ሳምንት ሊደፍን አንድ ቀን የቀረው የግብፅ ህዝባዊ አመፅ ዛሬም እንደቀጠለ ነው ። መንግስት ህዝባዊ ተቃውሞውን ለማገድ የሰዓት እላፊ ቢያውጅም ያካበረው አልተገኘም ። ይልቁንም አመጹ ተባብሶ ወደ አጠቃላይ የስራ ማቆም አድማ መሸጋገር ይዟል ።

በዓለም ዙሪያ የሚገኙ የአንደኛና የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ተማሪዎች፣ ከዚህ ቀደም ታይቶ ባልታወቀ ሁኔታ በሥነ ቅመማ አንዳንድ ሙከራዎችን ያከናወኑ ዘንድ በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት የሳይንስና ባህል ድርጅት ባልደረቦች በሆኑ አዘጋጂዎች ተጠይቀዋል።

የደቡብ ሱዳን ህዝበ-ውሳኔ ታዛቢዎች ምሥክርነት፣ የደምፅ አሰጣጡ ሂደትም ሰላማዊና ተዓማኒነት የተንፀባረቀበት ነበረ ነው ያሉት። የህዝበ ውሳኔው አጠቃላይ ውጤት የካቲት 8 ቀን 2003 ይነገራል ተብሎ ይጠበቃል።

የጀርመን የልማትና ትብብር ሚኒስትር ዴሪክ ኒብል ዛሬ የአራት ቀናት ጉብኝት በኢትዮዽያ ጀምሯዋል። ሚኒስትሩ የኢትዮዽያን የሰባዓዊ መብት ሁኔታ ትኩረት እንዲያደርጉ ተጠይቋል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ግጭት ተቀስቅሶ አምስት ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች መቁሰላቸው ተገለፀ። የግጭቱ መንስኤ በኦሮሚያና በደቡብ ክልል ነዋሪዎች ዘንድ የይገባኛል አተካሮ ያስነሳችው ኤዶ የተባለችው ቀበሌ መሆኗም ተነግሯል።

የዛሬ አስራ-ስምንት አመት ግድም ካስመራ-ተመሳሳይ ቃል ተስምቶ ነበር።በሁለት ሺሕ-ሁለት ከዲሊ-ምሥራቅ ቲሞር፥ ክዚያ በፊትና በመሐሉ ከብዙ የቀድሞ የሶቬት ሕብረት ሪፐብሎክ ርዕሠ-ከተሞች ብዙ ተስምቶ ነበር።ዛሬ ጁባ ነዉ-ተረኛዉ።ነገስ?

የፊታችን እሁድ ፣ የደቡብ ሱዳን ህዝብ ፤ የአገሪቱ አንድነት እንደተጠበቀ በካርቱም አገዛዝ ሥር ለመቆየት ወይም ተገንጥሎ የራሱን መንግሥት ለማቋቋም ፤–ከሁለት አንዱን ለመወሰን አደባባይ ወጥቶ ድምፅ ይሰጣል። አሁን ጁባ ውስጥ የምትገኘው የዶቸ ቨለ ባልደረባ ዚሞነ ሽሊንድቫይን ፣ ብዙኀኑ ነጻነትን እንደሚመርጡ ጥርጥር …

ከሰሜን ወደ ደቡብ የተመለሱት ሱዳናውያንና ህዝበ ውሳኔው Read more »

ዓመት አልፎ ዓመት በተተካ ቁጥር ያለፈውን መለስ ብሎ ማጤኑና በወደፊቱ ላይም ማተኮሩ የተለመደ ነው። የዓለም ኤኮኖሚ ባለፈው 2010 ዓ.ም. ከዓለምአቀፉ የፊናንስ ቀውስ ማገገሙን ቀጥሎ ቢታይም ከፈተናው ግን ጨርሶ አልተላቀቀም።