Ethiopia Zare (ዓርብ መስከረም 12 ቀን 2004 ዓ.ም. September 23, 2011)፦ ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ “ከሽብርተኞች ጋር ንክኪ አላቸው” የሚል መሰረተ ቢስ ክስ እየመሰረተ በርካታ

ዛሬ የምንገኝበት እውነታን አቶ አንዱዓለም አራጌ በመለስ ዜናዊ ችሎት በተናገራቸው ሁለት ዓረፍተ ነገሮች አጠቃሎታል፤ እንዲህ በማለት። ለመጀመርያና ለመጨረሻ ጊዜ የምለው አለኝ፤ በኢትዮጵያ የተያዘው ነገር የፖለቲካ ተቃውሞ አፈና ስለሆነ ፍርድ ቤቱ እስከ ሞት ድረስ መወሰን ይችላል፡፡ ከዚህ በኋላ ምንም ነገር አልናገርም። በመለስ ዜናዊ ዘረኛና አፋኝ ህግ መሠረት ህጋዊና ሰላማዊ ትግል በሽብርተኝነት ያስከስሳል። አቶ አንዱዓለም እንዳለውም ለዚህ […]

አስናቀች ተዋናይ የባህል ሙዚቀኛ፣ ክራር ተጫዋች፣ ድምጻዊት፣ የባህል ተወዛዋዥ፣ ዘመናዊ ዳንሰኛ፣ ገጣሚ ሁለገብ የጥበብ እመቤት ነበረች፣ ላትመለስ መስከረም አራት ሁለት ሽ አራት አመተ ምህረት ከዚህ አለም በሞት ተለይታናለች። በጀርመናዊዉ ፒት ቡደ በአስናቀች የክራር ድርደራ ተመስጠዉ፣ ዜማዋን አፍቅረዉ የአስናቀችን ሙዚቃ በዘመናዊዉ …

አስናቀች ወርቁ የመድረኳ ዕንቁ Read more »

ዘመኑ ሞላ ተወልዶ ያደገው ከዚሁ አዲስ አበባ ሲሆን፣ ባለትዳርና ያንዲት ሴት ልጅ አባት ነው፡፡ ልጁ ጎበዝ ተማሪ ስለሆነች በዚህ ዓመት ዩኒቬርስቲ እንደምትገባ በቅርብ የሚያውቋት ይናገራሉ፡፡
ዘመኑ ሞላ ነባር የሰላማዊ ትግል ታጋይ ሲሆን የኢዴፓ ነባር አባል በመሆኑ በ92 ዓ.ም በተደረገው ሁለተኛው አገራዊ ምርጫ አ.አ ክልል ተወዳድሮ ነበር፡፡
ቆይቶ ደግሞ ኢዴፓ የሚሄድበት መንገድ ስላላማረውና ስላልጣመው ከዚያ […]

አካባቢው አንድ ገጠር መንደር ነው፡፡ የዘመኑ የአካባቢው ገዢ ሕዝቡን ሰብስቦ ሲናገር ይውላል፡፡ ሕዝቡም ዝም ብሎ ያዳምጣል፤ እርሱ ያወራል ሕዝቡን ያዳምጣል። መናገር ሲስለቸው «አሁን ተራው የእናንተ ነው፤ ሐሳብ መስጠት ትችላላችሁ» ይላቸዋል፡፡
ሁሉም ዝም ይላል፡፡ «ተናገሩ» ይላል አሁንም በመደጋገም ። አሁንም ሕዝቡ ዝም አለ፡፡ “ጊዜው የዴሞክራሲ ነው ፤ የፈለጋችሁትን መናገር ትችላላችሁ፡፡ ተርበን፣ ሞተን፣ ቆስለን፣ ጓደኞቻችን ሞተው […]

በቅርቡ “በሽብርተኝነት”ተጠርጥረው የታሠሩትን እስረኞች «በምን ሁኔታ ላይ አንደሚገኙ ማወቅ አልቻልንም» ሲሉ ቤተሰተቻቸውና የሥራ ባልደረቦቻቸው ለዝግጅት ክፍላችን ገለጹ፡፡
የአንድነት ፓርቲ ም/ሊቀመንበርና የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ የሆኑት የአቶ አንዱዓለም አራጌ ወንድም ወጣት አብርሃም አራጌ እንደሚለው “ወንድሜ የታሠረበትን የእስር አያያዝ ማወቅ አልቻልኩም፡፡ በተደጋጋሚ ለመጠየቅ ሄጄ ምግብ ተቀብለው ዕቃ ከመመለስ ውጪ በአካል አግኝቼው አላውቅም”፡ ብሏል፡፡
የፓርቲው ማዕከላዊ ም/ቤት አባላት የሆኑት […]

አሣምነው ብርሃኑ ተወልዶ ያደገው ከዚሁ አዲስ አበባ ነው፡፡ የትምህርት ደረጃው በፊዚክስ ቢ.ኤስ.ሲ ዲግሪ አለው፡፡ ባሁኑ ጊዜ በኢኮኖሚክስ በዲግሪ መርሃ ግብር አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እየተማረ ነበር፡፡ መደበኛ ሥራውም መምህር ነው፡፡
ቤተሰብ አሣምነው ብርሃኑ ገና ወጣት በመሆኑ ለሥራና ለትምህርት እንዲሁም ለነፃነት ተግቶ ከመሥራት ውጭ ትዳር ለመመሥረት አስቦ እንደማያውቅ ቤተሰቦቹ ገልፀውልናል፡፡
የፖለቲካ አቋምአሳምነው ብርሃኑ አንድነት ፓርቲን ከመቀላቀሉ በፊት […]

ክቡር ጠ/ሚንስትር የሰው ልጅ የአገሩን የአስተዳደር መረጃ ካለማጤን ስህተት መፈጠሩ አይቀሬ ቢሆንም በተጓደኝ የተፈፀመውንና የተደረገውን በማስታወስ የተሠራ ጥፋት መታረም ይቻላል፡፡ ከዚህ አንፃር ባገራችን የሚታየውንና እየተፈፀመ ያለውን ግዙፍ ስህተት ቅኝ ገዥዎች እንኳን ይሠሩታል ብሎ ለመናገር የሚከብድ ይመስለኛል፡፡ ይህንን ጽሑፍ ለመዳፍ ያነሳሳኝ ሀገራዊ ስሜትና ፍቅር እየቆጠቆጠኝ አላስቆም አላስቀምጥ ስላለኝ ሰሚ ባይኖርም የድርሻዬን ልወጣ በሚል ነው፡፡
ኢሕአዴግ ሥልጣን ከተቆናጠጠበት […]

ከጥቂት ወራት ወዲህ ገዢው ፓርቲ ስርዓቱ ላይ የሠላ ሂስ በመሠንዘር የሚታወቁ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችና ጋዜጠኞችን የማሠር ዘመቻውን ጀምሯል፡፡ የእስራት ዘመቻው ማቆሚያ የት ጋ እንደሆነ የታወቀ ነገር እስካሁን የለም፡፡ የእስር ዘመቻው ያነጣጠረው ግን ከኢህአዴግ አቋም በተቃራኒው የቆሙ ግለሰቦች ላይ መሆኑ የአገራችንን የወደፊቱን የፖለቲካ አቅጣጫ አሳሳቢ አድርጎታል፡፡
ከታሪክ እንደምንማረው በዓለም ላይ በርካታ አምባገነን መንግስታት ኖረው አልፈዋል፡፡ አውሮፓን ሲያምሱት […]

ካፕቴን ተሾመ ተንኮሉ ባለፈው ሰሞን፡ የአንጋፋው የኢትዮጵያ ስፖርት ፎደሬሽን በሰሜን አሜሪካ፡ በአረብ/አበሻው ቱጃር ሰበብ ታምሷል መባሉን ሰምቼ፤ ይህንኑ ጉዳይ በተመለከተ አነስ ያለች ፅሁፍ ለዘወትር ወዳጄ ብሰድለት፤ በሃሳቤ መለስለስ ነው መሰለኝ ብዙም ሳይደሰት፤ “ወያኔን እየደጋገሙ ነጋ ጠባ መውቀስ ብቻውን ጠላት ከማብዛት …

ሰራዊቱ ከምድር ጦር እስከ አየር ሀይል – ካፕቴን ተሾመ ተንኮሉ Read more »

ኢህአዴግ የዴሞክራሲና የህግ የበላይነት ጥያቄ ሲቀርብለት ዘወትር የሚያሳው መቃብሩን ነው።የአንድነት ጥያቄ ሲቀርብ ምላሹ “እኛ ከፈለሰፍነው አንድነት ውጭ ሌላው አንድነት በኢህአዴግ መቃብር ላይ ካልሆነ በስተቀር የማይታሰብ ነው”የሚል ነው።የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ ሲነሳ “የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ ህያው የሚሆነው በኢህአዴግ መቃብር ላይ ብቻ ነው”በማለት ወደ መቃብሩ ያመላክተናል።አንቀፅ 39 በታኝ መሆኑን ህዝብ ሲገልፅ “የህዝብ ልጆች የተሰውለት የትግሉ የማዕዘን ድንጋይ ነው፣እኔ […]

ከዓለምአቀፍ የሲቪልና ፖለቲካዊ ንቅናቄ ለዴሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ በሕወሀት/ኢህአዴግ ወቅታዊና ስር የሰደደ ጭቆና ላይ የወጣ አስቸኳይ የጋራ መግለጫ እሁድ፡ መስከረም 18፡ 2004 የኢትዮጵያ ሕዝብ የስልጣን ባለቤት ይሆናል!! በሰሜን አሜሪካ የምንኖር፡ በኢትዮጵያ ለውጥ እንዲመጣ የምንታገል፡ የፖለቲካ ድርጅቶችና የሲቪል ማህበራት አባላትና ድጋፍ ሰጪ …

የኢትዮጵያ ሕዝብ የስልጣን ባለቤት ይሆናል Read more »