‹‹ … የዘይላን በር ነገር በሚቻልዎ ነገር ሁሉ ተጣጥረው በእኔ ዕጅ ቢሆን እንኳን በሐረርጌ፣ በአሩሲ፣ በከንባታ፣ በጅማ፣ በከፋ ያለን ነገር ሁሉ በዘይላ አደርገው ነበር። ይህም ማለቴ ለእርስዎ እንዳይቸግርዎ ባውቀው የኢትዮጵያ ልጆች በንጉሥ ኡምቤርቶ ብርታት የዘይላ በር እጃችን ተመልሶ ገባ እንዲሉ ሥምዎ በነገሥታት ታሪካችን ይተከላል። … ››
ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ፣ እ.አ.አ በ1876 ዓ.ም ለንጉሥ ኡምቤርቶ ከላኩት ደብዳቤ […]

በቅርቡ መንግስት ከሽብርተኝነት ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ ፖለቲከኞች እና ጋዜጠኞችን ማሰሩ ይታወሳል። ከእነዚህም እስረኞች መካከል የአንድነት ፓርቲ አመራር አባላት ይገኙበታል። በእነዚህ ጉዳዮች ዙሪያ፣ ከፓርቲው ዋና ጸሐፊ አቶ ዳዊት አስራደ ጋር ባልደረባችን ኤልያስ ገብሩ አጠር ያለ ቃለ-ምልልስ አድርጓል።
የፓርቲያችሁን ሊቀ-መንበር እና የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አንዷለም አራጌን ጨምሮ ፣ የብሔራዊ ምክር ቤት አባሎቻችሁ ከታሰሩ በኋላ ያላችሁ የሥራ እንቅስቃሴ […]

«መንግስት በምንም አይነት መልኩ ሊተች አይገባም» የሚል አላማን ለማራመድ ሲባል ብቻ የግል ኤፍ.ኤም ሬዲዮ የተሰጣቸው አንዳንድ ኢትዮ-አሜሪካዊያን፤ ከሌላው ጊዜ በተለየ ሁኔታ በአውራምባ ታይምስ ጋዜጣ ላይ መያዣ መጨበጫ የሌለው የመንደር ፕሮፓጋንዳ በመንዛት የተጠመዱበት ሰሞን ነው።
የጣቢያው ባለቤቶችና አዘጋጆች ነን ባዮቹ ጥንዶች ‹‹የጋዜጠኞች ክብ ጠረጴዛ›› በሚሉትና አንድም ጋዜጠኛ በማይገኝበት ፕሮግራማቸው፣ ይህቺኑ አውራምባ ታይምስ ጋዜጣን ዋነኛ የመነጋገሪያ አጀንዳቸው አድርገው […]

በሁለተኛው የአለም ጦርነት ወቅት የጀርመን ባህር ኃይል መርከቦች እንግሊዝን ከበዋል፡፡ የአሜሪካ መርከቦች ሲቀርቡ፣ በቀላሉ በጀርመን ሰብማሪንስ (በባህር ላይ ሳይሆን በባህር ውስጥ የሚሄዱ መርከቦች) እየተጠቁ በብዛት ይሰምጡ ጀምር፡፡ ጀርመኖች በባህር ላይ ጦርነት በበርካታ መስፈርቶች የበላይነት ነበራቸው፡፡ አሜሪካኖች ግን መርከቦች በሰጠሙባቸው ቁጠር፣ ሽንፈት ተቀብለውና ተስፋ ቆርጠው አልተቀመጡም፡፡ ሌሎች መርከቦች በብዛት ማሰማራት ጀመሩ፡፡ ወደ እንግሊዝ የሚላኩት የአሜሪካን መርከቦች፣ […]

የዚህ ጽሑፍ ዋና ዓላማ የደርግ አሃዳዊነትንና የኢህአዴግ ፌደራላዊነትን በተመለከተ ውይይት ለመክፈት ነው፡፡ ይህን ጉዳይ በተመለከተ እኔ አንድ አቋም አለኝ፡፡ ይህ አቋም የኢህአዴግ ፌደራላዊነት ከደርግ አሃዳዊነት የሚለየው በቅርጽ ብቻ ነው፡፡ በይዘት ወይም በአፈጻጸም ወይም በተግባር ግን ሁለቱም ከሞላ ጎደል ተመሳሳይ ናቸው የሚል ነው፡፡ በሌላ አነጋገር የኢሕዴግ ስርዓት ፌደራላዊ ያልሆነ ፌደራሊዝም ነው ማለት ነው፡፡
በውይይቱ ሂደት ይህ አቋም […]

– እስካሁን እስረኞች ያሉበትን ሁኔታ ማወቅ አልቻልንም (አንድነት ፓርቲ)
– ቤተሰብ፣ የትግል አጋሮቻቸውና የህግ አማካሪ እንዲያገኛቸው ተከልክለዋል (ቤተሰብ)
– የእስር አያያዛቸው አሳስቦናል
በእስር ላይ የሚገኙት የአንድነት ፓርቲው ም/ሊቀመንበርና የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ አንዱዓለም አራጌ፣ የብሔራዊ ም/ቤቱ አባላት የሆኑት መ/ር ናትናኤል መኮንንና መ/ር አሳምነው ብርሃኑ እንዲሁም ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋና ጋዜጠኛ ሾለሺ ሀጐስ የመኢዴፓ ዋና ፀሐፊ አቶ ዘመኑ ሞላ […]

አቶ በቀለ ገርባ በ1954 ዓ.ም በወለጋ ክፍለ ሀገር ልዩ ቦታው ቦጂ ድርመጂ በሚባል አካባቢ ተወልደው የመጀመሪያና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በዚያው አካባቢ አጠናቀዋል፡፡ ከዚያም በጤና ረዳትነት በመማር አሁን ደቡብ ክልል ጌዲኦ ዞን በሚባል ቦታ ለረጅም ዓመታት አገልግለዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እንግሊዘኛ ቋንቋ በመማር የመጀመሪያ እና የሁለተኛ ድግሪያቸውን (BA&MA)አግኝተው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ውስጥ በመምህርነት […]

ስለሺ ሐጎስ የተወለደው መቂ ከተማ በ1972 ዓ.ም ነው፡፡ እስከ 8ኛ ክፍል ድረስ በዚያው በመቂ ከተማ በካቶሊክ ት/ቤት ተምሯል፡፡ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ያጠናቀቀው በዝዋይ ከተማ ነው፡፡
ስለሺ ሐጎስ በኮተቤ መምህራን ኮሌጅ በመግባት በሥነ ጽሑፍ በዲፕሎማ ተመርቋል፡፡ እንዲሁም በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በመግባት በቴአትር ጥበብ የመጀመሪያ ዲግሪውን አግኝቷል፡፡
ሾለሺ ሐጎስ በሰላማዊ መንገድ ለውጥ ለማምጣት ከሚጥሩ ወጣቶች አንዱ ነው፡፡ በሚያቀርባቸው ግጥሞች […]

ስለሉሉ የማያውቅ እንደማይኖር ተስፋ አለኝ፡፡ ሉሉ የአፄ ኃይለ ሥላሤ ድንክ ውሻ ናት ወይም ነበረች – አፈሩ ይቅለላት ነፍሷም በየማነ ብፁዓን አክልብት ይቀመጥና፡፡ ያቺ ድንክዬ የጠቅል ውሻ ታሪከኛ ነበረች አሉ፤ ተራ ውሻ አልነበረችም፡፡ ሥልጣንና ማዕረጓ ልሹ ከንጉሡ በታች ከመኳንንትና መሣፍን በላይ እንደነበር በወቅቱ ለንጉሡ ቅርበት የነበራቸው አረጋዊ ዜጎች ያስታውሳሉ፡፡ የማንንም እግር እየሄደች ብትዘነጥል ከመብቶቿ አነስተኛው ነበር፡፡ […]

ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

ፍኖት- የጋዜጠኛ ሰርክዓለም ፋሲል ንብረቶች እስከአሁን አልተመለሱም
ባለፈው መስከረም 3 ቀን 2004 ዓ.ም በ “ሽብር” ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በዕለቱ ሲያሽከረክሯት የነበረች የቤት መኪና እና መተዳደሪያቸው የሆነውን የቤት ኪራይ ገንዘብ እንዲመለስላቸው ጋዜጠኛ ሰርክዓለም ፋሲል ቢጠይቁም እስከአሁን እንዳልተመለሰላቸው ገለፁ፡፡
ወ/ሎ ሰርክዓለም ንብረቶቹ በተያዙበት ማዕከላዊ እስር ቤት ሄደው የመኪናውን ሊብሬ በእሳቸው ስም እንደሆነ ለማስረጃነት ቢያቀርቡም “ከአንቺ […]

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)
UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY(UDJ)
ቁጥር፡-አንድነት /437/2ዐዐ4
ቀን 15/01/2004 ዓም
ግልጽ ደብዳቤ
ለኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ
አዲስ አበባ
ጉዳዩ፡- በሽብርተኝነት ስም የታሰሩ አባሎቻችንና ሌሎች ዜጎች ሕገ-መንግሥታዊ መብታቸው እንዲከበርላቸው ስለመጠየቅ፣
በኢትዮጵያ ሕዝብ ዘንድ በግልጽ እንደሚታወቀው አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) በሕገ-መንግሥቱ በተደነገገው የመደራጀት መብት መሠረት ሕጋዊና ሠላማዊ በሆነ መንገድ ለዜጎች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች እውን […]

አቶ ኦልባና ሌሊሳ በምዕራብ ሸዋ ጨሊ ወረዳ በ1966 ዓ.ም ተወለዱ፡፡ የመጀመሪያና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውንም በተወለዱበት አካባቢ አጠናቀው ወደ መንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋም በመግባት በግብርና ዲፕሎማ አግኝተዋል፡፡ ከዚያም በመንግሥት ግብርና ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ውስጥ በሚተዳደር መስሪያ ቤት ተቀጥረው ለዓመታት አገልግለዋል፡፡ በማታው መርሐ ግብር በአምቦ ዩኒቨርስቲ የትምህርት ደረጃቸውን ለማሻሻል እየተማሩ እንደነበርና በተደረገባቸው የፖለቲካ ጫና ምክንያት ሥራቸውን በፈቃዳቸው […]

ወ/ት ሊዲያ ዘሪሁን ትባላለች፡፡ በእስር ላይ የሚገኙት የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ /ኢብአፓ/ ፕሬዝደንት የአቶ ዘሪሁን ገ/እግዚአብሔር ልጅ ናት፡፡ በአባቷ ዙሪያ ባልደረባችን ብዙአየሁ ወንድሙ አነጋርሯታል፡፡ መልካም ቆይታ፡፡
አባትሽ አቶ ዘሪሁን ገ/እግዚአብሔር በእስር ላይ እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡ በመጀመሪያ አቶ ዘሪሁን የት ተወለዱ?
ወ/ት ሊዲያ- ዘርዬ የተወለደው እዚሁ አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ሥፍራው መርከቶ የሚባል አካባቢ ነው፡፡
ሾለ ትምህርታቸው አጠቃላይ ሁኔታ ብትገልጪልኝ […]

ሽብርተኝነት ከ20ኛው ክፍለ ዘመን ሁለተኛው አጋማሽ ጀምሮ እየጎላ የመጣ አደገኛ ክስተት ነው፡፡ አደገኛነቱ በግልጽ የታየው እ.ኤ.አ መስከረም 11 ቀን 2001 ዓ.ም በኒውዮርክ ከተማ የንግድ ማዕከል ላይ በደረሰው ጥቃት ነው፡፡ በዚህ ጥቃት በሺዎች የሚቆጠር ህይወት ጠፍቷል፡፡ በቢሊዮን ዶላር የሚገመት ንብረት ወድሟል፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ በዓለም ሕዝብ ላይ ይህ ነው የማይባል ድንጋጤና የመንፈስ ጭንቀት ፈጥሯል፡፡
ተንታኞች ሽብርተኝነትን በተለያየ […]

ከሽብር እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው የታሰሩትን ጋዜጠኞች ሁኔታ ዓለም አቀፍ የጋዜጠኞች ፌዴሬሽን (IFJ) ተወካዮች በአካል ተገኝተው እንደጎበኙ የኢትዮጵያ መንግስት መፍቀዱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ የጋዜጠኞች ህብረት (ኢብጋህ) አስታወቀ።
ዋና ጽህፈት ቤቱ በቤልጂየም ብራሰልስ ያደረገው ይኸው ፌዴሬሽን ልኡካኑን ወደ ኢትዮጵያ የሚልክበት ዋንኛ ዓላማ ከሽብርተኝነት እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው በፖሊስ ቁጥጥር ሾር የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና አውሮፓውያን ጋዜጠኞች የሚደረግላቸውን አያያዝና የታሰሩበትን ትክክለኛ […]

ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ሰሞኑን መንግሥት በአሸባሪነት የጠረጠራቸውን ጋዜጠኞችና የተቃዋሚ ፖለቲከኞች ማሰሩ ይታወሳል። በዚህ ጉዳይ እና በሌሎች ተያያዥ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ፣ ሱራፍኤል ግርማ ከቀድሞ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት እና ከወቅቱ የአንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)ሊቀ-መንበር ከሆኑት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ጋር ቆይታ አድርጓል።
የሰሞኑን የእስር ሂደቶች ፓርቲው እንዴት ነው የሚመለከተው?
በተለያዩ ጊዜያት እንደገለፅነው፣ ፓርቲያችን ለፍትህና ለዴሞክራሲ ይታገላል፤ ሕገመንግስቱ ያጎናፀፈንን መብቶች […]

‹‹ … የዓለም ሰላም ጠበቃዎች፣ የጋዜጠኞች መብቶች አስከባሪዎች፣ የዴሞክራሲ ሰብዓዊ መብቶች ተቆርቋሪዎች ነን ለሚሉትና በውጭ ሀገር የተቃዋሚዎች አፈ ቀላጤዎች በመሆን በማገልገል ላይ ለሚገኙ አንዳንድ ኃይሎች ሳይንበረከክ፣ መንግሥት የአመፅ ጥሪ የሚያቀርቡትን ኃይሎች ሀይ ሊላቸው ይገባል … ››
ከላይ የሰፈረው ጥቅስ የተወሰደው መስከረም 12 ቀን 2004 ዓ.ም ለንባብ ከበቃው አዲስ ዘመን ጋዜጣ ገፅ 3 ነው። ምንጣፍ የሚያክለው አዲስ […]

ቢሯችን እስኪጸዳ ድረስ በር አካባቢ ቆም ብለን ብሶታችንን ማውራት በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በጣም የለመድነው ነገር ሆንዋል፡፡ እናም ዛሬ ጧት እንደልማዳችን ወደ አራት የምንጠጋ አለቃና ምንዝሮች ባንድነት ቆመን ስለኢትዮጵያና ስለዓለም ወቅታዊ የፖለቲካ ትኩሳት ማውራት ያዝን፡፡ የኔን ጫጫሪነት ማንም ያውቃል ብዬ አላስብም፡፡ ሁላችንም እየፎገላን በተለይ ስላገራችን አሳሳቢና አስጨናቂ ሁኔታ ማውራታችንን ቀጠልን፡፡ የሚገርመው ነገር ማንኛችንም ብንሆን ለፖለቲካና […]

ዘመኑ ሞላ ተወልዶ ያደገው ከዚሁ አዲስ አበባ ሲሆን፣ ባለትዳርና ያንዲት ሴት ልጅ አባት ነው፡፡ ልጁ ጎበዝ ተማሪ ስለሆነች በዚህ ዓመት ዩኒቬርስቲ እንደምትገባ በቅርብ የሚያውቋት ይናገራሉ፡፡
ዘመኑ ሞላ ነባር የሰላማዊ ትግል ታጋይ ሲሆን የኢዴፓ ነባር አባል በመሆኑ በ92 ዓ.ም በተደረገው ሁለተኛው አገራዊ ምርጫ አ.አ ክልል ተወዳድሮ ነበር፡፡
ቆይቶ ደግሞ ኢዴፓ የሚሄድበት መንገድ ስላላማረውና ስላልጣመው ከዚያ […]

አካባቢው አንድ ገጠር መንደር ነው፡፡ የዘመኑ የአካባቢው ገዢ ሕዝቡን ሰብስቦ ሲናገር ይውላል፡፡ ሕዝቡም ዝም ብሎ ያዳምጣል፤ እርሱ ያወራል ሕዝቡን ያዳምጣል። መናገር ሲስለቸው «አሁን ተራው የእናንተ ነው፤ ሐሳብ መስጠት ትችላላችሁ» ይላቸዋል፡፡
ሁሉም ዝም ይላል፡፡ «ተናገሩ» ይላል አሁንም በመደጋገም ። አሁንም ሕዝቡ ዝም አለ፡፡ “ጊዜው የዴሞክራሲ ነው ፤ የፈለጋችሁትን መናገር ትችላላችሁ፡፡ ተርበን፣ ሞተን፣ ቆስለን፣ ጓደኞቻችን ሞተው […]

በቅርቡ “በሽብርተኝነት”ተጠርጥረው የታሠሩትን እስረኞች «በምን ሁኔታ ላይ አንደሚገኙ ማወቅ አልቻልንም» ሲሉ ቤተሰተቻቸውና የሥራ ባልደረቦቻቸው ለዝግጅት ክፍላችን ገለጹ፡፡
የአንድነት ፓርቲ ም/ሊቀመንበርና የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ የሆኑት የአቶ አንዱዓለም አራጌ ወንድም ወጣት አብርሃም አራጌ እንደሚለው “ወንድሜ የታሠረበትን የእስር አያያዝ ማወቅ አልቻልኩም፡፡ በተደጋጋሚ ለመጠየቅ ሄጄ ምግብ ተቀብለው ዕቃ ከመመለስ ውጪ በአካል አግኝቼው አላውቅም”፡ ብሏል፡፡
የፓርቲው ማዕከላዊ ም/ቤት አባላት የሆኑት […]

አሣምነው ብርሃኑ ተወልዶ ያደገው ከዚሁ አዲስ አበባ ነው፡፡ የትምህርት ደረጃው በፊዚክስ ቢ.ኤስ.ሲ ዲግሪ አለው፡፡ ባሁኑ ጊዜ በኢኮኖሚክስ በዲግሪ መርሃ ግብር አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እየተማረ ነበር፡፡ መደበኛ ሥራውም መምህር ነው፡፡
ቤተሰብ አሣምነው ብርሃኑ ገና ወጣት በመሆኑ ለሥራና ለትምህርት እንዲሁም ለነፃነት ተግቶ ከመሥራት ውጭ ትዳር ለመመሥረት አስቦ እንደማያውቅ ቤተሰቦቹ ገልፀውልናል፡፡
የፖለቲካ አቋምአሳምነው ብርሃኑ አንድነት ፓርቲን ከመቀላቀሉ በፊት […]

ክቡር ጠ/ሚንስትር የሰው ልጅ የአገሩን የአስተዳደር መረጃ ካለማጤን ስህተት መፈጠሩ አይቀሬ ቢሆንም በተጓደኝ የተፈፀመውንና የተደረገውን በማስታወስ የተሠራ ጥፋት መታረም ይቻላል፡፡ ከዚህ አንፃር ባገራችን የሚታየውንና እየተፈፀመ ያለውን ግዙፍ ስህተት ቅኝ ገዥዎች እንኳን ይሠሩታል ብሎ ለመናገር የሚከብድ ይመስለኛል፡፡ ይህንን ጽሑፍ ለመዳፍ ያነሳሳኝ ሀገራዊ ስሜትና ፍቅር እየቆጠቆጠኝ አላስቆም አላስቀምጥ ስላለኝ ሰሚ ባይኖርም የድርሻዬን ልወጣ በሚል ነው፡፡
ኢሕአዴግ ሥልጣን ከተቆናጠጠበት […]

ከጥቂት ወራት ወዲህ ገዢው ፓርቲ ስርዓቱ ላይ የሠላ ሂስ በመሠንዘር የሚታወቁ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችና ጋዜጠኞችን የማሠር ዘመቻውን ጀምሯል፡፡ የእስራት ዘመቻው ማቆሚያ የት ጋ እንደሆነ የታወቀ ነገር እስካሁን የለም፡፡ የእስር ዘመቻው ያነጣጠረው ግን ከኢህአዴግ አቋም በተቃራኒው የቆሙ ግለሰቦች ላይ መሆኑ የአገራችንን የወደፊቱን የፖለቲካ አቅጣጫ አሳሳቢ አድርጎታል፡፡
ከታሪክ እንደምንማረው በዓለም ላይ በርካታ አምባገነን መንግስታት ኖረው አልፈዋል፡፡ አውሮፓን ሲያምሱት […]

ኢህአዴግ የዴሞክራሲና የህግ የበላይነት ጥያቄ ሲቀርብለት ዘወትር የሚያሳው መቃብሩን ነው።የአንድነት ጥያቄ ሲቀርብ ምላሹ “እኛ ከፈለሰፍነው አንድነት ውጭ ሌላው አንድነት በኢህአዴግ መቃብር ላይ ካልሆነ በስተቀር የማይታሰብ ነው”የሚል ነው።የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ ሲነሳ “የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ ህያው የሚሆነው በኢህአዴግ መቃብር ላይ ብቻ ነው”በማለት ወደ መቃብሩ ያመላክተናል።አንቀፅ 39 በታኝ መሆኑን ህዝብ ሲገልፅ “የህዝብ ልጆች የተሰውለት የትግሉ የማዕዘን ድንጋይ ነው፣እኔ […]

የቦስትን አንድነት የድጋፍ ድርጅት በውቅታዊ ህገራዊ ጉዳዮች ላይ የአካባቢውን ነዋሪዎች ለማወያየት የውይይት ፎረም አዘጋጅታል
Date: Sunday Sept. 18, 2011
Time: 3:00PM
Pl…

ሽብርተኝነት የንፁሀንን ሕይወት በጅምላ የሚያጠፋ፣ አካልን የሚያጎድል፣ የሀገርን ሀብት፣ የልማት አውታሮችንና ተቋማትን የሚያወድም ኃላፊነት የጎደለው ተግባር በመሆኑ ፓርቲያችን በማያወላውል ቁርጠኝነት ያወግዘዋል፡፡ ሽብርተኝነት በሚያደርሰው ጉዳት ብቻ ሳይሆን ዓላማውም የራስን ፍላጎት በሌሎች ላይ መጫን በመሆኑ ተቀባይነት የሌለው የእቢተኞችና የጉልበተኞች ድርጊት በመሆኑ አጥብቀን እንኮንነዋለን፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ በሽብርተኝነት ስም ሽብር የሚነዛ አካልን አጥብቀን እናወግዛለን፡፡
የፓርቲያችን አቋምና እምነት ከላይ […]

ከትላንትና ወዲያ «በሽብር ሥራ ተሰማርተሃል» በሚል ወደ ማዕክላዊ የተወሰዱት የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ምክትል ፕሬዘዳንት እና የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ፣ አቶ አንዱዋለም አርጌ፣ በባለቤታቸው እና በአባታቸዉ ዛሬ እንደተጎበኙ ከአዲስ አበባ የደረሰን ዜና ያመለክታል።
የአቶ አንዱዋለም ባለቤት እና የአቶ አንዱዋለም አባት ፣ አቶ አንዱዋለምን ካነጋገሩ በኋላ ፣ አቶ አንዱዋለም በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ፣ በመንፈስ ጠንካራ እንደሆኑ ገልጸዋል።
«በአቶ […]

ፓርቲዉ ዛሬ በሰጠዉ ጋዜጣዊ መግለጫ ለሰላምና ለዲሞክራሲ በሚታገሉ ዜጎች ላይ እየደረሰ ያለዉ ተግባር እጅግ በጣም አሳፋሪና አሳዛኝ እንደሆነ ጠቅሶ ፣ መሰረት በሌለዉ በሽብር ክስ የታሰሩ ሰላማዊ ዜጎች ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ፣ ዜጎችን የማሰፈራራትና የማወክ ጸረ-ዲሞክራስያዊ ዘመቻ በአስቸኳይ እንዲቆም አሳስቧል።
ጠንካራ ተቃዋሚዎች ላይ ኢፍትሃዊ እርምጃ በመዉሰድ የሚታወቀዉ የመለስ ዜናዊ አገዛዝ፣ ሰሞኑን በነአንዱዋለም አርጌ ላይ የወሰደዉ እርምጃ፣ […]

መስከረም 5 ቀን 2004 ዓ.ም
የአንጋፋዉ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ባለቤት ወ/ሎ ሰርካለም ፋሲል ፣ በባለቤቷ መታሰር ዙርያ በፓልቶክ ከተሰባሰቡ ኢትዮጵያዉያን ጋር፣ አጭር ቃለ ምልልስ አድርጋለች። ወ/ሎ ሰርካለም ዳግመኛ ወደ እሥር ቤት ከተወሰደዉ ባለቤቷ፣ እስክንድር ነጋ ጋር፣ ከስድስት አመታት በፊት ለሃያ ወራት በቃሊቲ እሥር ቤት ታስራ የነበረ ሲሆን፣ አንድና የመጀመሪያ ልጇን ፣ ናፍቆት እስክንድርን የወለደችዉ […]

“አንድ ለመጀመሪያና ለመጨረሻ ጊዜ የምናገረው ሃሳብ አለኝ፡፡ እየተፈፀመ ያለው ተግባር የተቃዋሞ ፖለቲካውን ለማፈን የተወሰደ እርምጃ ነው፡፡ ከእንግዲ ወዲያ ፍርድ ቤቱ የፈለገውን እርምጃ ሞትም ቢሆን መውሰድ ይችላል፡፡ ሌላ የምሰጠው አስተያየት የለኝም” አቶ አንዱዓለም አራጌ
“በ2004 ዓ.ም. በሀገሪቱ ውስጥ የሽብር ተግባር ለመፈፀም በቡድን ተደራጅተው ሲንቀሳቀሱ ማስረጃ አግኝቼባቸዋለው” በማለት በትናንትናው እለት በቁጥጥር ሾር ያዋላቸው የፓርቲ አመራሮችና ጋዜጠኛ አራዳ […]

መስክረም 4 ቀን 2004 ዓ.ም
የአንድነት ለዲሞርካሲና ለፍትህ ፓርቲ ምክትል ፕሬዘዳንት አቶ አንዱዋለም አርጌ፣ እዉቁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ብሄራዊ ምክር ቤት አባላት አቶ አስማማዉ እና አቶ ናትናዔል ብርሃኑን ጨምሮ አምስት ኢትዮጵያዉያን ፣ ዛሬ ሐሙስ መስከረም 4 ቀን ከሰዓት በኋላ፣ ፍርድ ቤት እንደቀረቡ ከአዲስ አበባ የደረሰን ዘገባ ገለጸ።
«መረጃ የበለጠ ለማሰባሰብ ቀናቶች ያስፈልጉኛል» […]

መስክረም 4 ቀን 2004 ዓ.ም
የአንድነት ለዲሞርካሲና ለፍትህ ፓርቲ ምክትል ፕሬዘዳንት አቶ አንዱዋለም አርጌ፣ እዉቁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ብሄራዊ ምክር ቤት አባላት አቶ አስማማዉ ብርሃኑን እና አቶ ናትናዔል ጨምሮ አምስት ኢትዮጵያዉያን ፣ ዛሬ ሐሙስ መስከረም 4 ቀን ከሰዓት በኋላ፣ ፍርድ ቤት እንደቀረቡ ከአዲስ አበባ የደረሰን ዘገባ ገለጸ።
«መረጃ የበለጠ ለማሰባሰብ ቀናቶች […]

መስከረም 3 ቀን 2004 ዓ.ም
ዛሬ ከቀኑ አሰር ሰዓት (10፡00) አከባቢ የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበርና የህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ አንደዓለም አራጌ በአገዛዙ የዯህንነት ሰዎች ታስሮዋል፡፡ በተመሳሳይ ሰዓት እውቁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋም ተይዞዋል፡፡ አንደዓለምና እስክንድር ከሌሎች ሁለት የአንድት ፓርቲ አባለት ጋር ከቀኑ 8፡30 ገዯማ ጀምሮ አንድነት ፓርቲ አከባቢ በሚገኝ ካፍቴሪያ አከባቢ እሰከ […]

መስክረም 3 2004 ዓ.ም
እውቁ ጋዜጠኛ እስክድንር ነጋ፣ ዜጎችን የማሸበርን ተግባር በተያያዙት የወያኔ ታጥቂዎች፣ መታሰራቸዉን ከአዲስ አበባ የደረሰን ዘገባ ያመለክታል።
ከጥቂት ሰዓታት በፊት፣ የአንድነት ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ፣ አቶ አንዱዋለም አርጌ መታሰራቸዉን መዘገባችን ይታወቃል።
ትግሉ ወደ ሰላማዊ ትግል መሸጋገር እንዳለበት የሚገልጽ ጽሁፍ በቅርቡ ለአንባቢያን ያቀረቡት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ በሰላማዊ ትግል የሚያምኑ፣ ገዢዉን ፓርቲ በተለያዩ […]

መልካም አዲስ ዓመት/እንቁጣጣሽ!
ከአስቸጋሪ የእስር ቆይታ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የማከብራትን የዛሬዋን እንቁጣጣሽ ከምወዳችሁ በስዊድን እና አካባቢዋ ከምትኖሩ ኢትዮጵያውያን ጋር ላሳልፍ በመቻሌ ደስታዬ ለከት የለውም።
ስለዚህም በዚህ በደመቀ በዓል ላይ እንግዳ ሆኜ እንድገኝ የጋበዘኝን በስዊድን የኢትዮጵያውያን ማኅበርን እጅግ አድርጌ ላመሰግን እወዳለሁ። ከዚህም በላይ ከእስር ሰንሰለት ወጥቼ የዛሬዋ የነፃነት ቀን የእኔ እንድትሆን አቅማችሁ የፈቀደውን ሁሉ በማድረግ ከፍተኛ […]

(UDJ) — ዛሬ ከቀኑ አሰር ሰዓት (10፡00) አከባቢ የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበርና የህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ አንዱዓለም አራጌ በአገዛዙ የደህንነት ሰዎች ታስሮዋል፡፡ በተመሳሳይ ሰዓት እውቁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋም ተይዞዋል፡፡ አንዱዓለምና እስክንድር ከሌሎች ሁለት የአንድት ፓርቲ አባለት …

አንዱዓለም አራጌና እስክንድር ነጋ ታሰሩ Read more »

በወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ይመራ የነበረዉና በሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነትን እያገኝ የመጣዉ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ዋና ጸሃፊ ሆነዉ ከዚህ በፊት ያገለገሉት እና አሁን ደግሞ በሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊነት የሚሰሩት፣ ወጣት አንዱዋለም አርጌ፣ በገዢዉ ፓርቲ የደህንንት ሰዎች፣ አዲሱ አመት በገና በሁለት ቀናት ዉስጥ፣ ዛሬ፣ ታግተዉ መወሰዳቸዉን ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ከአዲስ አበባ የደረሰን ዘገባ ያመለክታል።

አቶ […]