ከድርቁ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያና የኬንያ አዋሳኝ ከተማ በሆነችው ሞያሌ ከተማ፣ የአተት ወረርሽኝ ተከስቶ የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ ወደ 90 ገደማ የሚሆኑ በበሽታው ተይዘው ህክምና እየተደረገላቸው መሆኑን የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ለአዲስ አድማስ አስታውቋል፡፡
በከተማው በአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት (አተት) ተይዘው በጤና ተቋማት የታከሙት 91 ያህል ሲሆኑ 71 ህክምናቸውን ተከታትለው ወደ ቤታቸው ሲመለሱ፣ 18 ደግሞ እስከ ትናንት በስቲያ ድረስ ህክምና ሲወስዱ ነበር ተብሏል፡፡
እስከ ትላንት በስቲያ ወረርሽኙ ከሞያሌ ከተማ እንዳይወጣ የህክምና ርብርብ እየተደረገ እንደነበር የጠቆሙት በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊው አቶ አህመድ አማኖ፤ ከተማዋ የንግድ ከተማ እንደመሆኗ የተጠቂዎች ቁጥር ሊቀንስም ሊጨምርም የሚችልበት ሁኔታ እንዳለ ገልፀው ጤና ጥበቃ የበሽታውን ስርጭት ለመቆጣጠር ሰፊ ርብርብ እያደረገ መሆኑን ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡
በድርቁ ምክንያት የውሃ እጥረት መከሰቱን ተከትሎ የንፅህና ጉድለት ስለሚፈጠር በቫይረስና በባክቴሪያ የሚፈጠሩ በሽታዎች በድርቁ ተጎጂ አካባቢዎች ሊቀሰቀሱ እንደሚችሉ የጠቀሱት አቶ አህመድ፤ እስካሁን መሰል ችግር ከሌሎች የድርቅ ተጎጂ አካባቢዎች ሪፖርት አለመደረጉንና መንግስት የሚከሰቱ ወረርሽኞችን ለመከላከል በዘረጋው የጤና ኤክስቴንሽን መርሃ ግብር ፕሮግራሙ ለመቆጣጠር እንቅስቃሴ እያደረጉ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
የዓለም የጤና ድርጅት ሰሞኑን ባወጣው ሪፖርቱ፤ በተለይ ወቅቱን ባልጠበቀ ዝናብ የሚፈጠር ጎርፍ በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ውሃ ወለድ በሽታዎችን ሊያስከትል እንደሚችል ጠቁሞ ድርጅቱ ችግሩን ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በጋራ ለመቋቋም ባለሙያዎችን ወደ ኢትዮጵያ ልኮ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን አስታውቋል፡፡
ከድርቁ ጋር ተያይዞም ከ400 ሺህ በላይ ህፃናትና ከ700 ሺህ በላይ እናቶች የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኙ በማድረግ ለወረርሽኝ ያላቸውን ተጋላጭነት መቀነስ እንደሚገባም የዓለም ጤና ድርጅት አሳስቧል፡፡ በተለይ ህፃናት የተመጣጠነ ምግብ ካላገኙና የጤና ክትትል ካልተደረገላቸው አደጋው የከፋ ይሆናል ያለው ድርጅቱ፤ አሁን ባለው ሁኔታ የተቀናጀ የጤና አገልግሎት ለማቅረብ ሀገሪቱ በቂ አቅም የላትም ብሏል በሪፖርቱ፡፡ ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ችግሩን ለመፍታት ጥረት እያደረገ ነው ያለው ይኸው ሪፖርት፤ የተለያዩ የአለማቀፍ ድርቶችን ድጋፍ እንደሚሻም አስታውቋል፡፡
በአጠቃላይ ድርቁና የኢሊኖ ክስተት ባስከተለው ችግር ምክንያት የሚፈጠርን የጤና መታወክ ለመከላከል 8 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ ተጠቅሷል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ለጉዳዩ የበለጠ ትኩረት እንዲሰጥም የዓለም ጤና ድርጅት አሳስቧል።
ሰሞኑን መንግሥትና የአለማቀፍ ተቋማት የድርቁን ሁኔታ አስመልክቶ ባቀረቡት የዳሰሳዊ ቅኝት ሪፖርት፤ የድርቅ ተጎጂዎች 10.2 ሚሊዮን መድረሳቸው እስከ ቀጣይ አመት ለሚቆየው የድርቅ አደጋ መቋቋሚያም ወደ 30 ቢሊዮን ብር ገደማ በጀት እንደሚያስፈልግ የታወቀ ሲሆን 1.9 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን እህልም ያስፈልጋል ተብሏል፡፡
ድርቁ 189 ወረዳዎችን ክፉኛ የጎዳ ሲሆን በ89 ወረዳዎች ደግሞ መለስተኛ ጉዳት ማድረሱ ተገልጿል፡፡

ታኀሳስ ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ገዢው ፓርቲ ሆን ብሎ እንደቀሰቀሰው በሚነገረው ግጭት ከትናንት ጀምሮ ከ10 በላይ ሰዎች የተገደሉ ሲሆን፣ የጎንደር መተማ መንገድ በመዘጋት የትራንስፖርት አገልግሎት ተቋርጧል። የመንግስት ካድሬዎች በቅማንትና አማራ መካከል ግጭት እንዲነሳ ለማድረግ ሰሞኑን ካድሬዎቹ መሳሪያ ታጥቀው ሰላማዊ ሰልፍ እንዲያደርጉ ተፈቅዶላቸው ነበር። ምንም እንኳ ህገመንግስቱ የጦር መሳሪያ ታጥቆ ሰላማዊ ሰልፍ …

• 10.12 ሚሊዮን ለረሃብ አደጋ የተጋለጡ ተረጂዎች
• 7.9 ሚሊዮን ከጥር እስከ ሰኔ ድረስ ድጋፍ የሚሹ ችግረኞች

   በድርቅ ሳቢያ ለረሃብ የተጋለጡ ኢትዮጵያዊያን ከአስር ሚሊዮን በላይ እንደሆነ በመጥቀስ በይፋ የእርዳታ ጥሪ የቀረበ ሲሆን፤ የተረጂዎች ጠቅላላ ቁጥር 18 ሚሊዮን እንደደረሰ ተገለፀ፡፡
የድርቁ አደጋ ከባድ መሆኑን በመግለጽ ለቀረበው የእርዳታ ጥሪ ፈጣን ምላሽ እንደሚያስፈልግ የተናገሩት የእንግሊዝ የውጭ ተራድኦ ሚኒስትር፤ በምግብ ዋስትና ፕሮግራም ድጋፍ የሚያገኙት 7.9 ሚሊዮን ሰዎችን ጨምሮ የተረጂዎቹ ቁጥር 18 ሚሊዮን ሆኗል ብለዋል፡፡  
በድርቁ ተጎጂ የሆኑ ዜጎች በጥር ወር ወደ 10.2 ሚሊዮን እንደሚያሻቅብ መንግስት ይፋ ያደረገ ሲሆን ለመጀመሪያው ዙር እርዳታ 516 ሺህ ሜትሪክ ቶን የምግብ እርዳታ ያስፈልገኛል ብሏል፡፡ መንግስት ለለጋሽ ሀገራትና ተቋማት የእርዳታ ጥሪ በይፋ አቅርቧል፡፡
ለምግብ ግዢ ብቻ 1.1 ቢሊየን ዶላር እንደሚያስፈልገው የጠቀሰው መንግስት፤ አጠቃላይ የድርቁን ችግር ለመቋቋም ከ1.4 ቢሊየን ዶላር በላይ ገንዘብ እንደሚያስፈልገው አስታውቋል፡፡
በትግራይ የድርቁ ተጎጂዎች 1.2 ሚሊዮን፣ በአማራ ክልል 2.3 ሚሊዮን፣ በአፋር 409,200፣ በኦሮሚያ 3.8 ሚሊዮን፣ በደቡብ ክልል 668,900፣ በሱማሌ 1.5 ሚሊዮን፣ በድሬደዋና በሐረሪ በድምሩ ከ80 ሺህ በላይ፣ በጋምቤላ 37 ሺህ 450 እንዲሁም በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል 83,476 መሆናቸውን የመንግሥት ሪፖርት አመልክቷል፡፡
ለድርቁ የውጭ ሀገራት ለጋሽ ድርጅቶችና ተቋማት ድጋፍ እንዲቸሩት በትናንትናው እለት መንግስት ጥሪ ያቀረበ ሲሆን ከ50 በላይ ለሚሆኑ ዲፕሎማቶችና አለማቀፍ ለጋሽ ተቋማት ስለድርቁ ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡
ከድርቁ ጋር በተያያዘ ከ400 ሺህ በላይ ህፃናት አስቸኳይ አልሚ ምግብ ይፈልጋሉ ያለው መንግሥት፤ 3.6 ሚሊዮን ዜጎች ደግሞ ድርቅ አምጪ በሆኑ የተለያዩ በሽታዎች ሊጠቁ እንደሚችል ሪፖርት አድርጓል፡፡  ድርቁ በአጠቃላይ 429 ወረዳዎች የተከሰተ ሲሆን 286 ሺህ 400 ሰዎችን ሊያፈናቅል ይችላል ተብሏል፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

የኦሮምያ ክልል መንግሥት እቅዱ በአዲስ አባባ ከተማ አካባቢ ያሉ የኦሮምያ ልዩ ዞን ከተሞችን ለማሳደግ መሰረተ ልማትን ለማስፋፋትና ከተሞቹንም ዘመናዊ ለማድረግ የታሰበ እቅድ እንጂ የህዝቡን ጥቅሞች አሳልፎ ለመስጠት ያለመ አይደለም ፣ተቃውሞውም የተሳሳተ መረጃን መሠረት ያደረገ ነው ሲል ይከራከራል ።

ከፍተኛ አካላዊ ድካም እና የሰውነት መዛል ታይቶባቸዋል የበዓታ ለማርያምን በዓል በዲሲ መድኃኔዓለም ያከብራሉ (ሰንደቅ፤ ረቡዕ፤ ኅዳር ፳፱ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም.) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፣ ለከፍተኛ ሕክምና ወደ አሜሪካ ማምራታቸውን የመንበረ ፓትርያርኩ ምንጮች ገለጹ። ከትላንት በስቲያ፣ ሰኞ ማምሻውን ከምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ እና ሌላ ረዳታቸው ጋር …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ኀዳር ፴ (ሠላሳ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በወሊሶ ላለፉት አምስት ቀናት ሲካሄድ የነበረው ተቃውሞ ተጠናከሮ የቀጠለ ሲሆን፣ ከሰአት በሁዋላ የፌደራል ፖሊስ አባላት እርምጃ መውሰድ ጀምረዋል። በሰላማዊ ዜጎች ላይ በቀጥታ በመተኮስ በርካታ ቁጥር ያላቸው ነዋሪዎች ቆስለው ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል። እስካሁን አንድ ሰው መሞቱን ለማወቅ ቢቻልም፣ በሞትና በህይወት መካከል ያሉ በርካታ ወጣቶችና አዛውንቶች ሳይቀር መኖራቸው …

ኀዳር ፴ (ሠላሳ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ታማኝ የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት በሰሜን ጎንደር መተማ ወረዳ ገዢው ፓርቲ ከተለያዩ አካባቢዎች አሰባስቦ መሳሪያ ያስታጠቃቸው ሰዎች አማራና ቅማንት በሚል ከፋፍሎ ግጭት ማስነሳቱን ተከትሎ ከባድ ጉዳት ደርሷል። ግጭቱ ሆን ተብሎ የተቀነባበረ ነው የሚሉት ምንጮች፣ ግጭቱ ወደ ጭልጋና አጎራባች ቀበሌዎች መዛመቱም ታውቋል። ግጭቱ በሽንፋና በኩመር አካባቢዎቸ ደም አፋሳሽ …

Students killed by federal police. የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተገደሉ፣ ተደበደቡአንተነህ መርዕድ

የመጀመሪያው የኬንያ ፕሬዝደንትና የነፃነት ታጋይ ጆሞ ኬንያታ ብዙ ጊዜ የሚጠቀስላቸው፣ ስለቅኝ ገዥዎች የተናገሩት እውነት ይህን ይመስል ነበር። “ሚሲዮኖች ወደ አፍሪካ ሲመጡ እነሱ መጽሐፍ ቅዱስ፤ እኛ ደግሞ መሬት ነበረን። ዐይናችንን ጨፍነን እንዴት እንደምንጸልይ አስተማሩን። ዐይናችንን ስንገልጠው ግን እነሱ መሬታችንን እኛ መጽሐፍ ቅዱሱን ታቅፈናል” አሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ሩት አማኑኤል

ተደጋግሞ የሚነገር አንድ ጉዳይ አለ። ዴሞክራሲ ሒደት ነው፤ መልካም አስተዳደር በሒደት የሚመጣ ነገር ነው፤ የዴሞክራሲ ተቋማትን መገንባት ሒደት ነው ወዘተ. ይባላል። ለጽሑፌ መነሻ የሆነኝ የጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ንግግር ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

በአዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል ውስጥ መብራት ለሀያ ሰዓታት ያህል በመቋረጡ ምክንያት በፅኑ ህክምና ክፍል (ICU) ውስጥ የነበሩ ሦስት ህሙማን ለሞት ተዳረጉ፡፡ ህዳር 20 ምሽት ላይ ለ20 ሰዓታት መብራት ተቋርጦ በመቆየቱና የሆስፒታሉ ጀነሬተር ተበላሽቶ በመቀመጡ የተነሳ በፅኑ ህክምና ክፍል የነበሩ አንዲት ወላድ እናትና ሁለት ሌሎች ህሙማን ህይወታቸው እንዳለፈ ምንጮች ገልፀዋል፡፡ ከይርጋለም ከተማ ወደ ሆስፒታሉ ሪፈር ተደርጋ […]

የሲሚንቶ ገበያ ተቀዛቀዘ

-የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ለሲሚንቶ ፋብሪካዎች ፈተና መሆኑ ተነገረ

በኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ እየተፈተነ የሚገኘው የሲሚንቶ ኢንዱስትሪ የገበያ መቀዛቀዝ አሳየ፡፡ አገር ውስጥ የሚገኙ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ዓመታዊ የማምረት አቅማቸው 13 ሚሊዮን ኩንታል ቢሆንም፣ ሽያጩ ግን ከሰባት ሚሊዮን ኩንታል ያልበለጠ መሆኑ ታውቋል፡፡ 

 

ከገበያ መቀዛቀዝ ባሻገር የመንግሥት የልማት ድርጅት የሆነው ሙገር ሲሚንቶ፣ ሰሞኑን አንድ ኩንታል ፒፒሲ ሲሚንቶ የሚሸጥበትን ዋጋ ከ210 ብር ወደ 190 ብር አውርዶታል፡፡ 

በኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥና ከቀትር በኋላ 11፡00 ሰዓት እስከ ምሽት 4፡00 ሰዓት ድረስ ኃይል እንዳይጠቀሙ በመንግሥት ትዕዛዝ በመሰጠቱ የገበያ መቀዛቀዝ መፈጠሩ የተነገረ ሲሆን፣ የተለያዩ ሲሚንቶ ፋብሪካዎችም ሥራ እያቆሙ ነው፡፡ 

ሥራ ካቆሙ ፋብሪካዎች ውስጥ ሲኤች ክሊንከር፣ ሁዎንግሽን ሲሚንቶና ኢስት ሲሚንቶ ይገኙበታል፡፡ የኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ተጠባባቂ ዋና ዳይሬክተር አቶ መኮንን ዘርጋው ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ ለሲሚንቶ ፋብሪካዎች ትልቁ ፈተና ሆኗል፡፡ 

የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ከአንድ ሺሕ ዲግሪ ሴንቲ ግሬድ በላይ ሙቀት ስለሚፈልጉ፣ ይህ ሙቀት ከተፈጠረ በኋላ ኃይል ሲቋረጥ በርካታ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች ለብልሽት እንደሚዳረጉ፣ እንደገና ኃይል ሲመጣ ደግሞ ፋብሪካዎቹን ወደ ሥራ ለመመለስ አስቸጋሪ እንደሆነ አቶ መኮንን ገልጸዋል፡፡ 

የገበያውን መቀዛቀዝ በተመለከተ ሁሌም በክረምት ወራትና ክረምት ከወጣ በኋላ ለተወሰኑ ወራት የሲሚንቶ ገበያ መቀዛቀዙ የተለመደ እንደሆነና ከመብራት ጋር እንደማይገናኝ ገልጸዋል፡፡ ይሁንና በዚህ ሐሳብ የማይስማሙ አሉ፡፡ 

ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ የአንድ ሲሚንቶ ፋብሪካ ሥራ አስኪያጅ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ መንግሥት በአንድ ጊዜ በርካታ ፕሮጀክቶችን ያስጀመረ በመሆኑ፣ ለሚያሠራው ሥራ ክፍያ ለመፈጸም እየተቸገረ ነው፡፡ 

መንግሥት የበጀት እጥረት ስላለበት መንግሥት ክፍያ እየፈጸመ ባለመሆኑ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው በመቀዛቀዙ የሲሚንቶ ገበያውም ሊቀዛቀዝ እንደቻለ አመልክተዋል፡፡ ባለፉት በርካታ ዓመታት የዋጋ ንረት ሲያጋጥመው የቆየው የሲሚንቶ ገበያ፣ በአሁኑ ጊዜ መቀዛቀዝ ስለታየበት፣ ሁሉም የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ከ190 ብር እስከ 210 ብር ድረስ ባለው ዋጋ በመሸጥ ላይ መሆናቸው ታውቋል፡፡ ቀደም ባሉት ጊዜያት ሲሚንቶ ገበያው ውስጥ በኩንታል እስከ 400 ብር ይሸጥ ነበር፡፡ 

አቶ መኮንን ሙገር የሲሚንቶ ዋጋ ሊቀነስ ከቻለባቸው ምክንያቶች አንዱ ሲጠቀም የቆየውን ጥቁር ናፍጣ ትቶ፣ በድንጋይ ከሰል እንዲጠቀም በመወሰኑ ነው ብለዋል፡፡ 

በ15 ቀናት ውስጥ በድንጋይ ከሰል መጠቀም እንደሚጀምር የተናገሩት አቶ መኮንን፣ ከጥቁር ናፍጣ ይልቅ የድንጋይ ከሰል ርካሽ በመሆኑ ሙገር ዋጋ ለመቀነሱ አንዱ ምክንያት መሆኑን አስረድተዋል፡፡ 

 

ዛሬ (Dec. 7) ፕሮግራማችን ባለመደመጡ ይቅርታ እንጠይቃለን። በዚህ እለት 44ቱም የአሜሪካ ድምፅ ራድዮና ቴሊቪዥን እንዲሁም በኢንተርነት የሚሰራጩ ፕሮግራሞች ያልተደመጡበት ምክንያት በሕንፃው የኤሌትሪክ ሓይል ሥርጭት በመግጠሙ መሆኑን በትህትና እንገልጻለን። ፕሮግራማችን በነገው እለት ይደመጣል።

የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅና የግዢና ንብረት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር በአሥር ሚሊዮን ብር ሙስና ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ታወቀ፡፡

ዋና ሥራ አስኪያጁ አቶ ኤፍሬም ደሳለኝና የግዥና ንብረት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ንጉሤ ታደሰ በቁጥጥር ሥር የዋሉት፣ ኅዳር 21 ቀን 2008 ዓ.ም. በፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን መርማሪ ቡድን ሲሆን፣ ኅዳር 22 ቀን 2008 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡ 

ተጠርጣሪዎቹ በድርጅቱ በከፍተኛ ኃላፊነት ላይ ተመድበው ሲሠሩ የመንግሥትንና የሕዝብን ጥቅም ማስጠበቅ ሲገባቸው፣ አቶ ገብረ አምላክ በርሄ ከሚባሉ ግለሰብ ጋር በመመሳጠር ግምቱ 8,974,000 ብር የሆነ የመንግሥት ንብረት (ምንነቱ አልተገለጸም) አውጥተው በመሸጥ ለግል ጥቅማቸው ማዋላቸውን፣ መርማሪ ፖሊስ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሁለተኛ ወንጀል ችሎት አስረድቷል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በተጨማሪ ያለምንም ስምምነትና ውል ከ1.9 ሚሊዮን ብር በላይ ከድርጅቱ ካዝና በማውጣት ለልኳንዳ ነጋዴዎች እንዲከፈል በማድረጋቸው፣ ሥልጣናቸውን ያላግባብ በመገልገል የሙስና ወንጀል መጠርጠራቸውን መርማሪ ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡ በመሆኑም መርማሪ ፖሊስ ለተጨማሪ ምርመራ 14 ቀናት እንዲፈቀድለት ጠይቆ ተፈቅዶለታል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ እንዲፈቀድላቸው ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄም ታልፏል፡፡ 

 

ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም

• ችጋር ምንድን ነው? ሰፊ ቦታንና ብዙ ሕዝብን የሚሸፍን፣ ለረጅም ጊዜ የሚቆይ፣ ምንም የሚላስ የሚቀመስ ጠፍቶ እንስሳት (ሰውንም ጨምሮ) ዕለት በዕለት የራሳቸውን አካል እስኪያልቅ ድረስ “እየበሉ” በመጨረሻም የሚሞቱበት ሁኔታ ነው፤ ረሀብ አካል ሲዳከም አካልን ለመገንባት የሚደረግ ጥሪ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Vacance ማስታወቂያጌቱ ኃይሉ

አቶ ዠ ደብዳቤ ጻፉ። 40 ዓመት ሙሉ መፈክር ሲጽፉ ኖረው፣ ኖረው፣ ኖረው አሁን አርቲስት ለመሆን የሚያበቃውን ዝግጅት የጨረሱ መስሎ ተሰማቸው። ሰሞኑን ለወጣው ማስታወቂያ “ብቁ ነኝ” ብለው አሰቡ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

PM Hailemariam Desalegn. ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝሩት አማኑኤል

ሕዝብ አዋቂ ነው። የፖለቲካ ሶሲዮሎጂስቷ ቴዳ ስኮፖል በሚያሳምን ሁኔታ እንደገለጸችውና በአገራችን በተግባር እንደሚታየው ሕዝብ ዝም ቢልም አፈናን ተቀብሏል ማለት አይደለም። በአፈና ውስጥ ያለ ሕዝብ ዝም ሲል እንድም ብናገርም ለውጥ አላመጣም ማለቱ ነው፤ አንድም ማኩረፉንና መከፋቱን መግለጹ ነው፤ አንድም የተመቻቸ ጊዜ እስኪያገኝ ድረስ አድብቶ መጠበቁ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Prof. Mesfin Woldemariam ፕ/ር መስፍን ወልደማርያምፕ/ር መስፍን ወልደማርያም

በፌስቡክ የምንሰባሰበው ለመወያየት፣ አንዱ ከሌላው እንዲማር፣ መረጃዎችን በነጻነት እንድንለዋወጥ፣ ይህንን ሁሉ በማድረግ ራሳችንን ለማሻሻል፣ የእኛ መሻሻል እየተራባና እየተባዛ የአገርና የሕዝብ መሻሻል እንዲሆን፣ ከተቻለንም ከአገራችንና ከሕዝባችን አልፈን የምንታይ የዓለም አካል እንድንሆን መስሎኝ ነበር፤ ሳየው በዚያ መንገድ ላይ ያለንና ፌስቡክን ለበጎ ዓላማ እየተጠቀምንበት ያለን አይመስለኝም፤ ስለዚህ ወይ መታረም፣ አለዚያም በፌስቢክ ጊዜ ማጥፋቱን መተው ምርጫ ሊሆንብን ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Ethiopia and the World Bank of Lies, Damned Lies and Statislies, by Prof. Almariamፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ)

ጆን ሚልተን ገነትን ማጣት/Paradise Lost በሚለው መጽሀፋቸው “የቱም ዓይነት ቅጥፈት ቢሆን ዘለቄታዊነት የለውም የሰማይ ቁጣንም ይስባል።” በማለት ጽፈዋል። በእርግጥ ሚልተን ሊጨበጥ ሊዳሰስ ስለማይችለው ባዶ ምናብ ስለሚፈጥረው ስለሰይጣን እና ስለዕኩይ ምግባሩ ነበር የጻፉት።

ሙሉውን አስነብበኝ …

በማረሚያ ቤት አለመኖራቸው በተገለጸው አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የቀረበው ይግባኝ ውድቅ ተደረገ

በሽብር ድርጊት ወንጀል ተጠርጥረው ክስ ተመሥርቶባቸው ማረሚያ ቤት በሚገኙት በእነ ዘመኑ ካሴ የክስ መዝገብ በመከላከያ ምስክርነት በተቆጠሩት የግንቦት ሰባት አመራር የነበሩት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ፣

በመከላከያ ምስክርነት እንዳይቀርቡ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ቀርቦ የነበረው ይግባኝ ኅዳር 23 ቀን 2008 ዓ.ም. ውድቅ ተደረገ፡፡

ተከሳሾቹ ከተመሠረተባቸው ክስ አንዱ የግንቦት ሰባት አመራር ከነበሩትና ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም. ከየመን ወደ አስመራ ሊሄዱ ሲሉ ከሰንዓ አውሮፕላን ማረፊያ ተይዘው ወደ ኢትዮጵያ ተላልፈው ከተሰጡት አቶ አንዳርጋቸው ጋር ተገናኝተው መመርያ መቀበላቸውን የሚመለከት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በመሆኑም አቶ አንዳርጋቸው በፌዴራል ማረሚያ ቤት ስለሚገኙ በመከላከያ ምስክርነት እንዲቀርቡ ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው፣ ክሱን እየመረመረ ለሚገኘው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት አመልክተው ፍርድ ቤቱም ተቀብሏቸዋል፡፡

የተከሳሾቹን አቤቱታ በመቃወም ለፍርድ ቤቱ ያመለከተው ከሳሽ ዓቃቤ ሕግ፣ አቶ አንዳርጋቸው በእነ ብርጋዴር ጄኔራል ተፈራ ማሞ የክስ መዝገብና በእነ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የክስ መዝገብ የዕድሜ ልክና ሞት ፍርደኛ መሆናቸውን በመጥቀስ፣ ምስክርነት ለመስጠት እንደማይችሉና መብታቸው የተገፈፈ መሆኑን አስረድቶ ተቃውሞ ነበር፡፡ ነገር ግን ፍርድ ቤቱ በሰጠው ብይን አቶ አንዳርጋቸው መብታቸው የተገፈፈው ስለራሳቸው እንጂ ስለሌሎች ምስክርነት መስጠት ስላልሆነ ሊመሰክሩ እንደሚገባ ገልጾ፣ የዓቃቤ ሕግን ማመልከቻ ውድቅ በማድረግ ቀርበው እንዲሰሙ ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር፡፡

አቶ አንዳርጋቸውን በመከላከያ ምስክርነት እንዲያቀርብ የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ታዞ የተለያዩ ምክንያቶችን በመስጠት ሳያቀርባቸው ቢቆይም፣ ጥቅምት 12 ቀን 2008 ዓ.ም. ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው ደብዳቤ ግን ‹‹አቶ አንዳርጋቸው ማረሚያ ቤት የሉም፤›› ብሎ መግለጹ ይታወሳል፡፡

ተከሳሾቹ የማረሚያ ቤቱን ምላሽ በመቃወም አቶ አንዳርጋቸው አገር ውስጥ መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የፀረ ሽብር ግብረ ኃይሉና በኢትዮጵያ የእንግሊዝ አምባሳደር እንደሚያውቁ በመጠቆም፣ ለእነሱ ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ፍርድ ቤቱን ጠይቀው ነበር፡፡ ፍርድ ቤቱ ተመካክሮ እንደሚያሳውቃቸው ገልጾ በቀጠሮ ላይ እንዳሉ፣ ከሳሽ ዓቃቤ ሕግ አቶ አንዳርጋቸው በመከላከያ ምስክርነት ሊቀርቡ እንደማይገባ ለሥር ፍርድ ቤት ያመለከተበትን ምክንያት ጠቅሶ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ አቅርቦ ነበር፡፡ ፍርድ ቤቱ መርምሮ በሰጠው ብይን በፍርድ ቤት እንዲቀርብ የታዘዘ ምስክር ‹‹ይቅረብ አይቅረብ›› ተብሎ ይግባኝ ሊባል እንደማይቻል በመግለጽ፣ የዓቃቤ ሕግን ይግባኝ እንዳልተቀበለው አስታውቋል፡፡ 
የጠቅላይ ፍርድ ቤትን ውሳኔ የተቃወመው ዓቃቤ ሕግ፣ መሠረታዊ የሕግ ጥሰት መፈጸሙን በመጥቀስ ለሰበር ሰሚ ችሎት ማመልከቻ ማቅረቡን ምንጮች ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡  

Prof. Getatchew Haile ፕ/ር ጌታቸው ኃይሌፕ/ር ጌታቸው ኃይሌ

መግቢያ፤

መጀመሪያ ለመግቢያ ያህል፥ “ዘመድ” የሚለውን ቃል እንዴትና ለምን እንደተጠቀምኩበት ላስረዳ። “ዘመድ” ማለት “ወገን” ማለት ነው። በእንግሊዝኛ “kin, family, tribe” ማለት ነው። በየሊቃቸው የሚመሩ የተለያዩ የመላእክት ሠራዊት “ዘመድ” ወይም “ነገድ” ነው የሚባሉት”–ዘመደ መላእክት፣ ነገደ መላእክት። ሌሎች ተመሳሳይ ትርጉም ያላቸው መጠሪያዎች “ቤት” (ቤተ አምሐራ)፣ “ጎሳ” (የጉጂ ጎሳ)፣ “ዘር” ናቸው። ዛሬ ደግሞ “ብሔረ ሰብ” የሚለው መጠሪያ ነግሧል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ሰሞኑን በአዲስ አበባ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደንበኞች በኤቲኤም ማሽን ገንዘብ ማውጣት ባለመቻላቸው፣ በአጭር የመልዕክት ጽሑፍ ገንዘብ ማውጣታቸውን በሚገልጸው መልዕክት ከፍተኛ መደናገጥ እየተፈጠረባቸው ነው፡፡

ባንኩ በበኩሉ በጊዜያዊ ገንዘብ ዝውውር የኔትወርክ ችግር ያጋጠመ ቢሆንም፣ የገንዘብ ኪሳራ እንደማይገጥማቸው ገልጿል፡፡

በከተማዋ የተለያዩ የባንኩ ቅርንጫፎችና በንግድ ተቋማት አካባቢ በተተከሉ የኤቲኤም ማሽኖች ደንበኞች ገንዘብ ለማውጣት ቢሞክሩም፣ ሙከራቸው አለመሳካቱን ከማሽኑ የመረጃ ሰሌዳ እየተገለጸላቸው መሆኑንም እየገለጹ ነው፡፡ ሪፖርተርም ይኼንኑ ችግር በተለያዩ ቦታዎች ተዟዙሮ አይቷል፡፡ በተለይ ደንበኞች ሙከራው እንዳልተሳካላቸው ዓይተው ከሄዱ በኋላ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ሞክረው ያልተሳካላቸውን የገንዘብ መጠን ማውጣታቸውን የሚገልጸው መልዕክት ሲደርሳቸው፣  ድንጋጤና ግራ መጋባት ተፈጥሮባቸዋል፡፡ 

ነገር ግን ከቆይታ በኋላ የተጠቀሰውን የገንዘብ መጠን ወደ አካውንታቸው መመለሱን የሚያሳይ መልዕክት ከባንኩ እንደሚደርሳቸውም ለመረዳት ተችሏል፡፡ ይኼንን በተመለከተ መገናኛ፣ አራት ኪሎ፣ ካዛንቺስና ቦሌ አካባቢዎች የሚገኙ የባንኩ ቅርንጫፎች ሪፖርት በሚያደርጉ ደንበኞች ተጨናንቀው መሰንበታቸውን ለማየት ተችሏል፡፡ በአንዳንዶቹ ቅርንጫፎች ደንበኞች በምሬት ከባንኩ ሠራተኞች ጋር ሲጨቃጨቁም ተስተውለዋል፡፡

የባንኩ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ኤፍሬም መኩሪያ በተወሰኑ ቅርንጫፎች አካባቢ ባሉ ማሽኖች ችግሩ መስተዋሉን አምነው ችግሩ ከኔትወርክ መቆራረጥ ጋር የተያያዘ መሆኑን ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ከቴክኖሎጂው ጋር ለመራመድ በሚደረገው ጥረትም ችግሮች እንደሚከሰቱ ጠቁመዋል፡፡

ችግሩ የተከሰተው በዝውውር (Transfer)  አለመሟላት ምክንያት ቢሆንም፣ በማዕከል ቋት አማካይነት የሚተላለፍ በመሆኑና ጥብቅ ክትትል ስለሚደረግበት፣ ደንበኞች ሥጋት ላይ ሊወድቁ እንደማይገባና በፍጥነት ሊስተካከል እንደሚችል አቶ ኤፍሬም ጨምረው ገልጸዋል፡፡

ሆኖም ደንበኞች እንዲህ ዓይነት ችግር በሚገጥማቸው ወቅት በአቅራቢያቸው በሚገኙ ቅርንጫፎች ወይም ኤቲኤም ካርዱን ያወጡበት ቅርንጫፍ በመሄድ ሪፖርት እንዲያደርጉ አሳስበዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የባንኩን ነፃ የስልክ መስመር በሆነው በ950 በመደወል ጥያቄ ሊያቀርቡ ይገባልም ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በመላው አገሪቱ ከ650 በላይ የኤቲኤም ማሽኖች  አሉት፡፡ በአዲስ አበባ ብቻ ከ250 በላይ መትከሉን ከባንኩ የተገኘው መረጃ ያሳያል፡፡

 

ዝናቡ በመቅረቱ የተዘራው ጤፍም ሆነ ስንዴ ምርት አለማፍራቱን የምዕራብ አርሲ አርሦ አደሮች ገልፀዋል።

በአፍሪቃ ሕብረት መቀመጫ መዲና አዲስ አበባ ላይ ስድስት አስርተ ዓመታትን ያስቆጠረዉ የጥበብ አድባር፤ በርካታ የጥበብ ፈርጦችን አፍርቷል። በኢትዮጵያ ኪነ-ጥበብ ጉልህ ድርሻ ያበረከቱት አንጋፋ አርቲስቶች ያላቸዉን እዉቀት ለአዲሱ ትዉልድ እያሻገሩ ብሔራዊ ቲያትር ዳግም 60ዓመታት እንዲጨምር የሞያ ትግል የሚያደረጉ ባለሞያዎች ምሥጋና ይገባቸዋል።

በእነዘላለም ወርቅአገኘሁ መዝግብ ተከሰው የነበሩት 4 የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እና አብርሃም ሰለሞን ነፃ ቢባሉም በይግባኝ ታግደው ፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት እየተመላለሱ እንደሆነ ይታወቃል። አሁንም ለቃል ክርክር ሕዳር 29, 2008 ተቀጥረዋል። ቀሪዎቹ፣ ማለትም ዘላለም ወ/አገኘሁ፣ ዮናታን ወልዴ፣ ባሕሩ ደጉ፣ ሰለሞን እና ተስፋዬ ከሕዳር 13–16, 2008 ድረስ ከፊል መከላከያዎቻቸውን ያስደመጡ ሲሆን ቀሪውን ዛሬ (ሕዳር 24, 2008) ያስደምጣሉ።
እነዘላለም ተከላከሉ የተባሉት በፀረ–ሽብር ሕጉ አንቀፅ 7/1 መሠረት የግንቦት 7 አባል በመሆን ሠርታችኋል በሚል ነው። በ5ቱም (ዘላለም፣ ዮናታን፣ ባሕሩ፣ ሰለሞን እና ነፃ ተብሎ በይግባኝ የተያዘው አብርሃም ሰለሞን) ላይ የመሰከሩት 3ተኛ የዐ/ሕግ ምስክር አቶ እዮብ ሲሆኑ፣ የምስክርነታቸው ጭብጥ በጥቅሉ ‘ዘላለም ወ/አገኘሁ መልምሏቸው ለግንቦት 7 ወታደርነት 3 ሰዎችን መልምለው ከወሰዱ በኋላ ጎንደር ላይ ባለመስማማታቸው እንደተመለሱ። ከ3ቱ አንዱ እዚሁ መዝገብ ላይ 8ኛ ተከሳሽ የሆኑት አቶ ሰለሞን መሆናቸውን። አቶ ዘላለም በባሕሩ እና ዮናታን ሥር የተደራጀ ቡድን መኖሩን እንደነገሯቸው’ የሚያስረዳ ነው።
አቶ ሰለሞን፣ ዮናታን እና ዘላለም ከፊል ምስክሮቻቸውን ያስደመጡ ሲሆን አቶ ተስፋዬ (10ኛ ተከሳሽ) ጉዳያቸው ከነዘላለም የተለየ ቢሆንም አንድ መዝገብ በመሆናቸው ምስክሮቻቸውን አስደምጠው ጨርሰዋል።
አቶ ሰለሞን ሁለት ምስክሮችን አቅርበው እዮብ “የተሻለ ሥራ አገናኝሃለሁ በሚል አቶ ሰለሞንን ወደጎንደር ከወሰዷቸው በኋላ ጎንደር ሲደርሱ ለግንቦት ሰባት ወታደርነት እንደሆነ ሲነግሯቸው” መመለሳቸውን አስመስክረዋል። ራሰቸውም በሰጡት ቃል እዮብ እየወሰዳቸው እያለ መቶ አለቃ እያለ ከሚጠራው ሰው ጋር በስልክ ይነጋገር እንደነበርና የዘላለምን ስም ጨርሶ እንዳልሰሙ ተናግረዋል። 
ዮናታንም በበኩሉ እስካሁን 4 ምስክሮችን አስደምጧል። የመጀመሪያው አብሮ አደግ ጓደኛው ሲሆን፣ ዮናታን ውጭ አገር ለሚደረግ የሰብኣዊ መብትና ሚዲያ ነክ ሥልጠና ሊሄድ መሆኑን ነግሮት እርሱም ከፈለገ ሲቪውን እንዲሰጠው ጠይቆት መስማማቱን፣ ነገር ግን ሥልጠናው ባልታወቀ ምክንያት መስተጓጎሉን ለችሎቱ አስረድቷል። በሁለተኝነት የቀረበው ምስክር አቶ አስማማው ኃ/ጊዮርጊስ ስለእነዚህ ዓይነት ሥልጠናዎች ሠላማዊነት እና ሰጪዎቹም ዓለምዐቀፍ ዕውቅና የተቸራቸው ስለመሆኑ የባለሙያ ምስክርነቱን ሰጥቷል። በሦስተኝነት የቀረበው ምስክር አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ እዮብ ማዕከላዊ እያለ አናግሮት እንደነበር፣ ዮናታንን ፍፁም እንደማያውቀው፣ በኋላ ግን በድብደባ ብዛት እግሩ ተጎድቶ ማንከስ ሲጀምር እና ሥራ የሌላት ሚስቱና ልጁ ዕጣ ሲያሳስበው ተስፋ በመቁረጥ ሌሎቹ ላይ መስክሮ ሊፈታ መሆኑን እንደነገረው ለችሎቱ ነግሯል። በአራተኝነት ዘላለም ወ/አገኘሁ ቀርቦ እዮብ “ዘላለም በዮናታን ሥር ቡድን አለ ብሎ ነግሮኛል ያለው ሐሰት ነው” ብሏል።
ዘላለም ወርቅአገኘሁም ለራሱ እስካሁን 4 መከላከያ ምስክሮችን ያስደመጠ ሲሆን በቀዳሚነት የቀረበው ጥበቡ የተባለው አብሮ አደግ ጓደኛው ነበር። ጥበቡ፣ በክሱ ላይ የግንቦት 7 አመራር ተብሎ የተጠቀሰው ተድላ ደስታ አብሮ አደግ ጓደኛቸው እንደሆነና፣ እንግሊዝ አገር ከሄደ በኋላም ተማሩ እኔ ገንዘብ እልክላችኋለሁ ብሎ ገንዘብ ለሁለቱም እንደላከላቸውና ዘላለም ከመያዙ በፊት ማስተርሱን መማር እንደጀመረ ተናግሯል። የዘላለም እናት ወ/ሮ የኔእናትም በበኩላቸው ተድላ ደስታን ከልጅነቱ ጀምሮ የሚያውቁት የልጃቸው ጓደኛ በመሆኑ መሆኑን ጠቅሰው በ2005 ብር ልኮለት እሳቸው ጨምረውበት ዘላለም ትምህርት መጀመሩን ለችሎቱ ገልጸዋል። ቀሪዎቹ ሁለት ምስክሮች ሙዘሚል እና አዲሱ የተባሉ በክሱ ላይ በዘላለም ለግንቦት 7 የተመለመሉ እንደሆኑ የተገለጹ ወጣቶች ናቸው። ሁለቱም ወጣቶች በየተራ ከዘላለም ጋር ያላቸው ዕውቂያ በሰፈር ልጅነት እንደሆነና ምንም ዓይነት የሚያውቁት ቡድን እንደሌለ እና በቁም ነገር ቁጭ ብለው ያወሩበት አጀንዳም እንደሌለ ተናግረዋል።
ዘላለምና ዮናታን በሰጡት መከላከያ ቃላቸውም ላይ ወደውጪ ለሰብኣዊ መብትና ሚዲያ ነክ ሥልጠናዎች ለመሄድ ክሱ ላይ የግንቦት ሰባት አመራር ተብሎ የተጠቀሰው እና እነርሱ በጋዜጠኝነቱ እንደሚያውቁት የተናገሩት አርጋው አሽኔ ጋር ከመነጋገራቸው በቀር ምንም የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ተናግረዋል። ዘላለም፣ ሌሎችን ላለማስፈራራት ሲል ዝርዝሩን እንደማይናገር ነገር ግን በሐምሌ ወር፣ በቀዝቃዛ እና ዘጠና ሳንቲሜትር በሆነች ጨለማ ክፍል ውስጥ 41 ቀን መቆየቱንና ጠባሳ የማይተው ነገር ግን የነርቭን ስርዓት በሚያዛባ ምት እየተመታ መመርመሩን ተናግሯል።
በጥቅሉ ዐ/ሕግ ያቀረበው ክስ እና ማስረጃ ጠቅላላ ምስል፣ «ከውጭ አገር ገንዘብ በሚላክለት ዘላለም አማካኝነት የተመለመለው እዮብ ለግንቦት ሰባት ወታደሮችን እየላከ፣ ዘላለምም በሠላማዊ ትግል ሥም ቡድኖችን እያዋቀረ እንደሆነ» ለማሳየት ሲሞክር፣ እነዘላለምም በመከላከያቸው «ከውጭ አገር የተላከው ገንዘብ የዘላለም አብሮ አደግ ጓደኛ ለዘላለም የግል ፍላጎት የላከው መሆኑን፣ እዮብ ለግንቦት ሰባት ወታደርነት [እያታለለ] በወሰዳቸው ሰዎች ውስጥ ዘላለም እጁ እንደሌለበት፣ ቡድን እየተባለ የሚጠራ ነገር እንደሌለ እና ዜጎች ሁሉ ቢወስዱት የሚመከር ሥልጠና ለመውሰድ መጻጻፋቸውን በዚያ መንገድ እንደተተረጎመባቸው» የሚያስረዳ የመከላከያ ምስል ለመፍጠር እየሞከሩ ነው።

በአንዳንድ የኦሮሚያ ከተሞች የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን በመቃወም በተማሪዎች የሚካሄድ ሰልፍ ዛሬም መቀጠሉ ታዉቋል።
በተቃዋሚዎች ላይ የጸጥታ አስከባሪዎች በሚወስዱት እርምጃም የሰዉ ሕይወት እንደጠፋ፥ የቁሰሉና የታሰራ እንዳሉ ለአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ የአፋን ኦሮሞ ቋንቋ ቃለ ምልልስ የሰጡ ነዋሪዎችና የተቃዋሚ ፓለቲካ ተወካዮች ተናግረዋል። በነሞ ዳንዲ የተጠናቀረዉን ዘገባ ዝርዝር ትዝታ በላቸዉ ታቀርባለች።

የብሪታንያ የጦር አይሮፕላኖች ሶርያ ውስጥ የአየር ድብደባ ጀምረዋል። ድብደባውን የጀመሩት የብሪታንያ የምክር ቤት አባላት እስላማዊ መንግስት ነኝ የሚለውን ጽንፈኛ ቡድን ለማሸነፍ እንዲቻል የሀገሪቱ ስትራተጂ እንዲሰፋ ዴቪድ ካምሩን ያቀረቡትን ሃሳብ ካጸደቀ በኋላ ነው – VIDEO ↓

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

የኃይል ማመንጫዎች ብልሽት በመላ አገሪቱ የኃይል አቅርቦት እያስተጓጎለ ነው

በጣና በለስና በጊቤ አንድ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች በደረሰ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያና የኤሌክትሮኒክ መቆጣጠሪያ ብልሽት፣ በመላ አገሪቱ የኃይል አቅርቦ ተስተጓጉሏል፡፡ ቅዳሜ ኅዳር 18 ቀን 2008 ዓ.ም. በአገሪቱ ትልቁና 460 ሜጋ ዋት

የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት ላይ በሚገኘው ጣና በለስ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ  የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መቆጣጠሪያ ተበላሽቷል፡፡

ይህንን ብልሽት ለማስተካከል እየተሞረከ ባለበት ወቅት በነጋታው እሑድ ኅዳር 19 ቀን 2008 ዓ.ም. ደግሞ በጊቤ አንድ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ ተመሳሳይ ብልሽት አጋጥሟል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ከጊቤ አንድ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ተነስቶ ከሰኮሩ ከተማ ወደ ጌዶ የተዘረጋው የኃይል መስመር አደጋ ደርሶበታል፡፡

በእነዚህ ምክንያቶች ኅዳር 18 ቀን 2008 ዓ.ም. ከቀኑ 6፡30 እስከ 10፡30 ሰዓት፣ ኅዳር 19 ቀን 2008 ዓ.ም. ደግሞ ከ9፡30 ሰዓት ጀምሮ በመላ አገሪቱ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጧል፡፡ በዚህ የኃይል መቋረጥ ነዋሪዎች በሚያካሂዱት የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ፣ ከጥቃቅንና ከአነስተኛ አምራቾች እስከ ግዙፍ ማምረቻ ተቋማት ችግር ገጥሟቸዋል፡፡ በቅርቡ በአዲስ አበባ ከተማ በሁለት አቅጣጫዎች አገልግሎት መስጠት የጀመረው የቀላል ባቡር ትራንስፖርትም መስተጓጎል ገጥሞት ነበር፡፡

የውኃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ባለሥልጣን ባለሙያዎች ወደ ሥፍራው ተንቀሳቅሰው ችግሩን ለመፍታት እየሞከሩ መሆኑ ታውቋል፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የውጭ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ምስክር ነጋሽ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ችግሩን ለመቅረፍ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ነው፡፡

460 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ የማመንጨት አቅም ያለው ጣና በለስና 184 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ የማመንጨቅ አቅም ያለው ጊቤ አንድ፣ በብሔራዊ የኃይል ቋት ውስጥ መግባት ባለመቻላቸው በአገሪቱ ችግር ተፈጥሯል፡፡

በዚህ ምክንያት በመላ አገሪቱ ኃይል ከመቋረጡም በላይ፣ ችግሩ እስካሁን ባለመፈታቱም በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች አሁንም የኃይል መቆራረጥ እያጋጠመ ይገኛል፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ እነዚህ ችግሮች  በአሁኑ ወቅት የጎላ ደረጃ ይድረሱ እንጂ ችግሮቹ ያልተፈቱባቸው በርካታ ምክንያቶች አሉ፡፡

ከእነዚህ ውስጥም የመለዋወጫ ዕቃዎች በወቅቱ አለማዘጋጀት፣ በግድቦች አስተዳደር የባለሙያ እጥረት፣ አሮጌ የማሰራጫና ማስተላለፊያ መስመሮች በአዲስ አለመተካትና አሻጥረኛ ሠራተኞች መኖራቸው ለችግሩ መባባስ እንደ ምክንያት ያስቀምጣሉ፡፡

አሁን በተፈጠረው ችግር ብቻ አዲስ አበባ ከ120 ሜጋ ዋት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረት መከሰቱን መረጃዎች አመልክተው፣ በአንዳንድ መንደሮች ኤሌክትሪክ ኃይል ማግኘት ቅንጦት እየሆነ ነው፡፡

አሁን ያጋጠመውን ችግር ለመቅረፍ በርካታ ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑን፣  በመስኩ ከሚገኙ ባለሙያዎች ጋር ግንኙነት በማድረግ ችግሩን ለመቅረፍ እየተሠራ እንደሆነ የውኃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስትሩ አቶ ሞቱማ መቃሳ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ 

 

 

 

 

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በአዲስ አበባና በኦሮሚያ ልዩ ዞን ማስተር ፕላን ላይ ተቃውሞ አሰሙ

‹‹አረጋግተን እንዴት ትምህርት መጀመር እንዳለባቸው እየተነጋገርን ነው›› የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የአዲስ አበባና ኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ ማስተር ፕላንን በመቃወም፣ ኅዳር 20 ቀን 2008 ዓ.ም. ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ውስጥ ሠልፍ ወጡ፡፡ 

ተማሪዎቹ በማስተር ፕላኑ ውስጥ ማንኛውም የኦሮሚያ ቦታ መወሰድ ወይም መካተት እንደሌለበት የሚያንፀባርቁ መፈክሮችን ይዘው ከዩኒቨርሲቲው ግቢ በመውጣት፣ ወደ ሐረማያ ከተማ ለመሄድ ባደረጉት ሙከራ ከፀጥታ ኃይሎች ጋር መጋጨታቸው ታውቋል፡፡ 

ተማሪዎቹ እንቅስቃሴውን የጀመሩት ኅዳር 18 ቀን 2008 ዓ.ም. ምሽት ላይ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ እንቅስቃሴውን በመስማቱ ወዳልተፈለገ አቅጣጫ እንዳያመራ ለፀጥታ ኃይሎች መረጃው በመድረሱ የዩኒቨርሲቲው ፖሊሶች፣ የክልሉ ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስና የፌዴራል ፖሊስ ባደረጉት መከላከል፣ የተማሪዎቹ ሠልፍ በቅጥር ግቢው መገታቱን ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ ተማሪዎች ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ 

የተቀናጀ ማስተር ፕላኑን በሚመለከት ባለፈው ዓመት ተነስቶ በነበረው ተቃውሞ የመንግሥት አካላት ትኩረት በመስጠት በተለይ በኦሮሚያ የተለያዩ አካባቢዎች ከሚገኙ ነዋሪዎችና ከዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ጋር ባደረጉት ውይይት፣ ተፈጥሮ የነበረውን ውጥረት ከማርገባቸውም በተጨማሪ ስምምነት ላይ እንደደረሱ መገለጹ ይታወሳል፡፡ 

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ነገሩን እንደ አዲስ እንዴት ሊያነሱት እንደቻሉ ተማሪዎቹ ተጠይቀው እንደገለጹት፣ ኅዳር 18 ቀን 2008 ዓ.ም. የከተማ ልማትና ቤቶች ሚኒስቴር በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስብሰባ አዳራሽ ጉባዔ ጠርቶ ነበር፡፡ ከስብሰባው አጀንዳዎች አንዱ የከተማ ማስተር ፕላኖችን ማስተካከል ነው፡፡ በመሆኑም ባለፈው ዓመት ተቃውሞ ተነስቶበት በቂ ማብራሪያ ሳይሰጥበትና ስምምነት ላይ ሳይደረስ በዝምታ ታልፎ፣ አሁን ሊፀድቅ እንደሆነ በመገመት ሳይሆን እንዳልቀረ፣ የተቃውሞውን ምክንያት መገመታቸውን ተማሪዎቹ አስረድተዋል፡፡ 

ተማሪዎቹ በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ እየተዟዟሩ መፈክር በማሰማት ላይ እያሉ፣ ለተቃውሞው መነሳት ምክንያት ናቸው የተባሉ ቁጥራቸው የማይታወቁ ተማሪዎች መታሰራቸውንና የተወሰኑ ተማሪዎች ተደብድበው ጉዳት እንደደረሰባቸው ተማሪዎቹ ገልጸዋል፡፡ ፖሊስ በወቅቱ ጥይት የተኮሰ ቢሆንም የተጎዳም ሆነ የሞት አደጋ እንዳልደረሰ አክለዋል፡፡ ቁጥራቸው የማይታወቅ ተማሪዎች ሠልፉ ከመደረጉ አስቀድመው ከግቢው በመውጣት ከዘመዶቻቸው ጋር መቀላቀላቸውንና ከተለያዩ ክልሎች የመጡም ወደ ቤተሰቦቻቸው ለመመለስ በተለያዩ ቦታዎች ተደብቀው እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡ 

ኅዳር 20 እና 21 ቀን 2008 ዓ.ም. (ኅትመት እስከገባንበት ምሽት ድረስ) በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የመማር ማስተማር ሒደት መቋረጡም ታውቋል፡፡ በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ከአዲስ አበባና ከኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ ማስተር ፕላን ጋር በተገናኘ ተማሪዎች ስላነሱት ተቃውሞ ማብራሪያ እንዲሰጡ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ጨመዳ ፊኒንሳ፣ ተማሪዎቹ ተቃውሞ ማንሳታቸውን አረጋግጠው ‹‹አረጋግተን እንዴት ትምህርት መጀመር እንዳለባቸው እየተመካከርን ነው፤›› ብለዋል፡፡ 

ተማሪዎቹ ኅዳር 20 ቀን 2008 ዓ.ም. ከንጋቱ 12፡00 ሰዓት እስከ ረፋዱ 2፡30 ሰዓት ድረስ፣ በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ ሰላማዊ ሠልፍ ማድረጋቸውን የተናገሩት ፕሮፌሰሩ የአካባቢው አስተዳደር፣ ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስና ፌዴራል ፖሊስ ወደ ውጭ እንዳይወጡ ማድረጋቸውን አስረድተዋል፡፡ 

የተማሪዎቹ ተቃውሞ ከማስተር ፕላኑ ጋር ብቻ የተገናኘ መሆኑን የገለጹት ፕሮፌሰሩ፣ እንዴት ስለማስተር ፕላኑ ሊያነሱ እንደቻሉ እሳቸውም እንዳልገባቸው አስረድተዋል፡፡ በሠልፉ ግርግር ትንሽ ጉዳት የደረሰባቸው ተማሪዎች ሕክምና የተደረገላቸው መሆኑን ጠቁመው፣ ሦስት ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው ክሊኒክ እየታከሙ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ 

ፖሊስ ወደ ሰማይ ከመተኮስ ባለፈ ተማሪዎችን የሚጎዳ ድርጊት አለመፈጸሙን፣ ለረብሻው ምክንያት ናቸው የተባሉ ተማሪዎች ተይዘው በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ ከፖሊስ፣ ከዩኒቨርሲቲውና ከተማሪዎች የተውጣጣ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ ምርመራ እያደረገባቸው መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የተወሰኑ ተማሪዎችም መለቀቃቸውን አክለዋል፡፡ 

ተማሪዎቹ ተረጋግተው ትምህርታቸውን እንዲጀምሩ እሳቸውን ጨምሮ መምህራኑ እየመከሩ መሆኑን ፕሮፌሰር ጨመዳ አስታውቀዋል፡፡ ለትምህርት ሚኒስትሩ ለአቶ ሽፈራው ሽጉጤና ለኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ማሳወቃቸውንም አረጋግጠዋል፡፡ 

 

በትናንቱ ዕለት በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች ተማሪዎች የተቃውሞ ሰልፍ አካሂደው ከፖሊስ ጋር በተፈጠረ ግጭት ሕይወታቸው ያለፈና የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ተማሪዎች እንደነበሩ ተገለጸ። በተለይም ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ (Haramaya University) በደረሰ ግጭት የመንግሥት ታጣቂዎች በወሰዱት እርምጃ ሁለት ተማሮች መሞታቸው ታውቋል።

የምሥራቅና የምዕራብ ሐረርጌ ዞን ተረጂዎች ቁጥር ከ50 በመቶ በላይ ጨምሯል

ከኤልኒኖ የአየር ንብረት ለውጥ ጋር በተያያዘ በተለያዩ የአገሪቱ ክልሎች የተከሰተው ድርቅ እያሳረፈ ያለው ተፅዕኖ እየሰፋ መምጣት የተረጂዎችን ቁጥር እንዲጨምር እያደረገ ነው፡፡

ሰሞኑን በድርቅ የተጎዱ አካባቢዎችን ለመቃኘት የተንቀሳቀሰው የጋዜጠኞች ቡድን ከተመለከታቸው አካባቢዎች መካከል፣ የምዕራብና የምሥራቅ ሐረርጌ ዞን ውስጥ ከወራት በፊት የነበሩት ተረጂዎች ቁጥር ከ50 በመቶ በላይ ጨምሯል፡፡በኦሮሚያ ክልል የምሥራቅ ሐረርጌ ዞን የአደጋ መከላከልና ዝግጁነት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሃረን አልዪ እንደገለጹት፣ እስካሁን¬ 549,000 ተረጂዎች ተለይተው ዕርዳታ ሲሰጣቸው ቆይቷል፡፡ ይሁን እንጂ ድርቁ አሁንም ለውጥ ሳያሳይ በመቀጠሉ የተረጂዎች ቁጥር እየጨመረ መጥቷል፡፡ በዚህም መሠረት በምሥራቅ ሐረርጌ ዞን ብቻ ከ320 ሺሕ በላይ ተጨማሪ ተረጂዎች የመንግሥትን ዕርዳታ የሚሹ በመሆናቸው፣ ከሚቀጥለው ወር ጀምሮ የተረጂዎች ቁጥር 900 ሺሕ ይደርሳል ተብሎ ተገምቷል፡፡ ለእነዚህ ተረጂዎች የሚሆን ተጨማሪ የምግብ ዕርዳታ የተጠየቀ መሆኑም ተገልጿል፡፡

በምዕራብ ሐረርጌ ዞንም በተመሳሳይ በድርቅ የተጎዱ ተረጂዎች ቁጥር እንደጨመረ፣ የዞኑ የአደጋ መከላከልና ዝግጁነት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቶፊቅ አብዱላሂ ገልጸዋል፡፡ እንደ አቶ ቶፊቅ ገለጻ ዕርዳታ ያስፈልጋቸዋል ተብለው ሲሰጣቸው የነበሩት ከ500 ሺሕ በላይ ተረጂዎች ነበሩ፡፡ በጥር ወር ግን የተረጂዎች ቁጥር ከ720 ሺሕ በላይ እንደሚሆን ይጠበቃል ብለዋል፡፡ 

የሁለቱም ዞኖች የሥራ ኃላፊዎች የተረጂዎቹ ቁጥር ከዚህም በላይ ሊሆን እንደሚችል ያላቸውን ሥጋት ገልጸዋል፡፡ በሁለቱም ዞኖች እስካሁን ዕርዳታ ሲሰጣቸው የነበሩት የባሰ ችግር የነበረባቸው ናቸው፡፡ ድርቁ እየተራዘመ በመምጣቱ ግን የተሻሉ ናቸው የተባሉትንም ጭምር ዕርዳታ የሚያስፈልጋቸው እየሆኑ መጥተዋል፡፡

በአርሲ ዞን ዶዶታ ወረዳም ባለፈው ዓመት 14,404 የነበሩ ተረጂዎች ቁጥራቸው ከ51 ሺሕ በላይ ሆኗል፡፡

እንደ ምሥራቅ ሐረርጌ ዞን የሥራ ኃላፊዎች ገለጻ፣ በ2007 የምርት ዘመን ይገኛል ተብሎ የታቀደው 12 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ነበር፡፡ በቅርቡ በተደረገ የዳሰሳ ጥናት ግን ሊገኝ የሚችለው ከሦስት ሚሊዮን ኩንታል ያነሰ ነው፡፡ በምዕራብ ሐረርጌም የሚጠበቀው ምርት ቀድሞ ከተገመተው በእጅጉ ያነሰ እንደሚሆን ታምኗል፡፡

በምሥራቅ ሐረርጌ ዞን የድርቅ ተጎጂዎች ከሆኑ ወረዳዎች ውስጥ አንዱ የሆነው የሚደጋ ቶላ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ሳርቱ ሙክታር እንደሚሉት፣ መንግሥት ዕርዳታ እየሰጣቸው ቢሆንም ዕርዳታው በቂ አይደለም፡፡ በአንድ ቤተሰብ 15 ኪሎ ስንዴ እየተሰጣቸው መሆኑንና ሦስት ጊዜ መውሰዳቸውንም ተናግረዋል፡፡

ከስንዴው ጋርም አንድ ሊትር ዘይት ቢሰጣቸውም ይህ ግን በቂ አይደለም ይላሉ፡፡ የውኃ ችግሩ ግን እጅግ የከፋ መሆኑን የሚገልጹት የሚደጋ ቶላ ወረዳ ነዋሪዎች፣ በአጋጣሚ በዘነበው ዝናብ በአንድ ኩሬ ላይ የተጠራቀመ ውኃ ለከብቶቻቸውም ለራሳቸውም ይጠቀሙበታል፡፡

ቀድሞ ለመጠጥ ይጠቀሙበት የነበረው ኩሬ በመድረቁ መንግሥት በቦቴ የሚያመጣውና የሚያሠራጨው ውኃ የማይዳረስ ስለሆነ፣ አንዳንድ ነጋዴዎች አምጥተው የሚሸጡትን አንድ ሊትር ውኃ በአንድ ብር እየገዙ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ ይህም ቢሆን በቂ እንዳልሆነ ገልጸዋል፡፡

አቶ ሃሮን አሊዪ እንደሚሉትም በአካባቢው ያለው የውኃ እጥረት ከፍተኛ ነው፡፡ ይህን ችግር ለመቅረፍ ጥረት እየተደረገ ቢሆንም፣ ካለው ሁኔታ አንፃር በዞኑ የከፋ ችግር ላለባቸው ወረዳዎች 30 የውኃ ማመላለሻ ቦቴዎች እንደሚያስፈልጉ ጠይቀዋል፡፡ ‹‹17ቱን አግኝተን በእነዚሁ ቦቴዎች እያከፋፈልን ነው፡፡ የጠየቅናቸው የውኃ ቦቴዎች ከመጡ የውኃ ሥርጭቱ መጠን ይጨምራል፤›› ይላሉ፡፡

በምዕራብ ሐረርጌ ሚኤሶ ወረዳ ሪፖርተር ያገኛቸው አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች፣ እንዲሁም በምሥራቅ ሐረርጌ በድርቅ የተጎዱ ነዋሪዎች እንደሚናገሩት የሚደረግላቸው ዕርዳታ በቂ ያለመሆኑ ብቻ ሳይሆን፣ ጨርሶ ዕርዳታ እየተሰጣቸው ያለመሆኑን ነው፡፡ የሚሰጣቸው ዕርዳታ ባለመኖሩም አንዳንዶቹ ወደ ጂቡቲና ወደተለያዩ አካባቢዎች ለመሰደድ መገደዳቸውን ይናገራሉ፡፡

እንደነ አቶ ዓሊ ኢንድሪስ ያሉት ደግሞ ከአዲስ አበባ – ጂቡቲ በተዘረጋው የባቡር ፕሮጀክት ላይ በቀን ሠራተኝነት ተቀጥረው በቀን 30 ብር እየተከፈላቸው ሕይወታቸውን ይመራሉ፡፡ ከዚህ ሲብስም በደህናው ጊዜ ያደለቧቸውን ከብቶች እየሸጡ ነው፡፡

በአርሲ ዞን ዶዶታ ወረዳ የሚገኙ ነዋሪዎችም ከብቶቻቸው በድርቁ ምክንያት ስለተጎዱና ከችግር ለማምለጥ ለመሸጥ ወደ ገበያ ሲያወጧቸው ዋጋ እየወደቀባቸው መቸገራቸውን፣ ሲብስም ቀድሞ እስከ 20 ሺሕ ብር ይሸጡ የነበሩትን ከብት ከአምስት ሺሕ ብር ባልበለጠ ዋጋ ለመሸጥ መገደዳቸውን ይናገራሉ፡፡

በዚህ ወረዳ ከ77 ሺሕ በላይ ከብቶች አስቸኳይ የመኖ ዕርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ቢገልጹም፣ እስካሁን ግን ምንም ዓይነት ምላሽ እንዳልተሰጣቸው የወረዳው የአደጋ መከላከልና ዝግጁነት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጣሂር ፊኒኖ ተናግረዋል፡፡ መንግሥት በቶሎ መኖውን ካላቀረበላቸውም በከብቶቹ ላይ የሚደርሰው ጉዳት የከፋ እንደሚሆን ሳይጠቁሙ አላለፉም፡፡ 

አቶ አብደላ መሐመድ የሚኤሶ ወረዳ ነዋሪ ናቸው፡፡ በአካባቢያቸው ያለው ድርቅ የከፋ እንደሆነና በአጭር ጊዜ ውስጥ ዕርዳታ ካላገኙም ችግር ውስጥ የሚወድቁ መሆኑን ይናገራሉ፡፡ ችግሩ ለከብቶቻቸው ሞት ምክንያት ሆኗል፡፡ እስካሁን በ2007 የምርት ዘመን ፍሬ ያላፈራውን የበቆሎና የማሽላ አገዳ እየመገቡ ያቆዩዋቸው ቢሆንም፣ ከብቶቻቸው አሁን ምንም መኖ የላቸውም፡፡

አቶ አብደላ ያሏቸውን ከብቶች ከሚኖሩበት መንደር ውኃ ወዳለበት አካባቢ ማምጣታቸውን ገልጸዋል፡፡ በ2007 የምርት ዘመን የዘሩት በቆሎና ማሽላ ሙሉ በሙሉ በመጥፋቱ፣ በእጃቸው የቀሩትን ከብቶች በአነስተኛ ትንሽ ኩሬ ውኃ እያጠጡ ከኩሬ ዳር ማደርና መዋል ከጀመሩ ሦስት ቀናት አልፏቸዋል፡፡

ይህችም ኩሬ ብትሆን ከአንድ ሳምንት በላይ የሚቆይ ውኃ የሌላት መሆኑን የገለጹት አቶ አብደላ፣ ሦስት ልጆቻቸውን ጥለው እሳቸው ከብቶቻቸውን ለማዳን ሲወስኑ ከከብቶቻቸው ሦስቱን ሸጠው ለቀለብ የሚሆን ገንዘብ ለቤተሰቦቻቸው በመተው ነው፡፡ 

እንደ አቶ አብደላ ገለጻ እስካሁን አምስት ከብቶቻቸውን አርደዋል፡፡ ከሚሞቱ ብለው የወሰዱት ይህ ዕርምጃ በቀሪዎቹ ከብቶቻቸው ላይ እንዳይደርስም የቻሉትን ያህል ውኃ ወዳለበት መጓዝ ግዴታቸው መሆኑን አስረድተዋል፡፡

በሁሉም ወረዳዎች ትልቁ ችግር ውኃ ሲሆን፣ በአንዳንዶቹ አካባቢዎች ሰዎችም ሆኑ ከብቶች ውኃ ለማግኘት በእጅጉ ተቸግረዋል፡፡ ድርቁ ያስከተለው ጉዳት ከዚህም በኋላ የከፋ ሊሆን እንደሚችል ገልጸዋል፡፡

በዚህችው አነስተኛ ኩሬ ዳርቻ ሪፖርተር ያገኛቸው ሌላው አርሶ አደር እየደረሰ ያለውን ጉዳት በማየት ዕርዳታ ያልተደረገላቸው መሆኑን በሐዘኔታ ይገልጻሉ፡፡ ‹‹በተደጋጋሚ ወደ አካባቢው የሚመጡት የመንግሥት ኃላፊዎች ችግሩን ሰምተው ይሄዳሉ እንጂ ዕርዳታ እያደረጉልን አይደለም፤›› ብለዋል፡፡ 

‹‹የልጆቻችን ሰውነት ቀንሷል፡፡ ከትምህርት ቤትም እየቀሩብን ነው፤›› የሚሉት እኚሁ አርሶ አደር፣ ለውኃ ችግር መፍትሔ ካልመጣ አካባቢውን ለቆ መሄድ ግድ ሊሆን እንደሚችል ገልጸዋል፡፡

‹‹ይህ የፈጣሪ ጉዳይ ስለሆነ ከዘራነው አላገኘንም፡፡ ከፈጣሪ በታች ያለን መንግሥት ነውና ዕርዱን ብለናል፤›› ያሉት አርሶ አደሩ፣ አሁንም ይህ ጥያቄያቸው ምላሽ እንዲያገኝ ይማፀናሉ፡፡ 

በሚኤሶ ወረዳ ሪፖርተር ያነጋገራቸው አርሶ አደሮች ዕርዳታ እየተሰጣቸው አለመሆኑን ቢገልጹም፣ የሚኤሶ ወረዳና የምዕራብ ሐረርጌ ዞን ኃላፊዎች ዕርዳታ እየተሰጠ ነው ይላሉ፡፡

የሚኤሶ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ መሐመድ ከማል፣ ‹‹በአጋጣሚ ያነጋገርናቸው በወረዳው ሊረዱ ይገባል ተብለው ከተያዙት ውጪ ሊሆኑ ይችላሉ፤›› በማለት የአልተረዳንም ጥያቄ ለሚያነሱት አርሶ አደሮች ምላሽ ይሰጣሉ፡፡

በአሁኑ ወቅት የተረጂዎች ቁጥር እየጨመረ የተሻሉ ናቸው የተባሉትም ዕርዳታ የሚሹ እየሆኑ በመምጣታቸው፣ ከሚቀጥለው ወር ጀምሮ ዕርዳታ ሊሰጣቸው ይገባል ከሚባሉት ውስጥ ይካተታሉ ብለዋል፡፡

ከዕርዳታ ሥርጭት ጋር በተያያዘ የተለያዩ አስተያየቶችም ይሰነዘራሉ፡፡ በአንዳንድ አካባቢዎች በቂ ዕርዳታ እየተሰጠ አለመሆኑን ሲገልጹም ዕርዳታ የሚያስፈልጋቸውን ያላካተተ አሠራር እንዳለ ያመለክታሉ፡፡

የዕርዳታ አሰጣጡ ፍትሐዊ ነው ብለው የሚያምኑ እንዳሉም የሚናገሩ አርሶ አደሮች አሉ፡፡ የሁለቱ ዞኖች አስተዳዳሪዎች ግን የዕርዳታ አሰጣጡ በግልጽነት የሚካሄድ መሆኑን ነው የሚናገሩት፡፡ በዚህ ዕርዳታ አሰጣጥ ላይ ችግር ቢፈጠር ወዲያው ዕርምጃ የሚወሰድበት አሠራር ተዘርግቷል ይላሉ፡፡ 

የምሥራቅ ሐረርጌ ዞን አስተዳደር እንደገለጸው ለቁጥጥር ከአስተዳደር፣ ከዓቃቤ ሕግና ከሕዝብ አደረጃጀት የተውጣጣ ኮሚቴ ተቋቁሞ እየተሠራ ነው ብለዋል፡፡ 

በሚኤሶ ወረዳ ዲርባ ቀበሌ ደግሞ ከዕርዳታ አሰጣጥ ጋር ተያይዞ የቀበሌው የሥራ ኃላፊና የጎጥ አመራሮች እንዲታሰሩ መደረጉን፣ የወረዳው አደጋ መከላከልና ዝግጁነት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዮሐንስ ጌታቸው ገልጸዋል፡፡

የቀበሌው ሊቀመንበርና የጎጥ አመራሮች የታሰሩት በዕርዳታ ዕደላው ወቅት የአንዳንዱን ቤተሰብ ቁጥር በማሳነሳቸው፣ የአንዳንዶቹን ደግሞ ቁጥራቸውን በመጨመር የተሻለ መጠን ያለው ዕርዳታ እንዲሰጣቸው በማድረጋቸው ነው፡፡ 

ወረዳው ይህንን መረጃ በሕዝብ ጥቆማ ካገኘ በኋላ ባደረገው ማጣራት፣ ድርጊቱ መፈጸሙ በመረጋጡ ዕርምጃው ለመውሰድ መቻሉን ነው የተናገሩት፡፡

በሁለቱም ዞኖች ያለው የከፋ ድርቅ በሰው ሕይወት ላይ ሞት አላስከተለም ተብሏል፡፡ በምዕራብ ሐረርጌ ዞን ሚኤሶ ወረዳ ብቻ እስካሁን ከ2,200 በላይ ከብቶች መሞታቸውን የወረዳው የአደጋ መከላከልና ዝግጁነት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ገልጸዋል፡፡

ድርቁ ባስከተለው ችግር የተሰደዱ አሉ የሚባለውን ያስተባበሉት የወረዳው አስተዳዳሪ፣ በዚህ አካባቢ ያለ ነዋሪ ወደ ጂቡቲ መሄድና መምጣት የተለመደ በመሆኑ በድርቁ የተሰደዱ ናቸው ሊባል እንደማይችል ገልጸዋል፡፡ ‹‹ይሁን እንጂ እንዳይሰደዱ በቂ ዕርዳታ እየተሰጣቸው ነው፡፡ ነገር ግን አንፈልግም ብለው የሚሄዱ አሉ፤›› ብለዋል፡፡ በወረዳቸው ደረጃ የበለጠ ዕርዳታ የሚያስፈልገው ተረጂ ቁጥር ከአንድ ወር በኋላ ስለሚጨምር ለዚህ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

የምሥራቅ ሐረርጌ ዞን አስተዳዳሪ አሁን ያለውን ችግር ለመቅረፍ የተለያዩ ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ‹‹ድርቁ ከቁጥጥር ውጪ እንዳይሆን በሁለቱም ዞኖች መንግሥት ከሚያደርገው ጥረት ባለፈ፣ የመንግሥት ሠራተኞች ከደመወዛቸው ከ53 ሚሊዮን ብር በላይ በፈቃዳቸው አዋጥተው ለድርቁ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል መጠባበቂያ ፈንድ ውስጥ ተይዟል፤›› በማለት ተናግረዋል፡፡

በቀጣይም ድርቁ ከቁጥጥር ውጪ እንዳይሆን መንግሥት ተከታታይ ዕርዳታዎችን እንደሚያደርግ በእርግጠኝነት አስታውቀዋል፡፡

 

 

ለመጀመርያ ጊዜ ለሳቅ ዉድድር ጀርመን ሀገር እንደመጣ የሚናገረዉ ለዓለም የሳቅ ንጉሱ ለበላቸዉ ግርማ፤ ሳቅ ፍቅር ነዉ፤ ሳቅ መላ አካላትን የሚያንቀሳቅስ ስፖርት ነዉ፤ ሳቅ ሰላምን መፍጠርያ መሣርያ ነዉ፤ ሳቅ ጤና ነዉ፤ ሳቅ ደስታ ነዉ፤ ሳቅ ሕይወት ነዉ፤ ሳቅ የሰላም መሣርያ ነዉ፤ ሳቅ የፍቅር መሣርያ ነዉ፤ ሳቅ ወጣት የሚያደርግ ነዉ።

ኀዳር ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በከተማዋ ውጥረት ነግሶ መሰንበቱን የገለጸው ወኪላችን፣ መንስኤውም አንድ የመከላከያ ሰራዊት አባል ተደብድቦና በጥይት ተመትቶ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት መሆኑን ተከትሎ ነው። ውጥረቱን ተከትሎ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ትራፊክ ዋና አዛዥ ኮማንደር አብዲ ኢብራሂም የተሰወሩ ሲሆን፣ በመከላከያ ሰራዊት አባላት በጥብቅ እየተፈለጉ ነው። ጉዳዩን ለማጣራት የመከላከያ ሚኒስትሩ ሲራጅ ፈርጌሳና የፌደራል ፖሊስ …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ኀዳር ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባለፈው ቅዳሜ፣ እሁድ እና ሰኞ ባል ድፍን አዲስ አበባ ጭለማ ውጧታል። ካለፉት ሁለት አመታት ወዲህ የሃይል መቆራረጡ እየተባባሰ የመጣ ሲሆን የመንግስት ሹማምንት አንዴ ችግሩ የመልካም አስተዳደር ብልሽት ውጤት ነው፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ የመስመር እርጅና ነው እያሉ ፣ እርስበርሱ የተምታታ መግለጫ ከመስጠት ባለፈ ሁነኛ መፍትሄ ሳያበጁለት ቀርተዋል። ችግሩ …

ፖሊስ መምህር ግርማን በነፍስ ግድያ በመጠርጠሩ በዋስ አልተፈቱም

በተጠረጠሩበት የማታለልና ሐሰተኛ ሰነድ መጠቀም ወንጀሎች የ50 ሺሕ ብርና የ40 ሺሕ ብር ዋስትና የተፈቀደላቸው [መምህር] ግርማ ወንድሙን፣ ፖሊስ በነፍስ ግድያ እንደሚጠረጥራቸው በማመልከቱ አለመፈታታቸው ታወቀ፡፡

ፖሊስ [መምህር] ግርማ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፈቃድ ሳያገኙ ፈቃድ እንደተሰጣቸው በማስመሰል ሐሰተኛ ሰነድ እንደተጠቀሙ በመግለጽ፣ ሰነዱን እያስመረመረ መሆኑን ገልጾ፣ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እንዲፈቀድለት ኅዳር 15 ቀን 2008 ዓ.ም. ፍርድ ቤቱን ጠይቆ ነበር፡፡ ፍርድ ቤቱ ጥያቄውን ውድቅ አድርጎ ተጠርጣሪው በ40 ሺሕ ብር ዋስ እንዲለቀቁ ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር፡፡ ነገር ግን ፖሊስ እሳቸውን በነፍስ ግድያ እንደሚጠረጥራቸው በመግለጽ ለፍርድ ቤቱ ማመልከቻ በማቅረቡ፣ ፍርድ ቤቱ ተጨማሪ ሰነዶችን እንዲያቀርብ ለኅዳር 20 ቀን 2008 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ተጠርጣሪው  ወሰን ግሮሰሪ አካባቢ የሚኖሩ ግለሰብን ቤት በማሸጥና ገንዘቡንም ‹‹ይፀለይበት›› በማለት መውሰዳቸውን በሚመለከት ፖሊስ ካቀረበባቸው ክስ፣ በ50 ሺሕ ብር ዋስ እንዲለቀቁ ትዕዛዝ መስጠቱ ይታወሳል፡፡

ነገር ግን በፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ቅር የተሰኘው ፖሊስ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ ያለ ቢሆንም፣ ፍርድ ቤቱ ኅዳር 17 ቀን 2008 ዓ.ም. በዋለው ችሎት የፖሊስን ማመልከቻ ውድቅ በማድረግ የሥር ፍርድ ቤትን ትዕዛዝ አፅድቆ በ50 ሺሕ ብር ዋስ እንዲለቀቁ አዟል፡፡ ነገር ግን ተጠርጣሪው በነፍስ ግድያ በመጠርጠራቸው ከእስር አልተፈቱም፡፡ 

ይህ በዚህ እንዳለ በሪፖርተር ቅጽ 21 ቁጥር 1622 ዕትም፣ ‹‹በ50 ሺሕ ብር ዋስ ይፈቱ የተባሉት [መምህር] ግርማ ይግባኝ ተጠየቀባቸው›› በሚለው ዜና ውስጥ ‹‹ከቤተ ክህነት እንደተሰጣቸው የገለጹት ሰነድ በፎረንሲክ ተመርምሮ ሐሰተኛ መሆኑን እንዳረጋገጠ ፖሊስ ለፍርድ ቤት አስረድቷል፤›› የሚለው አገላለጽ በስህተት ስለሆነ፣ ‹‹ሰነዱን ለምርመራ ለፎረንሲክ ሰጥቶ እየተጠባበቀ መሆኑን አስረድቷል፤›› ተብሎ ተስተካክሎ እንዲነበብ አንባቢያንን ከይቅርታ ጋር እንጠይቃለን፡፡

 

ኤጀንሲው የአቶ በረከት ስምዖንን መኖሪያ ቤት ለባለቤቱ እንዲያስረክብ ታዘዘ

ቤቱ ለባለቤቱ እንዲመለስ ከተወሰነ 17 ዓመታት አልፎታል

የመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 17 ቀበሌ 19 ውስጥ የሚገኘውን፣ የቤት ቁጥር 119 የሆነውንና የኢትዮጵያ ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር አቶ በረከት ስምዖን እየኖሩበት የሚገኘውን መኖሪያ ቤት፣ ታኅሳስ 18 ቀን 2008 ዓ.ም. እንዲያስረክብ ታዘዘ፡፡ 

 

ኤጀንሲው ቤቱን ለባለ ንብረቱ አቶ መሐሪ ተወልደ ብርሃን እንዲያስረክብ፣ የኢትዮጵያ ፕራይቬታይዜሽን ኤጀንሲ ከ17 ዓመታት በፊት ሚያዝያ 28 ቀን 1990 ዓ.ም. ትዕዛዝ ያስተላለፈ ቢሆንም፣ በተለያዩ ምክንያቶች እስካሁን አለማስረከቡ ተጠቁሟል፡፡

የቤቱ ባለቤት አቶ መሐሪ ጥቅምት 5 ቀን 1988 ዓ.ም. ለፕራይቬታይዜሽን ኤጀንሲ ባቀረቡት አቤቱታ እንዳስታወቁት፣ ቤቱ የተወረሰው ከአዋጅ ውጪ በመሆኑ እንዲመለስላቸው መጠየቃቸውን ሰነዶች ያስረዳሉ፡፡ ኤጀንሲውም ባደረገው ምርመራ የአመልካቹ ቤት በአዋጅ ቁጥር 110/87 አንቀጽ 2(3) መሠረት ከአዋጅ ውጪ የተወረሰ መሆኑን እንዳረጋገጠ ጠቁሞ፣ ኤጀንሲው ለቤቱ ማሠሪያ የዋለ የባንክ ዕዳ ካለ ተሳስቦ ለባንክ እንዲከፍልና ምንም ዓይነት የዕዳ ጥያቄ ሳያቀርብ ቤቱን ለአቶ መሐሪ እንዲያስረክብ አዞት እንደነበር ሰነዱ ያሳያል፡፡ ነገር ግን ቤቱ ተጨማሪ ማጣራት እንደሚያስፈልገው ተገልጾ፣ ከሰኔ 12 ቀን 1990 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ታኅሳስ 30 ቀን 2006 ዓ.ም. ድረስ ታግዶ የቆየ ቢሆንም፣ ቤቱ እንዲመለስላቸው የተሰጠው ውሳኔ ትክክል መሆኑ ስለተረጋገጠ፣ የፕራይቬታይዜሽንና የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ኤጀንሲ ቦርድ እግዱ እንዲነሳ ጥር 1 ቀን 2006 ዓ.ም. በመወሰኑ፣ ቤቶች ኤጀንሲ ቤቱን ለአቶ መሐሪ እንዲያስረክብ በድጋሚ ማዘዙን ሰነዶች ያስረዳሉ፡፡

ቤቶች ኤጀንሲ እንዲያስፈጽም ለተላለፈለት ትዕዛዝ በሰጠው ምላሽ፣ ‹‹ቤቱ ለባለቤቱ እንዲመለስ ውሳኔ ያስተላለፈው ፕራይቬታይዜሽን ኤጀንሲ ነው፡፡ ውሳኔው የሚፈጸመው በአዲስ አበባ ከተማ ፍርድ ቤት በውክልና ነው፡፡ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለማስፈጸም ሥልጣን የለውም፤›› በማለት ምላሽ ሰጥቷል፡፡

ፍርድ ቤቱ በሰጠው ብይን እንዳብራራው፣ ኤጀንሲው ፍርድ ቤቱ ሥልጣን እንደሌለው ቢገልጽም ማስረጃ አላቀረበም፡፡ ኤጀንሲው ጊዜ እንደሚያስፈልገው ቢገልጽም፣ እንዲያስፈጽም ከስምንት ወራት በላይ ስለተሰጠው በቂ ጊዜ እንደሆነና በቤቱ ውስጥ የሚኖሩት ከፍተኛ ባለሥልጣን ናቸው የሚለው ተቀባይነት እንደሌለው በመዘርዘር፣ ቀደም ብሎ ሌተና ጄኔራል ፃድቃን ገብረ ትንሳዔ፣ በአሁኑ ጊዜ ደግሞ አቶ በረከት ስምዖን የሚኖሩበት መኖሪያ ቤት ለባለቤቱ አቶ መሐሪ ተወልደ ብርሃን እንዲያስረክብ፣ የቤቶች ኤጀንሲ ከፌዴራል ፍርድ ቤቶች ፍርድ አፈጻጸም ዳይሬክቶሬት ኅዳር 16 ቀን 2008 ዓ.ም. ትዕዛዝ ተላልፎለታል፡፡     

የመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ሲሳይ ለከተማ ልማትና ቤቶች ሚኒስቴር በጻፉት ደብዳቤ፣ በቤቱ ውስጥ የሚኖሩትን ባለሥልጣን የሚመጥን ቤት ስላልተገኘ ለግ

‹‹ሌብነት የለመደ በአንድ ሳምንት ውስጥ ቴሌቪዥን ላይ ወጥተን ስለጮህን እጁን ይሰበስባል ማለት አይደለም›› ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ባለፈው ሐሙስ ኅዳር 16 ቀን 2008 ዓ.ም. ከሪፖርተር ጋዜጣ ዋና አዘጋጆች ዘካሪያስ ስንታየሁና አሥራት ስዩም ጋር በጽሕፈት ቤታቸው ቆይታ አድርገዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዲህ ዓይነት ቆይታ ከግል የኅትመት ሚዲያ ጋር ሲያደርጉ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቆይታቸውም ወቅታዊ በሆኑ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በቅርቡ ከተከሰተው ድርቅ አንስቶ ስለመልካም አስተዳደር ችግሮች፣ እንዲሁም በኤርትራ ጉዳይ ላይ ያደረጉት ልዩ ቃለ ምልልስ ለመመልከት እዚህ ላይ ይጫኑ፡፡  

 

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም

በፈረንጆች ባህል እውቀት ሥልጣን ነው፤ እንዲያውም እውቀት ኃይል ነው ይላሉ፡፡

በኢትዮጵያ ባህል እውቀት ሥልጣን የለውም፤ እንዲያውም ሥልጣን እውቀት ይመስለናል፡፡

በ1951 ዓ.ም. በትግራይ ችጋርን በዓይኔ አይቻለሁ፤ በጆሮዬ ሰምቻለሁ፤ በአካሌ ቀምሼዋለሁ፤ ጠኔ ይዞኝ ተደግፌ ወደቤቴ ገብቻለሁ፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

በኦሮሚያ – ጊንጪ ከተማ ህዳር ዘጠኝ ቀን የጀመረው የተማሪዎች ተቃውሞ ዛሬም በምዕራብ ወለጋ ሁለት ከተሞች መቀጠሉን የአካባቢው ነዋሪዎች ለቪኦኤ ገልፀዋል።

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

የስኳር በሽታን ተከትለው በዓይን ላይ የሚደርሱ ዋና ዋና የጉዳት ዓይነቶች ምን ይሆኑ? አስቀድሞ የሚታዩ ምልክቶችስ ይኖሩ ይሆን? ተከታታይ ቅንብራችን የሚመለከታቸው ጭብጦች ናቸው።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ኒው ዮርክ ከተማ (የተራድኦ ድግስ ምሽት፥ ኅዳር ፬ ቀን ፳፻፯ ዓ. ም. – November 14, 2015) [ ጌታቸው ኃይሌ ] ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን እንድታገለግሉ የተመረጣችሁ የተከበራችሁ ካህናትና ዲያቆኖት፥ የመድኃኔ ዓለም አባላት እንድትሆኑ የሐዋርያትን …

“በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የጽሑፍ ቅርስ ላይ ከአለኝ ትዝብት” (ዳንኤል ክብረት) Read more »

የኢትዮጵያ ወታደሮች ሰሞኑን የኬንያን ድንበር ተሻግረው ሦስት የኬንያን ፖሊሶች በደፈጣ መግደል የሚናገሩ ዘገባዎች በኬንያ ጋዜጦች መውጣታቸው ይታወሣል፡፡ እኛም ጉዳዩን ለማጣራት እያደረግን ባለነው ጥረት ትናንት ያነጋገርናቸው የኬንያ ፖሊስ ቃል አቀባይ ቻርልስ ኦዊኖ ደፈጣውን የፈፀሙትና የኬንያ ፖሊሶችን የገደሉት የኢትዮጵያ መንግሥት ወታደሮች ሳይሆኑ …

ኦነግ የመርሳቢቱን ጥቃት አልፈፀምኩም አለ – VOA Read more »