ዓለም ዓቀፍ የጤና ባለሙያዎች በአፍሪቃ በርካታ የፈጠራ ስራዎችና ባለሙያዎቹ የምርምር ዉጤታቸዉ ይፋ ስለማይወጣ ካሉበት ከፍ አለማለታቸዉንና ለተጠቃሚዉ ኅብረተሰብም መድረስ እንዳልቻለ አመለከቱ።

በኢትዮጽያ በቢዮ ፊዉል ልማት ማለት ለአማራጭ ነዳጅ የተክል እርሻ ስራ ተሰማርተዉ ከሚገኙት የዉጭ ድርጅቶች አንዱ ፍሎራ ኤኮ ፓወር ሃረር ባቢሌ አካባቢ የጀመረዉን ስራ አቋርጦ መዉጣቱን ማስታወቁ ይታወሳል።

የአራት ሃይማኖቶች አባቶች በእስር ላይ የሚገኙ የቀድሞ መንግስት ለስልጣናት እንዲፈቱ ጥረት መጀመራቸውን በይፋ አስታዉቀዋል። ላለፉት 20 ዓመታት የታሰሩት እነዚህ ባለስልጣናት የሚፈቱበት ሁኔታ ህጋዊ መሠረቱ ምን ይሆን?

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት መኢአድ ቅዳሜ እና ዕሁድ ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ ከፖለቲካው ዓለም ራሳቸውን እንዳገለሉ የተናገሩትን የድርጅቱን ፕሬዝዳንት ኢንጅነር ኃይሉ ሻውልን በድጋሚ ለሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ድርጅቱን እንዲመሩ መርጧል ። ኃይሉ ሻውል ይህን የፓርቲውን ከፍተኛ ሥልጣን ለሌላ ያስረክባሉ ተብሎ ሲጠበቅ ነበር …

የኃይሉ ሻውል ወደ መኢአድ መሪነት መመለስ Read more »

አውሮፓን ከብዙ ዕንቅስቃሴዎች የገታው በቅርብ ዓመታት ታሪክ ተወዳዳሪ ያልተገኘለት በረዶ ከቅዳሜ አንስቶ በመጠኑም ቢሆን ጋብ ብሏል ። ይሁን እንጂ የተቆለለው በረዶ እና ኃይለኛው ንፋስ በሰውና በንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱ አልቀረም ።

የመንግስታቱ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት በሶማሊያ የተሰማራው የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ሰራዊት ቁጥሩ በአራት ሺህ እንዲጨምር ወሰነ። የሰራዊቱ የቆይታ ጊዜ በ8 ወራት እንዲራዘምም ምክር ቤቱ ወስኗል።

ሲና በረሀ ውስጥ እንደታገቱ ከሚገመተው አብዛኛዎቹ ከኤርትራ ናቸው ከሚባሉ 250 የሚደርሱ ስደተኞች 8 ቱ ሳይሞቱ እንዳልቀረ የስደተኞች ካውንስል የተባለ ድርጅት አስታወቋል ። ድርጅቱ እንደሚለው ቀሪዎቹ ታጋቾች የሚገኙበት ሁኔታም አሳዛኝ ነው ።

በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ሰዎች በግፍ ተሰቅለው የሚገደሉበት በቁማቸውም የሚሰቃዩበት ስፍራ ነበር ፤ ኮሎኝ Appelhofplatz በተባለው አካባቢ የሚገኘው የቀድሞው የናዚ ጀርመን ሚስጥራዊ የፖሊስ ኃይል ማዕከል ዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ።

የጀርመን መራሂተ መንግስት አንጌላ ሜርክል ባለፈው ቅዳሜ ሳይታሰብ በአፍጋኒስታን የሚገኙትን የሀገራቸውን ወታደሮች ጎበኙ። ጀርመናውያኑ ወታደሮች በጦርነት ላይ እንደሚገኙ ሜርክል በዚሁ ጉብኝታቸው ወቅት ባሰሙት ንግግራቸው በግልጽ አስታውቀዋል።

በእስር ላይ የሚገኙ የቀደሞ የደርግ ባለስልጣናትና ዕርቀ-ሰላም ላይ ያተኮረ ውይይት ቅዳሜ ታህሳስ 9 ቀን 2003 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ተከናወነ። ውይይቱን ያካሄዱት የሀይማኖት መሪዎች በሀገሪቱ ዕርቅና ሰላም እንዲወርድም ጥሪ አድርገዋል ። መሰል የዕርቅና የሰላም ጥሪ በተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶች ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ …

የደርግ ባለስልጣናትና ዕርቀ-ሰላም Read more »

አንድ አባት ስለ ጠጅ፣ «ጠጅ እንዳል ተከበርክ ጥንት በዘመኑ፣ ዛሪ ነገሱብህ ዉስኪ ምናምኑ» ብለዉ ገጠመ አሉ! የቤተ-መንግስት መጠጥ የጨዋ መጠጥ በመባል የሚታወቀዉ ጠጃችን በባለሞያ በአዋቂ ሴት በመጣሉ በየቦታዉ ባለመገኘቱ

በየጊዜው፣ ከዓመት -ዓመት፣ በሳይንስ የሚደረገው ምርምር ፣ በሥነ ቴክኒክ ረገድ የሚቀርበው የፈጠራ ውጤት ፣ የሰውን ልጆች አኗኗር ለማቅለል፣ ለወቅታዊ ችግሮች መላ ለመሻት መሆኑ ቢታሰብም፣ ከቅንጦት ጋር የተያያዘም እንደሚገኝበት የሚያጠራጥር አይደለም።

የኬንያ የትምሕርት ሚንስትር፥ የኢንዲትሪ ሚንስትር፥ የራዲዮ ጣቢያ ሐላፊ፥ የካቢኔ ጉዳይ ሚንስትር እና የቀድሞ የፖሊስ ኮሚሽነር ከአንድ ሺሕ ሁለት መቶ በላይ ሰዎች ሕወት ለጠፋበት ወንጀልና መዘዙ ግንባር ቀደም ተጠያቂዎች ናቸዉ።