በኢትዮጵያ፥ በኦሮሞ ተቃዋሚዎችና በመንግሥቱ የፀጥታ ኃይሎች መካከል ለሁለት ወራት ግድም ግጭቶች ከተካሄዱ በኋላ፥ ባለሥልጣናቱ የአዲስ አበባን ግዛት ለማስፋት የኦሮሞ ገበሬዎችን ያፈናቅላል የተባለውን ማስተር ፕላን መሠረዛቸውን አስታውቀዋል።

ታዛቢዎች ግን፥ የመንግሥቱ ባለሥልጣናት የማስተር ፕላኑን ለመሰረዝ በወሰዱት እርምጃ ላይ ጥርጣሬ አላቸው።

እርምጃው በእርግጥ የፖሊሲ ለውጥ መደረጉን ያመለክታል? ወይስ ለቀረቡበት ተቃውሞዎች ማስታገሻ  ነው? ሲሉ ይጠይቃሉ።

ባልደረባችን ሳሌም ሰለሞን ያጠናቀረችው ዘገባ አለ። ሰሎሞን ክፍሌ አቅርቦታል።

ከዚህ በታች ካለው የድምጽ ፋይሉ ያድምጡ።

 

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ቡድን ከቻን አፍሪካ ዋንጫ ውድድር ተሰናበተ! ዘገባ፡- በናታ በሩዋንዳ አስተናጋጅነት ሲካሄድ በነበረው ፕሮፌሽናል ተጫዋቾችን በማያካትተው የቻን አፍሪካ ዋንጫ ዋሊያዎቹ ከምድባቸው ማለፍ ሳይችሉ ቀርተዋል። ጠባብ የማለፍ እድል ይዘው ወደ ሶስተኛው የምድብ ጫወታ ቢያቀኑም ከምድቡ ደካማ በሆነችው አንጎላ 2-1 ተረተዋል። ወደ ጫወታው ስናመራ በማግባት ቅድሚያውን የወሰዱት አንጎላዎች ሲሆኑ በ54 ኛው ደቂቃ ላይ የመሃል ሜድ … Continue reading “የኢትዮጵያ እግር ኳስ ቡድን ከቻን አፍሪካ ዋንጫ ውድድር ተሰናበተ!”

በገድለ ወለተ ጴጥሮስ ላይ እንዲህ የሚል ታሪክ አለ፡፡ እምነ ወለተ ጴጥሮስ ወደ ዋልድባ ገዳም በገባች ጊዜ ለአንዲት እናት ረድእ ሆነች፡፡ እኒህ እናት ፈጽሞ ጠባይ የሚባል ያልፈጠረባቸው ነበሩ፡፡ አሁን የተናገሩትን አሁን ይሽሩታል፣ በሆነው ባልሆነው ይቆጣሉ፤ ከእርጅናቸው ብዛት የተነሣ ይነጫነጫሉ፤ ትእዛዛቸው ሁሉ ውኃ ቀጠነ ነው፡፡ በዚህ ዐመላቸው የተነሣ ማንም ከእርሳቸው ጋር ለመኖር ፈቃደኛ አልነበረም፡፡ ከእርሳቸው ጋር ለመኖር ፈቃደኛ ሆና ለረዥም ጊዜ ያገለገለቻቸው ወለተ ጴጥሮስ ነበረች፡፡
አንድ ቀን መነከሳዪያቱ ተሰባስበው ‹እንዴት ከእኒህ እማሆይ ጋር ለዚህን ያህል ዘመን አብረሽ ለመኖር ቻልሽ? እንዴትስ ታገሥሻቸው? እንዴትስ መሮሽ ጥለሽ አልወጣሽም? ሲሉ ጠየቋት፡፡ ወለተ ጴጥሮስም ‹ንብ ታውቃላችሁ? እኒህ እናት ንብ ናቸው፡፡ ከእርሳቸው የሚገኝ ብዙ ዕውቀት፣ ብዙ ጥበብ፣ ብዙ ልምድ፣ ብዙ ታሪክ፣ ብዙም ጸጋ አለ፡፡ ነገር ግን እናንተ መናደፋቸውን ብቻ ነው የምታዩት፤ ስለዚህም ማሩን ከእርሳቸው ልትቆርጡ አልቻላችሁም፡፡ ንብ ትናደፋለች፣ ነገር ግን ማር የሚገኘው ከምትናደፈው ንብ ነው፡፡ የማትናደፈው ዝንብ ቆሻሻ እንጂ ማር የላትም፡፡ እኔ ግን ከንብ ጋር እንዴት እንደሚኖር ዐውቃለሁ፤ ከንብ ጋር እየኖርኩም ማሩን እቆርጣለሁ› አለቻቸው ይባላል፡፡

ትዳር ማለትም እንዲሁ ነው፡፡
‹አበባው አበበ ንቡም ገባልሽ
እንግዲህ አልማዜ ማር ትበያለሽ›
የሚለው የሠርግ ዘፈን ከዚህ ጋር ይስማማል፡፡ አፍንጅም ከጋብቻ በኋላ ያለውን ጫጉላ ‹ማር ጨረቃ› ሲለው ይኼ ታይቶት እንደሆነ እንጃ፡፡ አንዳንዶቹ የትዳር ንድፊያው ብቻ ስለሚታያቸው ወይ ትዳር ሳይመሠርቱ ወይም የመሠረቱትን ትዳር ሲፈቱ ይታያሉ፡፡ ሌሎቹ ደግሞ የትዳር በጎነቱን ብቻ ስለሚያውቁት እስኪገቡበት ሲጓጉ፣ ከገቡበት በኋላ ደግሞ
ስሳል እንዳልኖርኩኝ አስንቺን እስካገኝ
ካገኘሁሽ ወዲያ እላለሁ አውጣኝ
እያሉ ያንጎራጉራሉ፡፡
ምናልባትም ደግሞ በሠርግ ላይ የሚዘፈነው
ማን ፈርሚ አለሽ፣ ማን ፈርሚ አለሽ
በተወለወለው በአለንጋው ጣትሽ
የሚለው ዜማ ‹ትንቢት ይቀድሞ ለነገር› ዓይነት ሳይሆን አይቀርም፡፡
ትዳር ግን ሁለቱም ብቻ አይደለም፡፡ ትዳር ከንብ ጋር መኖር ነው፡፡ ንብ ሁለት ጠባይ አላት፡፡ አንዱ ያስደስታል፤ ሌላኛው ያስከፋል፡፡ አንዱ ጤና ይሆናል፣ ሌላኛው ግን ያማል፡፡ አንዱ ይጣፍጣል፤ ሌላው ግን ይመራል፡፡ አንዱን ይቆርጡታል፣ ሌላውን ግን ይከላከሉታል፡፡
ትዳርም እንዲሁ ነው፡፡ ሁለት ጠባይ አለው፡፡ አንደኛው ያስቃል አንዱ ያሰቅቃል፤ አንዱ ያስደስታል፣ ሌላው ያሳዝናል፡፡ አንዱ ግቡ ግቡ ሌላው ውጡ ውጡ ያሰኛል፡፡ አንዱ ይናደፋል፣ አንዱ ይጣፍጣል፤ አንዱ ጤና ሌላው ሕመም ይሰጣል፡፡ አንደኛው ግን ያለ ሌላው አይገኝም፡፡
ይኼን ለመድኃኒት፣ ለብርዝ፣ ለጠጅ፣ የምናደርገውን ማር የምትሰጠው ንብ ናት የምትናደፈው፡፡ ያቺ ስትናደፍ ፊት የምታሳብጠው፣ ውስጥን የምትመርዘው፣ የምትጠዘጥዘው፣ ንብ ናት ማሩን የምትሰጠው፡፡ በትዳርም ውስጥ ሁለቱም አሉ፡፡ ጭቅጭቁ፣ ንዝንዙ፣ ጠቡ፣ ኩርፊያው፣ አንዱ ለሌላው የግድ መታዘዙ፣ አንዱ የሌላው አገልጋይ መሆኑ፣ አንዱ ያለ ሌላው ለመወሰን አለመቻሉ፤ የሌላውን ጠባይ፣ የሌላውን ዐመል የግድ መታገሡ፤ ከሚታገሡት ሰው ጋር አብሮ መኖሩ፤ ይኼ ነው የንቧ ንድፊያ፡፡
ሰው የወለደውን አያገባም፡፡ ያሳደገውን አያገባም፣ የተዛመደውን አያገባም፡፡ የቤቱን ሰው አያገባም፡፡ ሰው ደግሞ በዐመልም፣ በፍላጎትም፣ በአመለካከትም ይበልጥ የሚቀራረበው አብሮት ከኖረና ካደገ ሰው ጋር ነበር፡፡ እምነቱና ባሕሉ ግን ጋብቻን እስከ ሰባት ቤት አርቆ ለባዕድ ይሰጠዋል፡፡ አብረነው ላልኖርነው፣ አብረን ላላደግነው አብረን ላልተወለድነው፣ ላልተዛመድነው ሰው፡፡ ከሌላ ተወልዶ፣ ሃያ ሠላሳ ዓመት ሌላ ቦታ ኖሮ፣ ከሌላ ጋር አድጎ፣ ሌላ ጠባይ ነሥቶ፣ በሌላ መንገድ መጥቶ ያገኘነውን ሰው ነው የምናገባው፡፡ ይኼንን ሰው ወይም ይህችን ሴትዮ በዕውቅ አላሠራናትም፣ አላሠራነውም፡፡ ዐመሉ እንዲህ፣ ሐሳቡ እንዲያ፣ መንገዱ እንዲህ፣ እምነቱ እንዲያ፣ ዕውቀቱ እንዲህ፣ ምግባሩ እንዲያ ብለን ዝርዝር ሰጥተን አላስመረትነውም፡፡ ‹ሬድ ሜድ› ነው ያገኘነው፡፡ ዓይተን እንመርጣለን እንጂ፣ መርጠን አናሠራም፡፡
ንብን እኛ ብናሠራት ኖሮ የርሷን መናደፍ ለዝንብ ሰጥተን የዝንብን ጠባይ ለንብ በመለስንላት ነበር፡፡ ግን ንብን እንዲሁ ሆና አገኘናት፣ አላመድናት፣ ወደ ቀፏችን አስገባናት እንጂ አንድም አልፈጠርናት፣ አንድም አላስፈጠርናት፡፡ ንቧን ማርና ንድፊያ እንደያዘች ነው ያገኘናት፡፡ ሰው በውስጡ ማርና ንድፊያ አለው፡፡ የተገዛ የሱፐር ማርኬት ማር የሚበላ ልጅ ንብ የምትባለውን የሚያውቃት በጣሳው ላይ ባለው ሥዕል ነው፡፡ መልኳን እንጂ ንድፊያዋን አያውቀውም፡፡ እርሱ እድሜ ልን በንብ እየተነደፈ ለጌቶቹ ማር ቆርጦ የሚሰጥ ገባርም ንብ እንደምትናደፍ እንጂ ማር እንደምትሰጥ አያውቅም፡፡ ‹ጌቶች ምን ምን ቢላቸው ነው ይህን የቀፎ እንጀራ የሚያስገፈግፉኝ› አለ የሚባለውም ለዚህ ነው፡፡
አንዳንዶች በሠርግ ዘፈን፣ በተረት፣ በሠርግ ሥነ ሥርዓት፣ በስብከት፣ በድራማና በፊልም ትዳርን ሲያዩ ምናልባት ማሩ ይሆናል የሚታያቸው፡፡ ያገኛቸውም ሰው ሁሉ ‹ምነው አንተ አታገባም እንዴ› ይላቸዋል እንጂ ተገብቶ ምን እንዳለ አይነግራቸውም፡፡ ‹የዛሬ ዓመት፣ የዛሬ ዓመት፣
የእንትናዬ አባት
ሲወለድ ማሞ፣ ሲወለድ ማሞ
እንመጣለን ደግሞ፤
ያሉት ሰዎች ደግመው ላይመጡ ይችላሉ፡፡ አንዳንዶችም ማሞ ሲወለድ እንደማይመጡ እያወቁት የሚዘፍኑት ዘፈን ነው፡፡ ‹የዛሬ ዓመት የእንትናዬ አባት› መሆን ለሁሉ ያልተሰጠ መሆኑን የሚናገርም የለም፡፡ ይኼ ያልተነገራቸው የዋሐንም ናቸው ልጅ የለም ብለው የሚፋቱት፡፡
ሌሎች ደግሞ ትዳር ሲባል የንቧ ንድፊያ ነው ትዝ የሚላቸው፡፡
‹ታሠረች አሉ በትዳር፣
ከንግዲህ ቀረ መሽርቀር› የሚለው ዘፈንም ውስጠ ዘ አለበት፡፡
ትዳር ምን ዕዳ ነው ትዳር ምን ዕዳ ነው
ጉልቻው ስሙኒ ምጣዱ ብር ነው
የሚለው ባሕላዊ ዜማ የምጣዱና የጉልቻው ዋጋ ዛሬ ሰማይ በነካበት ጊዜ ቀርቶ ትናንትም በርካሹ ዘመን ትዳርን ‹ዕዳ› ነው እያለ የንቧን መናደፍ እየነገረን ነው፡፡
ትዳር ግን ሁለቱም ብቻ አይደለም፡፡ ትዳር ከንብ ጋር መኖር ነው፡፡ ለማሩ ስንል ንድፊያውን መታገሥ፡፡ ቆይተህ ደግሞ ንድፊያውን መልመድ፡፡ ገበሬ ቀፎ ሰቅሎ ንብ ሲያንብ ንብ እንደምትናደፍ ሳያውቅ ቀርቶ አይደለም፡፡ የማትናደፍ ንብ ከፈለገ በየደጁ ቆሻሻ ፍለጋ የምትጓዘው ዝንብ ነበረችለት፡፡ ዝንብ ምን ጠባይዋ ሸጋ ቢሆን፤ ጠብ የሚላት ግን ሌላ ነገር ነው፡፡ ይህን ያውቃል ገበሬው፡፡ እያወቀም ንብ ያንባል፡፡ ማነብ ብቻ ሳይሆን ከንብ ጋር እንዴት መኖር እንደሚቻልም ያውቃል፡፡ ንብ ትናደፋለች፤ ግን እንዳትናደፍ ማድረግም ይችላል፡፡ የምትወደውና የማትወደው ሽታ አለ፡፡ ስትቀርብህ ምን ማድረግ እና ምን አለማድረግ እንዳለብህ ገበሬው ያውቃል፡፡ በሀገራችን ንብ አትገደልም፡፡ ነውር ነው፡፡ ብትነድፍም አትገደልም፡፡ የንቧን ማር ለመውሰድም ንቧን ገድሎ፣ አጥፍቶ፣ ጎድቶ ወይም አሰቃይቶ ሳይሆን በጭስ ራሱን እየተከላከለ፣ ፊቱን በጨርቅ ሸፍኖ፣ ወደ ንቧ ቀፎ ገብቶ ነው ማሩን የሚቆርጠው፡፡ ንቧም ሳትጎዳ፣ ማሩም ሳይጠፋ፣ እርሷም ሳትናደፍ፡፡
ትዳርም እንዲህ ነው፡፡ አኗኗሩን ነው ማወቅ፡፤ የንቧን ንድፊያ የመቀነሻውን መንገድ ነው ማወቅ፣ የማሩን አቆራረጥ መንገድ ነው ማወቅ፡፡ ደግሞምኮ አስገራሚው ገበሬው የሚከባከበው ይህቺኑ የምትናደፈውን ንብ መሆኑ ነው፡፡ የምትቀስመው አበባ ትፈልጋለች፣ ንጹሕ አካባቢ ትፈልጋለች፣ ከጉንዳንና ከአውሬ ነጻ የሆነ ቀፎ ትፈልጋለች፡፡ ግን ትናደፋለች፡፡ ደግሞም ማር ትሰጣለች፡፡ ትዳር አስደሳች ነገር ብቻ ሳይሆን አስመራሪ፣ አንገብጋቢ፣ አስጠሊታ፣ ጨጓራ አንዳጅ፣ አንጀት ቆራጭ፣ ልብ አቃጣይም ክፍል አለው፡፡ ይናደፋል፡፡ ግን ደግሞ ክብካቤም ይፈልጋል፡፡ ንጹሕ ልብ፣ ታማኝ ኅሊና፣ ቻይ አንጀት፣ ታጋሽ ሆድ፣ ጠቢብ አእምሮ፣ አሳላፊ ልቡና ይፈልጋል፡፡ ለምን ቢሉ? ማር ይሰጣልና፡፡
አንዳንዶች ቤት ካለችው ወይም ካለው ንብ ይልቅ ውጭ ያቺውን ወይም ያለው ዝንብ ሲያደንቁ ይሰማል፡፡ መቼም ከቀፎ ውጭ ምን እንደሚኖር የታወቀ ነው፡፡ ንብ ትናደፋለች ብሎ ንብ የማያነባ ገበሬ ስንፍናውን እንጂ የንቢቱን ክፋት ማንም አይረዳለትም፡፡ ጥበብ አልባ መሆኑን፣ ትዕግሥት አልባ መሆኑን፣ ተሸናፊነቱን እየተናገረ እንጂ የንቧን ጠባይ እየተናገረ አለመሆኑን ሁሉም ያውቅለታል፡፡ የትዳርን ችግር ብቻ የሚያወራ፣ በትዳር ተመርሮ ከቀፎው ውጭ የሚሄድም ስንፍናውንና ዐቅመ ቢስነቱን እንጂ የቀፎውን ችግር እየተናገረ አይምሰለው፡፡ ቀፈ ውስጥ ማር የምትሠራው ን እንዳለች ሁሉም ያውቃልና፡፡ ሌላው ቀርቶ ውጭ ያለቺው ዝንብም ይኼንን ታውቃለች፡፡   
አንዳንዶች ከንብ ጋር የመኖር ጥበብ ሲያንሳቸው የማትናደፍ ንብ ፍለጋ ይኳትናሉ፡፡ የማትናደፍ ንብ መፈለግ ከመረቁ አወጡልኝ ከሥጋው ጦመኛ ነኝ እንደማለት ነው፡፡ ወይም የማትዞር መሬት እንደመፈለግ፡፡ የመትናደፍ ንብ ከፈለግክ ከዝንብ ጋር ተጋባ፡፡ 
ይህ ጽሑፍ በአዲስ አድማስ ጋዜጣ የወጣ ነው፡፡

ኢሳት (ጥር 11 ፥ 2008) በሆሳዕና ከተማ ከመንጃ ፈቃድ ቅጣት እና አስተዳደር ብልሹነት ጋር በተያያዘ የህዝብ የትራስፖርት ማመላለሻ አገልግሎት ለሁለት ቀን ተቋርጦ መዋሉት ዛሬ ሰኞ ለኢሳት የደረሰው መረጃ አመለከተ። አንድ ሆሳዕና ወደሌላ ወረዳ ወይም ከወደ ዋና ዋና ከተሞች የሚያጓጉዙ የትራንስፖት መገናኛ አገልግሎቶች በመቋረጣቸው ህዝቡ ከፍተኛ የትራንስፖርት ችግር ውስጥ ላይ እንደሆነ አንድ ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ በሆሳዕና …

በባ/ዳር ከተማ በትናንትናው አለት ምሽት ላይ አንድ ጎይቶም ተወልደ የተባለ የወያኔ ደህንነት በባህርዳር ከተማ ወጣቶች ተደብድቦ ቀበሌ 12 ዲሽ ቦይ ውሰጥ ተከቶ በመገኘቱ የተበሳጩት የወያኔ ደህንነቶች ታጣቂወችን እና ፖሊሶችን በማሰማራት እና በመስተባበር ዛሬ ረፋዱ 4 ሰአት ገደማ ላይ ከ300 በላይ በመንገድ ላይ በገሩፕ ሲሄዱ ያገኞቸውን ወጣቶች እየደበደቡ በመኪና እየጫኑ ወደ ተለያ ፖሊስ ጣቢያ በመውሰድ እንዳሰሮቸው […]

ጥር ፲፪ (አሥራ ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- 7ቱ ዋና ዋና የአውሮፓ ህብረት የፖለቲካ ድርጅቶች ኢትዮጵያን በተመለከተ የቀረበውን ውሳኔ ሙሉ በሙሉ አጽድቀዋል። አነስተኛ ቁጥር ያላቸው የቀኝ አክራሪዎች ብቻ ውሳኔውን ተቃውመውታል። ለህጉ መጽደቅ ከፍተኛ ትግል ሲያካሂዱ የሰነበቱት የህብረቱ የፓርላማ አባል ሚስ አና ጎሜዝ በውሳኔው መደሰታቸውን ተናግረዋል። “በጣም ጠቃሚ የሆነ ሰነድ ነው፣ በተለይ ዋና ዋና …

ፖሊስ አምስት ተጠርጣሪዎችን ይዞ ምርመራ እያካሔደ ነው ከደረጃቸው ዝቅ የተደረጉት የሀገረ ስብከቱ ሓላፊ ይገኙበታል አማሳኞች፣ ጠንቋይ አስጠንቋዮችና መናፍቃን ፈተና ኾነዋል (ሰንደቅ፤ ረቡዕ፤ ጥር ፲፩ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም.) በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ በብፁዕ አቡነ ኤፍሬም የደብረ ብርሃን መኖርያ ቤታቸው፣ ታኅሣሥ 26 ቀን 2008 ዓ.ም. ምሽት ቦምብ መፈንዳቱ ተገለጸ፡፡ በመንበረ …

ጥር ፲፪ (አሥራ ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የከተማዋ ምንጮች እንደገለጹት ጥር 11 ፣ 2008 ዓም 11 ሰዓት አካባቢ በጤና ሳይንስ ኮሌጅ ግቢ ውስጥ በተነሳው ግጭት በርካታ ተማሪዎች ተጎድተዋል።ግጭቱ ወደ ከተማው በመስፋፋቱ በርካታ ሰዎች ሲቆስሉ ፣ መኪኖችም ተሰባብረዋል። የግጭቱ መንስኤ በትክክል አልታወቀም። የመከላከያ ሰራዊት አባላት እና የፈደራል አባላት ከተማዋን መቆጣጠራቸውን የገለጹት ነዋሪዎች፣ ግጭቱ …

ኢሳት (ጥር 11 ፥ 2008) ዳግም በኦሮሚያ የተቀሰቀሰው የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ተቃውሞ ረቡዕ በጥምቀት በዓል አከባበር ወቅትም በተለያዩ ቦታዎች ቀጥሎ መዋሉን ከሃገር ቤት የተገኘ መረጃ አመልክቷል። ከቀናት በፊት በምስራቅ ሃረርጌና በምስራቅ ወለጋ አካባቢዎች ሲካሄድ የሰነበተው ተቃውሞ አልባት አለማግኘቱንና የጸጥታ ሃይሎች በስፍራው እርምጃ መውሰድ መቀጠላቸውም ታውቋል። የፌዴራልና የክልል ባለስልጣናት ትምህርት ያቋረጡ ዩኒቨርስቲዎች ትምህራትቸውን እንዲቀጥሉ ጥረታቸውን …

አፈንዲ ሙተቂ

የስራ ግዴታዬ ሆኖ ከህዳር ወር 2007 (November 2014) ጀምሮ በመካከለኛው ዘመን የኢትዮጵያ ታሪክ ዙሪያ የተጻፉ ሰነዶችን እየመረመርኩ ነው፡፡ በዚህም ድሮ የማላውቃቸውን አስደናቂና አስገራሚ ታሪኮች ለማወቅ ችያለሁ፡፡ ለረጅም ጊዜ እንቆቅልሽ ሆነው ሲያስቸግሩኝ ለነበሩት ጉዳዮችም ምላሽ አግኝቻለሁ፡፡ ለብዙ ዓመታት ስፈልጋቸው የነበሩትን ምርጥ መጻሕፍትንም አግኝቼ ይዘታቸውን በቅርበት ለማወቅ ችያለሁ፡፡

 

ታዲያ በዚህ ምርመራዬ ያስተዋልኳቸው ሌሎች ጉዳዮችም አሉ፡፡ ከነርሱም አንዱ አንዳንድ ጮሌዎች ታሪክን በመጻፍ ስም ፖለቲካን የሚያሸከረክሩበት ጥበብ ነው፡፡ ለዚህ ዋቢ ይሆነኝ ዘንድ የአንድ ሀገር ዜጋ የሆኑ ሁለት ምሁራንን ልጥቀስ፡፡

—-

ሞርዴኻይ አቢር (Mordechai Abir) የሚባል ስም ታውቃላችሁ?…. አዎን! ስለ “ዘመነ መሳፍንት” የተጻፉ ጽሑፎችን ያነበበ ሰው “አቢር” የሚለውን ስም በደንብ ያስታውሳል፡፡ እኝህ ሰው የቀድሞው “ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሤ ዩኒቨርሲቲ” (የአሁኑ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ) የታሪክ ፕሮፌሰር ነበሩ፡፡ ደርግ ስልጣን ከተቆጣጠረ በኋላ ደግሞ ወደ እስራኤል በመጓዝ በኢየሩሳሌም በሚገኘው የሂብሩ ዩኒቨርሲቲ መምህርነት አገልግለዋል፡፡ አቢር “The Era of Princes” በሚል ርዕስ የጻፉት መጽሐፍ በምሁራን ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት አለው፡፡ እኔም በአንድ ወቅት (የዛሬ አስር ዓመት ገደማ) መጽሐፉን አንብቤው ነበር፡፡

 አቢር በጣም ዝነኛ የሆነ ሌላ መጽሐፍም አላቸው፡፡ ርዕሱ “Ethiopia and the Red Sea” ይሰኛል፡፡ በየትኛውም ወገን ሆኖ ስለኢትዮጵያ ታሪክ የሚጽፍ ሰው ይህንን መጽሐፍ እየደጋገመ ይጠቅሳል፡፡ ታደሰ ታምራት፣ ሪቻርድ ፓንክረስት፣ ነጋሶ ጊዳዳ፣ መርዕድ ወልደ አረጋይ፣ ሙሐመድ ሐሠን፣ ላጵሶ ድሌቦ፣ ኡልሪች ብራውኬምፐር፣ አባስ ሐጂ ገነሞ፣ አሌሳንድሮ ጎሪ እና ሌሎችም ፕሮፌሰሮች የአቢርን መጽሐፍ እንደ ምንጭ ይጠቀሙበታል፡፡ ሰለሰሜን ኢትዮጵያም ሆነ ስለደቡቡ ክፍል በተጻፈ መጽሐፍ ውስጥ “Abir” የሚለውን ስም በግርጌ ማስታወሻ እና በመጽሐፉ ማጣቀሻ ክፍል ውስጥ ማየት የተለመደ ነው፡፡ ነገር ግን “Ethiopia and the Red Sea”ን ለረጅም ጊዜ አይቼው ስለማላውቅ በምሁራን ዘንድ ተመራጭ የሆነበትን ምክንያት ለመረዳት ስቸገር ቆይቻለሁ፡፡ ዘንድሮ ግን ፈጣሪ ብሎልኝ  አግኝቼዋለሁ፡፡  ብዙ ጊዜ እየመላለስኩ ካየሁት በኋላም መጽሐፉ በምሁራን ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት ያገኘበትን ምክንያት ለመረዳት ችያለሁ!!

አዎን! ፕሮፌሰር አቢር ከልቡ ምሁር ናቸው፡፡ እውነተኛ ምሁር! መጽሐፋቸውን ያጠናቀሩት በእውነተኛ ምሁራዊ መንገድ ነው፡፡ ብዙዎችን እንቅ አድርጎ ሊያሰምጣቸው የሚታገላቸው ኢ-ምሁራዊ ሸፍጥና ውንብድና በመጽሐፋቸው ውስጥ የለም፡፡ አድሎ፣ መረጃ ማምታታት፣ የተወላገደ እይታ፣ ማስመሰል፣ መሸፈጥ ጂንኒ ጀቡቲ በመጽሐፉ ውስጥ አይታዩም፡፡ በመሆኑም “Ethiopia and the Red Sea” በህይወቴ ከገጠሙኝ አጃዒበኛ መጻሕፍት መካከል አንዱ አድርጌ መዝግቤዋለሁ፡፡ እውቀትን መገብየት ለሚሻ ሰው ግሩም መማሪያ ነው፡፡ ለተመራማሪዎችና ለተማሪዎች እጅግ በጣም አስፈላጊ የሆነ ማጣቀሻ ነው፡፡

ፕሮፌሰር አቢር በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ስድስት መጻሕፍትን ጽፈዋል፡፡ ሁሉም መጻሕፍት በምሁራን ዘንድ ከፍተኛ ከበሬታ አላቸው፡፡ ከነርሱ መካከል ከላይ የጠቀስኳቸው ሁለት መጻሕፍት የዓለማችን ቁጥር አንድ ኢንሳይክሎፒዲያ በሆነው “ኢንሳይክሎፒዲያ ብሪታኒካ” ቀዳሚ የማጣቀሻ ምንጮች በመሆን recommend ተደርገዋል፡፡

                       

ፕሮፌሰር አቢር እስራኤላዊ ናቸው፡፡ ታዲያ በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ምርምር ሲያደርጉ የነበሩት እስራኤላዊ እሳቸው ብቻ አልነበሩም፡፡ ሌሎችም በዘርፉ ብዙ ስራዎችን አቅርበዋል፡፡ ከነርሱም አንዱ ሀጋይ ኤልሪክ ነው፡፡ “ሐጋይ ኤርሊክ” የሚለውን ስም ካወቅኩ አስራ አምስት ዓመታት አልፏል፡፡ ነገር ግን ከመጽሐፎቹ ያነበብኩት Ethiopia and the Middle East የሚል ርዕስ ያለውን ብቻ ነው፡፡ ሀጋይ ከመጽሐፎቹ ይልቅ በሴሚናሮችና ዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶች ላይ የሚያቀርባቸውን በርካታ አጫጭር ጽሑፎችን ነው ያነበብኩት፡፡ ከህዳር 2007 ወዲህ ባለው ጊዜ ውስጥ ግን ሶስት ያህል መጽሐፎቹን አይቼለታለሁ፡፡ እናም አጃዒብ አልኩ!!

  ይገርማል!! ፕሮፌሰር ሃጋይ አወዛጋቢ ሰው ሆኖ ብቅ ያለው በቅርብ ዘመናት በሚጽፋቸው ጽሑፎቹ ይመስለኝ ነበር፡፡ ነገር ግን ሰውየው ከመነሻው ጀምሮ የተወላገደ እይታ ያለው መሆኑን ነው ያስተዋልኩት፡፡ ምሁራዊ ውንብድና በመጽሐፎቹ ውስጥ እግሩን አንሰራፍቷል፡፡ ከሀጋይ መጽሐፍ ፖለቲካ እንጂ አንዳች የታሪክ እውቀት አይጨበጥም፡፡ ደግሞም የብዙዎቹ መጻሕፍት ጭብጥ “ኢትዮጵያ ራሷን ካልጠበቀች በሙስሊም አክራሪዎች ልትዋጥ ትችላለች” የሚል ነው፡፡ ባጭሩ “ሃጋይ” የእስራኤሉ ሞሳድ በኛ ላይ የተከለው የማስፈራሪያ ሳይኮሎጂስት እንጂ የታሪክ ምሁር ሆኖ አልተገኘም፡፡

በጣም የሚገርመው ደግሞ ሃጋይ ሌሎች ፀሐፊዎችን የሚፈርጅበት ድፍረቱ ነው፡፡ አንድን ክስተት ከርሱ በተለየ አኳኋን ለጻፉ የታሪክ ምሁራን በቶሎ ስም ያወጣላቸዋል፡፡ ሰውዬው ክርስቲያን ከሆነ “ኮሚኒስታዊ አስተሳሰብ ስላለው ነው” ይለዋል፡፡ ሙስሊም ምሁራንን ደግሞ ሁለት ሰሞችን ይሸልማቸዋል፡፡ ጸሐፊው የመካከለኛው ዘመን ሰው ከሆነ “Fanatic writer” ይለዋል፡፡ ፀሐፊው የዘመናችን ሰው ከሆነ ግን “Radical Islamist writer” ይለዋል፡፡ ከርሱ የሚቃረን ትርክት የጻፉ ሰዎችን እንዲህ ብሎ በሚፈርጅ ሰው የተጻፈ መጽሐፍ የታሪክ ማጣቀሻ የሚሆንበት አግባብ በጭራሽ የለም፡፡

የሀጋይ የላሸቀ ምሁራዊ በዚህ ብቻ የተገታ አይደለም፡፡ የታሪክ መረጃዎችን ለራሱ እንደሚመቸው እየገለባበጠ ይጽፋል፡፡ ለምሳሌ ቅዱስ ቁርኣን የአማርኛ ትርጉም በብዙ ምሁራን ተሳትፎ የተከወነ ሆኖ ሳለ (ዋነኞቹ ተርጓሚዎች ሼኽ ሰይድ ሙሐመድ ሳዲቅ እና ሃጂ ሙሐመድ ሣኒ ሐቢብ ቢሆኑም) እርሱ ግን “ትርጉሙን ያከናወኑት ሃጂ ዩሱፍ ዐብዱራሕማን ነው” ይለናል፡፡ ሀጋይ እንዲህ የሚለው ሃጂ ዩሱፍን ለማድነቅ እንዳልሆነ ልብ በሉ፡፡ ይህንንም ትረካ የፈጠረው እርሱ በአድናቆት አቅሉን የሚስትላቸው ሼኽ ዐብዱላሂ ሙሐመድ (ዐብዱላሂ አል-ሐበሺ) በ1948 ከኢትዮጵያ የተባረሩት ሃጂ ዩሱፍ ዐብዱራሕማን በዶለቱት ሴራ ነው በሚል ለሚዘበዝበው ትረካ እንደማስረጃ ለመጠቀም ፈልጎ ነው፡፡ አንባቢያን “ሃጂ ዩሱፍ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሤን አባብለው ሼኽ ዐብዱላሂ ከሀገር እንዲጠፉ የማድረግ አቅም ነበራቸው እንዴ” ብለው ሲጠይቁ የሃጋይ ኤርሊክ ጽሑፍ “ሰውዬው እንዲያ ማድረግ ይቅርና በቅቤ ምላሳቸው ንጉሡን በማሳመን ቅዱስ ቁርኣን እንዲተረጎም ያደረጉ ሼኽ ነበሩ” የሚል መልስ ይሰጣቸዋል ማለት ነው፡፡ ይህቺ ነች ዘዴ!! ይህቺ ነች ሸፍጥ!!

በሌላ በኩል ሃጋይ ኤርሊክ በቀጥታ ጠብ ጫሪነትን የሚያንጸባርቁ ጽሑፎችንም ይጽፋል፡፡ ለምሳሌ የሃጋይ አንዱ ጽሑፍ “The Grandchildren of Abraha” የሚል ርዕስ አለው፡፡ አብረሃ ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) በተወለዱበት ዘመን የመንን ሲገዛ የነበረው የአክሱም ንጉሥ እንደራሴ ነው፡፡ ታዲያ ሀጋይ በዚህ ጽሑፍ የአሁኖቹን የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ መሪዎች “የአብረሃ የልጅ ልጆች ናቸው” ይላቸውና “እነዚህ ጀግኖች የተስፋፊውን የአክራሪውን የእስልምና ጂሃዲስቶች ድባቅ መምታት ይችላሉ” የሚል እድምታ ያለው ትረካ ይተረትራል፡፡ አብረሃ የጥንቱ የአክሱም ንጉሣዊ ግዛት ተወላጅ እንደነበረ ማንም አይክድም፡፡ ይሁን እንጂ የዛሬዎቹን የኢትዮጵያ ገዥዎች የአብረሃ ዝርያዎች ማለትም ሆነ የጥንቷ አክሱም ሌጋሲ አስቀጣይ አድርጎ ማቅረብ ስህተት ነው፡፡ የጥንቷ አክሱም በማህበራዊ ስብጥሯ ህብረ-ብሄር እንጂ የአንድ ብሄር ሀገር አልነበረችም፡፡ ግዛቷ ደግሞ ከትግራይ ባሻገር ኤርትራን፣ ሰሜን ምስራቃዊ ሱዳንና አብዛኞቹን የሰሜን ኢትዮጵያ ክልሎች ይጠቅላል፡፡  አብረሃ ከነዚህ ሁሉ ግዛቶች በየትኛው እንደተወለደ በትክክል አይታወቅም፡፡ በሁለተኛ ደረጃ የዘመናችን የኢትዮጵያ መሪዎች የጥንቱ አብረሃ ሌጋሲ ወራሾች ናቸው የሚያስብል የታሪክና የአንትሮፖሎጂ ማስረጃ የለም፡፡

  

 የጽሑፉ አደገኛነት ግን ይህ አይደለም፡፡ የሃጋይ ምሁራዊ ሸፍጥ የሚያስከፋው ጥንት የተፈጸመን ታሪክ አሁን ካለው ጂኦ-ፖለቲካዊ ትርምስ ጋር እየቀላቀለ የጠብ ጫሪነት ስሜትን ለማንገሥ በመጣሩ ነው፡፡ የታሪክ ምሁር ዋነኛ ግብ የሰው ልጆች ትናንት የፈጸሟቸው ስህተቶችን እንዳይደግሙ ማስተማር እና ድሮ የነበራቸውን በጎ የአዕምሮና የማቴሪያል እሴቶችን ጠብቀው ወደ ቀጣዩ ትውልድ እንዲያስተላልፉ ማስቻል ነው፡፡ ሀጋይ ግን ታሪክን ሸርና ብጥብጥን ለማውረስ ሲል ብቻ የሚጠቀምበት ነው የሚመስለው፡፡

—-

ከላይ የጠቀስኳቸው ሁለት ምሁራን (ሞርዴኻይ አቢር እና ሀጋይ ኤርሊክ) ይሁዲዎች ናቸው፡፡ ነገር ግን ሁለቱም የተለያየ ምሁራዊ ልቀትና ርትእ ያላቸው ሆነው ተገኝተዋል፡፡ ምሁራን “የአቢርን መጽሐፍ ማንበብ አለብህ” እያሉ ሲናገሩ የነበሩት “በአቢር መጽሐፍ ውስጥ እውቀት አለልህ” ማለታቸው እንደሆነ ገብቶኛል፡፡  ሀጋይ ኤርሊክ ግን በታሪክ ስም ጽዮናዊ ፖለቲካውን የሚያሰራጭ ሸፍጠኛ ነው እንጂ የምሁር “ኳሊቲ” የለውም፡፡

አንድ ነገር ግን አለ፡፡ ይሁዲ በሙሉ መጥፎ ነው የሚሉ ሰዎች አሉ፡፡ ስህተት ነው፡፡ በጣም ስህተት!! ይህ የአዶልፍ ሒትለርና የመሰሎቹ አስተሳሰብ ነው እንጂ የጤናማ ሰው አስተሳሰብ አይደለም፡፡ አይሁድ በሙሉ መጥፎ እንዳልሆነ ለመረዳት የሚሻ ሰው የፕሮፌሰር አቢርን መጽሐፍ ብቻ ማንበብ ይበቃዋል፡፡ የህዝብን አንድነት የሚያናጉትን እንደ ሀጋይ ኤርሊክ ዓይነቶቹን መሰሪ ጸሐፊዎች ግን ጠንቀቅ በሏቸው፡፡ 

—–

First written on August 13/2015
Re-written on January 19/2016

ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም

Bewketu Seyoum and Yared Tibebu በእውቀቱ ሥዩም እና ያሬድ ጥበቡ

ከሁለት ቀኖች በፊት ስለበእውቀቱ ሥዩም አድናቆታቸውን በፌስቡክ ላይ የገለጹ ሁለት ሰዎች ነበሩ፤ ለበእውቀቱ ያላቸውን አድናቆት እኔም እጋራቸዋለሁ፤ ነገር ግን የእነዚህ ሰዎች አድናቆት በእውቀቱ ራሱንና ማንነቱን እንዲከዳ ይቃጣቸዋል። አንዱን አውቀዋለሁ፤ ከፖሊቲካና ከትጥቅ ትግል ወደስደት ”ነጻነት” የተሸጋገረ ያሬድ ጥበቡ የሚል የሚያኮራ ስም ይዞ የስደት መምህር የሆነ ነው፤ ሁለተኛው ሚስተር ቴዲ ገብርኤል ይባላል። እነዚህ ሁለት ስደተኞች በእውቀቱ ሥዩምን በጣም ስለሚወድዱትና ስለሚያከብሩት በአሜሪካ ስደተኛ ሆኖ እንዲቀርላቸው ይፈልጋሉ፤ በዚህ ብቻ ለኢትዮጵያ ያላቸውን ስሜት መገመት በጣም የሚያሳዝን ነው፤ ወደዝርዝር አልገባም።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ግርማ ሠይፉ ማሩ

“የኢትዮጵያ የታሪክ ፈተናዎች እና የሚጋጩ ሕልሞች” ዶ/ር መረራ ጉዲና Dr. Merera Gudinas new bookዶ/ር መረራ ጉዲና “የኢትዮጵያ የታሪክ ፈተናዎች እና የሚጋጩ ሕልሞች” በሚል አዲስ መጽሐፍ አስነብቦናል። በአንድ ጋዜጣ ላይ የዶክተር መረራ ከዩኒቨርሲቲ መሰናበት ያመጣው አንድ በጎ ጎን መሆኑን አንብቤያሁ። እኔም በዚህ እስማማለሁ። ብዙ የሀገራችን ፖለቲካኞች ጋዜጠኛ መቅረፀ ድምፅ ይዞ በሚጠይቃቸው ጥያቄ መልስ ከመስጠት የዘለለ ብዕርና ወረቀት አገናኝተው የሚያምኑበትን የፖለቲካ መስመር እና በግላቸው ያላቸውን ምልከታ ማካፈል ይቸግራቸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ተስፋዬ ገብረአብ

የህወሓትን የጓዳ ወግ ማወቅ አስቸጋሪ የነበረበት ዘመን እንደዋዛ አልፎአል። ዛሬ ቀዳዳቸው በዝቶ፤ ቴክኖሎጂውም አግዞ የፈፀሙት ብቻ ሳይሆን ያሰቡትም በቀላሉ ይገኛል። ዘመኑ የመረጃ ዘመን ነው። መረጃ ከሌለ ምንም ነገር የለም። ለችግሮች መፍትሄም አይገኝም። ወያኔ ዛሬ በአስር ሺዎች ኦሮሞዎችን በገፍ የሚያስረው ስለ ቄሮ በቂ መረጃ ስለሌለው መሆኑ ይታወቃል። ተቃዋሚ የፖለቲካ ተንታኞች ወይም የማህበራዊ ድረገፅ ፀሐፊዎች አንዳንድ ጊዜ አስቂኝ ስህተት ይሰራሉ። ማለትም ሳያውቁ ለወያኔ የሚጠቅም መረጃና ምክር ይፅፋሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

By Eyob Dadi የቀድሞው የኤሲሚላን እና የጁቬንቱስ አማካይ የነበረው አንድሪያ ፒርሎ በእግርኳስ ቆይታው ያየው ምርጡ ወጣት ተጨዋች ተናግሯል። ፒርሎ የቡድን አጋሩ የነበረው ፓል ፓግባን ምርጡ ወጣት ተጨዋች ሲል ያወድሰዋል። ፓግባ 2012 ላይ በማንቸስተር ዩናይትድ በቂ የመሰለፍ እድል በማጣቱ ወደ ጣሊያኑ … Continue reading

ጥር 11፣2008 ዓ. ም ትናንትና ምሽት በጣሊያን ዋንጫ ኢንተርሚላን ናፓሊን ባሸነፈበት ጨዋታ ላይ ሁለቱ አሰልጣኞች ሮቤርቶ ማንቺኒ እና ማውሪዚዮ ሳሪ ሲጨቃጨቁ ታይተዋል። ከጨዋታው በኋላ ሪቤርቶ ማንቺኒ ከ ራይ ቲቪ ጋር ከማውሪዚዮ ሳሪ ጋር በአሰልጣኞች መቆሚያ(touchline) ላይ ስለተለዋወጡት ቃላት ስሜታዊ ሆነው ተናግረዋል። በአሰልጣኞች መቆሚያ ላይ ስለተነጋገራችሁት?ይህን ጥያቄ እሱን(ማውሪዝዮ ሳሪ) መጠየቅ አለባችሁ፣እሱ ዘረኛ ነው ብለው ይጀምራሉ ሮቤርቶ … Continue reading ““ማውሪዚዮ ሳሪ ዘረኛ ነው፣አንተ ጅል ነጭናጫ ብሎ ሰድቦኛል” – ሮቤርቶ ማንቺኒ”

የብሔራዊ ቡድኑ የፊት መስመር ተሰላፊ ነው ፡፡ የአይረሴው የደቡብ አፍሪካው የአፍሪካ ዋንጫ ቡድን አባል፡፡ በ2014 አለም ዋንጫ ማጣሪያ ላይ ለብሄራዊ ቡድኑ ቁልፍ ነበር በስሙ ሶስት ጎሎች አስቆጥሮ ዋልያውን የአፍሪካ ምርጥ አስር ውስጥ ሲካተት ትልቅ የሆነ ድርሻን ተወጥቷል ፡፡ የዋልያው ድንቅ የፊት መስመር ተጫዋች ጌታነህ ከበደ ከኢትዮ አዲስ ስፖርት አዘጋጅ ህሊና አዳነ ጋር በፕሮፌሽናልነተ እግር ኳስ … Continue reading “” እስካሁን ካሰለጠኑኝ አሰልጣኞች ሁሉ ሰውነት ቢሻው የኔ ምርጥ አሰልጣኝ ነው” ጌታነህ ከበደ”

ጥር 8፣ 2008 ዓ. ም ኤቨርተኖች ከቸልሲ ጋር ያደረጉት የዛሬው የፕሪምየር ሊግ ጨዋታ 3ለ3 በሆነ ውጤት ተጠናቋል። በጨዋታው በመጨረሻዎቹ ጭማሪ ሰዓት ላይ ሁለት ጎሎች የተቆጠሩ ሲሆን፣ የጆን ቴሪ የመጨረሻ ደቂቃ ጎል አጨቃጫቂ ነበረች። ሮቤርቶ ማርቲኔዝ ቴሪ ያስቆጠረው ጎል ከተጨመረው ሰዓት ማለፉ ብቻ ሳይሆን ከጨዋታ ውጭ የነበረ በመሆኑ የዕለቱ ውሳኔን “ሰይጣናዊ” ሲሉ ይገልጹታል። “ለደጋፊዎች ጥሩ ጨዋታ … Continue reading ““የዳኛው ውሳኔ ሰይጣናዊ ነበር”- ሮቤርቶ ማርቲኔዝ”

ለመጀመሪያ ጊዜ የኢትዮጵያ ፊደል በላፕቶፕና በዲስክቶፕ ተቀርጾ አገልግሎት መስጠት ቻለ

The first Amharic, Geez laptop

Ethiopia Zare (ዓርብ ጥር 6 ቀን 2008 ዓ.ም. January 15, 2016)፡- ጋዜጠኛና ፀሐፊ ገነት አየለ የኢትዮጵያ ፊደላት እንደሌሎቹ የቋንቋ ፊደላት በላፕቶፕና በዴስክቶፕ ለመጀመሪያ ጊዜ ተቀርጸው ለተጠቃሚዎች አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረግ መቻላቸውን ከደረሰን መረጃ ለማወቅ ችለናል። ይኸው የመጀመሪያው በኢትዮጵያ ፊደል የሚጽፍ ኮምፒዩተር በገበያ ላይ መዋሉ ታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

በኦሮሚያ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሐላፊ እንደሚሉት ዕቅዱን ሕዝቡ፤ በእሳቸዉ አገላለጥ «ከጫፍ እስከ ጫፍ» ተቃዉሞታል።በማስተር ፕላኑ ሰበብ በተነሳው ተቃውሞ በሁለት ወራት ጊዜ ዉስጥ ወደ 140 ሰዎች እንደተገደሉ ና በርካቶች እንደቆሰሉ የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ በምህፃሩ ኦፌኮ አስታውቋል

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

  ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው እንደሚታወቀው በተማሪዎች የተጀመረው ተቃውሞ ሌላው የኅብረተሰብ ክፍልም ተቀላቅሎት ሲደረግ የቆየው ሕዝባዊ ተቃውሞ እነሆ ሁለት ወራት እየሆነው ነው፡፡ እያየነው እንዳለነው እስከአሁን ተቃውሞው ያመጣው ውጤት ወይም ለውጥ የለም፡፡ ወደፊትም ሕዝቡ በዓመፁ የመቀጠል ብርታት የሚኖረው ከሆነ “በእኔ ግምት ይኖረዋል ብየ ስላልገመትኩ ነው ምክንያቶች አሉኝ” እንዲያው ከሆነ ግን ወያኔ ሁሉንም ለቃቅሞ እስኪፈጅ ድረስ ሳይሰለች […]

ሱዳን፣ ግብፅ እና ኢትዮጲያ ለብዙ ግዜ እየተንከባለለ ከመጣ ድርድር በኋላ በጎርጎሮሳዊው አቆጣጠር ታህሳስ 29 2015 ካርቱም ሱዳን ሊይ Declaration of Prinicples ወይም የመሰረታዊ መ መርሆዎች ሰነድ ተብሎ የምጠራዉን ሰነድ መፈራረማቸዉ ተዘግቧል ።

ከአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጋር ተያይዞ በኦሮሚያ ክልል ከስምንት ሳምንታት በፊት የጀመረው የተቃውሞ እንቅስቃሴ በተለያዩ ከተሞች እንደቀጠለ መሆኑን ምንጮች ተናግረዋል።

በኦሮሚያ ክልል የአዲስ አበባንና የፊንፊኔን ልዩ ዞኖችን ለማቀናጀት የተነደፈዉን ማስተር ፕላን በመቃወም የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ትላንትና በዛሬዉ እለት በጂማና በሃሮማያ ዩኒቬርሲቲዎች ተካሂደዋል፥ የመንግስት ጸጥታ አስከባሪ ሃይሎችም ተማሪዎቹን በመደብደብ ተቃዉሞዉን መበተናቸዉ ታዉቋል።

ሰሞኑን በኦሮሚያ እና በሰሜን ጎንደር የተከሰተው የተቃውሞ ንቅናቄ ሀገሪቱን ውጥረት ውስጥ ከትቷታል፡፡ አመጹ እየተጋጋለ መሄድ እንጂ የመቀዛቀዝ ባህሪ አላሳይ ብሏል፡፡ አሁንም በልዩ ልዩ አካባቢዎች ቀጥሏል፡፡ በአራቱም አቅጣጫዎች ውጥረት ሰፍኗል፡፡ በህይወት ዘመኔ ይህንን ያህል ዘላቂ ሆኖ የቆየ አመጽ አይቼ አላውቅም፡፡ በዚህ አመጽ ለጠፋው ህይወትና ንብረት እናዝናለን፡፡ በየትኛውም ወገን ሆኖ በትርኢቱ ውስጥ የተሳተፈው የኛው ዜጋ በመሆኑ ነፍሱና […]

የኢትዮጵያ የምግብ የመድኃኒት ጤና ክብካቤ አስተዳደር እና ቁጥጥር ባለስልጣን ወደሀገር ዉስጥ በሕጋዊ መንገድ የሚገቡትንም ሆነ እዚያዉ የሚመረቱትን መድኃኒቶች የጥራት ደረጃ ይከታተላል።

በአርባምንጭ ከተማ ብዙ ወጣቶች የግንቦት 7 አባል ናችሁ በሚል ሰበብ ተጠርጥረው ዕርቃናቸውን ግርፋትና የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንደተፈጸሙባቸው ከስፍራው የደረሰን ዜና አመለከተ። 20 አመት እድሜ ላይ የሚገኙ ዮሴፍ ይስሃቅና፣ እንዳሻው ወንድይፍራው ከዚህ በፊት በአርባምንጭ ከተማ ከጓደኞቻቸው ጋር ሲዝናኑ ተይዘው ከታሰሩ በኋላ እያንዳንዳቸው በ2ሺ ብር ዋስትና እንደተለቀቁ፣ “ወያኔን ሰድበዋል፣ ከአርበኞች ግንቦት ሰባት ግንኙነት አላቸው” በሚል ሰበብ እንደተደበደቡ […]

ከአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጋር ተያይዞ ሰሞኑን ኦሮሚያ ውስጥ በተፈጠረው ተቃውሞና አለመረጋጋት ምክንያት “ተገደለ” ያሉት ሰው ቁጥር ሰማንያ ዘጠኝ መድረሱን የመድረክ ምክትል ሊቀመንበርና የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊው አቶ ጥላሁን እንደሻው ገልፀዋል።

ተቃዉሞ-ግጭቱ ቆመም-ተዳፈነ እስካሁን በነበረዉ ግጭት ከ100 በላይ ሰዎች ተገድለዋል። የተገደሉት ሰዎች ቁጥር የታሠሩና ብዛት፤ የጠፋዉ ሐብትና ንብረት መጠን ብዙ እንዳከራከረ ነዉ። መንግሥት ግጭቱ በተቀሰቀሰ ሰሞን አምስት ሰዎች መገደላቸዉን ከማሳወቁ ባለፍ በሰዉ ሕይወት፤ አካልና ንብረት ላይ ሥለደረሰዉ ጥፋት እስካሁን ይፋ ያደረገዉ ነገር የለም

የአዲስ አበባና የፊንፊኔ ዙሪያ የተቀናጀ ማስተር ፕላን ተግባራዊ ይደረጋል መባሉን ተከትሎ በኦሮሚያ ከተሞች ከሕዳር ወር አጋማሽ ጀምሮ ሲካሄድ የነበረዉ ተቃዉሞ ዛሬም በአንዳንድ አካባቢዎች ቀጥሏል። ተቃዋሚዎቹ፣ የታሰሩ እንዲፈቱ ለተገደሉት ሰዎች ቤተሰቦች ካሳ እንዲከፈል የሚል መፈክርም ጨምረዋል።

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ባለፉት ሁለት ወራት በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ ከተሞች በተፈጠረው የተማሪዎች ተቃውሞ 140 ሰዎች ሳይገደሉ እንዳልቀረ መቀመጫውን በኒውዮርክ ከተማ ያደረገው የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት Human Rights Watch ገልጿል።

More than 100 towns (with population more than 5,000) in Oromia have witnessed protests; more than 140 people were killed; and, more than 5000 people were arrested following the ongoing Oromo protests. Yet, it seems the protests are limited in Oromia region and didn’t show any sign of dispreading to other regions.

It is a serious issue but no political analyst seemed to be seriously concerned about it. Will the protest grow to be Ethiopia-wide? Is there even a need for it to be? If so, how? I will try to raise similar questions with my own answers. My hope is you will proceed in elaborating it.

Will Oromo Protests Continue?

Oromo protests are not only about the Addis Ababa expansion plan. As many Oromo civil rights activists are explaining, the protests are about anonymous self-administartion of Oromia, proprotional representation of its people in Federal administration, upraisal of Afaan Oromo to Federal working language status and etcetra. Therefore, lone-cancellation of the master plan would not stop the protests.

Harrassment, intimidation, mass arrest and killing are traditional instruments of Ethiopian government to stop social movements. In Oromo protests, however, this system had been applied against protesters in 2014 but failed to prevent explosion of the protests again for the second time in far more strength. This is an implication for that it continues even further regardless of government actions to silence them. Thus, we can conclude that the protests will continue but (in my opinion) their success will be dependent of two reasons: (1) they have to stick with non-violence startegies; i.e. they have to avoid any chance of turning the protests to violence; (2) the protests have to be coordinated not only intraregionally (within regional subdivison) but also interregionally (with other regions small, on and off protests).

Should Oromo Protests Continue?

There is no consensus among scholars as to what kind of social movement will result in grievances resolved. However, most scholars agree, the more popular a social movement gets, chances are more for it to succeed. It is in this understanding that many are seeking the protests in Oromia to dispread to the rest of regions in Ethiopia.

In addition, land grab – the primary cause of the current protests – is even worse in some regions such as Gambella. Liberal opposition groups have been blaming the constitution, which disgranted ownership rights of land from individuals, for not giving land owners the bargaining power over the land they till. Therefore, these groups, at least until Article 40 of the constitution gets amended to this regard, oppose the expansion of Addis to Oromia region. Moreover, there are other groups who are in continuous disagreement with the authoritarian regime of Ethiopia. Ethiopian muslims, who for the past four years non-violently resisted reported regime interference in religious affairs, are one example. TPLFites supermacy has been a disappointment of everyone for the past two decades. Everybody agrees democratization has declined backwards. Civil societies, free press, and the right to freely associate and demonstrate are weakened. Only a contested economic growth spared EPRDF led government from a total dark image.

All the above reasons make up the need for a coordinated, continued, Ethiopia-wide protests to be held for either the government will open doors for improvement or it will be changed by the will of the supreme people.

Do Ethiopians Protest?

Two scholars (whose name I forgot to mention) have two contrasting models of protest. (see pic.) The first model argues that social movements are high in either closed or open systmes; the assumption is that when a system is closed people need a scape, so they protest. When it is open, people see hope to get what they want through protests. Either way they protest. The other model (numberd two in the pic.), argues that people protest when a system is not open nor closed but lies in the middle. The assumption for this is that if a system is open, then there is no need to protest and if the system is closed, there is no way to. Emperical researches are said to support model two. It is in authoritarian regimes that people usually protest where the n-curve reaches its maximum peak.

Ethiopian government fits authoritarian regimes definition. It is founded in democratic principles according to the written constitution and have the structure to allow that. Practically, it is totalitarian system with extremely limited legitemacy and accountability. Therefore, it is a matter of time that all the rest Ethiopians, along with their Oromo brothers join in the protest.

There are, however, conditions to head to Ethiopia Protests starting from Oromo Protests:

1). Getting settled with Hagos vs. Tolla issue: while symbolizing inequality in simple terms, it is also important to recognize all individuals in an ethnic group can not be categorized in the same basket with elites who exploit the ethnic group for their own interest;

2) Establishing an anonymous and diversified activists’ group that leads protests: DimtsachenYisema (the online group that leads Ethiopian Muslims protests) is a good example. This assumed group, its leaders preferebly living abroad, plans peaceful strategies, creates public awareness, coordinates nation-wide movements and keeps the pace of the protest according to sought possibilities.

ባል ሚስቱን ገድሎ ራሱን ሳያጠፋ አልቀረም ተብሏል

   በአዲስ አበባ ቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 7 ጃክሮስ አደባባይ አካባቢ በሚገኝና ትናንት ጠዋት የእሣት ቃጠሎ በደረሰበት ቤት ውስጥ ባልና ሚስት ሞተው የተገኙ ሲሆን የሰዎቹ ሞት ከቃጠሎው ጋር የተገናኘ እንዳልሆነ ታውቋል፡፡
የእሣት አደጋ ሠራተኞች በደረሳቸው ጥሪ መሰረት ትናንት ጠዋት 2 ሰዓት ገደማ በስፍራው ደርሰው እሣቱን ያጠፉ ሲሆን ባልና ሚስቱ የቃጠሎ አደጋ ሳይደርስባቸው ሞተው መገኘታቸውን የጠቆሙት የአዲስ አበባ እሣትና ድንገተኛ አደጋ መከላከል የኮሚኒኬሽን ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ፤ 30ሺ ብር የሚገመት ንብረት መውደሙንም ገልፀዋል፡፡
ሟቾች የ60 ዓመቱ አቶ ብርሃኑ ቡሌና የ44 ዓመቷ ወ/ሮ አስቴር አሰፋ፤ የ6 ልጆች ወላጆች ሲሆኑ ባል፣ ሚስቱን ገድሎ ራሱን ሳያጠፋ እንዳልቀረ መጠርጠሩን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡
የእሣቱ መነሻ ሲሊንደር ነው ያሉት ምንጮቹ፤ ፖሊስ በእሣቱ መነሻና በባልና ሚስቱ አሟሟት ላይ ተጨማሪ ምርመራ እያደረገ መሆኑን አመልክተዋል፡፡

የዛምቢያ መንግስት፤ በህገ ወጥ መንገድ የሃገሬን ድንበር ጥሰው ገብተዋል ያላቸውን 77 ስደተኛ ኢትዮጵያውያን ማሰሩን የሀገሪቱ የመገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል፡፡
የሀገሪቱ ፖሊስ እንደሚለው፤ በመጀመሪያ የተያዙት 10 ኢትዮጵያውያን መነሻቸውን ከዛምቢያ ዋና ከተማ ሉሳካ በማድረግ በክፍት መኪና ተጭነው ለመውጣት ሲሞክሩ፣ በአካባቢው ሰዎች ጥቆማ የተያዙ ሲሆን በምርመራ ወቅትም ሌሎች 67 ኢትዮጵያውያን በአንዲት ጠባብ ክፍል ውስጥ ታጭቀው እንደሚገኙ በመግለፃቸው በክትትል ተይዘዋል፡፡  ከታሰሩት 77 ኢትዮጵያውያን መካከል 19 ያህሉ ህጋዊ ፓስፖርት እንዳላቸው የገለጸው ፖሊስ፤እንዲያም ሆኖ ሁሉም ወደ ሀገሪቱ የገቡት በህገወጥ መንገድ በመሆኑ በህግ ከመጠየቅ አያመልጡም ብሏል፡፡
ኢትዮጵያውያኑ በሉሳካ ማዕከላዊ እስር ቤት ውስጥ እንደሚገኙ ያስታወቀው ፖሊስ፤በአገሪቱ ህግ መሰረት ፍ/ቤት ቀርበው ተገቢው ቅጣት እንደሚተላለፍባቸው ጠቁሟል፡፡

በውጭ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ወደ አገር ቤት የሚልኩት የገንዘብ መጠን መጨመሩን የዓለም ባንክ በቅርቡ ባወጣው ዘገባ አስታውቋል። በውጭ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ግን ሁልጊዜም ገንዘብ የሚልኩት በህጋዊ መንገዶች አይደለም።

በውቀቱ ብዙዎቻችሁ እንደምታውቁት ሰው መኮርኮር ይችላል። የተማረው ሳይኮሎጂ ነው። ሳይኮሎጂ የሳቅ ስስ ብልት የት እንደሆነ አስተምሮት ይሆን እላለሁ። ነገር ግን ማሳቅ የጀመረው ትምህርቱን ከመጨረሱ በፊት ስለሆነ ብቻ ሳይሆን ሌሎች ሳይኮሎጂስቶች ሲያስቁ ስላልገጠመኝ በዚህ ረገድ ግንኙነት (co-relation) መፈለጌን አቋርጫለሁ።

በውቀቱን እንደ ኮሜድያን አልቆጥረውም [ነበር]። እንደዛ እንድቆጥር የተገደድኩበት አንድ ጊዜ ቢኖር ሀብቴ ከሞተ በኋላ ሀብቴን ተክቶ ሲመጣ ነው፤ ደረጄና በውቄ ነገር ሁኖ። እዚያ ላይ በውቄ ሀብቴን ተክቶ መምጣቱ ከቀልዶቹ የተሻለ ያስቅ ነበር፤ የተሻለ። በውቀቱ ያንን ሚና ደግሞ ላይመለስበት ባደባባይ ቃል ገብቷል።

በውቀቱ ፈላስፋ ነው፤ ኮሜድያን አይደለም። በነገራችን ላይ ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋም በውቀቱን ፈላስፋ ነው ይላል። “ስንት ፕሮፌሰሮች ሁለት ክላስ የሚያሰተምሩበትን ሐሳብ እሱ በሁለት መሥመር ቁጭ ያረገዋል፣” በማለት፦
ሉላዊነት

“የጋራችን ዓለም፣ የጋራችን ሰማይ
የብቻችን ሕመም፣ የብቻችን ስቃይ።”

***

“አገር ድንኳን ትሁን ፣ ጠቅልዬ የማዝላት
ስገፋ እንድነቅላት፣ ስረጋ እንድተክላት።”

***

“ከተመኙ ላይቀር ወንዝነት መመኘት፣
አገርን ሳይለቁ ሰው አገር መገኘት።”

በራሪ ቅጠሎች ላይ የመጀመሪያዋ ጽሑፍ ትመስለኛለች በሕይወት ላይ የሚስቅባት ገፀ–ባሕሪይ አለ። ሕይወት ግን ዝም ብላ የምታስቅ እንዳልሆነች የልቦለዱ መጨረሻ ይተርካል። በመጨረሻው መጽሐፉ (መውጣትና መግባት) መግቢያ ላይ ደግሞ፣ ግጥም ተርጉሞ እንደመግቢያ አስቀምጧል። ታዲያ ዘነበ ወላ አዲስ አድማስ ላይ መጽሐፉን ሲተቸው (መጽሐፉ እንደበፊቶቹ ሲሪዬስ አይደለም ብሎ በማሰብ ይመስላል) “ተመልሰህ ግባ በወጣህበት በር” ብሎ ነበር ትችቱን የቋጨው (ከመግቢያ ግጥሙ ስንኝ ተውሶ)። የበውቀቱ መግቢያ ግጥም አሁን በቃሌ እንደማስታውሳት እንዲህ ትላለች፣

“በወጣኒነቴ በድሜዬ አፍላ ጀምበር፣
የሊቅ የጣዲቁን ሐተታ ቁም ነገር፣
አዘወትር ነበር፣
እና ምን ተረፈኝ?
ተመልሼ ወጣሁ፣ በገባሁበት በር።”

ወጥቶ ከሆነ እንኳን ወጣ። ውጪው በጣም ሰፊ ነው። በውቀቱ ደሞ ሲሪዬስሊ የማትወስደንን ተፈጥሮ ሲሪዬስሊ የማይወስድ፣ ለጥፊና ካልቾዋ የማያለቅስ ጸሐፊ ነው (ቢያንስ እኔ እንደተረዳሁት)። በውቀቱ ለኔ የዘመናችን ‘አይከን’ ነው። በለበጣ የሚመለከተንን ዘመን በተመጣጣኝ ለበጣ የሚመክትልን አሽሙረኛ። የኛ ማርክ ትዌይን፣ ወይም የኛ ቮልቴር ነው – በውቀቱ ስዩም!

የበውቀቱ ግጥሞች (በተለይ የኗሪ አልባ ጎጆዎቹ) የሐዘን እንጉርጉሮ ይበዛባቸዋል። ያኔ ተረከዙ የተበሳ ጫማ አድርጌ አዲስ አበባን ስዞር እነሱን በቃሌ እየወጣሁ ነበር ዕጣ ፈንታን እተች የነበረው። ሎሬት ፀጋዬ «ወንድ ልጅ ብቻውን ነው የሚያለቅስ» ሲል፣ በውቀቱ ደግሞ፣

“እምባ ታዛዥ ሆኖ የሚገደብበት፣
ያባት ቅኔና ቀን አለፈ እንደዘበት” እያለ ከውነቱ ያጋፍጠናል።

በሳት ዳር ሐሳቦች ስብስቡ “ከንፍገት እጦትን ማካፈል ይሻላል” ብሎ በፈገግታ ሲመጣ፣ እኔም ዓለምን በሽሙጥ ፈገግታ መመልከት ጀምሬ ነበር። በውቀቱ ከጉርምስና ወደጉልምስና ሳዘግም እንደ ሳውንድ ትራክ ተከትሎኛል። የኔን ትውልድ የሚወክል አይከን ነው የምለውም በዚህ መመዘኛ ነው። ዓለም ሲሪዬስ ሲሆኑላት ሲሪዬስ እንደማትሆን አሳይቶኛል። “የፀጋዬ ቤት ከፀጋዬ በፊት” ብሎ ሲል ዛቻ፣ “እግር አልባው ባለ ክንፍ” ብሎ ሲል ቡጢ ነው የገጠመው። የተሻለው ሽሙጥ ነው። የገባው ቁም ነገሩን ይጨብጣል፤ ያልገባው ስቆ ያልፋል። መሳቅ፥ መሳቀቅን ተካ።

እንደ በውቀቱ በቃላት የሚቀናጣ ባለቅኔ የለም። “ለካስ ያባቶች faith ፌዝ ብቻ ነበረ” እያለ የማይተዋወቁትን ቃላት ድንገት ማዛመድ የሚችለው እሱ ብቻ ነው። በውቀቱ የዶ/ር እጓለ ምናባዊ ሥልጣኔ ቢሰፍን የሚገኘው ውጤት ነው። የአገር በቀል ዕውቀትን ከምዕራባውያኑ ጋር ያዋሃደ ሰው። ስትፈልጉ ከቅኔ ቤት ወጎች፣ ስትፈልጉ ከአቴና ሰማይ ላይ ፊሎዞፊያን ጎትተው ባወረዱ ሰዎች ወግ ያጨዋውታችኋል።

ከቁምነገር መጽሔት እስከ ሮዝ (አዲስ ጉዳይ) መጽሔት ድረስ ያሉ ጽሑፎቹን ደጋግሜ በማንበብ «ጽሑፎችህን ካንተ የበለጠ አውቃቸዋለሁ» ወደሚል ትምክህት ደርሼ ነበር። ተነፈስኩ እንጂ። አሁን ደሞ፣ ፌስቡክ ላይ መጥቷል። እንደ ኗሪ አልባ ጎጆዎቹ ዘመን ሰዎች ጎጆዎቹን መሬት ላይ ቀልሰው መሬት ላይ ብቻ ተጋበዙልኝ ብለው ድርቅ እንደሚሉት ጸሐፍት ሆኖ አልቀረም። ትውልዱ ፌስቡክ ላይ ሲወጣ እሱም ጎጆውን እዚያው ቀልሷል። ጎጆው ውስጥ በቀልድ እያስመሰለ የዘመናችንን እውነት ይተርክልናል። ጎጆውን መቀለስ በጀመረ ጊዜ እኔም እዚሁ ሰፈር ነበርኩ። ጓዙን ጠቅልሎ ፌስቡክ በከተመ ጊዜ ግን “እረፍት” ላይ ነበርኩ። ስለዚህ አሁን “እንኳን ደህና መጣህ” ብለው ረፈደብህ አልባልም። እዚህ ሰፈር ለማይደራደሩብህ አድናቂዎችህ ታስፈልገናለህ።
———
ግጥሞቹን በቃሌ ስለወጣኋቸው ቢሳሳቱ አያገባኝም።

“ሐሳብን የመግለጽ ነጻነት ምንድን ነው? ማበሳጨትን ካላካተተ፣ ሕልውና የለውም፡፡” ~ ሰልማን ሩሽዲ
፩ – ማበሳጨት

‹‹በመስከረም ወር 1997፣ ዢላንድስ ፖስተን የተባለ የዴንማርክ ጋዜጣ ነብዩ መሐመድ ላይ የሚሳለቁ ካርቱኖችን ይዞ ወጣ፡፡ የዚህ ሕትመት ዜና በመላው ዓለም እንደተሰማ በየቦታው ያሉ ሙስሊሞች ቁጣቸውን በአደባባይ መግለጽ ጀመሩ፡፡ የተቃዋሚዎቹ ምክንያቶቻቸው ሁለት ናቸው፤ አንደኛ፣ ነብዩ መሐመድን በምስል መግለጽ በእስልምና ሃይማኖት አይፈቀድም የሚልና፤ ሁለተኛ፣ ካርቱኖቹ በጥቅሉ እስልምናን እና ሙስሊሞችን ከሽብር ጋር አቆራኝተው ይገልጻሉ የሚል ናቸው፡፡  ሠላማዊ ሰልፎችና ሕዝባዊ ተቃውሞዎች በጋዜጣው አዘጋጆች እና በዴንማርክ መንግሥት ላይ ተቀሰቀሰ፡፡ ከነዚህ ውስጥ አንዳንዶቹ ሕይወት እስከመቅጠፍ የዘለቀ አመጽ የተቀላቀለባቸው የተቃውሞ ሰልፎች ነበሩ፡፡ ካርቱኖቹ ግን በመላው ዓለም በሚገኙ በሌሎች ጋዜጦች ላይ ለዢላንድስ ፖስተን ጋዜጠኞች የሞራል አጋርነት ለማሳየት በሚል ሰበብ ድጋሚ ታትመው ይበልጥ ተሰራጩ፡፡›› (Paul Sturges, 2006)

ሌላ ምሳሌ እንውሰድ፡፡ አንድ ወንድ “‹ሴቶችን ማስተማር የአገርን ሀብት ማባከን ነው፤ ስለዚህ ሴቶችን ማስተማር ካለብን የቤት አያያዝ፣ ምግብ ማብሰል እና ልጅ አስተዳደግ እናስተምር እንጂ ሌላ ‹የነጭ ኮሌታ› ሥራ የሚያስይዝ ትምህርት ማስተማር የለብንም› የሚል አስተያየት ሲሰጥ በቴሌቪዥን ተላለፈ፡፡ ይህን ተከትሎ የከተማው ሴቶች የተቃውሞ ሰልፍ አደረጉ፡፡ ወንድ አሽከርካሪዎች የሚነዷቸውን መኪኖች ሰባበሩ፡፡ ወንዶችን እያሳደዱ ደበደቡ፡፡” በዚህ የፈጠራ ታሪክ ውስጥ የአስተያየት ሰጪው ሐሳብ ሴቶቹን አበሳጭቷቸው ይሆናል፡፡ ነገር ግን ለአመጹ እነርሱን አነሳስቷቸዋል ብሎ መደምደም ከባድ ይሆናል፡፡ አማጺዎቹ ሴቶች ስሜታቸውን መቆጣጠርና ሐሳቡን በሐሳብ መመከት ካልቻሉ ድክመቱ የነርሱ የራሳቸው ይሆናል፡፡

የዴንማርክ ፍርድቤት የፈረደውም፣ እኔ በላይኛው አንቀጽ አመጸኞቹ ሴቶች ላይ የሰጠሁትን ዓይነት ብይን ነው፡፡ “እርግጥ ነው ስዕሎቹ የተወሰኑ ሙስሊሞችን ማበሳጨታቸው አይካድም፤ነገር ግን የካርቱኖቹ ዓላማ ሙስሊሞችን ማንኳሰስ አልነበረም›› ብሏል ፍ/ቤቱ፡፡ ሲያብራራውም፣ “ስዕሎቹን አመጽ ወይም ቦንብ የመወርወር ድርጊት በእስልምና ሥም እየተደረገ ነው፤” በሚል መረዳት የካርቱኖቹ ተመልካቾች ድርሻ ነበር ብሏል፡፡ የዴንማርክ ፍርድ ቤት ብይን ለካርቱኒስቶቹ ያደላ ቢመስልም ካርቱኒስቶች ራሳቸው ላይ ቅድመ ምርመራ እንዲያደርጉ ክስተቱ አስገድዷቸዋል፡፡ ነገር ግን የአንድ ሐሳብ (expression) አንባቢ፣ ተመልካች ወይም አድማጭ የራሱን ስሜት መቆጣጠር ድርሻ የራሱ መሆን ካልቻለ ቢያንስ የሆነ ሰውን የማያበሳጭ ሐሳብ ማፍለቅ በጣም አስቸጋሪ ስለሚሆን፣ ‹በነጻ› ቀርቶ ሐሳብን መግለጽ የሚባለው ጉዳይ ራሱ አይኖርም፡፡

 አምና የፈረንሳዩ ‹ሼርሎ ሆብዶ› መጽሔት ባወጣቸው ካርቱኖች ተበሳጭተው ጋዜጠኞችን፣ ካርቱኒስቶችን እና ፖሊሶችን የገደሉ ፅንፈኛ-ሃይማኖተኞች ጉዳይም ሊታይ የሚችለው በዚሁ ዓይን ነው፡፡ ፅንፈኞቹ የእነርሱን እሴት ያላከበረ፣ በእነርሱ እሴት መሠረት መቀጣት አለበት የሚል እርምጃ ነው የወሰዱት፡፡ ክስተቱ ለሐሳብ ነጻነት አራማጆች መርዶ ነው፡፡ አጋጣሚውን ተከትሎ ተቀጣጥሎ የመጣውም ውይይት ሰዎች ራሳቸውን በራሳቸው ሳንሱር እንዲያደርጉ የሚያስፈራራ ነው፡፡ ይሁን እንጂ አጋጣሚው የኢትዮጵያውን ጨምሮ ለአምባገነን (authoritarian) መንግሥታት ፕሮፓጋንዳ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል፡፡ ሐሳብ እንዴት መገደብ እንዳለበት ክስተቱን አስታክከው ደስኩረዋል፡፡ እነዚህ መንግሥታት ሊያስተውሉት ያልፈለጉት ነገር ቢኖር ከዴንማርክ እስከ ፓሪስ የተከሰተው ነገር ጋዜጠኞች ሐሳባቸውን በነጻነት ሲገልጹ የመንግሥት ከለላ እንደሚያስፈልጋቸው እንጂ ሐሳባቸውን በበነጻነት ከመግለጽ እንዲቆጠቡ የሚመክራቸው አልነበረም፡፡
ሌሎችን ማበሳጨት የተወሰኑ የማኅበረሰብ ክፍሎች ላይ ወይም ግለሰቦች ላይ ሲከሰት ከሞላ ጎደል ከላይ ባየነው ሁኔታ ሊያልፍ ይችላል፡፡ ችግሩ የተበሳጨው አምባገነን መንግሥት (የመንግሥት ባለሥልጣናት) ሲሆኑ ነው፡፡ እነ ኤልያስ ገብሩ (አምሳሉ ገ/ኪዳን ዕንቁ መጽሔት ላይ በሚያዝያ ወር 2006 የጻፈውን ጽሑፍ ተከትሎ ጅማ ዩንቨርስቲ አካባቢ በተነሳው የተቃውሞ ብጥብጥ ሳቢያ) የተከፈተባቸው የአመጽ ማነሳሳት ክስ መታየት የሚኖርበት በዚህ ዓይን ነው፡፡ መንግሥት ጸሐፊዎቹንም፣ ለጽሑፉ የጽሑፍ ምላሽ በመስጠት ፈንታ በኃይል የጸሐፊውን ሐሳብን የመግለጽ ነጻነት የተቃወሙትን፣ ሁለቱንም በክስ በማስተናገድ ጉዳዩን ለመፍታት እየጣረ፣ ጉዳዩ እስካሁን በእንጥልጥል ነው፡፡ ተመስገን ደሳለኝ ሦስት ዓመት የተፈረደበት የመንግሥት ባለሥልጣናትን የማያስደስት አልፎም የሚያበሳጭ ጽሑፍ ስለጻፈ ነው፡፡ የዚህ ጽሑፍ ጸሐፊ ክሱ ከሽብር ወደ ‹በጽሑፍ አመጽ ማነሳሳት› የተቀየረው በተመሳሳይ ምክንያት ነው፡፡ ተጠያቂነት የሌለባቸው የመንግሥት ባለሥልጣናት በሐሳብ ሲበሳጩ ውጤቱ የከፋ ይሆናል፡፡

፪ – የጥላቻ ንግግር እና አመጽ ማነሳሳት

በ1987 ሩዋንዳ በዓለማችን የቅርብ ጊዜ ታሪክ ውስጥ ሰቅጣጭ የሆነውን ዜና ለዓለም አርድታለች፡፡ በ100 ቀናት ውስጥ 800 ሺሕ ያህል ሰዎች ተጨፍጭፈዋል፡፡ በጭፍጨፋው 70 በመቶ ቱትሲዎች (ወይም 20 በመቶ ሩዋንዳውያን አልቀዋል)፡፡ የጭፍጨፋው መነሾ ላይ የታሪክ ባለሙያዎች ሙሉ ለሙሉ ባይስማሙም በጎሳ ስም አመጽ እንዲቀጣጠል ያደረገው ግን የሚዲያ የጥላቻ ንግግር እንደሆነ ብዙዎቹ ይስማማሉ፡፡ ከዘር ጭፍጨፋው ዓመት ቀድሞ የተቋቋመው ሬዲዮ-ቴሌቪዥን ሊብሬ ደስ ሚል ኮሊንስ (አር.ቲ.ኤል.ኤም.ሲ) ዋነኛ ሚና ተጫውቷል፡፡ አንዳንድ ጥናቶች በዘር ጭፍጨፋው የዚህን ሚዲያ ተቋም ሚና እስከ 10 በመቶ ያደርሱታል፡፡ ሬዲዮው በጣም ተወዳጅ ከመሆኑ የተነሳ ከዜጎቹ ጋር በአጭር ጊዜ ለመዋሃድ በቅቷል፡፡ ይህ ሬዲዮ ነበር ቱትሲዎችን “በረሮ” ብሎ መጥራት የጀመረው፡፡ “በረሮዎቹን ደግሞ ማስወገድ አስፈላጊ ነበር፡፡” አለበለዚያ ችግር ያስከትላሉ፡፡ ሬዲዮው በተጨማሪም “በረሮ” ብሎ የጠራቸውን ዜጎች ማስወገድ ስለማስፈለጉ ብቻ ሳይሆን እንዴት መወገድ እንዳለባቸው ጭምር ተንትኗል፡፡ የጭፍጨፋው ፈፃሚዎች በአንድ እጃቸው ቆንጨራ፣ በሌላኛው ሬዲዮ ይዘው እንደነበር ሪፖርት ተደርጓል፡፡

በሩዋንዳ ጭፍጨፋ የነበረው ሬዲዮ ብቻ አልነበረም፡፡ ጋዜጣም የበኩሉን ተጫውቷል፡፡ ካንጉራ የተባለ ሳምንታዊ ጋዜጣ ‹የሁቱ ዐሥርቱ ትዕዛዛት› የተሰኘ ተወዳጅ ጋዜጣ ነበረው፡፡ ጋዜጣው በይፋ ሁቱዎች ከቱትሲዎች ጋር ምንም ወዳጅነት እንደሌላቸው አውጇል፡፡ ጠላት ናቸው በሚል ሚስቶች በባሎቻቸው፣ ጎረቤት በጎረቤቱ ላይ በዚህ የማንነት ጠላትነት ላይ ተመሥርተው እንዲነሱ አድርጓል፡፡

የሩዋንዳ ሚዲያዎች የጥላቻ ፕሮፓጋንዳ እና ዘመቻ ውጤቱ እልቂት ሆኗል፡፡ ሚዲያዎቹ ወደዘር ጭፍጨፋ የደረሱት በሦስት ደረጃዎች ነው፤ መንግሥት ሚዲያውን በተሳሳተ መንገድ ተጠቅሞበታል – በጥላቻ ፕሮፓጋንዳ ለዘር ጭፍጨፋ ማዘጋጃ አድርጎታል (1)፣ በጭፍጨፋው ወቅት አመፁን አቀጣጥሏል (2)፣ ከዚያም የጥፋቱ መጠን በትክክል ለሕዝብ እንዳይደርስ አድርጓል (3)፡፡

አሁን የሩዋንዳ መንግሥት ያንን መጥፎ ጠባሳ የጣለበትን ታሪክ ለማጥፋት በማሰብ የሁለቱንም ጎሳዎች ማንነት ክዷል፡፡ በሩዋንዳ አንዱ ሌላውን የእከሌ ጎሳ አባል ነው ብሎ በይፋ መናገር አይፈቀድለትም፡፡ ይህንን የዘር ጭፍጨፋን በማፈን ፈንታ ሐሳብን የመግለጽ ነጻነትን ያፈነ እርምጃ እንደሆነ አጥኚዎች ይከራከራሉ፡፡ (Yakaré-Oulé (Nani) Jansen, 2014) ለሩዋንዳ መንግሥት ግን ጉዳዩ ግራ አጋቢ ነው፡፡ ለሩዋንዳ መንግሥት ብቻ ሳይሆን ለብዙዎች ሌሎችን እስከ ማበሳጨት በሚደርሰው ሐሳብን የመግለጽ ነጻነት፣ በጥላቻ ንግግር እና በአመጽ ቅስቀሳ መካከል ያለውን ልዩነት መረዳት አስቸጋሪ ፈተና ይሆንባቸዋል፡፡

ኢትዮጵያም ጭምር የፈረመችው የሲቪል እና ፖለቲካዊ መብቶች ዓለምዐቀፍ ቃልኪዳን እንደሚለው “ማንኛውም ዓይነት በብሔር፣ ዘር፣ ወይም ሃይማኖት ላይ የተመሠረተ የማግለል፣ ጠላትነት ወይም አመጽ የሚያነሳሳ መልዕክት በሕግ መከልከል አለበት፡፡” ሆኖም አንድ ንግግር ወይም መልዕክት የጥላቻ ሊባል የሚችለው የትኛው ደረጃ ላይ ሲደርስ እንደሆነ መግባቢያ የለም፡፡

አስቀድመን ባየናቸው ምሳሌዎች የሚዲያ እና አመጽን ግንኙነት ስንመለከት፤ አበሳጭ የተባሉ ይዘቶችን ይዘው የወጡ የሕትመት ውጤቶች፣ አመጽ አልቀሰቀሱም፡፡ ይልቁንም የተቃውሞ አመጽ ተቀስቅሶባቸዋል፡፡ የሩዋንዳው የዘር ጭፍጨፋ ደግሞ በተቃራኒው አመጹ የተካሄደው በሚዲያዎቹ የጥላቻና ጥፋት ስብከት መሪነት ነው፡፡ በነዚህ ሁለት ምሳሌዎች መካከል ያለውን ልዩነት መረዳት ከባድ ላይሆን ይችላል፡፡ የአመጽ ቅስቀሳ ከመደረጉ በፊት ለመከላከል ያንን ዓይነት አዝማሚያ ያለውን የሚዲያ ተቋም ቀድሞ መቆጣጠር ግን ከባድ ይሆናል፡፡ የማይቻል ግን አይደለም፡፡ ይህንን የሚቻል-ከባድ የመንግሥት ሥራ ክፍተት የሚረዱ አምባገነኖች ሚዲያን (ወይም ሐሳብን የመግለጽ ነጻነትን) ለማፈኛ እንደምክንያት ይጠቀሙበታል፣ እየተጠቀሙበትም ነው፡፡

ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው መንግሥት በብሔር ላይ ያተኮሩ አንዱን የሚያጠለሹ፣ ሌላውን ተበዳይ የሚያደርጉ የቁርሾ ታሪኮችን እንዲያውም በበጎ ሲመለከታቸውና ሲታገሳቸው ይታያል፡፡ የገዢው ፓርቲ አመሠራረትም ሆነ አቋቋም የብሔር በዳይ-ተበዳይ ግንኙነትን አጠፋለሁ በሚል ሥም ስለሆነ እነዚህ ዓይነቶቹ ትረካዎች የተስማሙት ይመስላል፡፡ ነገር ግን መንግሥት ለእነዚህ አደገኛ አዝማሚያ ላላቸው ሐሳቦች/ጽሑፎች ያለውን ትዕግሥት ቅንጣት ታክል እንኳን ስርዓቱን ለሚተቹት የለውም፡፡ ይህም የሚያስገነዝበው መንግሥት ለሐሳብ ነጻነትም፣ ይሁን ሕዝቦች ላይ ለሚደርሰው አመጽ እንደማይጨነቅ፤ ይልቁንም ለሥልጣኑ ብቻ እንደሚሳሳ ነው፡፡ ሐሳብን በመግለጽ ነጻነት እና አመጽ በመቀስቀስ መካከል ያለው ልዩነት ጠርቶ በሕግና መመሪያ እንዲደነገግ የማይፈልገውም ለዚያው ነው፡፡

“ማንም ከብስጭት የመጠበቅ መብት የለውም፡፡ ይህ መብት እስከዛሬ ባነበብኳቸው ድንጋጌዎች ሁሉ ላይ የለም፡፡ ከተበሳጫችሁ፣ የራሳችሁ ችግር ነው፤ እንደእውነቱ ብዙ ነገሮች ብዙ ሰዎችን ያበሳጯቸዋል፡፡” ~ አሕመድ ሰልማን ሩሽዲ!

This article is published on Addis_Gets magazine, on Tahsas 3, 2008 issue. 

የሰማያዊ ፓርቲ የቀድሞ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ በዛሬው ዕለት መታሠራቸውን የፓርቲው ሊቀመንበር ኣቶ ይልቃል ጌትነት ኣስታወቁ። ኣቶ ይልቃል ጌትነት ይህንና ወቅታቂ ጉዳዮችን በተመለከተም በነገው ዕለት መግለጫ እንደሚሰጡ ተናግረዋል።ይህ ጉዳይ በተመለከተ ከቶ ይልቃል ጌትነት ጋር አጠር ያለ ቆይታ ያደረገችው ጽዮን ግርማ ነች ።

     የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ትራንስፖርት በመብራት መቆራረጥ አገልግሎቱ እየተደናቀፈ ሲሆን ተጠቃሚዎች ላይም እንግልት እየፈጠረ ነው ተባለ፡፡
ባለፈው ሣምንት ቅዳሜና እሁድ ለረዥም ሰአታት አገልግሎቱ ተቋርጦ እንደነበር የጠቀሱት ተገልጋዮች፤ ማክሰኞ ዕለትም ተመሳሳይ ችግር ማጋጠሙን ጠቁመዋል፡፡
መብራት ሲጠፋ ባቡሩ ለረዥም ሰዓት ቢቆምም ለምን እንደቆመ ገልፆ ሌላ የትራንስፖርት አማራጭ ተጠቀሙ የሚል አካል እንደሌለ ተገልጋዮች ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን በበኩሉ፤ የመብራት መቆራረጥ በአገልግሎቱ ላይ እንቅፋት እየሆነበት መምጣቱን ጠቁሞ ችግሩ በዚሁ የሚቀጥል ከሆነ ሌሎች አማራጮችን ለመጠቀም እያጠና እንደሆነ አስታውቋል፡፡
ከአዲስ አበባ ከተማ ውጭ ለብቻው ለባቡሩ የሃይል አቅርቦት መዘጋጀቱን ኮርፖሬሽኑ ጠቁሞ፤ የሃይል መቋረጡ እያጋጠመ ያለው ከምንጩ ነው ብሏል፡፡
ህብረተሰቡ በከፍተኛ መጠን የባቡር ተጠቃሚ እየሆነ በመጣበት ሰዓት በሃይል መቋረጥ አገልግሎት መስተጓጐሉ አግባብ አለመሆኑን የተናገሩት የኮርፖሬሽኑ የህዝብ ግንኙነት ምክትል ሃላፊ፤ ችግሩ ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት የተከሰተ በመሆኑ መፍትሔ እስኪገኝ ህብረተሰቡ  አገልግሎቱን በትዕግስት እንዲጠቀም ጠይቀዋል፡፡

ኦፌኮ ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ ከ500 በላይ አባላት ታስረውብኛል አለ

• “ግጭቱን ተከትሎ እስከ 4ሺ ሰዎች ታስረዋል” ፓርቲው
• “በፓርቲ ሽፋን የሻዕቢያን ተልዕኮ ለማሳካት በተሯሯጡት ላይ እርምጃ ይወሰዳል” – ጠ/ሚ ኃይለማርያም

የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ በቀለ ገርባና 6 ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ ከ500 በላይ አባላት ሰሞኑን እንደታሠሩበት ፓርቲው ገለፀ፡፡ የኦፌኮ ዋና ፀሐፊ አቶ በቀለ ነጋ ለአዲስ አድማስ እንደተናገሩት፤ ጉርሜሣ አያኖ የፓርቲው ም/ሊቀመንበር፣ አዲሱ ቡላላ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ፣ ደረጀ መርጋ የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ፣ መ/ር አለሙ አብዲሳ ፀሐፊ፣ መ/ር ታሪኩ ኦዲተር፣  አቶ ደጀኔ ጣፋ ም/ዋና ፀሐፊ እንዲሁም አቶ በቀለ ገርባ ተቀዳሚ ም/ሊቀመንበር ሰሞኑን በፖሊስ ተይዘው ታስረዋል፡፡
ከፓርቲው አማካሪ ም/ቤት አባላት መካከልም የታሠሩ እንዳሉ የገለፁት ዋና ፀሐፊው፤ ከዞን አመራሮች የቄለም ወለጋ ዞን አመራር አቶ መሠረት ዳባ፣ የምስራቅ አርሲ ዶዶላ አመራር አህመድ ኢቦ፣ የባሌ አመራር አቶ ሁሴን አምዳ፣ የሆሮ ጉዱሩ አቶ ደገባስ ዋቀዩ፣ የኢሊባቡር አመራር አቶ እስማኤል ሁሴንና አቶ ያዛቸው አብዲሣ ታስረዋል ብለዋል፡፡
የወረዳ አመራሮችና ባለፈው ግንቦት በምርጫ የተሳተፉ ግለሰቦችን ጨምሮ እስከ 500 የሚደርሱ የፓርቲው አባላት በተለያዩ አካባቢዎች መታሠራቸውን አቶ በቀለ ገልፀው፤ ፓርቲው ባለው መረጃ መሰረት በአጠቃላይ ተቃውሞውን ተከትሎ የታሠረው ሰው ብዛት እስከ 4ሺ ይደርሳል ብለዋል፡፡
ከ300 በላይ የደረሱበት ያልታወቁ ሰዎች እንዳሉ የተናገሩት ዋና ፀሐፊው፤ በግጭቱ የቆሰሉ ከ1500 በላይ ተጎጂዎች በወሊሶ ሉቃስ ሆስፒታል፣ በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል፣ በሚኒልክና በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ህክምናቸውን እየተከታተሉ እንደሚገኙ ገልፀዋል፡፡
የፓርቲው አመራሮችና አባላት የታሠሩበት ምክንያት ባይገለጽም በሌላ በኩል ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ትናንት በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ባደረጉት ገለፃ “የራሳቸውን ድብቅ አጀንዳን ይዘው የሃሰት ፕሮፖጋንዳ በማሠራጨት ህዝብን በማደናገር የሰው ህይወት እንዲጠፋ አቅደው የመሩ አካላት በህጋዊ ፓርቲ ሽፋን የሻዕቢያን ተልዕኮ የማሳካት በተሯሯጡ ሃይሎች ላይ መንግስት ህገመንግስታዊ እርምጃ ይወስዳል ብለዋል፡፡

በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በተመሠረተባቸው ክስ ምክንያት በእስር ላይ የሚገኙት የትድሀር ኤክስካቬሺን ኤንድ ኧርዝ ሙቪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ዋና ሥራ አስኪያጅ እስራኤላዊው ሚናሼ ሌቭ ዮሴፍ፣ በሌላ የውጭ አገር እስረኛ ተደብድበው ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ተጠቆመ፡፡ ሚስተር ዮሴፍ በእስር ላይ በሚገኙበት በአዲስ አበባ ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር እስር ቤት ውስጥ ታኅሳስ 13 ቀን 2008 ዓ.ም. ጉዳት የደረሰባቸው፣ የሱዳን […]

ከአዲስ አበባ ማስተር ፕላንና ከኦሮሚያ ከተሞች ዐዋጅ ጋር ተያይዞ ኦሮሚያ ውስጥ በተነሣው ተቃውሞና ግጭት የብዙ ሰው ሕይወት መጥፋቱና ከ3500 ሰው በላይ መታሠሩን ኦ.ፌ.ኮ አስታወቀ፡፡ከአምስት ወራት በፊት የተፈቱት የቀድሞ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ዋና ጸሐፊ አቶ በቀለ ገርባም መታሠራቸው ታውቋል፡፡

ከህዝብ ተቃውሞ ጋር በተያያዘ ድርጅቱ ውስጥ ብዙ መከፋፈል እንደተፈጠረ ከዛው ከድርጅቱ ኣባሎች ሚስጥር ማፈትለክ ጀምሯል። 1፡በስርቆትና በወገን ባብሮ ኣደግ ጠ/ሚ ከዚ በፊት በይፋ ባይሆንም ስብሰባን ኣግጣሚ ኣድርጎ የተናገራቸው ትግራይን ጨምሮ መላ ሃገሪትዋ ላይ ብልሽውና ላይ የተዘፈቁ ሌባነታቸውን ለመሸፋፈንና ስማቸውን ለማደስ በኦህዴድ ኣባላት ላይ ዘምተዋል። ይህም ኣልበቃ ብሏቸው መከላከያና ፖሊስ ውስጥ ብዙ ወሳኝ ባይሆንም ኣደጋ ሊጥሉ […]

ታኀሳስ ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከክረምቱ መግባት ጀምሮ በከተማዋ በተደጋጋሚ የሚታየው የመብራት መቆራረጥ ነዋሪውን ያስመረረ ሲሆን፣ በአስቸኳይ ጥገና መስክ የተሰማሩት ሰራተኞች የሚጠቀሙበት መኪና ከአስርት አመታት በፊት የነበረ አሮጌ ከመሆኑም በላይ በቁጥርም አንድ ብቻ መሆኑ ስራውን እንዳወሳሰበው ባለሙያዎቹ ተናግረዋል፡፡ የደንበኞች ቁጥር እየበዛ በሄደ ቁጥር ያሉት ገመዶች የኤሌክትሪክ ኃይሉን መሸከም ባለመቻላቸው መቀየር ሲገባቸው …