ከሎሬት ጸጋዬ ገብረመድን በጦቢያ  መጽሄት  ቅጽ 12 ቁጥር 10 ግንቦት ወር 1997 ወጥቶ ከነበረ የተወሰደ ይድርስ ግንቦት ሰባት ይድረስ እናት ዓለም ግንቦት ሰባት፣ ተራሮችሽ ተሰለፋ! ግንቦት ሃያን አሳፈሩ! በድል ድባብ ተንሳፈፉ የጥላቻን ዓይን ጥላ፣ በአንድነታቸው ገፈፉ ትውልድሽ እምቦቀቅላሽ፣ በአገር ፍቅር ተቃቀፉ የኢትዮጵያዊነትን ማተብ፣ በቁርጥ ቃል አበሰሩ የምስራች ተቀዳጁ! የምስራች ተባበሩ። እናት ዓለም ግንቦት ሰባት፣ ትውልድሽ […]

ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ለባለሙያዎች ከፍተኛ ክብር አለው። ሆኖም ግንቦት 7 ነፃነት በሌለበት ሃገር ውስጥ ሙያም ሆነ ባለሙያ ክብር የማይሰጣቸው፤ በክፍያም ሆነ በማስገደድ የአምባገነኑ ፈቃድ ፈፃሚዎች እንደሚሆኑ ይገነዘባል። ነፃነት በሌለበት ሃገር ባለሙያዎች ተገደው አሊያም ለመኖር በሚል ሰበብ ገንዘብ ለሚከፍል የጊዜው አምባገነን ሥርዓት በሎሌለነት ያድራሉ። ግንቦት 7  እንዲህ ያለው ሁኔታ በሀገር ላይ የሚያደርሰውን ከፍተኛ […]

በቱኒዚያ ተቀጣጥሎ የሰሜን አፍሪቃ ሃገራት አምባገነኖችን እየጠራረገ ያለው የህዝብ አመጽ በሊቢያ ከተቀሰቀሰ ሰባት ወራት ቦኋላ ተቃዋሚዎቻቸውን አንዴ ሽብርተኞች፤ ሌላ ጊዜ ደግሞ የውጪ ቅጥረኞች ከማለት አልፈው አይጦች እያሉ ሲሳደቡ የነበሩት ሙአመር ጋዳፊ ለተቃዋሚዎቻቸው በተመኙት የአይጥ ጉድጓድ ውስጥ ለ2 ወራት ያህል ከመሸጉ ቦኋላ ከትናንት ወዲያ የሚያሳፍር ሞት መሞታቸው መላውን የአለም ህዝብ እያነጋገረ መሆኑ ታወቀ። ሙአመር ጋዳፊ በሥልጣን […]

ዘረኛውና ፋሽስቱ የመለስ ዜናዊ አገዛዝ በህዝባችን ላይ እያደረሰ ያለው  አፈናና ጭቆና ባስመረረው የአርባምንጭና አካባቢዋ ነዋሪዎችና በአገዛዙ መካከል በተነሳው ውዝግብ እስካሁን ወደ 65 የሚጠጉ ሰዎች መታሰራቸውን የኢትዮጵያ ሳታላይት ቴለቪዥን ኢሳት የዘገበ ሲሆን፤ አካባቢው በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሎአል። ኢሳት በአካባቢው ያሉትን ወኪሎቹን ዋቢ አድርጎ እንዳጠናቀረው መረጃ ከሆነ፤ውጥረቱ ይበልጥ እየተባባሰ የመጣው፤ ከሁለት ሳምንት በፊት በወረዳቸው፣ በዞናቸውና […]

“ዘረኛው የወያኔ አገዛዝ በአገራችንንና በህዝባችን ላይ እያደረሰ ያለው ሰቆቃ ሰልባ ነኝ “በሚል ሽፋን የሃሰት ማስረጃ በማቅረብ በአውሮጳና በሰሜን አሜሪካ የፖለቲካ ጥገኝነት ካገኙ ቦኋላ መልሰው በአገር ቤት ውስጥ የሚፈጸመውን የመብት አፈናና የሰብአዊ መብት ጥሰት ለማጋለጥ የሚንቀሳቀሱትን ኢትዮጵያዊያንን፣ በመሰለል ለአገዛዙ መረጃ የሚያቀብሉ ኢትዮጵያዊያንን ተከታትሎ የሚመዘግብና እንደአስፈላግነቱ ለየሚኖሩበት አገራት መንግሥታት የሚያጋልጥ  አንድ ኮሚቴ ተቋቁሞ  ከሰሞኑ እንቅስቃሴ መጀመሩን  ለዝግጅት […]

በተለያዩ አንስተኛ ጥቅማጥቅሞች በመደለል በአገራቸውና በወገናቸው ላይ ታሪክ ይቅር የማይል ወንጀል በመሥራት  የዘረኛውን አምባገነን ስርአት አገዛዝ እድሜ ለማራዘም ከፍተኛ አስተዋጽኦ ሲያደርጉ ከነበሩ በርካታ የወያኔ ሆድ አደሮች መካከል አንዱ የሆነው ያረጋል አይሸሹም ከሰሞኑ ከሥራ እንደታገደና በቁም እስር ላይ እንደሚገኝ ለዝግጅት ክፍላችን የደረሰ መረጃ አጋለጠ። ያረጋል አይሸሹም ቀደም ሲል የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፕሬዚዳንት ሆኖ ሲያገለግል ከቆየ ቦኋላ […]

ባለፈው አንድ ሳምንት ብቻ በተለያዩ ቦታዎች ተመድበው የነበሩ 14 ወጣት የኢትዮጲያ ሠራዊት አባላት የዘረኛና አፋኙን  የመለስ አገዛዝ በመቃወም ከትግራይ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ ጋር መቀላቀላቸውን የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን ኢሳት ዘገበ። እንደ ኢሳት ዘገባ  በምህፃረ-ቃል “ትህዴን” በመባል የሚታወቀው የትግራይ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ የወጣቶቹንና የወታደሮች ፎቶ አያይዞ ለኢሳት መግለጫ መላኩ የታወቀ ሲሆን በመግለጫው፤ የዘረኛው መለስን ሥርዓት ከድተው ወደ […]

በተፈጥሩአዊ መስህብነቱ በአለማችን የሚታወቀው የራሽ ደጀን ተራራ በሚገኝበት በዬዳ ወረዳ አካባቢ የሚኖሩ የሏሪ ቀበሌ ነዋሪዎችን፣ በትግራይ ክልል ውስጥ እንዲካተቱ ለማሳመን ለ7 ተከታታይ ቀናት የተደረገው ውይይት ሳይሳካ መቅረቱን ስማቸው እንዳይገለጥ የፈለጉ የአካባቢው ነዋሪዎች መግለጻቸውን የኢትዮጵያ ሳተካይት ቴሌቪዥን ኢሳት ዘገበ። እንደ ኢሳት ዘገባ የትግራይ ክልል ባለስልጣናት የቀበሌው ነዋሪዎች ወደ ትግራይ ክልል እንዲዛወሩ ተደጋጋሚ ሙከራ ቢያደርጉም፣ ህዝቡ ግን […]

የፋሽስቱ መለስ ዜናዊ አገዛዝ ከጊዜ ወደ ጊዜ በህዝብ ላይ እየፈጸመ ስላለው የሰብኣዊ መብት ረገጣ በሰፊው የተነጋገረ አንድ ታላቅ ሀዝባዊ ስብሰባ ከትናንትና ወዲያ እሁድ (16/10/2011) በእንግሊዝ አገር በሎንደ ከተማ በፍሬንድ ሃዉስ አዳራሽ ውስጥ መካሄዱን ከስፍራው የደረሰን ዜና አመለከተ። ቁጥራቸው ወደ ሁለት መቶዎች የሚገመቱ ኢትዮጵያዊያን  በተገኙበት በተካሄደው በዚህ ታላቅ ስብሰባ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የ3ኛዉ አለም […]

ወያኔ መላውን አገራችንን በመሳሪያ ሃይል በመቆጣጠር ከዛሬ 20 ዓመት በፊት ስልጣን ሲቆጣጠር የኢትዮጵያን ህዝብ በመጀመሪያው 10 አመት ቢያንስ በቀን ሶስት ጊዜ እንዲበላ እናደርገዋለን በማለት የሃሰት ተስፋ የሰጠ ሲሆን መለስ ዜናዊና ጥቂት ግብረአበሮቹ በተከተሉት የአገር ሃብት ምዝበራና ዘረፋ ምክንያት ከ20 ዓመታት የወያኔ የስልጣን ዘመናት ቦኋላ ዛሬ አገራችን ታይቶ በማይታወቅበት የድህነት አረንቋ ውስጥ እንደገባችና በቀን አንድ ጊዜ […]

የመለስ ዜናዊ አገዛዝ በከፍተኛ ሽብር ውስጥ ገብቷል። ይህ አገዛዝ የቆመበት መሠረት በጣም ስስና ደካማ በመሆኑ በዘወትር ስጋት ውስጥ ነው። በአንድ ወይም በሌላ ምክንያት ለመለስ ዜናዊ የወገኑ ኢትዮጵያዊያን መኖራቸው የመለስ ዜናዊ አገዛዝ የሌለው ጥንካሬ ያለው እንዲመስል አድርጓል። ይህ ደግሞ በተራው የኢትዮጵያንና የኢትዮጵያዊያንን  መከራ አብዝቷል። በመለስ ዜናዊ እና ዘረኛ ቡድኑ ዙሪያ ያሉ ሰዎች ሁሉ የመለስን አገዛዝ ከልባቸው […]

ላለፉት ሃያ ዓመታት በመለስ ዜናዊ ዘረኛ አገዛዝ የተጫነብን ቀንበር መከራችንን አብዝቷል። መከራውም መሸከም ከምንችለው በላይ በመሆኑ ሮሮአችን ገደቡን ጥሶ ሦስት ትውልድን በአንድ ላይ እያስለቀሰ ነው። ህጻናት ልጆች ደጋግ አባቶቻቸው በካቴና ታስረው ወደ ወይኒ ሲጨመሩ እያዩ አምርረው እያለቀሱ ነው።የሚንከባከባቸው ውድ አባታቸው ለምን እንዲህ በአደባባይ ተይዞ እንደሚታሰር የሚነግራቸው ባለመገኝቱ ለጋ አእምሯቸው ለጭንቀት ተጋልጧል። የቤቱ ምሶሶ አባት በመታሰሩ […]

በስደተኛነት ገብቶ የአሜሪካ ዜግነት የተሰጠዉና አብረዉት በዩናይትድ ስቴትስ ነዋሪ የሆኑ የሶሪያ ዜጎች የአገራቸዉ መንግስት በወገኖቻቸዉ ላይ የሚያደርሰዉን የሰብአዊ መብት ረገጣ በመቃወም  የሚያደርጉትን ሰላማዊ ሰልፍ በተለያየ መልክ እየመዘገበና እየቀረፀ ለሶሪያ መንግስት በድብቅ መረጃ ሲያቀብል የተገኘ ሶሪያዊ ክስ የተመሰረተበት መሆኑን አሶስየትድ ፕሬስ ዘግቧል። መሃመድ አናስ ሃታም ስኡድ የተባለዉ ቅጥረኛ የራሱን ወገኖች በመሰለል መረጃዉን ለሶሪያ መንግስት እንደሚሰጥና በየጊዜዉ […]

በአዲስ አበባ ከተማ የተደራጁ የአነስተኛ እና ጥቃቅን ዘርፍ ታዳሚ የሆኑ አያሌ ወጣቶች “የፖለቲካው መሣሪያ ሊያደርገን ያሰባሰበን ኢሕአዴግ ፍጹም ህሊና-ቢስ እና ከማህበረሱቡ ጋር ማንኛውም ዓይነት ግንኙነት የሌለን ፍጡራን አድርጎ በመቁጠር እራሱ የፈጠረውን ችግር ህብረተሰቡን እያወናበድን እንድንቀርፍለት ጫና እየፈጠረብን ይገኛል” ማለታቸውን የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን ኢሳት ዘገበ። ኢሳት በሪፖርቱ እንደገለጸው መስከረም 30 ቀን 2004 ዓ.ም ከቀትር በኋላ ለዘጋቢያችን […]

በያዝነው ጥቅምት ወር ዘረኛው የወያኔ አገዛዝ በይፋ ያመነው መረጃ እንደሚያመለክተው በሃገሪቱ እየታየ ያለው የገንዘብ ግሽበት መጠን አሁንም እያሻቀበ ሲሆን በተመሳሳይ መልኩ የምግብ ሸቀጦች ዋጋም እየናረ መሆኑ ታወቀ። ይሄው ሪፖርት እንደአመለከተው የገንዘብ ግሽበት መጠን ከ 40.1 በመቶ በላይ ሲሆን በምግብ ዋጋዎች ላይ ያለው የግሽበት መጠን ደግሞ 51 በመቶ መድረሱ ታውቁአል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ባለፈው መስከረም ወር […]

በምስራቅ አፍሪቃ በተለይም በኢትዮጵያ የተከሰተውን የርሃብ አደጋና እልቂት ጨካኙና ዘረኛው  የወያኔ አገዛዝ የማለባበስና የመደበቅ ሙከራ ቢያደርግም የርሃብ አደጋው ስፋትና ጥልቀት ከዘረኛው አገዛዝ የመደበቅ ሙከራ የላቀ በመሆኑ ችግሩ ለአለም ህዝብ ይፋ እየሆነ መምጣቱ ታወቀ። በደቡብ ኢትዮጵያ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ የተከሰተው ረሃብ ለበርካታ ዜጎች እልቂት ምክንያት መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን ይሄው ርሃብ በተከሰተበት አካባቢ ባሉት አዋሳኝ ክልሎችም የተከሰተው […]

በእንግሊዝኛ አጠራሩ “Energy for All” ማለትም ሃይል ለሁሉም በሚል መርህ በኖርዎይ ሃገር ኦስሎ ከተማ ላይ በተካሄደ ባለው ዓለም አቀፍ ስብሰባ ንግግር ለማድረግ የተጋበዘው ዘረኛውና አምባገነኑ የወያኔ አገዛዝ ቁንጮ መለስ ዜናዊ፤ በኖርዎይና አካባቢዋ ከሚገኙ አጎራባች ሃገራት የተሰባሰቡ ኢትዮጵያዊያን ባደረጉት ከፍተኛ የሆነ የተቃውሞ ሰልፍ ምክንያት ተሸማቆና አንገቱን ደፍቶ ወደስብሰባ አዳራሽ እንዲገባና እንዲወጣ መገደዱን ዘጋቢያችን ከኖርዎይ ኦስሎ ከተማ […]

በአገራችን ውስጥ ለዘመናት የኖረውን የባህል፤ የቋንቋና የሃይማኖት ልዩነቶችን ለሥልጣን እድሜ ማራዘሚያ እንደ አይነተኛ መሳሪያ ሲጠቀምበት የኖረው የመለስ ዜናዊ አገዛዝ፤ ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ አንዱን እምነት ተከታይ በሌላው ላይ በጠላትነት ለማስነሳት ሲያደርገው የነበረው የውስጥ ለውስጥ ሥራ አደባባይ ላይ መታየት በመጀመሩ ”የአገሪቱን ደህንነት ሊያሰጋ ከሚችልበት ደረጃ ላይ ደርሶአል” በማለት ህዝብ ለማሸበር እየተንቀሳቀሰ መሆኑን የግንቦት 7 ዘጋቢ ከአዲ አበባ […]

አለም አቀፍ ህግንና የቪየና ስምምነትን በመፃረር የህወሃት የፀጥታ ሃይሎች ባሳለፍነዉ ሳምንት አንድ ኤርትራዊ ዲፕሎማትን በቦሌ አለም አቀፍ አዉሮፕላን ጣቢያ የያዟቸዉን የግል ንብረቶችና ሰነዶች በመንጠቅና በመፈተሽ ወንጀል መፈፀማቸዉን አምባሳደር ፍስሃ ፅዮን ጴጥሮስ በኤርትራ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መ/ቤት ከፍተኛ ባለስልጣን ገለጸዋል። ከአዲስ አበባ በካይሮ በኩል ወደ አስመራ በመሄድ ላይ የነበሩት ዲፕሎማት፣ ተገቢዉን ህጋዊ የኢሚግሬሽን ደንቦችን ያሟሉ ቢሆንም […]

አፍተን ፖስተን በመባል የሚታወቅ ዋንኛው የኖርዎይ ጋዜጣ ባለፈው ማክሰኞ እትሙ ይፋ እንዳደረገው ኖርዌይን ጎብኝቶ የተመለሰው ፋሽስቱ መለስ ዜናዊ ስለ ኢኮኖሚ እርዳታና የልማት ትብብር እንጂ በሰባዊ መብት አያያዝና በዲሞክራሲ ላይ ምንም አይነት አስተያየት ከምዕራባዊያኑ ለጋሾች ለመቀበል ፍቃደኛ እንዳልሆነ መናገሩን  ገለጸ። በኖርዌይ አገር በተጠራው አለም አቀፍ ስብሰባ ከተጋበዙ መረዎች መካከል የስብሰባ አዳራሹን ያናወጠ የተቃውሞ ሰልፍ የተካሄደው በአምባገነኑ […]

ወያኔ ስልጣን ከተቆጣጠረበት 1983 ጀምሮ በኢትዮጵያ ስም በልማት እርዳታና በብድር ከአለም አቀፍ ህበረተሰብ ካገኘው መጠነ ሰፊ ገንዘብ ውስጥ ከአስራ አንድ ቢሊዮን በላይይ የሆነ ገንዘብ በባለስልጣናቱ መዘረፉን በአለም ባንክ ለረጅም ጊዜ ያገለገሉና በኢትዮጵያ ምጣኔ ሃብት ላይ ሰፊ ጥናት ያካሄዱት ታዋቂው ኢኮኖሚስት ዶ/ር አክሎግ ቢራራ ገለጹ። ዶ/ር አክሎግ ቢራራ ይህን የገለጹት ባለፈው እሁድ መስከረም 28 ቀን አዲስ […]

አፋኙና አረመኔው የወያኔ አገዛዝ ሽብርተኞች ናቺሁ በማለት ሁለት የስዊድን ጋዜጠኞችን አስሮ እንደሚገኝ የሚታወስ ሲሆን የጋዜጠኞቹን የፍርድ ቤት ክስ ሂደት ለመከታተል ጥያቄ ያቀረቡትን የታሳሪ ጋዜጠኛ ባልደረቦች የወያኔው አገዛዝ ወደ ኢትዮጵያ እንደይገቡ መከልከሉ ታወቀ። የሁለቱ ታሳሪ ጋዜጠኞች ማለትም ማርቲን ሺቤይ እና ጆሃን ፕርሰን ክስ የሚሰማዉ በመጪዉ ሳምንት ዉስጥ ኦክቶበር 18 ቀን መሆኑ የታወቀ ሲሆን፣ በችሎት ላይ ለመገኘት […]

አዲሱ ግንባር ከጥቅምት 2 ቀን 2004 ባወጣው መግለጫ ላይ እንዳመለከተው መለስተኛ የፖለቲካ ፕሮግራሙ የግንባሩ ፕሮግራም ሆኖ እንዲያገለግል በመስማማት መድረክን እስካሁን ከነበረበት የቅንጅት አደረጃጃት ከፍ ወዳለ የግንባር አደረጃጀት ለማሸጋጋር የመድረኩ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ወስኗል። መድረክ በግንባሩ ዙሪያ የተሰባሰቡት የአረና ትግራይ ለፍትህና ለዲሞከርአሲ፣ የኦሮሞ ፌደራሊስት ዲሞከርአሲያዊ ንቅናቄ፣ የኦሮሞ ህዝብ ኮንግረስ፣ የኢትዮፕያ ሶሻል ዲሞከርአሲያዊ ህብረት እንዲሁም አንድነት ለዲሞክራሲና […]

የገንዘብና የልማት ተቋማቱ በያዝነው ወር ባወጡት ሪፖርት የኢትዮጵያ የአምስት አመት እቅድ የተጋነነና ውጤታማ ለመሆኑም የሚያጠራጥር መሆኑን ገልጸዋል። ድርጅቶቹ በመነሻቸው የወያኔ አገዛዝ ባለፉት አመታት አገኘሁ የሚለውን 11 በመቶ የኢኮኖሚ እድገት አጣጥለው አገሪቱ ከ 7 እስከ 8 በመቶ የሚሆን እድገት ማስመዝገቡዋንና በአምስት አመት እቅዱም አገሪቱ ከስድስት እስከ ሰባት በመቶ እድገት ልታስመዘገብ እንደምትችል ጠቁሟል። ይህ የእድገት አሀዝ አገዛዙ […]

በዛሬይቱ ኢትዮጵያ “ሽብርተኛ” የሚለው ቃል ትርጉሙ ተዛብቷል። በአገራችን ሰዎች “ሽብርተኝነትን” ቢያንስ በሚከተሉት ሶስት መንገዶች ይረዱታል። የመለስ ዜናዊ አገዛዝ “በአሸባሪነት” “ጠርጥሮ” ያሰራቸውን ዜጎችን ስብዕና ያስተዋሉ፤ “ሽብርተኛ” የጨዋነት፣  የመልካም ሥነ-ምግባርና የመልካም ዜግነት መጠሪያ አድርገው  ወስደውታል።  እናቶች ልጆቻቸው ሲያድጉ እንደ አቶ አንዱዓለምና አራጌ፣ እንደ አቶ እስክንድር ነጋ ወይም እንደ ወ/ት ርዕዮት ዓለሙ ስም አስጠሪ እንዲሆኑላቸው ይመኛሉ። ህዝብን የስልጣን […]

ከምድር በታች ኢትዮጵዊያንን የሚያስተዳድር አንድ ህግ ብቻ አለ።ይህ ህግ የመለስ ዜናዊ ስሜት ነው። ይህ ስሜት ደግሞ በጫት፤በሲጋራና በመጠጥ ሱሶች የተበከለ ብቻ ሳይሆን ጥልቅ በሆነ ክፋትና ጥላቻ መንፈስ የተሞላ ነው። ይሄም መንፈሱ ጭካኔን፤ ጭካኔውም ፍርሃትን ፈጥሮበት አገራችንን እያሸበራት ይገኛል። መለስ ዜናዊ ጫቱን ቅሞ ሲያበቃ የራሱ ጥላ ጭምር ግንቦት ሰባትን እየመሰለው ያየውን ሁሉ ያዙልኝ እሰሩልኝ ግደሉልኝ እያለ […]

በቅርቡ ሰላማዊ ሰልፍ ለመጥራት ሲዘጋጁ የነበሩ 6 ወጣቶች ከተያዙ በሁዋላ፣ የወጣቶቹ ጉዋደኞች ናቸው የተባሉት ሁሉ እየታደኑ በመያዝ ላይ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሎአል። ሰሞኑን በወያኔ ጸጥታ ሃይል ከተያዙት ወጣቶች መካከል 4ቱ በመገናኛ አካባቢ፣ 2ቱ ደግሞ በመርካቶ እንደተያዙና በ እስር ቤት ከተወሰዱ ቦኋላ በሽብረተኛው የመለስ ዜናዊ የጸጥታ ሰራተኞች እጅግ አሰቃቂ የሆነ ድብደባ እንደተፈጸመባቸው የደረሰን መረጃ ያመለክታል። ወያኔ አለኝ […]

ወያኔ የአዲስሰ አበባ መስተዳደር  በ2005 ዓ.ም. ለሚያደርገው ምርጫ የቅስቀሳ ሥራ እንዲሠሩ በሚል ሰበብ  በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲና ሌሎች  ዩኒቨርሲቲዎችና ኮሌጆች  በተለያየ የትምህረት ደረጃ  በመጀመርያ ዲግሪና በሁሉተኛ ዲግሪ መርሐ ግብሮች በማመር ላይ የሚገኙ  አባላቱን፣ ትምህርታቸውን እንዲያቋርጡና አስፈላጊዉን ቅድመ ምርጫ ዝግጅት እንዲያደረጉ  አሳሰበ። 99 ነጥብ 6% ህዝብ መርጦኛል ከኔም ፍቅር አለዉ እያለ የሚመጻደቀዉ የወያኔዉ ዘረኛ አገዛዝ  ያዲስ አበባን […]

ህዝባችን በሳምንት 3 ግዜ ብቻ መብራት በሚያገኝባት ሀገር የአገሪቱ መብራት ሃይል ኩባንያ ለጅቡቲ መንግስት እስከ 200 ሜጋ ዋት የሚደርስ የኤሌክትሪክ ሃይል ለመሸጥ ዝግጅት እያደረገ መሆኑ ታወቀ። በኢትዮጵያው ሚሊኒየም አከባበር ሥነሥርዓት ላይ የኢትዮጵያ ህዝብ ከአሁን ቦኋላ ሻማ የሚያበራው ለልዴት ቀን  ብቻ ይሆናል ተብሎ በመለስ ዜናዊ የተለመደው የውሽት ተስፋ ቃል የተገባ ቢሆንም ችግሩ እስከዛሬ ተባብሶ እንደቀጠለ ይታወቃል። […]

ህወሀትን ከተቀላቀለበት ከ 1968 ዓመተምህረት ጀምሮ በተሰጠው የአፈናና የግድያ አስተባባሪነት ቦታ በትንሹ ከ 10 ሺህ በላይ ሰዎችን በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለውና ያስገደለው ብስራት አማረ ዛሬ ደግሞ አሜሪካ ተመድቦ ውጪ የሚኖረውን ኢትዮጵያዊ እየሰለለ እንደሚገኝ አቶ ገብረመድህን አርአያ አጋለጡ። ቅጥረኛዉ ነፍሰ ገዳይ ብስራት አማረ፤ አክሱም ተወልዶና እስከ ዘጠነኛ ክፍል ድረስ እዚያው ከተማረ በሁዋላ ህወሀትን መቀላቀሉን የጠቀሱት አቶ ገብረመድህን፤ […]

የሥልጣን ዘመኑን እስከወዲያኛው ለማራዘም የሚችል መስሎት የሚቃወሙትን ሁሉ በሽብርተኝነት እየፈረጀ ዘጎችን ወደ እስር ቤት ማጎር የጀመረው የመለስ ዜናዊ አገዛዝ ያለአገባብ እያሰቃያቸው ያለውን ወገኖቻችንን እንዲፈታ ለመጠየቅ በ እንግሊዝና  በኖርዌዬ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ባለፈው አርብና እሁድ በየሚኖሩባቸው አገሮች ዋና ከተሞች በሎንዶንና ኦስሎ ሰልማዊ ሰልፍ ማድረጋቸውን የግንቦት 7 ዘጋቢዎች ባስተላለፉት ዜና ገለጹ። መለስ ዜናዊ ሽብርተኛ ነው፤ መለስ ዜናዊ ፋሽስት […]

ባለፈው ሳምንት በመኪና አደጋ ህይወታቸውን ያጡትና በከባድ ሁኔታ የቆሰሉት የነባር ህወሀት ታጋይ አርቲስቶች ጉዳይ፤ የትግራይን ህዝብ ክፉኛ እንዳስቆጣ የቀድሞ የህወሃት አመራር አባል የነበሩ አቶ አስገደ ገብረሥላሴ መግለጻቸውን ኢሳት ዘገበ። ታጋይ አርቲስቶቹ በሱዳን ዝግጅታቸውን ለማቅረብ  በመስቀል ዋዜማ በአሮጌ አውቶቡስ ከመቀሌ ተነስተው ጉዞ ቢጀምሩም፤በስተደቡብ 200 ያህል ኪሎ ሜትር ከተጓዙ በሁዋላ ቆቦ አካባቢ ሲደርሱ አውቶቡሱ ተገልብጡ 10 ታጋዮች […]

በሃዲያ ዞን የባዳወቾ ወረዳ ውስጥ ነዋሪ የሆኑ የአላባ ብሄረሰብ አባላት የሚኖሩበት አከባቢ በአላባ ልዩ  ወረዳ ስር እንዲካለል ቀድም ሲል ያቀረቡት ጥያቄ መልስ ባለማግኘቱ የተነሳ በተፈጠረው ችግር፤ ችግር ፈጣሪ የሆነው የወያኔ ጸጥታ ሰራተኞች በህዝቡ ላይ በከፍቱት የተኩስ እሩምታ ከ20 ሰዎች በላይ በጥይት መመታታቸውና ከመካከላቸው የ4ቱ ህይወት ወዲያውኑ ማለፉን ዘጋቢያችን ከስፍራው ካስተላለፈው ዜና ለመረዳት ተችሎአል። የአላባ ህዝብ […]

በአለፈው 2003 መጨረሻ አካባቢ የብርታኒያ የዜና አውታር (ቢቢሲ) የምርመራ ጋዜጠኞቹን በስውር ወደ ኢትዮጵያ ልኮ እንደነበር ይታወሳል። ጋዜጠኞቹ በኦጋዴን፣ በባሌ፣ በወላይታ፣ በደቡብና ምዕራብ ኦሮሚያ እና አዲስ አበባ በመዘዋወር ከታዘቡት ውስጥ ጥቂቱን በነሐሴ ወር ለዓለም ህዝብ አሳይተዋል። በዚያም ጊዜ ባቀረቡት ዘገባ መሠረትም የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታን ሳይጨምር ለልማት እየተባለ ከምዕራባዊያን በየዓመቱ የሚጎርፈው 3 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ማለትም አምሳ […]

የግንቦት7 ርዕሰ አንቀጽ ቁጥር 75 ላይ ወጥቶ የነበረ “ለስድስት ተከታታይ ዓመታት ከአስር በመቶ በላይ የኢኮኖሚ እድገት አሳይተናል” የሚለው ዓይን ያወጣ ውሸት፤ “ድህነትን ተረት እናደርጋለን” የሚለው ጉረኛ መፈክር፤ የወያኔዎችና ጀሌዎቻቸው በፎቅና ቪላዎች መንበሽበሽ፤ ለም መሬቶች በአበባ እርሻዎች መተካታቸው እና የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ራድዮ ”የህዳሴ ብስራቶች” ለሕዝባችን ምሳና እራት አልሆኑም። የረሃቡ ስጋት እየገፋ ሲመጣ መለስ ከአፄ ኃይለሥላሴም ሆነ […]

ዘረኛው የወያኔ አገዛዝ አለኝ በማለት በሚኩራራው ህገ መንግሥት በመተማመን ለነገ መስከረም 21 ቀን በአዲስ አበባ ከተማ ወስጥ የሚካሄድ ሰላማዊ ሰልፍ ለማዘጋጀት ሲንቀሳቀሱ በወያኔ ደህንነትና ፖሊስ ተይዘው እስር ቤት ከተወረወሩት የሰላም ታጋዮች መካከል አቶ ክንፈ ሚካኤል ደበበ፣ ወጣት ተስፋሁን አናጌ፣ ወጣት ታምራት ሻማና ሌሎች ከእነሱ ጋር የታሰሩ 3 ግለሰቦች በትናንትናው እለት ፍርድ ቤት ቀርበው እንደነበር የግንቦት […]

ነዋሪነታቸው በስዊድን የሆኑ ኢትዮጵያውያን ትናንት መስከረም 19 ቀን 2004 ዓም በስዊድን ዋና ከተማ ስቶክሆልም ከአገሪቱ ፓርላማ ፊት ለፊት ባደረጉት የተቃውሞ ሰልፍ ወያኔ የአገዛዝ ዘመኑን ለማራዘም ሲል ያለአግባብ በእስር ቤት ያጎራቸው የፖለቲካ እስረኞችና ጋዜጠኞች በሙሉ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በአስቸኳይ እንዲፈቱ ጠይቀዋል። ሰልፈኞቹ በያዙዋቸው መፈክሮች መለስ ዜናዊ በዘጎች ላይ ለፈጸመው ፍጅት ለፍርድ ይቅርብ፣ የኢትዮጵያ ህዝብ የስልጣን ባለቤት […]

የአለማችን ጠንካራው የሰብአዊ መብቶች ተሟጋች የሆነው ሂውማን ራይተስ ወች ለእንግሊዙ የውጭ የልማት ትብብር ሚኒስትር አንዲሪው ሚቼል በጻፈው ደብዳቤ፣ ባለስልጣኑ ለኢትዮጵያ የሚሰጠው የውጭ እርዳታ ኢትዮጵያውያንን ለመጨቆኛነት መዋሉን ማረጋገጥ አልቻልም በማለት ለቢቢሲ የሰጡት ቃል ተአማኒነት የሌለውና ህዝብን ሆን ብሎ ለማደናገር የቀረበ ነው በማለት ወቅሷል። ሂውማን ራይትስ ወች ለኢትዮጵያ የሚሰጠው እርዳታ ለተገቢው ህዝብ ከሚደርስ ይልቅ የመለስ መንግስት የፖለቲካ […]

የአባይ ግድብ የህዝብ አደራጅ ኮሚቴ ተብሎ የተቋቋመው ድርጅት ሀላፊ የሆነው በረከት ስምኦን ለብሉምበርግ እንደተናገረው ፣ የመንግስት ሰራተኛው ከደሞዙ እየቀነሰ የአባይን ግድብ ቦንድ እንዲገዛ መታዘዙ የሚያዛልቅ አልሆነም በማለት ቀደም ሲል ከፍተኛ የህዝብ መነቃቃት ታይቶበታል ተብሎ በወያኔና ተባባሪዎቹ ሚዲያ ሲራገብ የነበረውን ባዶ ፕሮፖጋንዳ አጋለጠ። ላለፉት በርካታ ወራት ጠዋትና ማታ ህዝብ በነቂስ ወጥቶ ለግድቡ ማሰሪያ ገንዘብ እያዋጣ ነው […]

በምዕራባዊያን የገንዘብና የፖለቲካ ድጋፍ ህዝባችንን አፍኖና ረግጦ እየገዛ ያለው የዘረኛው መለስ ዜናዊ አገዛዝ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዜጎቻችን ላይ አጠናክሮ የቀጠለውን እስር በማውገዝ ቁጥራቸው በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን በትናንትናው ዕለት በአሜሪካን ስቴት ዲፓርትሜንት ፊት ለፊት ተገኝተው ደማቅ ሰላማዊ ሰልፍ ማካሄዳቸውን ሪፖርተራችን ከሥፍራው በላከልን ዜና ገለጸ። ሞት ለወያኔ-፤ ሞት ለጎጠኞች ፤ ሞት ለሽብርተኛው መለስ ዜናዊ፤ መለስ ዜናዊ […]

ዘረኛውና አምባገነኑ የወያኔ አገዛዝ በተለይም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ንጹሃን ዜጎችን ሽብርተኞች ናችሁ በማለት የጀመረው የጅምላ እስራት፣ የአምባገነኑ ስርአት ማብቂያ ዋዜማ መሆኑን የሚያመለክት ሲሆን አገዛዙ እየፈጸመ ያለው ድርጊት ደግሞ የራሱን መቀበሪያ ጉድጉአድ እየቆፈረ እንደሆነ የሚያረጋግጥ ነው በማለት በርካታ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ለዘጋቢያችን ገለጹ:: እንደዘጋቢያችን ሪፖርትና በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ ክፍለ ከተሞች በመዘዋወርም ያነጋገራቸው በርካታ የአዲስ […]

ዘረኛው የወያኔ አገዛዝ በወገኖቻችን ላይ የጀመረውን የእሥር ዘመቻ ለማስቆምና ሽብርተኝነትን በመከላከል ሥም በአገዛዙ እየተካሄደ ያለውን መንግሥታዊ ሽብር ለአለም አቀፉ ህብረተሰብ ለማሳወቅ ኢትዮጵያዊያኑ በየሚኖሩበት የምዕራብ አገሮች ከፍተኛ የሆነ እንቅስቃሴ እያካሄዱ መሆኑን ወደ ዝግጅት ክፍላችን እየደረሱ ያሉ መረጃዎች አመለከቱ። ባለፈው ሰኞ በአሜሪካን አገር ስቴት ዲፓርትመንት ፊት ለፊት የተጀመረው የኢትዮጵያዊያን ተቃውሞ፤ በነገው ዕለት መስከረም 19 ወይም እንደ ፈረንጆቹ […]

ዘረኛው የወያኔ አገዛዝ በድህረ ምርጫ 97 የቅንጅት መሪዎችን፤ ጋዜጠኞችንና የስብአዊ መብት ተሟጋቾችን እስር ቤት ባጎረበት ወቅት፤ ዳግም ለወያኔ እስር በተዳረገው ባለቤቷ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ጋር እስር ቤት እየማቀቀች የተገላገለቺው ህጻን ልጇ እንደ አባቱ የነጻነት ታጋይ እንዲሆን ምኞቷ መሆኑን ጋዜጠኛ ስርካለም ፋሲል አዲስ ጉዳይ በተባለ መጽሄት ላይ ባሳተመቺው ጽሁፍ መግለጿን ለማወቅ ተችሎአል። ጋዘጠኛ ስርካለም በአመዛኙ ስለ […]

ዛሬ የምንገኝበት እውነታን አቶ አንዱዓለም አራጌ በመለስ ዜናዊ ችሎት በተናገራቸው ሁለት ዓረፍተ ነገሮች አጠቃሎታል፤ እንዲህ በማለት። ለመጀመርያና ለመጨረሻ ጊዜ የምለው አለኝ፤ በኢትዮጵያ የተያዘው ነገር የፖለቲካ ተቃውሞ አፈና ስለሆነ ፍርድ ቤቱ እስከ ሞት ድረስ መወሰን ይችላል፡፡ ከዚህ በኋላ ምንም ነገር አልናገርም። በመለስ ዜናዊ ዘረኛና አፋኝ ህግ መሠረት ህጋዊና ሰላማዊ ትግል በሽብርተኝነት ያስከስሳል። አቶ አንዱዓለም እንዳለውም ለዚህ […]

ለገዛ ራስና ለሃገር ነፃነት አርበኛ መሆን በመለስ ዜናዊ እና እሱ በሚቆጣጠራቸው ሚዲያዎች “ሽብርተኛ” ያስብላል፤ ያስከስሳል፤ ያሳስራል። አርበኝነት ክብር ነው። አርበኝነት የመልካም ዜግነት ከፍተኛው መገለጫ ነው። አርበኝነት የታላቅ ስብዕና መገለጫ ነው። በመለስ ዜናዊ እና እሱ በሚቆጣጠራቸው ሚዲያዎች “ሽብርተኛ” መባል የአንድ ኢትዮጵያዊ ግለሰብ ወይም ኢትዮጵያዊ ድርጅት አርበኝነት ማሳያ ሆኗል። እናም በመለስ ዜናዊ “ሽብርተኛ” መባልና የሚያኮራና የሚያስደስት ነገር […]

የግንቦት7 ንቅናቄ ሊ/መንበር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የ2004 አዲስ አመት አስመልክተው ለኢትዮጵያ ህዝብ ያስተላለፉት መልዕክት ሙሉ ቃል ውድ የኢትዮጵያ ህዝብ! በቅድሚያ በግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ እና በራሴ ስም “እንኳን ከዘመን ወደ ዘመን አሸጋገረን” እላለሁ። ያሳለፍነው 2003 ዓመተ ምህረት በዓለም ላይ ብዙ አስደናቂና ተስፋ ሰጪ ኩነቶች የታዩበት ዓመት ነበር። እኛ በነፃነት ስንኖር በቅኝ ግዛት ባርነት […]

ጥምረት ለፍትህ ለነጻነትና ለእኩልነት ባለፈው ቅዳሜ ጳጉሜ 3 ቀን በአሜሪካን አገር በዳላስ ከተማ አዘጋጅቶት በነበረው ስብሰባ ላይ ለተገኙት ኢትዮጵያዊያን ንግግር ያደረጉት የኦሮሞ ነጻነት ግምባር ዋና ጸሃፊ ፤ ዘረኛውና አምባገነኑ የወያኔ አገዛዝ በህዝባችን ላይ እያደረስ ያለውን ሰቆቃ ለማስቆምና ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ለመገንባት ኦነግ ከግንቦት7 እና ለዲሞክራሲ ከሚታገሉ ሌሎች ድርጅቶች ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችለውን ውይይት እያደረገ መሆኑን አስታወቀ። […]

የግንቦት ሰባት ንቅናቄ ሊቀመንበር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ በራሳቸውና በድርጅታቸው በግንቦት 7 ሥም ለኢትዮጵያዊያን ባስተላለፉት የአዲስ አመት መልእክት በስልጣን ላይ ያለው ዘረኛ አገዛዝ ተወግዶ ነጻና ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ የምትገነባበት እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል። በተመሳሳይ መልኩ አንድነት ፓርቲ 2004 የለውጥ አመት እንዲሆን፣ ወጣቱ በአንድነት ለነጻነቱ እንዲነሳ ጥሪ አቅርቧል። አንድነት ባወጣው በዚሁ መግለጫው የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዘመናት የተነጠቀውን ነፃነቱን ለመቀዳጀት ዛሬውኑ […]

ያለህዝብ ፈቃድ ለዘመናት ሥልጣን ላይ ሆነው የህዝብና የአገራቸውን ደም የሚመጡ አምባገነኖችን የሥልጣን መሠረት እያናጋ የመጣው የሰሜን አፍሪካ ህዝባዊ አብዮት ያስደነገጠው የወያኔ አገዛዝ፤ ተመሳሳይ ህዝባዊ አመጽ ሊቀሰቀስብኝ ይችላል ከሚል ስጋት በአገር ውስጥ ተመዝግበው ሠላማዊ ትግል ለማካሄድ የሚንቀሳቀሱትን የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት መሪዎችና፣ የዲሞክራሲ አክትቪስቶችን በገፍ ማሰር እንደቀጠለ የግንቦት 7 ዜና ዘጋቢ ከአዲስ አበባ በላከልን ዜና አስታወቀ። እንደዘጋቢያችን […]

መስከረም ወር ላይ በአዲስ አበባ ከተማ ለሶስት ሰዎች ህይወት ማለፍ ምክንያት የሆነውንና በርካታ ንብረት ያወደመውን የቦምብ ፍንዳታ ያቀነባበረውና ሴራውንም የሸረበው ዘረኛውና አጥፊው የወያኔ አገዛዝ ቁንጮ መለስ ዜናዊ እንደነበር በዊኪ ሊክስ ላይ አፈትልኮ የወጣው የአሜሪካ መንግሥት መረጃ አጋለጠ። በወቅቱ በአዲስ አበባ ፍንዳታ በደረሰበት ወቅት ዘረኛውና አምባገነኑ የወያኔ አገዛዝ በቁጥጥሩ ስር በሚገኙት የቴሌቪዥንና ራዲዮ ጣቢያዎች ፍንዳታውን የፈጸሙት […]