4 ሺህ ተጨማሪ ሃይል በሶማሊያ ሊሰማራ ነው

የመንግስታቱ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት በሶማሊያ የተሰማራው የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ሰራዊት ቁጥሩ በአራት ሺህ እንዲጨምር ወሰነ። የሰራዊቱ የቆይታ ጊዜ በ8 ወራት እንዲራዘምም ምክር ቤቱ ወስኗል።