsawi ( አንባበ_ ) ድንገተኛው እድገት : ከፖለቲከኝነት ወደ ኢንቨስተርነት – የኢዴፓ ምሪ የነበረው ልደቱ አያሌው በላሊበላ ሆቴል ሊገነባ ነው::የቀድሞ ቅንጅት በታኝ እና የወያኔ ታላላኪ እንደሆነ የሚነገርለት ልደቱ ከወያኔ አገዛዝ 6000 ካሬ ሜትር ቦታ ተረክቧል::በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ የወያኔን ስልጣን …
ድንገተኛው እድገት : ከፖለቲከኝነት ወደ ኢንቨስተርነት – የኢዴፓ ምሪ የነበረው ልደቱ አያሌው በላሊበላ ሆቴል ሊገነባ ነው:: Read more »
ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።
ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና
ከትግራይ የሚሰደዱ በርካታ ወጣቶች ከፍተኛውን ቁጥር ይይዛሉ · በአንድ ፍተሻ ጣቢያ ብቻ በቀን ከ100 በላይ ስደተኞች ይያዛሉ · በጥቃቅንና አነስተኛ ተደራጅተው ብድር የወሰዱ ወጣቶች ገንዘቡን ይዘው ይሰደዳሉ በተሽከርካሪና በእግር የሀገሪቱን ድንበር አቋርጠው በህገወጥ መንገድ ወደ አረብ አገራት የሚሰደዱ ወጣቶች ቁጥር …
ህገወጥ ስደት በከፍተኛ ደረጃ ተባብሷል:: ከትግራይ የሚሰደዱ በርካታ ወጣቶች ከፍተኛውን ቁጥር ይይዛሉ Read more »
ሰሞኑን ባህር ዳር ላይ የህወህት ስኬት የሆነው የአማራ እልቂት በራሱ በአማራው እየተዘከረ ይገኛል። የአማራ ህዝብም «በግ ካራጁ ኋላ እንደሚጎተት» እየተጎተተ ሞቱን እያነገሰ ገዳዮቹን አበጃችሁ እያለ ያለበት ሁኔታ ነው ያለው። ይህንን እንድል ያስደፈረኝ «35ኛውን የብዓዴን ዝክረ በዓል» ለማክበር የተሰበሰበው አማራ ሁሉ …
ወሲብ ፈጣሪ ለሰው ልጆች ካደላቸው ተፈጥሮአዊ እርካታ ማግኛ መንገዶች አንዱ ነው፡፡ በአግባቡ ከተጠቀሙበት። የወሲብ እርካታን/ፍላጎት የማጣት ችግር በሁለቱም ፆታዎች ሊታይ የሚችል ሲሆን በባህልና በልማድ ምክንያቶች በይፋ አይወራም። በዚህ ምክንያት ስንቱ እደተቸገረ ስንቱ ትዳሩ እንደፈረሰ ቤቱ ይቁጠረው። ይህ ችግር በተለምዶ ‹‹ስንፈተ …
የወሲብ እርካታን/ፍላጎት ማጣት (በዶር ቤተል ደረጀ – የማህፀን እና ጽንስ ስፔሺያሊስት) Read more »
ኢሕአዴግን ወደ መቃብር ለማውረድ ለትግሉ መቀጣጠል የእያንዳንዳችን ሚና በጽናት ይጠበቅብናል። #Ethiopia #EPRDF #EthiopianOppositionparties #MinilikSalsawi Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) :- ከሕወሓት/ኢሕአዴግ ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን የጠበቃችሁ፤ ከሕወሓት/ኢሕአዴግ ሥልጣን መጋራት የፈለጋችሁ፤ ከሕወሓት/ኢሕአዴግ የእምነት፣ የፕሬስና የሃሳብ ነጻነት የጓጓችሁ፤ ‘ከሕወሓት/ኢሕአዴግ ጋር ተስማምቶ መሥራት ይቻላል’ የምትሉ፤ ተስፋ …
ኢሕአዴግን ወደ መቃብር ለማውረድ ለትግሉ መቀጣጠል የእያንዳንዳችን ሚና በጽናት ይጠበቅብናል። Read more »
በአገራችን በስፋት ከሚተረክላቸው ፓርቲዎች መካከል ኢህአፓ ግንባር ቀደሙ ነው፡፡ ይሁንና ‹‹ያ ትውልድ›› ተብሎ የሚነገርለትን ያህል ሳያበረክት በአጭሩ ተቀጭቷል፡፡ ለዚህም በዋነኝነት ከሚነሱት ምክንያቶች መካከል አንዱ በፓርቲው ውስጥ የተነሳው ‹‹አንጀኝነት›› ነው፡፡ በፓርቲው ‹‹የአንጃ›› ታሪክ በነ ብርሃነ መስቀል ረዳና ጌታቸው ማሩ የሚመራው ቡድን …
በኢትዮጵያ ኬንያ ድንበር ከፍተኛ ውጥረት ነግሷል::በኢትዮጵያ ኬንያ ድንበር በኦነግ ወታደሮች እና በወያኔ ወታደሮች መካከል ጦርነት መደረጉን ተከትሎ የኦነግ ወታደሮች ወደ ኬንያ ሸሽተው ድንበር ዘልቀዋል በሚል ጥርጣሬ አሰሳ ላይ የነበሩ የወያኔ ወታደሮች ሶስት የኬንያ የፖሊስ መኮንኖችን መግደላቸው አንድ የኬንያ ጋዜጣ አስታወቀ:: …
በኢትዮጵያ ኬንያ ድንበር ከፍተኛ ውጥረት ነግሷል:: ሶስት የኬንያ የፖሊስ ኦፊሰሮች በወያኔ ወታደሮች ተገደሉ:: Read more »
የልቤን ምጥ ልፃፈው ብዬ ደጋግሜ ብዕሬን ይዤ ወረቀቱ ላይ ብፅፍም እንደተራበው ወገኔ ሆድ ብዕሬ ባዶ ሆኖ ቀለም አልነጥበው አለ፡፡ በቅሊንጦ ማጎሪያ ቤት ሰማይ ስር ነፍሴ ሀዘን አቆርዝዛ በማይገፉ ቀንና ሌሊቶች ውስጥ ባዘነች፡፡ ለወትሮው ወገኔ እንደከፋው ስሰማ እንደወፍ በርሬ ችግሩን ልጋራው …
የሀብታሙ አያሌው መልዕክት ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ? በሞት ጥላ መካከል ብሄድ እንኳን ክፉን አልፈራም !!! Read more »
• ‹‹የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የፖለቲካ ቁርጠኝነት ማነስ ኢትዮጵያን ከመፍትሄ አካልነት ወደ ችግርነት እያንደረደራት ነው›› • ‹‹በቀጠናው የሚደረገው የእሳት ማጥፋት ፖለቲካ ኢትዮጵያን ወደ አለመረጋጋት እየመራ ነው›› ኢ/ር ይልቃል ጌትነት በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት በኢትዮጵያና በአፍሪካ ህብረት …
Sport News #Ethiopia Wetatoch Dimts —– ስፖርት ዜና የ#ኢትዮጵያ ወጣቶች ድምፅ [youtube http://www.youtube.com/watch?v=pQ08d4RuMm4]
ይድረስ ለሀፍረተ ቢሱ ብአዴን እና ለ35ኛ በዓል አክባሪዎች (ግልፅ ደብዳቤ ከቂሊንጦ እስር ቤት) ፅሁፍ ዝግጅት – ዘመነ ምህረት (የቀድሞው መኢአድ ም/ፕሬዝደንት) (አቶ አሸናፊ አካሉ አበራ ሀሳብን በማንሳት አግዞኛል) ይህንን ፅሁፍ በአማራ ስም አማራውን ለሚያቆስለውና ለህወሓት ስሪት ለሆነው ብአዴን አመራሮችና አባላት …
ይድረስ ለሀፍረተ ቢሱ ብአዴን እና ለ35ኛ በዓል አክባሪዎች – ዘመነ ምህረት (ግልፅ ደብዳቤ ከቂሊንጦ እስር ቤት) Read more »
በተለያዩ ርቀቶች 27 የዓለም ክብረ ወሰኖችን የሠበረውና በቅርቡም የምንጊዜውም የዓለም ምርጥ አትሌት ተብሎ የተመረጠው ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ከነገ በስቲያ እሁድ በይፋ ከአትሌቲክሱ ዓለም ይሰናበታል።
በኢትዮጵያ በዝናብ እጥረት የተነሳ በተከሰተው ድርቅ 8.2 ሚሊዮን ሰዎች የምግብ ዋስትና ችግር እንደገጠማቸው የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምጣኔ ሀብት አማካሪ አቶ ንዋይ ገብረዓብ ለአሜሪካ ድምጽ ሬድዮ ገልጸዋል።
በተለያዩ የማላዊ እስር ቤቶች የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞች በቅርቡ ወዳገራቸው እንደሚጓጓዙ፣ IOM-ዓለማቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅትና ማላዊ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለቪኦኤ ገለጹ። ይህ የተገለጸው ዋና ጽ/ቤታቸው ኬንያ-ናይሮቢ የሆነውና ማላዊንም የሚያካትቱት አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በትናንቱ ዕለት ማላዊ ተገኝተው እዚያ ለሚገኙ የIOM, የMSF-ድንበር-የለሽ የሐኪሞች ድርጅትና የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ አባላት ባረረጋገጡበት ወቅት ነው።
ኀዳር ፲ (አስር) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ ክልል በጉጂ ዞን የሚኖሩ የተለያዩ ብሄረሰቦች በአንድ ላይ በመሆን ያቀረብነው የመልካም አስተዳደር እና የፍትህ ጥያቄ ካልተመለሰ የህዝባዊ እምቢተኝነት ተቃውሞአቸውን እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል። የዞኑ የአገር ሽማግሌዎች፣ ታዋቂ ሰዎችና የአካባቢው ባለስልጣናት በአንድነት ሆነው ኦሮምያ ክልል በመሄድ ጥያቄ ቢያቀርቡም፣ መልስ ሊያገኙ አልቻሉም። ጥያቄያቸውን ይዘው ወደ ጠ/ሚኒስትሩ ጽ/ቤት ማምራታቸውንም ጉዳዩን በቅርብ …
ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።
ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)
የአዲስ አበባና የኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ የጋራ ማስተር ፕላንን በተመለከተ፤ የፌድራል መንግስትም ሆነ የኦሮሚያ ምክር ቤት፤ ሕዝብን ጠርቶ ያላወያየበት ምክንያት፤ የኦሮሞ ወይም የአከባቢ አርሶ አደሮችን አፈናቅለዉ መሬት ዘረፋ ላይ የተመሰረተ እንቅስቃሴ ለማድርግ በመታቀዱ ነዉ ሲሉ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ ከፍተኛ አመራሮች ተናገሩ።
ጥቂት ስለ ሸዋሮቢት እስር ቤት ናትናኤል ያለምዘውድ በንጉሱ ዘመን እንደተመሰረተ የሚነገርለት የሺዋሮቢት ማረሚያ ቤት ከአ.አ በደብረ ብርሃን ጠመዝማዛውን መንገድ ተከትሎ ከተጓዙ በኋላ ከተራሮች ግርጌ የሚገኝ ረባዳ መሬት ላይ የሰፈረ ማረሚያ ቤት ነው፡፡ በዚህ ማረሚያ ቤት ውስጥ አራት ዞኖች ያሉ ሲሆን …
ረዥም ጉዞ የሚጠብቀን መንገደኞች መተማመን ይገባናል፡፡ በአንድ ልብ የማይጓዙ መንገደኞች አገር አይገነቡም፡፡ ይልቁንም ቶሎ የመፈራረስ፣ እርስ በርስ የመጠራጠር፣ አንዱ አንዱን ለመጣል የመጣር፣ የመተነኳኮስና የመካካድ ባህሪ ያነግሳሉ፡፡ ተቋማዊ አደረጃጀታቸውን ጥያቄ ላይ የሚጥለው ይህን ዓይነት ባህሪ ሲኖር ነው፡፡ ቡድናዊነትና ወገናዊነት ከበዛ መንገዶች …
እየተሞዳሞዱ ሥራ በሚያንቀሳቅሱበት መልካም አስተዳደርን መመኘት የዋህነት ነው፡፡ Read more »
የወያኔ አገዛዝ ዋና ደጋፊ የሆኑት ቢሊየነሩ መሃመድ አላሙዲን በአሜሪካን አትላንታ በኢትዮጵያ ሪቭው አዘጋጅ በጋዜጠኛ ኤሊያስ ክፍሌ ላይ የከፈቱት ክስ ውድቅ መሆኑ ታወቀ:: በአትላንታ የሚገኘው ፍርድ ቤት አላሙዲን እና ግብረ አበሮቹ እነ ጀማል አህመድ ከነሃሴ 2012 ጀምሮ በጠበቃቸው ዲኤልኤ በኩል በኢትዮጵያ …
አቶ አላሙዲና የዘረፋ ግብረአበሮቹ በአሜሪካ ፍርድቤት ሽንፈትና ቅሌት ተከናነቡ:: Read more »
‹‹…ይወስዳል መንገድ፣ ያመጣል መንገድ
አንድ የሚጠላ፣ አንድ የሚወደድ…››
ኀዳር ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባለፈው ማክሰኞ ሸዋ ሮቢት በቀወት ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው የነበሩ እስረኞች በሙሉ ያመለጡ ሲሆን፣ እስረኞቹ እስካሁን አልተያዙም። አብዛኞቹ እስረኞች በህገወጥ መንገድ ትነግዳላችሁ ተብለው የተያዙ ነበሩ። እስረኞቹ ሌሊት ላይ የጭቃ ቤቱን ግድግዳ በውሃ አርሰው ከቀደዱት በሁዋላ ሁሉም በአንድ ላይ አምልጠዋል። ካለፈው ማክሰኞ ጀምሮ እስረኞችን ለመያዝ ፍተሻ በመካሄድ ነው። …
የኢትዮጵያ መንግስት በሙስሊሙ ማህበረሰብ የእምነት ጉዳዮች በይፋ ጣልቃ መግባቱን ተከትሎ ህዝበ ሙስሊሙ በድምጹ የመረጣቸዉ የህዝብ ወኪሎች በአለም አቀፍ ደረጃ ተጽእኖ መፍጠራቸዉ የሚታወቅ ነው። በአይነቱ ልዩ የሆነንን የሰላማዊ ትግል ዘይቤን የቀየሱት የህዝበ ሙስሊሙ ወኪሎች፤ በኢትዮጵያ መንግስት የደህንነት ባለስልጣናት ለከፍተኛ መከራና ስቃይ …
የህዝበ ሙስሊሙ ወኪሎች ከከፍተኛ የአሜሪካ የዉጭ ጉዳይ መቤት ልኡካን ጋር መገናኘታቸዉ ታወቀ Read more »
የዞን ዘጠኝ የድረ-ገጽ ጻሕፍት አባል የሆነው ዘላለም ክብረት የድንበር የለሽ የጋዜጠኞች ተሟጋች ድርጅት ሽልማትን ለመቀበል ወደ ፈረንሳይ ለመጓዝ ሲሞክር ተከለከለ። በእስር ቆይተው ከተፈቱት ጋዜጠኞችና የድረ-ገጽ ጻሕፍት መካከል ፓስፖርቶቻቸው ያልተመለሰላቸው ወደ ቀድሞ የስራ ገበታቸው መመለስ የተከለከሉ መኖራቸውንም አስታውቀዋል።
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) : የቀድሞውን ወታደራዊ ስርኣት ለመጣል የአሁኑን የሽምቅ ሽብራዊ መንግስት ለማንገስ በበረሃ ትግል የተሳተፉት የኢሕኣዴግ ድርጅቶች በሃገሪቱ የትግል ታሪክ ውስጥ ጉልህ ድርሻ አላቸው::በኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ስራትን ለማስፈን እጅ ለእጅ ተያይዘን በጋራ ታግለን ህዝባዊ ነጻነትን እናረጋግጣለን በማለት ጫካ የተደባለቁት …
በሕወሓት የበላይነት የብአዴን አስረሽ ምችው – ፈንጠዝያ ባርነት እስከመቼ ? Read more »
እነ የሺዋስ አሰፋ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መልዕክት አስተላለፉ ‹‹ርሃቡን ለዓለም ለማሳወቅ ከፍተኛ የህዝብ ግንኙነት ስራ መሰራት አለበት›› በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር የሽብርተኝነት ክስ ተመስርቶባቸው በፌደራል ክፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነፃ እንዲሰናበቱ ከተበየነላቸው በኋላ አቃቤ ህግ ይግባኝ ጠይቆባቸው …
እስር ቤት የሚገኙት የሰማያዊ፣ የአንድነትና የአረና ፓርቲዎች አመራሮች በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለህዝብ መልዕክት አስተላለፉ፡፡ Read more »
ከኤፍል ታወር የገዘፈች፣ የፓሪስ የፍቅር ሃውልት – ኤልሳ!… . እሷ ለልጇ የተተኮሰን የአሸባሪ ጥይት፣ በደረቷ የተቀበለች እናት ናት! (በሰሞኑ የሽብር ጥቃት የተከሰተ እውነተኛ ታሪክ) . . ኤልሳ ዴልፕላስ ሙዚቃ ትወዳለች፡፡ ስለምትወድም ነው፣ ያለፈችዋን አርብ ከብቸኛ ልጇ ከሉዊስ እና ከእናቷ ፓትሪሺያ …
ቢቢኤን በዛሬው ኅዳር 8 ዝግጅታችን http://goo.gl/kBkE2M -በአፋር ክልል ያለው የድርቅና ረሃብ ምን ይመስላል የቢቢኤን ተባባሪዎች ከአፋር ክልል ነዋሪዎች ጋር ቆይታ አድረገዋል -የአንድ ብር ሳንቲም እጥረት መከሰቱን ኢቲቪ በቢዝነስ ዘገባው ገለጹ የሳንቲም ማሰባሰብ መርሃግብሩ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ተባለ ታላቁ አሊም ሸህ …
የአንድ ብር ሳንቲም እጥረት መከሰቱን የሳንቲም ማሰባሰብ መርሃግብሩ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ተባለ Read more »
ከዲሞክራሲያዊነት ወደ ‹‹ ልማታዊ ነት›› የተሸጋገረው ድርቅን ወደ ድርቅና ያሸጋገረው መንግስታችንን ስንዳስስ፤ 1.ዲሞክራሲያዊ መንግስት –ለዜጎች ሰብአዊና ዲሞክራሲዊ መብቶች ቅድሚያ የሚሰጥና የአስተዳደሩ ፖሊሲ ትኩረት ያደረገ፤ 2.ልማታዊ መንግስት– ከዲሞክራሲ ይልቅ ልማትን በማስቀደምና የፖሊሲው ትኩረት በማድረግ የሚመራ መንግስት፤ 3.ድርቅ — የውኃ/እርጥበት እጥረት፣ 4.ድርቅና— …