‹‹ 
 ዹዘይላን በር ነገር በሚቻልዎ ነገር ሁሉ ተጣጥሚው በእኔ ዕጅ ቢሆን እንኳን በሐሚርጌ፣ በአሩሲ፣ በኚንባታ፣ በጅማ፣ በኹፋ ያለን ነገር ሁሉ በዘይላ አደርገው ነበር። ይህም ማለቮ ለእርስዎ እንዳይ቞ግርዎ ባውቀው ዚኢትዮጵያ ልጆቜ በንጉሥ ኡምቀርቶ ብርታት ዹዘይላ በር እጃቜን ተመልሶ ገባ እንዲሉ ሥምዎ በነገሥታት ታሪካቜን ይተኚላል። 
 ››
ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ፣ እ.አ.አ በ1876 ዓ.ም ለንጉሥ ኡምቀርቶ ኚላኩት ደብዳቀ […]

በቅርቡ መንግስት ኚሜብርተኝነት ጋር በተያያዘ ዚተጠሚጠሩ ፖለቲኚኞቜ እና ጋዜጠኞቜን ማሰሩ ይታወሳል። ኚእነዚህም እስሚኞቜ መካኚል ዚአንድነት ፓርቲ አመራር አባላት ይገኙበታል። በእነዚህ ጉዳዮቜ ዙሪያ፣ ኚፓርቲው ዋና ጾሐፊ አቶ ዳዊት አስራደ ጋር ባልደሚባቜን ኀልያስ ገብሩ አጠር ያለ ቃለ-ምልልስ አድርጓል።
ዚፓርቲያቜሁን ሊቀ-መንበር እና ዚሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አንዷለም አራጌን ጚምሮ ፣ ዚብሔራዊ ምክር ቀት አባሎቻቜሁ ኚታሰሩ በኋላ ያላቜሁ ዚሥራ እንቅስቃሎ […]

«መንግስት በምንም አይነት መልኩ ሊተቜ አይገባም» ዹሚል አላማን ለማራመድ ሲባል ብቻ ዹግል ኀፍ.ኀም ሬዲዮ ዚተሰጣ቞ው አንዳንድ ኢትዮ-አሜሪካዊያንፀ ኹሌላው ጊዜ በተለዹ ሁኔታ በአውራምባ ታይምስ ጋዜጣ ላይ መያዣ መጚበጫ ዹሌለው ዹመንደር ፕሮፓጋንዳ በመንዛት ዚተጠመዱበት ሰሞን ነው።
ዚጣቢያው ባለቀቶቜና አዘጋጆቜ ነን ባዮቹ ጥንዶቜ ‹‹ዚጋዜጠኞቜ ክብ ጠሚጎዛ›› በሚሉትና አንድም ጋዜጠኛ በማይገኝበት ፕሮግራማ቞ው፣ ይህቺኑ አውራምባ ታይምስ ጋዜጣን ዋነኛ ዚመነጋገሪያ አጀንዳ቞ው አድርገው […]

በሁለተኛው ዹአለም ጊርነት ወቅት ዹጀርመን ባህር ኃይል መርኚቊቜ እንግሊዝን ኚበዋል፡፡ ዚአሜሪካ መርኚቊቜ ሲቀርቡ፣ በቀላሉ በጀርመን ሰብማሪንስ (በባህር ላይ ሳይሆን በባህር ውስጥ ዚሚሄዱ መርኚቊቜ) እዚተጠቁ በብዛት ይሰምጡ ጀምር፡፡ ጀርመኖቜ በባህር ላይ ጊርነት በበርካታ መስፈርቶቜ ዚበላይነት ነበራ቞ው፡፡ አሜሪካኖቜ ግን መርኚቊቜ በሰጠሙባ቞ው ቁጠር፣ ሜንፈት ተቀብለውና ተስፋ ቆርጠው አልተቀመጡም፡፡ ሌሎቜ መርኚቊቜ በብዛት ማሰማራት ጀመሩ፡፡ ወደ እንግሊዝ ዚሚላኩት ዚአሜሪካን መርኚቊቜ፣ […]

ዹዚህ ጜሑፍ ዋና ዓላማ ዹደርግ አሃዳዊነትንና ዚኢህአዎግ ፌደራላዊነትን በተመለኹተ ውይይት ለመክፈት ነው፡፡ ይህን ጉዳይ በተመለኹተ እኔ አንድ አቋም አለኝ፡፡ ይህ አቋም ዚኢህአዎግ ፌደራላዊነት ኹደርግ አሃዳዊነት ዹሚለዹው በቅርጜ ብቻ ነው፡፡ በይዘት ወይም በአፈጻጞም ወይም በተግባር ግን ሁለቱም ኹሞላ ጎደል ተመሳሳይ ናቾው ዹሚል ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ዚኢሕዎግ ስርዓት ፌደራላዊ ያልሆነ ፌደራሊዝም ነው ማለት ነው፡፡
በውይይቱ ሂደት ይህ አቋም […]

– እስካሁን እስሚኞቜ ያሉበትን ሁኔታ ማወቅ አልቻልንም (አንድነት ፓርቲ)
– ቀተሰብ፣ ዚትግል አጋሮቻ቞ውና ዹህግ አማካሪ እንዲያገኛ቞ው ተኹልክለዋል (ቀተሰብ)
– ዚእስር አያያዛ቞ው አሳስቊናል
በእስር ላይ ዚሚገኙት ዚአንድነት ፓርቲው ም/ሊቀመንበርና ዚህዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ አንዱዓለም አራጌ፣ ዚብሔራዊ ም/ቀቱ አባላት ዚሆኑት መ/ር ናትናኀል መኮንንና መ/ር አሳምነው ብርሃኑ እንዲሁም ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋና ጋዜጠኛ ስለሺ ሀጐስ ዚመኢዎፓ ዋና ፀሐፊ አቶ ዘመኑ ሞላ […]

አቶ በቀለ ገርባ በ1954 ዓ.ም በወለጋ ክፍለ ሀገር ልዩ ቊታው ቩጂ ድርመጂ በሚባል አካባቢ ተወልደው ዚመጀመሪያና ዹሁለተኛ ደሹጃ ትምህርታ቞ውን በዚያው አካባቢ አጠናቀዋል፡፡ ኚዚያም በጀና ሚዳትነት በመማር አሁን ደቡብ ክልል ጌዲኊ ዞን በሚባል ቊታ ለሹጅም ዓመታት አገልግለዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ በአዲስ አበባ ዩኒቚርስቲ እንግሊዘኛ ቋንቋ በመማር ዚመጀመሪያ እና ዹሁለተኛ ድግሪያ቞ውን (BA&MA)አግኝተው አዲስ አበባ ዩኒቚርስቲ ውስጥ በመምህርነት […]

ስለሺ ሐጎስ ዹተወለደው መቂ ኹተማ በ1972 ዓ.ም ነው፡፡ እስኚ 8ኛ ክፍል ድሚስ በዚያው በመቂ ኹተማ በካቶሊክ ት/ቀት ተምሯል፡፡ ሁለተኛ ደሹጃ ትምህርቱን ያጠናቀቀው በዝዋይ ኹተማ ነው፡፡
ስለሺ ሐጎስ በኮተቀ መምህራን ኮሌጅ በመግባት በሥነ ጜሑፍ በዲፕሎማ ተመርቋል፡፡ እንዲሁም በአዲስ አበባ ዩኒቚርስቲ በመግባት በ቎አትር ጥበብ ዚመጀመሪያ ዲግሪውን አግኝቷል፡፡
ስለሺ ሐጎስ በሰላማዊ መንገድ ለውጥ ለማምጣት ኚሚጥሩ ወጣቶቜ አንዱ ነው፡፡ በሚያቀርባ቞ው ግጥሞቜ […]

ስለሉሉ ዚማያውቅ እንደማይኖር ተስፋ አለኝ፡፡ ሉሉ ዹአፄ ኃይለ ሥላሀ ድንክ ውሻ ናት ወይም ነበሚቜ – አፈሩ ይቅለላት ነፍሷም በዹማነ ብፁዓን አክልብት ይቀመጥና፡፡ ያቺ ድንክዬ ዹጠቅል ውሻ ታሪኚኛ ነበሚቜ አሉፀ ተራ ውሻ አልነበሚቜም፡፡ ሥልጣንና ማዕሹጓ ራሱ ኚንጉሡ በታቜ ኚመኳንንትና መሣፍን በላይ እንደነበር በወቅቱ ለንጉሡ ቅርበት ዚነበራ቞ው አሹጋዊ ዜጎቜ ያስታውሳሉ፡፡ ዹማንንም እግር እዚሄደቜ ብትዘነጥል ኚመብቶቿ አነስተኛው ነበር፡፡ […]

ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

ፍኖት- ዹጋዜጠኛ ሰርክዓለም ፋሲል ንብሚቶቜ እስኚአሁን አልተመለሱም
ባለፈው መስኚሚም 3 ቀን 2004 ዓ.ም በ “ሜብር” ተጠርጥሚው በእስር ላይ ዚሚገኙት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በዕለቱ ሲያሜኚሚክሯት ዚነበሚቜ ዚቀት መኪና እና መተዳደሪያ቞ው ዹሆነውን ዚቀት ኪራይ ገንዘብ እንዲመለስላ቞ው ጋዜጠኛ ሰርክዓለም ፋሲል ቢጠይቁም እስኚአሁን እንዳልተመለሰላ቞ው ገለፁ፡፡
ወ/ሮ ሰርክዓለም ንብሚቶቹ በተያዙበት ማዕኹላዊ እስር ቀት ሄደው ዚመኪናውን ሊብሬ በእሳ቞ው ስም እንደሆነ ለማስሚጃነት ቢያቀርቡም “ኚአንቺ […]

አንድነት ለዎሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)
UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY(UDJ)
ቁጥር፡-አንድነት /437/2ዐዐ4
ቀን 15/01/2004 ዓም
ግልጜ ደብዳቀ
ለኢትዮጵያ ፌዎራላዊ ዎሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ
አዲስ አበባ
ጉዳዩ፡- በሜብርተኝነት ስም ዚታሰሩ አባሎቻቜንና ሌሎቜ ዜጎቜ ሕገ-መንግሥታዊ መብታ቞ው እንዲኚበርላ቞ው ስለመጠዚቅ፣
በኢትዮጵያ ሕዝብ ዘንድ በግልጜ እንደሚታወቀው አንድነት ለዎሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) በሕገ-መንግሥቱ በተደነገገው ዚመደራጀት መብት መሠሚት ሕጋዊና ሠላማዊ በሆነ መንገድ ለዜጎቜ ሰብዓዊና ዎሞክራሲያዊ መብቶቜ እውን […]

አቶ ኊልባና ሌሊሳ በምዕራብ ሾዋ ጹሊ ወሚዳ በ1966 ዓ.ም ተወለዱ፡፡ ዚመጀመሪያና ዹሁለተኛ ደሹጃ ትምህርታ቞ውንም በተወለዱበት አካባቢ አጠናቀው ወደ መንግስት ኹፍተኛ ዚትምህርት ተቋም በመግባት በግብርና ዲፕሎማ አግኝተዋል፡፡ ኚዚያም በመንግሥት ግብርና ሚኒስ቎ር መስሪያ ቀት ውስጥ በሚተዳደር መስሪያ ቀት ተቀጥሚው ለዓመታት አገልግለዋል፡፡ በማታው መርሐ ግብር በአምቩ ዩኒቚርስቲ ዚትምህርት ደሹጃቾውን ለማሻሻል እዚተማሩ እንደነበርና በተደሚገባ቞ው ዚፖለቲካ ጫና ምክንያት ሥራ቞ውን በፈቃዳ቞ው […]

ወ/ት ሊዲያ ዘሪሁን ትባላለቜ፡፡ በእስር ላይ ዚሚገኙት ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ /ኢብአፓ/ ፕሬዝደንት ዚአቶ ዘሪሁን ገ/እግዚአብሔር ልጅ ናት፡፡ በአባቷ ዙሪያ ባልደሚባቜን ብዙአዚሁ ወንድሙ አነጋርሯታል፡፡ መልካም ቆይታ፡፡
አባትሜ አቶ ዘሪሁን ገ/እግዚአብሔር በእስር ላይ እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡ በመጀመሪያ አቶ ዘሪሁን ዚት ተወለዱ?
ወ/ት ሊዲያ- ዘርዬ ዹተወለደው እዚሁ አዲስ አበባ ኹተማ ልዩ ሥፍራው መርኚቶ ዚሚባል አካባቢ ነው፡፡
ስለ ትምህርታ቞ው አጠቃላይ ሁኔታ ብትገልጪልኝ […]

ሜብርተኝነት ኹ20ኛው ክፍለ ዘመን ሁለተኛው አጋማሜ ጀምሮ እዚጎላ ዚመጣ አደገኛ ክስተት ነው፡፡ አደገኛነቱ በግልጜ ዚታዚው እ.ኀ.አ መስኚሚም 11 ቀን 2001 ዓ.ም በኒውዮርክ ኹተማ ዚንግድ ማዕኹል ላይ በደሹሰው ጥቃት ነው፡፡ በዚህ ጥቃት በሺዎቜ ዹሚቆጠር ህይወት ጠፍቷል፡፡ በቢሊዮን ዶላር ዚሚገመት ንብሚት ወድሟል፡፡ ኹሁሉም በላይ ደግሞ በዓለም ሕዝብ ላይ ይህ ነው ዚማይባል ድንጋጀና ዚመንፈስ ጭንቀት ፈጥሯል፡፡
ተንታኞቜ ሜብርተኝነትን በተለያዚ […]

ኚሜብር እንቅስቃሎ ጋር በተያያዘ ተጠርጥሚው ዚታሰሩትን ጋዜጠኞቜ ሁኔታ ዓለም አቀፍ ዚጋዜጠኞቜ ፌዎሬሜን (IFJ) ተወካዮቜ በአካል ተገኝተው እንደጎበኙ ዚኢትዮጵያ መንግስት መፍቀዱን ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ዚጋዜጠኞቜ ህብሚት (ኢብጋህ) አስታወቀ።
ዋና ጜህፈት ቀቱ በቀልጂዚም ብራሰልስ ያደሚገው ይኾው ፌዎሬሜን ልኡካኑን ወደ ኢትዮጵያ ዚሚልክበት ዋንኛ ዓላማ ኚሜብርተኝነት እንቅስቃሎ ጋር በተያያዘ ተጠርጥሚው በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዹሚገኙ ኢትዮጵያውያንና አውሮፓውያን ጋዜጠኞቜ ዹሚደሹግላቾውን አያያዝና ዚታሰሩበትን ትክክለኛ […]

ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ሰሞኑን መንግሥት በአሞባሪነት ዚጠሚጠራ቞ውን ጋዜጠኞቜና ዹተቃዋሚ ፖለቲኚኞቜ ማሰሩ ይታወሳል። በዚህ ጉዳይ እና በሌሎቜ ተያያዥ ወቅታዊ ጉዳዮቜ ዙሪያ፣ ሱራፍኀል ግርማ ኚቀድሞ ዚኢፌዎሪ ፕሬዝዳንት እና ኚወቅቱ ዚአንድነት ለዎሞክራሲ እና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)ሊቀ-መንበር ኚሆኑት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ጋር ቆይታ አድርጓል።
ዹሰሞኑን ዚእስር ሂደቶቜ ፓርቲው እንዎት ነው ዹሚመለኹተው?
በተለያዩ ጊዜያት እንደገለፅነው፣ ፓርቲያቜን ለፍትህና ለዎሞክራሲ ይታገላልፀ ሕገመንግስቱ ያጎናፀፈንን መብቶቜ […]

‹‹ 
 ዹዓለም ሰላም ጠበቃዎቜ፣ ዚጋዜጠኞቜ መብቶቜ አስኚባሪዎቜ፣ ዚዎሞክራሲ ሰብዓዊ መብቶቜ ተቆርቋሪዎቜ ነን ለሚሉትና በውጭ ሀገር ዚተቃዋሚዎቜ አፈ ቀላጀዎቜ በመሆን በማገልገል ላይ ለሚገኙ አንዳንድ ኃይሎቜ ሳይንበሚኚክ፣ መንግሥት ዹአመፅ ጥሪ ዚሚያቀርቡትን ኃይሎቜ ሀይ ሊላቾው ይገባል 
 ››
ኹላይ ዹሰፈሹው ጥቅስ ዹተወሰደው መስኚሚም 12 ቀን 2004 ዓ.ም ለንባብ ኹበቃው አዲስ ዘመን ጋዜጣ ገፅ 3 ነው። ምንጣፍ ዚሚያክለው አዲስ […]

ቢሯቜን እስኪጞዳ ድሚስ በር አካባቢ ቆም ብለን ብሶታቜንን ማውራት በተለይ ኚቅርብ ጊዜ ወዲህ በጣም ዚለመድነው ነገር ሆንዋል፡፡ እናም ዛሬ ጧት እንደልማዳቜን ወደ አራት ዹምንጠጋ አለቃና ምንዝሮቜ ባንድነት ቆመን ስለኢትዮጵያና ስለዓለም ወቅታዊ ዚፖለቲካ ትኩሳት ማውራት ያዝን፡፡ ዹኔን ጫጫሪነት ማንም ያውቃል ብዬ አላስብም፡፡ ሁላቜንም እዚፎገላን በተለይ ስላገራቜን አሳሳቢና አስጚናቂ ሁኔታ ማውራታቜንን ቀጠልን፡፡ ዹሚገርመው ነገር ማንኛቜንም ብንሆን ለፖለቲካና […]

ዘመኑ ሞላ ተወልዶ ያደገው ኹዚሁ አዲስ አበባ ሲሆን፣ ባለትዳርና ያንዲት ሎት ልጅ አባት ነው፡፡ ልጁ ጎበዝ ተማሪ ስለሆነቜ በዚህ ዓመት ዩኒቬርስቲ እንደምትገባ በቅርብ ዚሚያውቋት ይናገራሉ፡፡
ዘመኑ ሞላ ነባር ዹሰላማዊ ትግል ታጋይ ሲሆን ዚኢዎፓ ነባር አባል በመሆኑ በ92 ዓ.ም በተደሹገው ሁለተኛው አገራዊ ምርጫ አ.አ ክልል ተወዳድሮ ነበር፡፡
ቆይቶ ደግሞ ኢዎፓ ዚሚሄድበት መንገድ ስላላማሚውና ስላልጣመው ኚዚያ […]

አካባቢው አንድ ገጠር መንደር ነው፡፡ ዹዘመኑ ዚአካባቢው ገዢ ሕዝቡን ሰብስቊ ሲናገር ይውላል፡፡ ሕዝቡም ዝም ብሎ ያዳምጣልፀ እርሱ ያወራል ሕዝቡን ያዳምጣል። መናገር ሲስለ቞ው «አሁን ተራው ዚእናንተ ነውፀ ሐሳብ መስጠት ትቜላላቜሁ» ይላ቞ዋል፡፡
ሁሉም ዝም ይላል፡፡ «ተናገሩ» ይላል አሁንም በመደጋገም ። አሁንም ሕዝቡ ዝም አለ፡፡ “ጊዜው ዚዎሞክራሲ ነው ፀ ዚፈለጋቜሁትን መናገር ትቜላላቜሁ፡፡ ተርበን፣ ሞተን፣ ቆስለን፣ ጓደኞቻቜን ሞተው […]

በቅርቡ “በሜብርተኝነት”ተጠርጥሚው ዚታሠሩትን እስሚኞቜ «በምን ሁኔታ ላይ አንደሚገኙ ማወቅ አልቻልንም» ሲሉ ቀተሰተቻ቞ውና ዚሥራ ባልደሚቊቻ቞ው ለዝግጅት ክፍላቜን ገለጹ፡፡
ዚአንድነት ፓርቲ ም/ሊቀመንበርና ዚሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ዚሆኑት ዚአቶ አንዱዓለም አራጌ ወንድም ወጣት አብርሃም አራጌ እንደሚለው “ወንድሜ ዚታሠሚበትን ዚእስር አያያዝ ማወቅ አልቻልኩም፡፡ በተደጋጋሚ ለመጠዹቅ ሄጄ ምግብ ተቀብለው ዕቃ ኚመመለስ ውጪ በአካል አግኝቌው አላውቅም”፡ ብሏል፡፡
ዚፓርቲው ማዕኹላዊ ም/ቀት አባላት ዚሆኑት […]

አሣምነው ብርሃኑ ተወልዶ ያደገው ኹዚሁ አዲስ አበባ ነው፡፡ ዚትምህርት ደሹጃው በፊዚክስ ቢ.ኀስ.ሲ ዲግሪ አለው፡፡ ባሁኑ ጊዜ በኢኮኖሚክስ በዲግሪ መርሃ ግብር አዲስ አበባ ዩኒቚርስቲ እዚተማሚ ነበር፡፡ መደበኛ ሥራውም መምህር ነው፡፡
ቀተሰብ አሣምነው ብርሃኑ ገና ወጣት በመሆኑ ለሥራና ለትምህርት እንዲሁም ለነፃነት ተግቶ ኚመሥራት ውጭ ትዳር ለመመሥሚት አስቊ እንደማያውቅ ቀተሰቊቹ ገልፀውልናል፡፡
ዚፖለቲካ አቋምአሳምነው ብርሃኑ አንድነት ፓርቲን ኹመቀላቀሉ በፊት […]

ክቡር ጠ/ሚንስትር ዹሰው ልጅ ዚአገሩን ዚአስተዳደር መሹጃ ካለማጀን ስህተት መፈጠሩ አይቀሬ ቢሆንም በተጓደኝ ዹተፈፀመውንና ዹተደሹገውን በማስታወስ ዚተሠራ ጥፋት መታሚም ይቻላል፡፡ ኹዚህ አንፃር ባገራቜን ዚሚታዚውንና እዚተፈፀመ ያለውን ግዙፍ ስህተት ቅኝ ገዥዎቜ እንኳን ይሠሩታል ብሎ ለመናገር ዚሚኚብድ ይመስለኛል፡፡ ይህንን ጜሑፍ ለመዳፍ ያነሳሳኝ ሀገራዊ ስሜትና ፍቅር እዚቆጠቆጠኝ አላስቆም አላስቀምጥ ስላለኝ ሰሚ ባይኖርም ዚድርሻዬን ልወጣ በሚል ነው፡፡
ኢሕአዎግ ሥልጣን ኚተቆናጠጠበት […]

ኚጥቂት ወራት ወዲህ ገዢው ፓርቲ ስርዓቱ ላይ ዹሠላ ሂስ በመሠንዘር ዚሚታወቁ ዚፖለቲካ ፓርቲ መሪዎቜና ጋዜጠኞቜን ዹማሠር ዘመቻውን ጀምሯል፡፡ ዚእስራት ዘመቻው ማቆሚያ ዚት ጋ እንደሆነ ዚታወቀ ነገር እስካሁን ዚለም፡፡ ዚእስር ዘመቻው ያነጣጠሚው ግን ኚኢህአዎግ አቋም በተቃራኒው ዹቆሙ ግለሰቊቜ ላይ መሆኑ ዚአገራቜንን ዚወደፊቱን ዚፖለቲካ አቅጣጫ አሳሳቢ አድርጎታል፡፡
ኚታሪክ እንደምንማሚው በዓለም ላይ በርካታ አምባገነን መንግስታት ኖሹው አልፈዋል፡፡ አውሮፓን ሲያምሱት […]

ኢህአዎግ ዚዎሞክራሲና ዹህግ ዚበላይነት ጥያቄ ሲቀርብለት ዘወትር ዚሚያሳው መቃብሩን ነው።ዚአንድነት ጥያቄ ሲቀርብ ምላሹ “እኛ ኹፈለሰፍነው አንድነት ውጭ ሌላው አንድነት በኢህአዎግ መቃብር ላይ ካልሆነ በስተቀር ዚማይታሰብ ነው”ዹሚል ነው።ዚመሬት ባለቀትነት ጥያቄ ሲነሳ “ዚመሬት ባለቀትነት ጥያቄ ህያው ዹሚሆነው በኢህአዎግ መቃብር ላይ ብቻ ነው”በማለት ወደ መቃብሩ ያመላክተናል።አንቀፅ 39 በታኝ መሆኑን ህዝብ ሲገልፅ “ዚህዝብ ልጆቜ ዚተሰውለት ዚትግሉ ዹማዕዘን ድንጋይ ነው፣እኔ […]

ዚቊስትን አንድነት ዚድጋፍ ድርጅት በውቅታዊ ህገራዊ ጉዳዮቜ ላይ ዚአካባቢውን ነዋሪዎቜ ለማወያዚት ዚውይይት ፎሹም አዘጋጅታል
Date: Sunday Sept. 18, 2011
Time: 3:00PM
Pl…

ሜብርተኝነት ዹንፁሀንን ሕይወት በጅምላ ዚሚያጠፋ፣ አካልን ዚሚያጎድል፣ ዹሀገርን ሀብት፣ ዚልማት አውታሮቜንና ተቋማትን ዚሚያወድም ኃላፊነት ዹጎደለው ተግባር በመሆኑ ፓርቲያቜን በማያወላውል ቁርጠኝነት ያወግዘዋል፡፡ ሜብርተኝነት በሚያደርሰው ጉዳት ብቻ ሳይሆን ዓላማውም ዚራስን ፍላጎት በሌሎቜ ላይ መጫን በመሆኑ ተቀባይነት ዹሌለው ዚእቢተኞቜና ዚጉልበተኞቜ ድርጊት በመሆኑ አጥብቀን እንኮንነዋለን፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ በሜብርተኝነት ስም ሜብር ዹሚነዛ አካልን አጥብቀን እናወግዛለን፡፡
ዚፓርቲያቜን አቋምና እምነት ኹላይ […]

ኚትላንትና ወዲያ «በሜብር ሥራ ተሰማርተሃል» በሚል ወደ ማዕክላዊ ዚተወሰዱት ዚአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ምክትል ፕሬዘዳንት እና ዚሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ፣ አቶ አንዱዋለም አርጌ፣ በባለቀታ቞ው እና በአባታ቞ዉ ዛሬ እንደተጎበኙ ኚአዲስ አበባ ዹደሹሰን ዜና ያመለክታል።
ዚአቶ አንዱዋለም ባለቀት እና ዚአቶ አንዱዋለም አባት ፣ አቶ አንዱዋለምን ካነጋገሩ በኋላ ፣ አቶ አንዱዋለም በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ፣ በመንፈስ ጠንካራ እንደሆኑ ገልጞዋል።
«በአቶ […]

ፓርቲዉ ዛሬ በሰጠዉ ጋዜጣዊ መግለጫ ለሰላምና ለዲሞክራሲ በሚታገሉ ዜጎቜ ላይ እዚደሚሰ ያለዉ ተግባር እጅግ በጣም አሳፋሪና አሳዛኝ እንደሆነ ጠቅሶ ፣ መሰሚት በሌለዉ በሜብር ክስ ዚታሰሩ ሰላማዊ ዜጎቜ ያለ አንዳቜ ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ፣ ዜጎቜን ዚማሰፈራራትና ዹማወክ ጾሹ-ዲሞክራስያዊ ዘመቻ በአስ቞ኳይ እንዲቆም አሳስቧል።
ጠንካራ ተቃዋሚዎቜ ላይ ኢፍትሃዊ እርምጃ በመዉሰድ ዚሚታወቀዉ ዚመለስ ዜናዊ አገዛዝ፣ ሰሞኑን በነአንዱዋለም አርጌ ላይ ዹወሰደዉ እርምጃ፣ […]

መስኚሚም 5 ቀን 2004 ዓ.ም
ዹአንጋፋዉ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ባለቀት ወ/ሮ ሰርካለም ፋሲል ፣ በባለቀቷ መታሰር ዙርያ በፓልቶክ ኚተሰባሰቡ ኢትዮጵያዉያን ጋር፣ አጭር ቃለ ምልልስ አድርጋለቜ። ወ/ሮ ሰርካለም ዳግመኛ ወደ እሥር ቀት ኹተወሰደዉ ባለቀቷ፣ እስክንድር ነጋ ጋር፣ ኚስድስት አመታት በፊት ለሃያ ወራት በቃሊቲ እሥር ቀት ታስራ ዹነበሹ ሲሆን፣ አንድና ዚመጀመሪያ ልጇን ፣ ናፍቆት እስክንድርን ዚወለደቜዉ […]

“አንድ ለመጀመሪያና ለመጚሚሻ ጊዜ ዹምናገሹው ሃሳብ አለኝ፡፡ እዚተፈፀመ ያለው ተግባር ዹተቃዋሞ ፖለቲካውን ለማፈን ዹተወሰደ እርምጃ ነው፡፡ ኚእንግዲ ወዲያ ፍርድ ቀቱ ዹፈለገውን እርምጃ ሞትም ቢሆን መውሰድ ይቜላል፡፡ ሌላ ዹምሰጠው አስተያዚት ዹለኝም” አቶ አንዱዓለም አራጌ
“በ2004 ዓ.ም. በሀገሪቱ ውስጥ ዚሜብር ተግባር ለመፈፀም በቡድን ተደራጅተው ሲንቀሳቀሱ ማስሚጃ አግኝቌባ቞ዋለው” በማለት በትናንትናው እለት በቁጥጥር ስር ያዋላ቞ው ዚፓርቲ አመራሮቜና ጋዜጠኛ አራዳ […]

መስክሚም 4 ቀን 2004 ዓ.ም
ዚአንድነት ለዲሞርካሲና ለፍትህ ፓርቲ ምክትል ፕሬዘዳንት አቶ አንዱዋለም አርጌ፣ እዉቁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ ዚአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ብሄራዊ ምክር ቀት አባላት አቶ አስማማዉ እና አቶ ናትናዔል ብርሃኑን ጚምሮ አምስት ኢትዮጵያዉያን ፣ ዛሬ ሐሙስ መስኚሚም 4 ቀን ኚሰዓት በኋላ፣ ፍርድ ቀት እንደቀሚቡ ኚአዲስ አበባ ዹደሹሰን ዘገባ ገለጞ።
«መሚጃ ዹበለጠ ለማሰባሰብ ቀናቶቜ ያስፈልጉኛል» […]

መስክሚም 4 ቀን 2004 ዓ.ም
ዚአንድነት ለዲሞርካሲና ለፍትህ ፓርቲ ምክትል ፕሬዘዳንት አቶ አንዱዋለም አርጌ፣ እዉቁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ ዚአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ብሄራዊ ምክር ቀት አባላት አቶ አስማማዉ ብርሃኑን እና አቶ ናትናዔል ጚምሮ አምስት ኢትዮጵያዉያን ፣ ዛሬ ሐሙስ መስኚሚም 4 ቀን ኚሰዓት በኋላ፣ ፍርድ ቀት እንደቀሚቡ ኚአዲስ አበባ ዹደሹሰን ዘገባ ገለጞ።
«መሚጃ ዹበለጠ ለማሰባሰብ ቀናቶቜ […]

መስኚሚም 3 ቀን 2004 ዓ.ም
ዛሬ ኹቀኑ አሰር ሰዓት (10፡00) አኚባቢ ዚአንድነት ለዎሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበርና ዚህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚ቎ ሰብሳቢ አቶ አንደዓለም አራጌ በአገዛዙ ዚዯህንነት ሰዎቜ ታስሮዋል፡፡ በተመሳሳይ ሰዓት እውቁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋም ተይዞዋል፡፡ አንደዓለምና እስክንድር ኚሌሎቜ ሁለት ዚአንድት ፓርቲ አባለት ጋር ኹቀኑ 8፡30 ገዯማ ጀምሮ አንድነት ፓርቲ አኚባቢ በሚገኝ ካፍ቎ሪያ አኚባቢ እሰኚ […]

መስክሚም 3 2004 ዓ.ም
እውቁ ጋዜጠኛ እስክድንር ነጋ፣ ዜጎቜን ዹማሾበርን ተግባር በተያያዙት ዚወያኔ ታጥቂዎቜ፣ መታሰራ቞ዉን ኚአዲስ አበባ ዹደሹሰን ዘገባ ያመለክታል።
ኚጥቂት ሰዓታት በፊት፣ ዚአንድነት ፓርቲ ዚሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ፣ አቶ አንዱዋለም አርጌ መታሰራ቞ዉን መዘገባቜን ይታወቃል።
ትግሉ ወደ ሰላማዊ ትግል መሾጋገር እንዳለበት ዚሚገልጜ ጜሁፍ በቅርቡ ለአንባቢያን ያቀሚቡት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ በሰላማዊ ትግል ዚሚያምኑ፣ ገዢዉን ፓርቲ በተለያዩ […]

መልካም አዲስ ዓመት/እንቁጣጣሜ!
ኚአስ቞ጋሪ ዚእስር ቆይታ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ዚማኚብራትን ዚዛሬዋን እንቁጣጣሜ ኚምወዳቜሁ በስዊድን እና አካባቢዋ ኚምትኖሩ ኢትዮጵያውያን ጋር ላሳልፍ በመቻሌ ደስታዬ ለኚት ዚለውም።
ስለዚህም በዚህ በደመቀ በዓል ላይ እንግዳ ሆኜ እንድገኝ ዹጋበዘኝን በስዊድን ዚኢትዮጵያውያን ማኅበርን እጅግ አድርጌ ላመሰግን እወዳለሁ። ኹዚህም በላይ ኚእስር ሰንሰለት ወጥቌ ዚዛሬዋ ዚነፃነት ቀን ዚእኔ እንድትሆን አቅማቜሁ ዹፈቀደውን ሁሉ በማድሚግ ኹፍተኛ […]

(UDJ) — ዛሬ ኹቀኑ አሰር ሰዓት (10፡00) አኚባቢ ዚአንድነት ለዎሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበርና ዚህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚ቎ ሰብሳቢ አቶ አንዱዓለም አራጌ በአገዛዙ ዚደህንነት ሰዎቜ ታስሮዋል፡፡ በተመሳሳይ ሰዓት እውቁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋም ተይዞዋል፡፡ አንዱዓለምና እስክንድር ኚሌሎቜ ሁለት ዚአንድት ፓርቲ አባለት …

አንዱዓለም አራጌና እስክንድር ነጋ ታሰሩ Read more »

በወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ይመራ ዹነበሹዉና በሕዝብ ዘንድ ኹፍተኛ ተቀባይነትን እያገኝ ዚመጣዉ ዚአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ዋና ጾሃፊ ሆነዉ ኹዚህ በፊት ያገለገሉት እና አሁን ደግሞ በሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊነት ዚሚሰሩት፣ ወጣት አንዱዋለም አርጌ፣ በገዢዉ ፓርቲ ዚደህንንት ሰዎቜ፣ አዲሱ አመት በገና በሁለት ቀናት ዉስጥ፣ ዛሬ፣ ታግተዉ መወሰዳ቞ዉን ኚጥቂት ደቂቃዎቜ በፊት ኚአዲስ አበባ ዹደሹሰን ዘገባ ያመለክታል።

አቶ […]