ይህን ያለው ማነው? “ትግሬን ወደ መቀሌ!ንብረቱን ወደ ቀበሌ!” በደረጀ ሀብተወልድ -ሆላንድ
ይህን ጥያቄ፤ ለአንድ ጤነኛ ሰው ቢያቀርቡለት፤”እንደዚህ የሚሉት(ያሉት)፤ለትግሬዎች ጥላቻ ያላቸው ናቸው”ሊል እንደሚችል ግልፅ ነው።ይህ አያከራክረንም።አከራካሪ የሚሆነው፤እነዛ፤ ለትግሬዎች ጥላቻ ያላቸው፤ እነማን ናቸው?” የሚለው ተከታይ ጥያቄ ነው። ግን.. ይህን ያለው ማን ይመስላችሁዋል? ቅንጅት? የቅንጅት ደጋፊዎች?ህብረት? የግል ጋዜጦች? ወይስ ሌሎች ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች? “ትግሬን ወደ መቀሌ፤ንብረቱን ወደ ቀበሌ” ብሎ በአደባባይ ያወጀው፤ ህወሀት ቢሆንስ ምን ይሰማችሁዋል?ምንስ ትላላችሁ? በእርግጥ ህወሀት፤በገዛ አባሎቹ […]