በሲናይ በረኃ የታገቱት ኤርትራውያን ስደተኞች ጉዳይ
ሁለት መቶ ሀምሳ የሚሆኑ የኤርትራ ስደተኞች ሲናይ በረሃ ውስጥ ሳይታገቱ እንዳልቀረ ተሰማ።
ሁለት መቶ ሀምሳ የሚሆኑ የኤርትራ ስደተኞች ሲናይ በረሃ ውስጥ ሳይታገቱ እንዳልቀረ ተሰማ።
በደንማርክ መዲና በኮፐንሄገን፣ ከኅዳር 28 እስከ ታኅሳስ 9 ቀን 2002 ዓ ም፣ በዓለም ውስጥ በዓይነቱ የመጀመሪያ የተባለው ዐቢይ የዓለም የአየር ንብረት ጥበቃ ነክ የመሪዎች ጉባዔ ከተካሄደ ወዲህ ፣ በቀጣይነት ካንኩን ሜክሲኮ ላይ ፣ 194 መንግሥታት የተወከሉበት ተመሳሳይ ጉባዔ ከተጀመረ እንሆ …
የኤኮኖሚ ትብብር እና ልማት ድርጅት፡ በምህጻሩ ኦ ኢ ሲ ዲ በስድሳ አምስት ሀገሮች የሚገኙ ወደ አምስት መቶ ሺህ የሚጠጉ ተማሪዎች ከተሳተፉበት በምህጻሩ ፒሳ የተባለው የተማሪዎች ዕውቀት መለኪያ ፈተና በኋላ ትናንት በበርሊን ይፋ ባወጣው የ 2009ዓም ዘገባ መሰረት፡ የጀርመን የትምህርት ደረጃ …
ከሳምንታት በፊት የዩናይትድ ስቴትስንና የተጓዳኞቿን ዲፕሎማሲያዊ ምስጢር ይፋ ማዉጣት መጀመሩ ትኩረት የሳበዉ ዊኪሊክስ የተሰኘዉ ድረ ገጽ ባለቤት ትናንት እጁን ለብሪታንያ ፖሊስ ሰጥቷል።
ለሶስት ቀናት አዲስ አበባ ላይ የተካሄደዉ የአፍሪቃ ኅብረት የመከላከያ ሚኒስትሮችና የጦር ኃይል ኤታማዦር ሹሞች ጉባኤ ተጠናቀቀ።
በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ቁጥር እንደአስፈላጊነቱ እንዲጨምር መደረጉ ትክክለኛና ማለፊያ ተግባር መሆኑን ማንም አይስተውም።
የኬንያ ፖሊስ ስደተኞቹን ለመያዝ በባልደረቦቹ ላይ የደረሰዉን አደጋ ሰበብ አደረገ እንጂ ገንዘብ ለመቀበል በየአመቱ የሚያደውገዉ ዘመቻ አካል ነዉ።
በምዕራብ አፍሪቃ በምትገኘው ሀገር በኮት ዲቧር ኅዳር 19 ቀን 2003 ዓ ም፣ ዳግመኛ የማጣሪያ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ተካሂዶ አላሳነ ዑታራ ማሸነፋቸውን የምርጫ ኮሚሽን ቢያረጋግጥም፣
የአዉሮጳ አሜሪካኖችን አንድነት ሸርሽሮ-ልዩነታቸዉን፣ የአረብ-እስራኤሎችን የጠላትነት መጋረጃ በርቅሶ ተቀራራቢነታቸዉን አፈጋዉ።ዊኪ ሊክስና-ዘገባዉ።
የአፍሪቃ ህብረት የመከላከያ ሚንስትሮች ስብሰባ በአዲስ አበባ ተጀምሮዋል።
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባዔ ረዘም ያሉ ጊዜያት ካለፉ ወዲህ መደበኛ መግለጫውን አውጥቷል። ጌታቸው ተድላ እንደዘገበልን ፣ ኢ ሰ መ ጉ፣ ዘገባውን ያጠናቀረውም
እ ጎ አ በ 2018 ሩሲያ፣ በ 2022 ዓ ም ደግሞ ቓታር፣ የዓለም የእግር ኳስ ዋንጫ ውድድር እንዲያዘጋጁ ተወሰነ።
ጀርመን የዉጭ ዜጎች ከአገሪቱ ህዝብና ባህል ጋ ተዋህደዉ እንዲኖሩ መርሃ ግብር ዘርግታ እየሰራች ነዉ።
የኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት ያላቸዉን ንብረትና ሃብት ማስመዝገብ ጀምረዋል።
መንዙማ አንዱ የታሪካችን የባህላችን መገለጫ ነዉ። የባህል መድረካችን የያዘዉ ርዕሱ ነዉ። መንዙማ ምንድን ነዉ። ታሪካዊ መነሻዉስ? በእዚሁ ርዕስ ስር ከአስር ቀናት በፊት በአዲስ አበባ ዪንቨርስቲ በኢትዮጽያ ጥናት እና ምርምር ተቋም በርካታ ምሁራኖች
በየዓመቱ ህዳር ሀያ ሁለት ቀን የሚውለው የዓለም የኤድስ ቀን ሁሉን አቀፍ የፀረ ኤች አይ ቪ አገልግሎቶች አቅርቦትና ሰብዓዊ መብት በሚል መሪ ቃል በመላው ዓለም በተለያዩ ዝግጅቶች እየታሰበ ነው ።
የአሜሪካን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት የሚስጥራዊ መረጃዎች ልውውጥ ላይ ከፍተኛ ገደብ አደረገ ።
ዓለም ዓቀፉ የእግር ኳስ ማህበር ፊፋ አንዳንድ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላቱ በጉቦ ቅሌት ስማቸው አደባባይ ወጥቶ መነጋገሪያ ሆነዋል።
ፕላኔታችን ከተቀጣባት የጥፋት አደጋ እንድታመልጥ፣ አየሩን የብሱንና ባህሩን ከብክለት ለመከላከልም ሆነ ለማጽዳት፤ በአጭሩ የተፈጥሮ አካባቢን ለመጠበቅ፣ ይበጃሉ በሚባሉ ጉዳዮች ላይ ፣ ዓለም አቀፍ ጠበብትና ውሳኔ ሰጪ መሪዎች በየጊዜው በጋራ ከመምከር አለመቦዘናቸውን እንሰማለን።
አፍሪቃና የአውሮፓ ሕብረት ሕዝባዊት ቻይናን የመሳሰሉት በፍጥነት በመራመድ ላይ ያሉ ሃገራት የአፍሪቃን ክፍለ-ዓለም የተፈጥሮ ጸጋ መሻማት በያዙበት በአሁኑ ወቅት መሰናክል ገጥሞት የቆየ የኤኮኖሚ ትስስራቸውን ለማጠናከር ሰሞኑን ትሪፖሊ ላይ ባካሄዱት የመሪዎች ጉባዔ ተስማምተዋል።
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ፣ ዜጎች፣ በበጎ ፈቃድ ለህሙማን ፣
ዓለም ዓቀፍ የኤድስ ቀን ነገ ሲታሰብ፤ ዓለማችን ዛሬስ ከዚህ ወረርሽኝ ተላቀቀች የሚል ዜናን አልያዘም።
ከትናንት በስትያ በግብፅ የተካሄደው የምክር ቤት ምርጫ ማጭበርበር እንደተከሰተበት ተቃዋሚዎች ገለፁ። ሁኔታዎች እንደሚያመለክቱት ከሆነ በምክር ቤቱ ምርጫ የፕሬዚዳንት ሆስኒ ሞባረክ ፓርቲ ከፍተኛ መቀመጫ እንደሚያገኝ ተገምቷል። ተቃዋሚዎች ውጤቱን እንደማይቀበሉት እየዛቱ ነው። ማንተጋፍቶት ስለሺ ዝርዝር ዘገባ አጠናቅሯል።
(DW) — ዊኪ ሊክስ የተሰኘው የኢንተርኔት መረብ ሰሞኑን ይፋ ያደረጋቸው ሚስጥር ነክ መረጃዎች ከአሜሪካን እስከ ጀርመን ዓለምን እያነጋገሩ ነው። ዊኪ ሊክስ በአሜሪካን የጦር ሄሊኮፕተር አብራሪዎች ኢራቅ ውስጥ ተፈፀመ ያለውን የሰላማዊ ሰዎች ግድያ የሚያሳየውን ቪዲዮ ጨምሮ እስካሁን በርካታ መረጃዎችን ይፋ አድርጓል። …
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ የኡጋንዳውን ሎርድ ሬዚስታንስ አርሚ የተሰኘውን አማፂ ቡድን ትጥቅ ለማስፈታት አዲስ ስልት ቀይሰው ለምክር ቤት አቅርበዋል።
በ 32 የተለያዩ ቋንቋዎች በዓለም ዙሪያ ፕሮግራሞችን የሚያሠራጨው ዶቸ ቨለ ራዲዮ ጣቢያ፣ ቋሚ ሠራተኞቹ ብቻ ሳይሆኑ፣ በተለያዩ አገሮች የሚገኙ ዘጋቢዎቹም በየጊዜው ሙያዊ ማሠልጠኛ እንዲያገኙ ያደርጋል።
ሰሞኑን ከጀርመን ፓርቲዎች አንደኛው የሆነው አረንጓዴው ፓርቲ ኢትዮዽያን በተመለከተ ጠንከር ያለ ውሳኔ አስተላልፏል። ፓርቲው ይህንን ውሳኔ ያስተላለፈው በጠቅላላው ጉባዔው ላይ ነው።
የታዋቂዉ ጋዜጠኛ እና ደራሲ አበራ ለማ ናጋቲ ካ ያ ጓሼ ኮ ከሚለዉ ለሎሪት ጸጋዮዪ ገብረመድህን ማስታወሻነት ከጻፉት የተወሰደን ግጥም ነዉ በመፕሮግራሙ መጀመርያ የምታደምጡት የጋዜጠኛና የደራሲ አበራ ለማ ሃያ አምስት ምርጥ ስነ-ግጥሞች ስብስብ በዲቪዲ በከለር ድምጽ ቅንብር ለታዳሚዎች እይታና ጆሮ ቀርበዋል።
የጀርመን ኢንዱስትሪዎች የጥሬ ሃብት እጥረት ስለመኖሩ መናገር ከጀመሩ ሰነባብተዋል።
በአዲስ አበባ የአፍሪቃ የዉሃ ሳምንት አህጉራዊ የሚኒስትሮች ስብሰባ እየተካሄደ ነዉ።
የደቡብ ብሔር ብሔሮችና ህዝቦች ክልል መዲና ሀዋሳ የተቆረቆረችበትን 50ኛ ዓመት ከዛሬ ጀምሮ ለሚቀጥሉት አምስት ቀናት በተለያዩ ዝግጅቶች እያከበረች ነው።
የአውሮፓ ሕብረት በአሕጽሮት ኤ.ሢ.ፒ. በመባል ከሚታወቁት ከአፍሪቃ፣ ካራይብና ፓሢፊክ አካባቢ አገሮች ጋር የኤኮኖሚ ሽርክና ውል ለማስፈን በሚያደርገው ግፊት ዕርምጃው ሚዛን የጠበቀ አይደለም ሲሉ የሚወቅሱት ታዛቢዎች ብዙዎች ናቸው።
ትናንት ለገበያ የቀረበው የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቤኔዲክት 16 ተኛ አዲስ መፀሀፍ በስፋት ማነጋገሩን ቀጥሏል ።
ሰሜን ኮርያ ከደቡብ ኮርያ ወደምታወዛግባት የደሴት ግዛት ሮኬቶችን መተኮሷ ከሴዉል ብቻ ሳይሆን፤ የተመድን ጨምሮ ከተለያዩ ወገኖች ትችትና ዉግዘትን አስከትሎባታል።
የኢትዮዽያው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ግብጽ በአባይ ጉዳይ ጦርነት ብትገጥም ኢትዮዽያን አታሸንፍም ሲሉ ትላንት አስታወቁ።ግብጽ የጠቅላይ ሚኒስትር መለስን መግለጪያ አስገራሚ ብላዋለች።
ፍጥረተ ዓለም፣(ዩኒቨርስ) የተዘረጋው፣ ፀሐይና ሌሎች ከዋክብትና ፕላኔቶች የተፈጠሩት፣ በፍንዳታም ይሁን በሌላ፣ በተፈጥሮ የቅመማ ውሑደነት ወይም ቅልቅል መሆኑ የሚታበል አይደለም።
የተመድ ዓለም ዓቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤ የፊታችን ሰኞ በሜክሲኮ ካንኩን ከተማ ይከፈታል።
« እነዚህ ደንቦች በርግጥ ለመረዳት ቀላል ናቸው ። እዚህ መኖር የሚፈልግ ጀርመንኛ መማር አለበት ። እዚህ የሚኖር ሰው ህጎቻችንንና እሴቶቻችንን ማክበር ይገባዋል ። ይህን የሚያደርግ ማንኛውም ሰው በኛ ዘንድ ተቀባይነት አለው ። ይህን ማድረግ የማይፈልግ ማዕቀብ ይጠብቀዋል ። ያን ያህል …
CPJ እንዳስታወቀዉ ጋዜጠኛ ዳዊት ለዘንድሮዉ የአለም የፕረስ ነፃነት ሽልማት የበቃዉ የሚደርስበትን ፖለቲካዊ ጫናና ወከባ ተቋቋሞ ፖለቲካዊ መረጃን ለሕዝብ በማቅረቡ ነዉ
በባህር ላይ ውንብድና የተጠረጠሩ 10 ሱማሌያውያን ዛሬ በሰሜናዊቱ የጀርመን ከተማ ሀንቡርግ ለፍርድ ይቀርባሉ።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያን የስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎች ከብዙ ክርክርና ድርድር በኋላ ያነሷቸው ጥያቄዎች ባለመመለሳቸው ትምህርት አቁመው መሰንበታቸው ተጠቆመ። ሰኞ ህዳር 13ቀን 2003ዓ.ም. ደግሞ ተማሪዎቹ ግቢውን ለቀው እንዲወጡ መደረጋቸውም ተገልጧል። ተማሪዎቹ ችግራቸውን ለኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን እንዲሁም ለኢትዮጵያ ወጣቶችና ሴቶች ጉዳይ …
…በአዲሱ የኔቶ-ሥልት መሠረት ሚሳዬል መከላከያ ጦር መሳሪያ ለመገንባት ግን አለም አቀፍ የሰላም ንቅናቄ ባልደረባ ራይነር ብራዉን እንዳሉት የኔቶ አባላት በፕሬዝዳንት ሮናልድ ሬጋን ዘመን ለጦር መሳሪያ ከወጣዉ ከፍተኛ ገንዘብ ይበልጥ ቢሊዮነ-ቢሊዮናትን ለመከስከስ ተስማሙ።
በኮሎኝ ከተማ የኢትዮጲያውያን ተማሪዎችና ምሩቃን ማህበር በጀርመንኛ ምህፃሩ(DÄSAV)ከተመሰረተ አንድ አመት ሆኖታል። እራሱን ለህዝብ ሲያስተዋውቅ ግን ያለፈው አርብና ቅዳሜ የመጀመሪያው ነው።
ናምቢያ የተያዘው ቦምብ መሳይ ጥቅል ቦርሳ ለሙከራ የተዘጋጀ እንደሆነ ተገለጸ። ጀርመን እስከመጪው ታህሳስ መጨራሻ የሚዘልቅ የደህንነት ቅጥጥር እንደምታደርግ አስታወቀች።
ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ኪር ስታርማን ትናንት እንዳሉት ቢ በሚል ፊደል የሚጠራዉ የብሪታንያ የሐገር ዉስጥ የስለላ ድርጅት M15 ባልደረባ በሕግ የማይጠየቀዉ የተከሰሰበትን ወንጀል የሚያረጋግጥ መረጃ ሥላልተገኘበት ነዉ።
የኢትዪጽያ የወራት ስያሜና ፍችዉ በሚል ርእስ ባለፈዉ ሳምት የጀመርነዉ ጥንቅራችን
የሐገር ዉስጥ ጉዳይ ሚንስትሩ ከሁለት ሳምንት በፊት አጠቃላይ የአሸባሪዎች ጥቃት ሥጋት መኖሩን አስታዉቀዉ ሕዝቡ አጠራጣሪ እንቅስቃሴዎችንና ሰዎችን ለፖሊስ እንዲጠቁም መክረዉ ነበር።ያሁኑ ማስጠንቀቂያቸዉ ግን ካለፈዉ ጠንካራና በተጨባጭ መረጃ ላይ የተመሠረተ ነዉ።
በእስራኤል እና በፍልስጤማውያን መካከል ለጊዜው የተቋረጠው ውይይት እንደገና እንዲጀምር እስራኤል በምዕራባዊው ዳርቻ የጀመረችውን የሰፈራ ግንባታ ለሶስት ወራት እንድታቆም ዩኤስ አሜሪካ ጠይቃለች።
አንድ ሺህ ያህል ኢትዮዽያውያን ስደተኞች በየመንና ሳዑዲ አረቢያ ድንበር አከባቢ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙ ዓለም ዓቀፉ የስደተኞች ጉዳይ ድርጅት አይ ኦ ኤም ገለጸ።
የአውሮጳ እና የአፍሪቃ ሀገሮች ከሶስት ዓመታት በፊት በሊዝበን፡ ፖርቱጋል በደረሱት ስምምነት መሰረት፡ በጠበቀ የጋራ ስልት በመጠቀም ግንኙነታቸውን ለማጠናከር እና ለማስተባበር ወስነዋል።