አኀዙን በማየትም ሆነ በመስማት ሲያሰላስሉት እጅግ የሚያስደነግጥ ነው ፤ ንፁህ የሚጣጣ ውሃ የማያገኘው የዓለም ህዝብ ቁጥር ከ አንድ ቢሊዮን በላይ ነው። በመሆኑም በቀላሉ ሊወገዱ በሚችሉ ተውሳኮች ሳቢያ ብዙ ህዝብ በአጭር ይቀጫል።

የብሪታኒያ መንግስት ለቀድሞ የዋንታሞ ዕስረኞች ካሳ ለመክፈል መወሰኑን ትናንት አስታውቋል ። መንግስት እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰውም በእስር ላይ ሳሉ በደል ደርሶብናል ሲሊ ከከሰሱ የቀድሞ እስረኞች ጠበቆች ጋር ለሳምንታት ከተካሄደ ድርድር በኃላ ነው ።

ቻይና በአፍሪቃ ክፍለ-ዓለም የኤኮኖሚ ተጽዕኖዋን ለማስፋፋት በምታደርገው ጥረት በተለይም በማዕድን ሃብት የታደለችውንና በአካባቢዋ በፊናንስ አገልግሎት ረገድ ቀደምት የሆነችውን ደቡብ አፍሪቃን ዋና ማተኮሪያዋ ታደርጋለች።

እዚህ ጀርመን የሚኖሩ የውጭ ዜጎችን ከህብረተሰቡ ጋር የማዋሃድ ዓላማ ይዞ የተጀመረው የውህደት መርሀ ግብር ከተጀመረ 5 ዓመታትን አስቆጥሯል ። የቋንቋ የታሪክና የባህል ትምህርት ን ያካተተውን ይህን መርሀ ግብርም በመጪዎቹ 5 ዓመታት አስፋፋቶ ለመቀጠል ታስቧል ።

ለሽብርተኝነት ጥቃት በመጋለጥ ሶማልያ በዓለም ውስጥ ቀዳሚውን ቦታ መያዟ ተገለጠ።እ ጎ አ ከ 1991 ዓ ም አንስቶ ከሞላ ጎደል ለ 20 ዓመታት ያህል ሥርዓት አልበኛነት ነግሦባት በቆየችው፣

ማንዴላ የፈጠሯትን ደቡብ አፍሪቃን መሰል-በርማ ወይም ምያንማርን ለመፍጠር ከማንዴላ ድንቅ ተጋድሎ-አላማ የወረሱት ትግል-ተጋድሎ ፥ከሕዝባቸዉ እና ከምዕራቦች የሚጎርፈዉ ድጋፍ ብቻዉን በቂ አይሆንም።ምያንማር ማንዴላን ብቻ ሳይሆን በወዲያኛዉ ጠርዝ-ፍሬድሪክ ዴ ክላርክንም ትሻለች።

የዩናይትድ እስቴትስ ባለሥልጣናት፣ የናዚዎች ሰለባዎች ለሆኑ ሰዎች ካሣ ይሆን ዘንድ የተከፈገንዘብን አጭበርብረዋል ሲሉ 17 ሰዎችን መክሰሳቸውን የአሜሪካ የወንጀል ተከታታይ መሥሪያ ቤት (FBI) ከትናንት በስቲያ አስታውቋል።

የጀርመን የልማት እርዳታ ጉዳይ ድርጅቶች፣ የነጻ ዴሞክራቱ ፓርቲ (FDP) ባልደረባ የሆኑት ዲርክ ኒበል፣ የኤኮኖሚና የልማት ተራድኦ ሚንስትር ከሆኑ ወዲህ፣ የልማት እርዳታ ፖለቲካ አዲስ አቅጣጫ ይዟል በማለት ሲወቅሱ ይሰማል።

አሜሪካ ከትላንት በስቲያ ይዛ ብቅ ያለችው የመፍትሄ ሀሳብ ዋንኛዋን አጨቃጫቂ ቦታ የሚመለከት ነው–አቢዬን። በደቡብ ሱዳን ጥር 9/2010 ህዝበ ውሳኔ ይካሄዳል ተብሎ በመጠበቅ ላይ ቢሆንም በነዳጅ ዘይት በከበረችው አውራጃ አቢዬ ፤ ምርጫው የጊዜ ሰሌዳውን ተከትሎ የሚከናወን አይመስልም።

ኮምፕዩተርና የሞባይል ስልኮችን የመሳሰሉ የመረጃ ቴክኖሎጂ ውጤቶች ለአፍሪቃ በርካታ ጥቅሞችን ያስገኛሉ ። ይሁንና የተበላሹ የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች ወደ አፍሪቃ ሲጣሉ የጤናና የአካባቢ ችግሮችን ማስከተላቸው አይቀርም ።

በታሽጉ ፓኬቶች ውስጥ ተደብቀው የተጓጓዙ ቦንቦች ጉዳት ሳያደርሱ በፊት ከተደረሰባቸው ወዲህ በአውሮፓ ስጋቱ እያየለ መጥቷል። ሰኞ ጥቅምት 29 ቀን 2003 ዓ.ም. ብራስልስ ላይ የአውሮፓ የሀገር ውስጥ ሚንስትሮች ስጋቱን ተከትሎ ተወያይተዋል።

የኢትዮጽያ በርካታ ባህላዊ እሴቶች የሚገኝበት አንዱ የሲዳማ ክልል በደቡብ ክልል ከሚገኘኑት ከአስራ ሶስት ዞኖች አንዱ ነዉ። በለቱ ዝግጅታችን ስለ ሲዳማ ክልል በባህላዊ ሙዚቃዉ እና ጭፈራ የሚያጫዉቱን የባህል ኤክስፐርት የለቱ እንግዳችን ናቸዉ ሌላዉ ፎክሎር ማለት ምን ማለት ነዉ?

ባንድ ኤይድ የተባለው የዕርዳታ ድርጅት ለ 1977 ቱ የኢትዮጵያ ረሀብ መርጃ ያሰባሰበው በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ በህዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ ለጦር መሣሪያ መግዣ ውሏል ሲል የብሪታኒያ ዜና መሰራጫ ኮርፖሬሽን ቢቢሲ ባለፈው ዓመት ላሰራጨው ዘገባ ዛሬ ይቅርታ ጠየቀ ።

ለብዙ ዘመናት ፣ በድንጋይ ከሰል የማዕድን ቁፋሮና አቅርቦት የታወቀው በሰሜን ምዕራብ ጀርመን የሚገኘው ሩር በመባል የታወቀው አውራጃ፣ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በባህል፣ በሳይንስና ሥነ ቴክኒክ አዲስ ፈር የመቅደድ ዝንባሌም ሆነ እንቅሥቃሴ እየታየበት ነው።

(DW) — እንዲሕ መሰሉ-ጅምር ደፍርሶ-ሲጦዝ-ሲረግብ አምስት ወራት አስቆጥሮ-የሆነዉ ሆነ። ግጭት፥ ግድያ፥ እስራት ፍርሐት – እና ፅልመት። ኢትዮጵያ የቀይ-ነጭ ሽብር እልቂት-ፍጅትን ተገላገለች ከተባለ ወዲሕ የኢትዮጵያ ከተሞች በጣሙን የርዕሠ-ከተማይቱ አደባባይ አዉራ መንገዶች በሰዉ ደም፥ አካል፥ በሐብት ንብረት ስብርባሪ የጨቀዩበት-ሳምንት አምስተኛ አመት ዛሬ …

የ1997 የኢትዮጵያ ምርጫ ዉዝግብ ያስከተለዉ ግጭት 5ኛ ዓመት Read more »

የሲኖዶስ አባላት፣ በቦሌ ደብረ-ሳሌም መድኃኔ-ዓለም የቆመው የአባ ፓውሎስ ሀውልትም ሆነ በየአድባራቱ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተሠቀሉ ፎቶግራፎች ተነስተው በመዘክር እንዲቀመጡ ውሳኔ አስተላልፏል።

በሰሜናዊ ጀርመን የወደብ ከተማ በሆነዉ በሃንቡርግ ከተማ የአዉሮጻ አገራትን ያሳተፈ የዳንስ ዉድድር መካሄዱ ሰሞኑን የጀርመን የባህል ድረ-ገጾች ካነስዋቸዉ ርዕሶች አንዱ ነበር። ይህ በአይነቱ ምናልባትም የመጀመርያ የተባለለት የዳንስ ዉድድር ከአለም አስቀያሚ ዳንስ በመደነስ አንደኛ የተባለን በማወዳደር ነዉ ሽልማትን ያበረከተዉ።

በአውሮፓ፣ እ ጎ አ በ 1740 እና 1760 ዓ ም መካከል ፣ 200 ሚሊዮን ያህል ከብቶች በደስታ በሽታ ካለቁ በኋላ፤ በፈረንሳይ አገር በ Lyon ከተማ በዓለም ውስጥ የመጀመሪያው የከብቶች ሀኪሞች ማሠልጠኛ ጣቢያ መቋቋሙ ይነገራል።