በምስራቅ አፍሪቃዊቱ ሀገር ዩጋንዳ ትናንት ምክር ቤታዊ እና ፕሬዚደንታዊ ምርጫ ተካሄደ። በፕሬዚደንታዊው ምርጫ ሰባት የተቃዋሚ ወገን ዕጩዎች ዩጋንዳን ላለፉት ሀያ አምስት ዓመት በመሩት የስድሳ ስድስት ዓመቱ ፕሬዚደንት ዮዌሪ ሙሴቬኒ አንጻር ተወዳድረዋል።

የአዋሳ ከተማ አስተዳደር በህገ ወጥ መንገድ የአርሶ አደር መሬት ገዝተው መኖሪ ቤትና የተለያዩ ግንባታዎችን ያከናወኑ ናቸው ባላቸው ሰዎች ላይ እርምጃ ሊወስድ እንደሚችል ገልጿል። ከ1985 ጀምሮ በተለይ ዳቶ በተሰኘው አከባቢ መኖሪያ ቤት ሰርተው እየኖሩ እንደሆኑ የሚገልጹት ነዋሪዎች መንግስት ያለምንም አማራጭ ሊያፈናቅለን …

40 ሺህ የአዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ቤታችሁን ልቀቁ ተባሉ Read more »

ከአገራችን ባህል አኳያ በዳይና ተበዳይ ይቅር መባባል ይቅርታን መቀበል መስጠት የተለመደ ጥንታዊ ባህላችን ነዉ። ተበዳይ ለዘለቄታ አብሮ ለመኖር ቂም በቀልን ትቶ በዳይን ይቅር ብሎ በሽምግልና ችግርንም መፍታት ለአገር ልማት በጋራ ለመኖር እና ለመስራት ታላቅ መፍትሄ መሆኑ የሚታወቅ ነዉ።

ህዝባዊ አመጽ በግብፅና ቱኒዚያ ከተቀጣጠለበት ጊዜ አንስቶ ሁኔታዎች በቻይናም ሊገነፍሉ የደረሱ ይመስላል። አንድ ቻይናዊ ፖለቲከኛ ነገሮች በኛም ሀገር በቋፍ ላይ ነው ያሉት ሲሉ ገልፀዋል። በእርግጥ በግብፅና ቱኒዚያ የተከናወነው አይነት ህዝባዊ አመፅ በቻይናም ቢቀጣጠል ምን ይከሰት ይሆን?

በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ኢራናውያን ትናት ሰኞ (08. 06.2003 ዓ.ም.) አደባባይ መውጣታቸው ተዘገበ። ሰልፈኞቹ የኢራን መንግስትን ሲቃወሙ በአንፃሩ ለግብፅና ቱኒዚያ የዲሞክራሲ ንቅናቄ ድጋፋቸውን አሳይተውበታል። የኢራን የፀጥታ ሀይላት በሰልፈኛው ላይ ምህረት አልባ ርምጃ መውሰዳቸውም ተጠቅሷል። በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ኢራናውያን በግብፅና ቱኒዚያ የተከናወኑ …

ኢራናውያን እገዳውን ጥሰው ሰልፍ ወጡ Read more »

ካላፉት 3 ቀናት አንስቶ የኢጣልያዋ ደሴት ላምፔዱዛ በቱኒዝያ ስደተኞች ተጥለቅልቃለች ። እነዚህ ቁጥራቸው ከነዋሪዎቿ በላይ የሆነው በጀልባ ወደ ደሴቲቱ የጎረፉና የሚጎርፉ ስደተኞች ኢጣልያን በእጅጉ አስጨንቀዋል ።

ማሳሰቢያ የዶቸ ቬለ የፕሮግራም ሥርጭቶች ሆን ተብሎ መታወክ ደረሰባቸው፣ መታወክ የደረሰባቸው የሞገድ መስመሮች፤ Hotbird 8 ሳተላይት በኩል የሚሰራጩት ናቸው ። ሞገዶቹ ሆን ተብሎ በአዋኪ ድምፅ መሰናክል ገጥሟቸዋል ። ቀደም ባለው ጊዜ ይህ ዓይነቱ የሚያውክ ድምፅ ያጋጥም የነበረው ከኢራን በኩል ነው …

በኢራናን፤ ግብፅና ቱኒዚያን የደገፈው ሰልፍ Read more »

የቱኒዝያ ስደተኞች በባህር በኩል ወደ ኢጣልያ ጠረፍ መጉረፋቸዉ አሁንም እንደቀጠለ ነዉ። በዚህም ጣልያን የአስቸኳይ ጊዜ ደምብ አስፍሮአል። በኢጣልያ ጠረፍ ጥበቃ ሃይል መግለጫ መሰረት ባለፈዉ ሌሊት ብቻ አንድ ሺህ ገደማ የሚጠጉ ስደተኞች ላፓዱዛ ደሴት ደርሰዋል። ቀደም ባሉት ቀናት ቢያንስ ሶስት ሹህ …

ኢጣልያና የቱኒዝያ ስደተኞች ጎርፍ Read more »

ማንተጋፍቶት ስለሺ የግብፅ ጦር በቀድሞ ፕሬዚዳንት ሆስኒ ሞባረክ 20 ታማኞች ላይ የጉዞ እገዳ አስቀመጠ። የጎዞ እገዳውን ያስተላለፈው የግብፅ ጦር ሲሆን፤ ባለስልጣናቱ ሀገር ለቀው እንዳይሸሹ በሚል ያስተላለፈው ውሳኔ እንደሆነም ተጠቅሷል። ባለስልጣናቱ መጓዝ ከፈለጉም ከጦሩ ፍቃድ ማግኘት እንዳለባቸው ተጠቁሟል። ይህ በእንዲህ እንዳለ …

በግብፅ ባለስልጣናቱ እገዳ ተጣለባቸው Read more »

በብዙ ሺህ የሚቆጠር ህዝብ በትልቅ ጉጉት የጠበቀው እና ፕሬዚደንት ሙባራክ ከስልጣን እንደሚወርዱ ያስታውቁበታል ያለው ዲስኩራቸው ህዝቡ የጠበቀውን ውጤት አላስገኘለትም ነበር፤ ግን የህዝብ ተቃውሞ ተጠናክሮ በመቀጠሉ ፕሬዚደንት ሙባራክ ትናንት ስልጣናቸውን መልቀቅ ተገደዋል። ይህም በህዝቡ ዘንድ ትልቅ ደስታና ፈንጠዝያ ፈጥሮዋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት ቀደም ሲል 1.8 ሚልዮን ሄክታር መሬት፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህም (የዚያኑ እጥፍ) 3.6 ሚልዮን ሄክታር ለም መሬት ፣ ለውጭ ሀገር ኩባንያዎች ከ 40-99 ዓመት ገደማ በኪራይ ይሁን በሽያጭ እንዲቀራመቱ ፈቅዷል። ቻይናውያን ፣ ህንዳውያን፣ ዐረቦችና ኮሪያውያን በሽሚያ ላይ ናቸው። አውሮፓውያንም …

በኢትዮጵያ የለም መሬት ቅርምትና ከጀርመን የተሠነዘረው ተቃውሞ Read more »

የግብፅ ፕሬዝደት ሆስኒ ሙባረክ ከ18ቀናት ዉዝግብ በኋላ ስልጣን ለቀቁ። ለቀናት አደባባይ ወጥቶ ስንብታቸዉን ሲጠይቅ የከመዉ ህዝብ ደስታዉን እየገለፀ ነዉ። ሙባረክ፤ ትናንት ማታ በተስፋ ሲጠብቃቸዉ ለነበረዉ ህዝብ ከፊል ሥልጣናቸውን ለምክትል ፕሪዚዳንትነት  ለመረጧቸው ዖማር  ሱሌይማን ማስተላለፋቸውን ከመጠቆም በስተቀር ከሥልጣን እንደሚወርዱ ሳይገልጹ ነበረ …

ሆስኒ ሙባራክ ከሥልጣን ተሠናበቱ Read more »

የጀርመን መዲና በርሊን ዛሪ ስድሳ አንደኛዉን አለም አቀፍ የፊልም ትዕይንት ማስተናገድ ይጀምራል። ለአስር ቀናት የሚዘልቀዉ ይህ የፊልም ትዕይንት በአለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ የሆኑ የፊልም ስራ አዋቂዎችን የፖለቲካ ሰዎችን እና ታዋቂ የህብረተሰብ አባላትን በመጋበዝ በተለያየ አለም አገሮች የተሰሩ ፊልሞችን በማወዳደር ሽልማት …

61 ኛዉ አለም አቀፍ የሲኒማ መድረክ- በርሊናለ Read more »

የካይሮዉ ተሕሪር ወይም የነፃነት-አደባባይ ዛሬም እንደ መሰንበቻዉ መብት ነፃነቱን በሚጠይቀዉ የግብፅ ሕዝብ እንደተጨናነቀ ነዉ።የአሌክሳንዴሪያ፥ የስዌዝና የሌሎችም ትላልቅ ከተሞች አዉራ ጎዳኖች የሙባረክ ተቃዋሚች ይርመሰመሱባቸዋል

አብዛኛዎቹ የአዲስ አበባ ነዳጅ ማደያዎች ዛሬ ለደንበኞቻቸው የተለመደውን የነዳጅ ሽያጭ አገልግሎት ማስጠት ማቆማቸውን የአዲስ አበባው ወኪላችን ታደሰ እንግዳው ዘግቧል ። ምክንያታቸውም ኢታኖል የተደባለቀበት ነዳጅ የለም የሚል ነው ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ድርጅት በበኩሉ ምንም ዓይነት የነዳጅ ዕጥረት የለም ባይ ነው ። …

የነዳጅ እጥረት በአዲስ አበባ Read more »

በኢትዮጽያን የሚያዉቁ በኢትዮጽያ የኖሩ የዉጭ አገር ዜጎች በተለይ ኢትዮጽያን ጥለዉ ሲወጡ ስለ አገሪቷ ዉበት በአገሪቷ ስላለዉ ብሄር ብሄረሰብ ስለ ህዝቧ ፍቅር፣ ስለወንዝ ተራራ እና ሜዳዉ በአጠቃላይ በአኢትዮጽያ ስላገኙት ተመክሮአቸዉ ተናግረዉ አይጨርሱም።

ፕሬዚደንት ሆስኒ ሙባራክ እንዲወርዱ በመጠየቅ በተለያዩ የግብጽ ከተሞች የተጀመረው የህዝብ ተቃውሞ ዛሬም እንደቀጠለ ነው። አዲሱ የሀገሪቱ ምክትል ፕሬዚደንት ኦማር ሱሌይማን ከተቃዋሚ ቡድኖች ጋ ለመወያየት ትናንት ሀሳብ አቅርበዋል።