“ይህ አገዛዝ በቃው! አንፈልገውም! 27 ዓመት + 1 አንቀበልም!”

Image
ቡርኪናፋሶን ያለገደብ ሲመሩ የነበሩት ብሌዝ ኮምፓዎሬ ለተጨማሪ ዓመታት ሥልጣናቸውን ለማራዘም ያደረጉት ሙከራ በመክሸፉ ከሥልጣናቸው እንደሚለቁ ገለጹ፤ ለአንድ ዓመት የመሸጋገሪያ መንግሥት ተመስርቶ ምርጫ እስከሚደረግ በሥልጣን እንደሚቀጥሉ አስታወቁ፡፡ ሕዝቡና የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ግን ይህንን የሚቀበሉበት ትከሻ እንደሌላቸውና የኮምፓዎሬ አገዛዝ አሁኑኑ መውረድ እንዳለበት በተቃውሟቸው እየገለጹ ነው፡፡ ከ27ዓመት አምባገነናዊ ሥርዓት በኋላ ቡርኪናፋሶ ወደ ሌላ አምባገነናዊ ሥርዓት ልትሄድ እንደምትች ተጠቆመ፡፡

በቀድሞው ፕሬዚዳንት ቶማስ ሳንካራ ዘመን የመንግሥት ባለሥልጣንና የሳንካራ ወዳጅ የነበሩት ብሌዝ ኮምፓዎሬ፤ ቶማስ ሳንካራ ባልታወቀ ሁኔታ በመፈንቅለ መንግሥት ከተገደሉ ከዛሬ 27ዓመት ጀምሮ ቡርኪናፋሶን መግዛት ጀመሩ፡፡ መፈንቅለ መንግሥቱን በመምራት የተሳተፉት ኮምፓዎሬ የሳንካራን መገደል በወቅቱ “ድንገተኛ” በማለት ከመጥቀስ በስተቀር ምርመራ እንዲካሄድ አላዘዙም፤ ምስጢሩም እንዳይወጣ ተደርጎ ቆይቷል፡፡

ቶማስ ሳንካራን ከሥልጣን ካስወገዱ በኋላ ለሦስት ዓስርተ ዓመታት ያህል የዘለቀውን አገዛዛቸውን የጀመሩት ኮምፓዎሬ እኤአ በ1990ዎቹ በተደጋጋሚ የተመረጡት ሲሆን የአገሪቱ ሕገመንግሥት ከተሻሻለ በኋላ በሁለት ሺዎቹም ሁለት ጊዜ ተመርጠዋል፡፡

በአገዛዝ በቆዩበት ዘመን ሁሉ የአውሮጳውያንና የአሜሪካ ወዳጅ በመሆን ሥልጣናቸው ሳይደፈር በአምባገነንነት ለመቆየት ችለዋል፡፡ አክራሪ እስላማዊነትን እዋጋለሁ በማለት የአሜሪካ ወዳጅነታቸውን ያጠናከሩት ኮምፓዎሬ በላይቤሪያና ሴራሊዮን እጅግ አስከፊ ጭፍጨፋ ያካሄዱትን እና በአሁኑ ወቅት 50ዓመት እስራት የተበየነባቸው የቀድሞው የላይቤሪያ መሪ ቻርልስ ቴለር የቅርብ ወዳጅ ነበሩ፡፡ ሳንካራን ለመገልበጥና ለመግደል የቴይለር ጦር እንደተሳተፈና በምላሹ ኮምፓዎሬ ለቴይለር ወደ ሥልጣን መምጣትና ከዚያ ጋር ተያይዞ ለተፈጸመው ወንጀል ተባባሪ ናቸው በማለት ሁኔታዎችን የሚያገናኙ ወገኖች አሉ፡፡

በአገራቸው የሚነሱ ተቃውሞዎችን ስልታዊ በሆነ መንገድና በምዕራባውያን ድጋፍ ሲያከሽፉ የኖሩት ብሌዝ ኮምፓዎሬ በአካባቢው አገራት ዘንድ የሰላም ዘንባባ አቅራቢ፣ አስታራቂ፣ አስማሚ፣ ሸምጋይ፣ … ሆነው ምስላቸውን እና ማንነታቸውን ሲገነቡ ቆይተዋል፡፡ በአምባገነንነት በቆዩባቸው ዓመታት በሙስና በተለይም ከአልማዝ ሽያጭ ከሚገኘው ገንዘብ ያላቸው ተሳታፊነት ከፍተኛ እንደሆነ ይነገራል፡፡

በቀጣዩ የአውሮጳውያን ዓመት 2015 ሥልጣናቸው የሚያበቃው ኮምፓዎሬ “ደህና ሁኑ” ብለው ለመሄድ የተዘጋጁ አልነበሩም፡፡ በመሆኑም የአገሪቱን ሕገመንግሥት በማሻሻል እንደገና ለመመረጥ ደፋ ቀና ማለት ጀመሩ፡፤ ፓርላማቸውን አሰብስበው ሕገመንግሥቱ እንዲሻሻል በማድረግ ሂደት ላይ እያሉ ሕዝቡ “በቃኝ” አለ፡፡

የ27 ዓመታት አገዛዝ የመረራቸው ዜጎች ሐሙስ ዕለት ፓርላማውን ጥሰው በመግባት ድምጽ እንዳይሰጥ ከማድረግ አልፈው በእሣት አጋዩት፡፡ ተቃውሞ በየቦታው ፈነዳ፡፡ ቡርኪናፋሶ መጋየት ጀመረች፡፡ ሁኔታው ያላማራቸው ኮምፓዎሬ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጁ፡፤ ሰሚ ግን አላገኙም፡፡ ሕዝቡ “ይህንን አገዛዝ አንፈልግም፣ በቃን” አለ፡፡ ሕዝባዊ ዓመጽ በየቦታው ተቀጣጠለ፡፡ በተለይ ዋና ከተማዋ ዖጋዱጉ የዓመጹ ዋና ማዕከል ሆነች፡፡

መንግሥት ሥራ አቆመ፣ ፓርላማውም ፈረሰ፡፡ ድህነት ያስመረራቸው ዜጎች አሁንም ተቃውሟቸውን ቀጥሉ፡፡ ኮምፓዎሬን ማየትም ሆነ መስማት በጭራሽ አይፈልጉም፡፡ ወታደሮች በየአካባቢው ሥነሥርዓት ለማስጠበቅ እየጣሩ ቢሆንም ዓመጹ ግን ቀጥሏል፡፡ ንብረት እየወደመ ነው፤ ባንኮችም ተዘርፈዋል፡፡

ዛሬ አርብ ዳግም ለመመረጥ ሲመኙ የነበሩት ኮምፓዎሬ ሥልጣን በቃኝ፤ መንግሥት ፈርሷል፤ ፓርላማውም አይሰራም፤ ከሥልጣኔ እለቃለሁ ነገር ግን በ2015 ምርጫ እስከሚካሄድ የሽግግር አስተዳደር ተመስርቶ ሁሉም ነገር መረጋጋት አለበት በማለት አስቀድሞ በተቀዳ የቴሌቪዥን መልዕክት ቢያስተላልፉም ሰቆቃ የመረራቸው፣ ኑሮ ያቃጠላቸው፣ ነጻነት የጠማቸው ዜጎች ግን አሁንም “አንሰማም” ብለው ተቃውሟቸውን በመቀጠል ፕሬዚዳንቱ ከሥልጣን እንዲወርዱ ጠይቀዋል፡፡

ሰላሳ አራት የሚሆኑ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ፕሬዚዳንቱ ያቀረቡትን ቅደመ ሁኔታ አንቀበልም ብለዋል፡፡ ለኮምፓዎሬ ምላሽ ሲሰጡም “አንድ የምንቀበለው አጭርና ግልጽ ቅድመ ሁኔታ ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ብሌዝ ኮምፓዎሬ ከሥልጣን እንዲለቁ ነው” በማለት ተናግረዋል፡፡

ጦሩ ሥልጣኑን የተረከበ እንደሆነ እየተጠቆመ ሲሆን አገሪቱን በበቂ ሁኔታ ለማረጋጋት እንዳልቻለ ከዋና ከተማዋ የሚመጡ ዜናዎች ይጠቁማሉ፡፡ የሕዝቡ ዓመጽም ወደ ሌሎች ከተሞች እየተዛመተ መሆኑን ከተለያዩ የዜና ማሰራጫዎች እየተሰማ ነው፡፡

በአንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች ዘንድ ከአረብ ጸደይ ቀጥሎ የተጀመረ “የአፍሪካ ጸደይ” ሊሆን ይችላል በማለት ግምት የሰጡበት የቡርኪናፋሶ ሕዝባዊ አመጽ ተመልሶ በአምባገነናዊ አገዛዝ እንዳይወድቅ ስጋት አላቸው፡፡ ለዚህም ጠንካራ ተቋማት መመሥረት አስፈላጊነትን ያሰምሩበታል፡፡ በተለይ ከአምባገነናዊ አገዛዝ ወደ ሕዝባዊ ሥርዓት በሚደረግ ጉዞ በቅድሚያ የሚደረጉ መሰናዶዎች ሳይከናወኑ በጭፍን አምባገነኖችን ከሥልጣን እንዲወርዱ ማድረግ በበርካታ አገራት እንደተደረገው መልኩን የቀየረ አምባገነናዊ ሥርዓት ለመመሥረት እንደሚጋብዝ ይናገራሉ፡፡ ከዚህ አንጻር የሕዝብ ንቃተ ኅሊና መዳበር፣ የእርሰበርስ ውይይት መጀመር፣ የተቋማት መመሥረት፣ … ወሳኝነት ያላቸው ቅድመ ሁኔታዎች እንደሆኑ ያሰምሩበታል፡፡

*********************
“ይህ አገዛዝ በቃው! አንፈልገውም! 27 ዓመት + 1 አንቀበልም!”
ቡርኪናፋሶ ከአምባገነን ወደ አምባገነን?
http://www.goolgule.com/it-is-over-for- … rkinafaso/

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ቡርኪና ፋሶ ከፈረንሳይ ቅኝ ነጻ ከወጣችበት እ.ኤ.አ. 1984 ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ የምታውቀው ሁለት መሪዎች ብቻ ነው። አፍሪካዊው ቼ ጉቬራ ይባሉ የነበሩት ቶማስ ሳንካራን እና ብሌዝ ኮምፓዎሬን ። ብሌዝ ኮምፓዎሬ ወደ ስልጣን የመጡት ቶማስ ሳንካራ በወታደሮች መገደላቸውን ተከትሎ እ.ኤ.አ. በ1987 ዓ.ም. ነበር።

ኢትዮ -ኮሎኝ የተባለው የስፖርት እና የባህል ማህበር በኮሎኝ ከተማ ከአንድ የስደተኞች ምክር መስጫ ማዕከል ጋር በመተባበር የብዙ ስደተኞችን ጥያቄ የሚመልስ ድረ ገፅ በአማርኛ ተርጉሞ ለስደተኞች አቅርቧል። ስለዚሁ ድረ ገፅ በዛሬው የወጣቶች ዓለም እናወራለን።

የዛኑ-ፒ ኤፍ ፖለቲከኞች አንጋፋዉን የነፃነት አርበኛ እና መሪ ፕሬዝዳንት ሮበርት ሙጋቤን ለመተካት እርስ በርስ እየተጠላለፉ ናቸዉ።ከዛኑ-ፒ ኤፍ ጋር ተጣማሪ መንግሥት የመሠረተዉ የዴሞክራሲያዉዊ ለዉጥ ንቅናቄ (MDC) አንዳድ ፖለቲከኞችም የፓርቲዉ መሪ ሞርጋን ሻንግራይ ሥልጣን ያስረክቡ የሚል ጥያቄ አንስተዋል

የኢጋድ አደራዳሪዎች ኬንያዊዉ ጄኔራል ላዛሮ እና ኢትዮጳዊዉ አምባሳደር ስዩም መስፍን በጋራ በሰጡት መግለጫ ለደቡብ ሱዳን ጦርነት መቀጠል የሁለቱንም ተፋላሚ ሐይላት መሪዎች ወቅሰዋል።

Image
ስብሓት ነጋና የኤርትራ ጉዳይ
ስብሓት ነጋ በቪኦኤ የትግርኛ ፕሮግራም ላይ የሚከተለውን ብሏል (ግርድፍ ትርጉም ነው፤ ሙሉ ዝግጅቱ ሲቀርብ ወደ አማርኛ እንመልሰው ይሆናል) ፥
«የኤርትራ ጉዳይ የቅኝ ግዛት ችግር ነው የሚለው አመለካከታችን ዳግም መፈተሽ አለበት። የአገዛዝ ችግር እንጂ የቅኝ ግዛት አልነበረም።»
ለምን አሁን???
«የኤርትራ ህዝብ ለነፃነት ከነበረው ጉጉትና ከደረሰበት ግፍ አንፃር፤ ነፃነቱን «በመረጠው መንገድ» መቀዳጀቱ ባያስቆጨንም፤ ችግሩ «የቅኝ ግዛት ችግር» ነበር የሚለው አመለካከታችን መስተካከል ያለበት ይመስለኛል።»
አሁንም በድጋሚ፤ ለምን አሁን???
የኤርትራ ጉዳይ የቅኝ ግዛት ነበር የሚል አመለካከት የህውሓትና የሻዕቢያ ብቻ እንጂ የማንም እንዳልነበር ግልፅ ነው። (የኤርትራ ህዝብ ሳይቀር ከኢትዮጵያ ጋር በአብሮነት መቀጠል እንደሚፈልግ ቀደም ሲል በጥናት የተረጋገጠ መሆኑን በዘውዴ ረታ መፅሃፍ ላይ «የኤርትራ ጉዳይ» ያነበብኩ መሰለኝ። ) ሟች መለስ እስከ ግብአተ መሬቱ ፍፃሜ ድረስ ኤርትራ የኢትዮጵያ ቅኝ ተገዢ እንደነበረች ሲያውጅ ኖሯል። ችግራቸው የአስተዳደር እንጂ የቅኝ ተገዢነት አይደለም ያሉ ኢትዮጵያውያን ተገድለዋል፤ ታስረዋል፤ ተሳደዋል፤ ወዘተ። ችግሩ የቅኝ ግዛት ነው፤ ጥያቄውም የነፃነት ጥያቄ ተብሎ፤ ያለ ህዝበ ውሳኔ መፍትሄ ተሰጥቶበታል። መፍትሄውም ጦስና ግሳንግሱን በሁለቱ ህዝብ መሃል አራግፎ፤ ኤርትራን ህዝብ አልባ ዋሻ አድርጓታል። ስንት ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን በነሱ ምክንያት አልቀዋል።
ይሄ የአገሪቱ ብቸኛ «ሉዓላዊ ግለሰብ»፤ ይህ አመለካከታቸው ዛሬ መታረም እንዳለበት የሚነግረን ለምን ይሆን? ምን ተንኮል አስቦ ነው??

በሽብር ተጠርጥረው በማዕከላዊ እስር ላይ የሚገኙት እነ ሀታብሙ አያሌው ልደታ ፍ/ቤት ቀረቡ
**************************************
በማዕከላዊ እስር ቤት ከ115 ቀን እስር በኋላ ዛሬ ክስ ተመሰረተባቸው
****************************

<a href=”http://www.abugidainfo.com/amharic/wp-content/uploads/2014/07/10557351_10202411521670248_5400861717310665444_n.jpg”><img src=”http://www.abugidainfo.com/amharic/wp-content/uploads/2014/07/10557351_10202411521670248_5400861717310665444_n.jpg” alt=”10557351_10202411521670248_5400861717310665444_n” width=”252″ height=”144″ class=”alignleft size-full wp-image-15235″ /></a>
በትላናው ዕለት አራዳ ምድብ ችሎት ይቀርባሉ ተብሎ ቢጠበቅም ሊቀርቡ ያልቻሉት የፓርቲ አመራሮች፣ በድብቅ ትላንትናውኑ ልደታ ፍ/ቤት መቅረባቸውንና ዳኛ ባለመሟላቱ ለዛሬ ጠዋት ተቀጠረው ነበር፡፡ ዛሬ ጠዋት ከታሰሩበት ማዕከላዊ ፍርድ ቤ/ት ፖሊስ አጅቦ ቢያመጣቸውም ከቀኑ በግምት 5፡00 ሰዓት አካባቢ 4ኛ ወንጀል ችሎት ካስገቡዋቸው በኋላ፣ 6፡00 ሰዓት ሲሆን ወደ መኪናቸው በመመለስ ከሰዓት በኋላ በ8፡00 ሰዓት እንደሚቀርቡ ለመጣው ታዳሚ ከችሎት አስተናጋጇ በመገለጹ፣ ከሰዓት በ 8፡00 ሠዓት 4ኛ ወንጀል ችሎት ቀረቡ፡፡ እስከ ዛሬ ድረስ ችሎት መግባት ይከለከል የነበረ ሲሆን በዛሬው ዕለት ግን ታዳሚው ችሎት እንዲገባ ተፈቀደ፡፡

በችሎቱ የቀረቡት 10 ተከሳሾች ሲሆኑ እነሱም፡-

1ኛ. ተከሳሽ የአ/አ ዩኒቨርስቲ ማስትሬት ተማሪ የሆነው ወጣት ዘላለም ወርቅአገኘሁ
2ኛ. ሃብታሙ አያሌው
3ኛ. ዳንኤል ሺበሺ
4ኛ. አብርሃ ደስታ
5ኛ. የሺዋስ አሰፋ
6ኛ. ዮናታን ወልዴ
7ኛ. አብርሃም ሰለሞን
8ኛ. ሰለሞን ግርማ
9ኛ. ባህሩ ደጉ
10ኛ. ተስፋዬ ተፈሪ ናቸው፡፡

በችሎቱ ላይ 3 ዳኞች የተሰየሙ ሲሆን የመሀል ዳኛው የዘገየነው ዳኞች ባለመሟላታቸው መሆኑን ከገለጹ በኋላ ተከሳሾችን ክሱ እንደደረሳቸው ጠየቁ፡፡ ተከሳሶችም ክሱ እንዳልደረሳቸው መለሱ፡፡ ክሱ የቀረበው ጥቅምት 20 ቀን2007 ዓ.ም መሆኑን ዳኛው ከገለጹ በኋላ ክሱ እንዲታደላቸው አደረጉ፡፡

ከ1ኛ እስከ 5ኛ ያሉት ተከሳሶች አቃቤ ህግ ያቀረበባቸው ክስ ህገመንግስቱንና ህገመንግስታዊ ስርዓቱን ለመናድ የሚንቀሳቀሰው ራሱን ግንቦት 7 የሚባለው ድርጅት አባል በመሆን ከድርጅቱ አባሎች ጋር ግንኙነት በመፍጠር፣ አባላት በመመልመል፣ ህጋዊ የፖቲካ ፓርቲን ሽፋን በማድረግ ሕዝቡ በመንግስት ላይ እምነት እንዲያጣ በማድረግ፣ በደቡብ ክልል ግጭት እንዲቀሰቀስ በማድረግ መግለጫ በመስጠት፣ እንዲሁም ትህዴን ከሚባል ድርጅት ጋር በህቡዕ ግንኙነት በመፍጠር የሽብር ተልዕኮ ለመፈጸም በዋና የወንጀል ድርጊት ተካፋይ በመሆን የተከሰሱ ሲሆን ከ6ኛ እስከ 10ኛ ድረስ ያለት ተከሳሾች ክስ ህገመንግስቱንና ህገመንግስታዊ ስርዓቱን ለመናድ ማህበራዊ ተቋማትን ለማፈራረስ የሽብር ድርጊቱን ለመፈጸም በውጭ ሀገር በተማሩት የማህበራዊ ድህረ ገጽ አጠቃቀም የተለያዩ የፌስ ቡክ አካውንቶችን በመጠቀም ለድርጊቱ መፈጸም ሲሰሩ እንደነበር የአቃቤ ህግ ክስ ያመለክታል፡፡

እንደ ቅደም ተከተሉ ክሳቸው ተነቦ ካለቀ በኋላ ዳኛው ተከሳሾች ጠበቃ ማቆም ትችላላችሁ ወይስ መንግስት ያቁምላችሁ ብለው በጠየቁት መሰረት ከ8ኛው ተከሳሽ በስተቀር ሁሉም ጠበቃ እንደሚያቆሙ ገለጹ፡፡ ነገር ግን እኛ ጠበቃ ብናቆምም ከታሰርንበት ሀምሌ 1 ቀን ጀምሮ ከጠበቆቻችን ጋር መገናኘት አልቻልንም ክቡር ፍ/ቤቱ ልንገናኝ እንድንችል ትዕዛዝ ይስጥልን፣ እስካሁን ከታሰርንበት ማዕከላዊ ወደ ማረሚያ ቤት እንድንሄድ እንዲታዘዝልን በማለት አቶ ሀብታሙ አያሌው ለፍ/ቤቱ ጠይቋል፡፡

አቃቤ ህግ አንቀጽ ጠቅሶ በሽብር የተጠረጠረ የዋስትና መብትን አይፈቅድም ይላል በመሆኑም ተከሳሾች በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ እንደረግ ጠየቀ፡፡

ዳኛውም በዋስትና ላይ ያላችሁን አስተያየት ይዛችሁ ረቡዕ ጥቅምት 26 ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት መልሳችሁን በጽሑፍ ይዛችሁ ቅረቡ ተከሳሾች በአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ይደረግ በማለት ፍርድ ቤቱ አዟል፡፡

በሽብር ተጠርጥረው በማዕከላዊ እስር ላይ የሚገኙት እነ ሀታብሙ አያሌው ልደታ ፍ/ቤት ቀረቡ ************************************** በማዕከላዊ እስር ቤት ከ115 ቀን እስር በኋላ ዛሬ ክስ ተመሰረተባቸው **************************** በትላናው ዕለት አራዳ ምድብ ችሎት ይቀርባሉ ተብሎ ቢጠበቅም ሊቀርቡ ያልቻሉት የፓርቲ አመራሮች፣ በድብቅ ትላንትናውኑ ልደታ ፍ/ቤት መቅረባቸውንና ዳኛ ባለመሟላቱ ለዛሬ ጠዋት ተቀጠረው ነበር፡፡ ዛሬ ጠዋት ከታሰሩበት ማዕከላዊ ፍርድ ቤ/ት ፖሊስ አጅቦ […]

Image
አብርሃ ደስታ የሁለት ድርጅቶች አባል ነው የሚል ክስ ተመስርቶበታል
#Ethiopia #UDJ #Blueparty #Ginbot7 #EPRDF #MinilikSalsawi

– ወደ አዲስ አበባ ማረሚያ ቤት እንዲዘዋወሩ ታዟል
– እነ የሽዋስን ጨምሮ 10ር ተጠርጣሪዎች በይፋ ክስ ተመሰረተባቸው

Minilik Salsawi
በልደታ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራተኛ ምድብ ወንጀል ችሎት ዛሬ ጥቅምት 21/2007 ዓ.ም ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ በተሰየመው ችሎት 10 ተከሳሾች በፌደራል አቃቢ ህግ በይፋ ክስ ተመሰረተባቸው፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ከ100 ገጽ በላይ የክስ ቻርጅ የተነበበላቸው ሲሆን ከክስ ቻርጁ ጋር ከ300 ገጽ በላይ የምርመራ ሰነድ ቀርቦባቸዋል፡፡

የክሱ መዝገብ የተከፈተው ዘላለም ወርቃገኘሁ በተባለውና ‹‹የግንቦት 7 አመራር ነው፡፡›› ተብሎ ክስ በተመሰረተበት ግለሰብ ሲሆን በዚህ የክስ መዝገብ የተካተቱትም፡-

1ኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ
2ኛ ተከሳሽ ሀብታሙ አያሌው
3ኛ ተከሳሽ ዳንኤል ሺበሺ
4ኛ ተከሳሽ አብርሃ ደስታ
5ኛ ተከሳሽ የሽዋስ አሰፋ
6ኛ ተከሳሽ ዮናታን ወልዴ
7ኛ ተከሳሽ አብርሃም ሰለሞን
8ኛ ተከሳሽ ሰለሞን ግርማ
9ኛ ተከሳሽ ብርሃኑ ደጉ
10ኛ ተከሳሽ ተስፋዬ ተፈሪ ናቸው

ለሁሉም ተከሳሾች ከዛሬ በፊት ክስ እንዳልደረሳቸውና ዛሬ ፍርድ ቤት ውስጥ እንደተሰጣቸው ታውቋል፡፡ በችሎቱ 6ኛ ተከሳሽ ከሆነው ዮናታን ወልዴ በስተቀር ሁሉም ያለ ጠበቃ የቀረቡ ሲሆን ጠበቃዎቹ ያልቀረቡበት ምክንያትም ጠበቆቹ ደምበኞቻቸው የሚቀርቡበት ቦታና ጊዜ ስላልተነገራቸው እንዲሁም ቀደም ብለው እንዳይገናኙ በመደረጋቸው መሆኑን አቶ ኃብታሙ አያሌው ችሎቱ ላይ ተናግሯል፡፡

ከሳሹ የፌደራል አቃቢ ህግ በ1996 የወጣው የወንጀል ህግ እና የጸረ ሽብር ህግ ጠቅሶ ክስ ያቀረበ ሲሆን ክሶቹ በሁለት ዋና ዋና ጭብጦች ቀርበዋል፡፡ የመጀመሪያው ጭብጥ ‹‹ከሽብርተኛ ቡድኖች ጋር በጋራ በመስራት›› የሚል ሲሆን ‹‹ህገ መንግስቱንና ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ፣ የመንግስትን መሰረተ ልማት በማፈራረስ፣ ህዝብን ለአመጸ በማነሳሳት መንግስትን መለወጥ አላማው አድርጎ ከሚሰራውና ራሱን ግንቦት 7 ብሎ ከሚጠራው ቡድን ጋር አባል በመሆንና በወንጀል ድርጊቶች በመሳተፍ›› በሚል ቀርቧል፡፡

ሁለተኛው የክስ ጭብጥ ‹‹የሽብር ቡድን አመራር በመሆን›› የሚል ሲሆን በተለይም የአንደኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ ‹‹የሽብር ቡድኑ አመራር በመሆንና አባል በመመልመል›› በሚል የክስ ጭብጥ ቀርቦበታልል፡፡

ከ2-5ኛ የክስ መዝገብ የሚገኙት ማለትም ሀብታሙ አያሌው፣ ዳንኤል ሺበሽ፣ አብርሃ ደስታና የሸዋስ አሰፋ ‹‹ህጋዊ የፖለቲካ ፓርቲን ከለላ በማድረግ ግንቦት 7 የተባለውን የሽብር ቡድን አላማ ለማሳካት ተንቀሳቅሰዋል፡፡ ፋሲል የኔ ዓለምና ሌሎች የሽብር ቡድኑ አባላት ጋር በስልክ በመነጋገርና በማህበራዊ ድህረ ገጸ የተለያዩ መልዕክቶችን ተለዋውጠዋል›› የሚል ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡ አብርሃ ደስታ ከግንቦት 7 በተጨማሪ ‹‹ደምኢት የተባለ ቡድን አባል ነው፡፡›› የሚል ክስ ቀርቦበታል፡፡

በስተመጨረሻም ፍርድ ቤቱ ሁለት ጉዳዮች ላይ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ አንደኛው ረቡዕ ጥቅምት 26/2007 ዓ.ም 3 ሰዓት ተከሳሾቹ ዋስትና ይሰጣቸው አይሰጣቸው በሚለው ጉዳይ ላይ ፍርድ ቤቱ ከተከሳሾቹ ጠበቆች ጋር ተማክሮ ውሳኔ ይሰጣል ተብሏል፡፡ በሁለተኛነት ተጠርጣሪዎቹ ባቀረቡት አቤቱታ መሰረት ቀደም ሲል ለአራት ወራት ወደቆዩበት ማዕከላዊ እስር ቤት እንዳይመለሱ ፍርድ ቤቱን ስለጠየቁ ፍርድ ቤቱ በአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት (3ኛ) እንዲቆዩ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡

ተከሳሾቹ ትናንት ጥቅምት 20/2007 ዓ.ም አራዳ ምድብ ችሎት ይቀርባሉ ተብሎ የነበር ቢሆንም ሳይቀርቡ ቀርተዋል፡፡ በተመሳሳይ ዛሬ ጥቅምት 21/2007 ዓ.ም ጠዋት ወደ ልደታ ፍርድ ቤት ተወስደው የነበረ ቢሆንም እንደገና ወደማዕከላዊ ተመልሰው ከሰዓት እንዲቀርቡ ተደርገዋል፡፡

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬ፣ ጥቅምት ፳፩ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም. ዐሥረኛ ቀን የቀትር በፊት ውሎው ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስን በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ ኾነው እንዲሠሩ መደበ፡፡ ብፁዕነታቸው፣ ትላንት በተጠናቀቀው የሕገ ቤተ ክርስቲያን ማሻሻያ፣ የፓትርያርኩ ልዩ ሀገረ ስብከት ኾኖ በተደነገገው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት፣ የፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ ኾነው እንዲሠሩ በምልአተ ጉባኤው የተመደቡት …

“አንድ ሰው በፖሊስም ሆነ በሌላ የሕግ አስፈጻሚ አካል ለሚቀርብለት ጥያቄ፤ ካልፈቀደ በስተቀር መልስ ያለመስጠት መብት አለው።” አቶ ደረጀ ሰምሴ ቡልቶ፤ የአሜሪካ ድምጽ ያነጋገራቸው የሕግ ባለሞያ።

ነገም እኛ ከሕዝብ ጥያቄ እንደማናመልጥ ልናውቅ ግድ ይለናል!!!
Minilik Salsawi
እውነትን ብንውጣት ምናለ? በሃሰት ሕዝብን እያታለልን እስከመቼ እንኖራለን ? እስከመቼ ያልሆነ እንደሆነ ያልተደረገ እንደተደረገ እስከመቼ እየተደበቀ እየተሹለከለከ። የሕዝብን የነጻነት እና የመብት ጥማትን ተገን አድርገን በማይረቡ ወንፊቶች ስር ተሸሽገን የተሸሸግን መስሎን እየታየን ለምን ? የማያዛልቅ ጸሎት …. ባለፉት አመታቶች እኮ እያየን ነው ምንም ውጤት የለም አላየንም አልሰማንም የምንልበት ደረጃ ላይ ነን ያለነው። ታዲያ ምንን እንመን ? ማን እውነትን ይዟል እንበል? በፕሮፓጋንዳ አብዮት ተወጥረን እስከመቼ?

ያሌለ ነገር እንዳለ ያልተሰራ እንደተሰራ አይ አንቺ መሬት !! አዎን ያው እውነትን እንያዝ ለህዝብ ከህዝብ በህዝብ የሆነ ስኬታማ ትግል እናድርግ በማለታችን ምናልባት ልንሰደብ ልንዋረድ ልንዘረጥጥ እንችላለን ለምን በፕሮፓጋንዳ የሞሉን እውነትን መዋጥ ስለሚከብዳቸው መግቢያ ሲጠፋ ግለሰቦች ላይ ይዘምታሉ። ግለሰቦችን ከኢትዮጵያዊ ጨዋነት ውጪ ይሳደባሉ ያዋርዳሉ ይወነጅላሉ። ትላንትና ምን አሉ? ዛሬ ምን አሉ? ነገ ምን ይላሉ ? በትግል ላይ ነን እያሉን መስመሩ አያዋጣም ያሉ ሰዎችንስ እንዴት አስዋጡ ? እያንዳንዱን መለስ ቀለስ እያልን በፖለቲካ እና አገራዊ ህዝባዊ ምንዛሬ ላይ ካጤነው መጭውን ጊዜ ለመወሰን አንገታችንን የሚያስደፋን ነገር አፍንጫችን ስር ይወተፋል።

በግልጽ መውጣት ሲገባን ለሌላ የተለመደ ፕሮፓጋንዳ መስመር እና ስልት ቀይረን ስንመጣ ቀን ጠብቆ ከህዝብ ጥያቄ ማምለጥ እንደማይቻል ለመናገር እንደፍራለን። አለማቀፍ ድርጅቶች እና ሚዲያዎች የእሚነግሩን ሌላ መሬት ላይ ያለው ሌላ ፕሮፓጋንዳው የሚነግረን ሌላ ታዲያ የነጻነት ጥማታችንን እንዴት እንወጣ። ያለን የመጨረሻ እድል ሕዝቡ ሆ ብሎ አደባባይ እንዲወጣ ከማድረግ ውጪ አለ አለን በሚሉት ላይ መተማመኑ እንደማያዋጣ ሊሰመርበት ይገባል እኔም እንደ ዜግነቴ የኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባኛል አውቅልሃልሁ የሚል የህሰት ፕሮፓጋንዳ አንገሽግሾናል ። ነጻነት በጃችን ነውና ራሳችንን ነጻ እናውጣ ።

በርካታ ቁጥር ያላቸው የመከላከያ ሰራዊት አባላት በቴፒ ከተማ በብዛት መታየታቸውን ተከትሎ መንግስት የከተማውን ህዝብ አርብ ጥቅምት 20፣ በትልቁ አዳራሽ በመሰብሰብ፣ በአካባቢው የሚታየውን ችግር በጋራ እንፍታ በማለት ጥሪ አቅርቧል። ለግማሽ ቀን በተካሄደው ስብሰባ ነዋሪዎችና የመንግስት ባለስልጣናት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ሲወዛገቡ አርፍደው ሳይግባቡ መለያየታቸውን በስብሰባው የተሳተፈው ወኪላችን ገልጿል።
የከተማዋ ነዋሪዎች ችግሩን የምትፈጥሩት እናንተ ሆናችሁ ሳለ እኛን መፍትሄ አምጡልን ማለታችሁ ተገቢ አይደለም በማለት በከተማዋ የሚታዩ የጸጥታና የኢኮኖሚ ችግሮችን በማንሳት ለባለስልጣኖቹ ሲያስረዱ ውለዋል።
ሀሙስ ከሰአት በሁዋላ በቴፒ መውጫ በሮች ላይ በመቶዎች የሚቆጠሩ ወታደሮች ቅኝት ማድረግ መጀመራቸውና አልፎ አልፎ የተኩስ ድምጽ መሰማቱ በከተማው ህዝብ ላይ አለመረጋጋት መፍጠሩን ነዋሪዎች ገልጸዋል
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ በቴፒ ካምፓስ ፈንጅ ተገኝቷል በሚል የተጠናከረ ፍተሻ ሲካሄድ ሰንብቷል።

የሸኮና መዠንገር ታጣቂዎች ከፌደራልና ከመከላከያ ሰራዊት አባላት ጋር አልፎ አልፎ የተኩስ ልውውጥ እንደሚያደርጉም የአካባቢው ሰዎች ተናግረዋል። በሌላ ዜና ደግሞ ለወራት በጋምቤላ በዘለቀው ግጭት ተሳታፊ ናቸው የተባሉ በርካታ የጋምቤላ ክልል ነዋሪዎች ጥቅምት 20/2007 ዓ.ም በአራዳ ምድብ ችሎት መቅረባቸውን ነገረ ኢትዮጵያ ዘገበ። ቁጥራቸው 50 የሚጠጉ የጋምቤላ ነዋሪዎች ፍርድ ቤት መቅረባቸውን ምንጮችን ዋቢ በማድረግ ጋዜጣው ዘግቧል።
“ከጋምቤላ ክልል የመጡት ዜጎች በአራዳ ምድብ ችሎት በቀረቡበት ተመሳሳይ ሰዓት የሸዋስ አሰፋ፣ ሀብታሙ አያሌው፣ ዳንኤል ሺበሺና አብርሃ ደስታ የሚቀርቡ በመሆኑ በዚህ ችሎት ለመታደም የሄደው ህዝብ ከጋምቤላ የመጡትን ዜጎች ተከትሎ በተደረገው ጥብቅ ምክንያት ከፍተኛ ፍተሻ ” መደረጉን ገልጿል፡፡
ጥቅምት 19/ 2007 ዓ.ም ወደ ማታ አካባቢ ከጋምቤላ የመጡ በርካታ ዜጎች በአውቶቡስ ተጭነው ወደ ማዕከላዊ መግባታቸውን የአይን እማኞችን ጠቅሶ ነገረ ኢትዮጵያ ዘግቧል፡፡
መንግስት በክልሉ ካለፈው መስከረም ወር ጀምሮ ግጭት ሲፈጥሩ ነበሩ ያላቸውን ሰዎች መያዙን አስታውቋል። የአካባቢው ግጭት የህወሃት ሰዎች ከሚያደርጉት የመሬት ቅርምት ጋር የተያያዘ መሆኑን ኢሳት ያነጋገራቸው ሰዎች መግለጻቸውን ተናግረዋል።

 

የዩናይትድ ስቴትስ የኤሮኖቲክስና የጠፈር አስተዳደር – ናሳ የጠፈር ምልልሱን ሥራ ለግል ኩባንያዎች ኮንትራት እየሰጠ ነው፡፡

ከእነዚህ የግል ኩባንያዎች አንዱ ዋና መሥሪያ ቤቱ ቨርጂንያ የሆነው ኦርቢታል ሳይንስስ ኮርፐሬሽን በሚያንቀሳቅሰው የ1 ነጥብ 9 ቢሊዮን ዶላር ኮንትራት ኅዋ ውስጥ ለሚገኘው ዓለምአቀፍ ጣቢያ ስንቅና ቁሳቁስ እየላከ ይገኛል፡፡

ከእነዚህ ተልዕኮዎች አንዱ ከትናንት በስተያ ተስተጓጉሏል፡፡

በአንታርስ ሮኬት ከቨርጂንያው ማስወንጨፊያ ከሁለት ቶን በላይ ውኃ፣ ምግብና የምርምር ቁሣቁስ ይዛ የተነሣችው መንኩራኩር ከተተኮሰች ከጥቂት ሰከንዶች በኋላ ፈንድታለች፡፡

በሰው ላይ ምንም ጉዳት አይድረስ እንጂ መላው ጭነት በፍንዳታውና በእሳቱ ወድሟል፡፡

የማስወንጨፊያው ማማ ብዙ ጉዳት ደርሶበታል፡፡

በናሳ…

በቅርቡ፣ ግንቦት ሰባት የተባለው ድርጅት ፣ የተባበሩት መንግስታት የጸጥታው ምክር ቤት የሶማሊያና የኤርትራ ሞኒተሪንግ ግሩፕ በለቀቀዉ ሪፖርት ዙሪያ አንድ መግለጫ አዉጥቷል። አንዳንድ የተወሰኑ ድህረ ገጾች የግንቦት ሰባትን መግለጫ ለጥፈው፣የተባበሩት መንግስታ ሪፖርትን ግን ሳያያይዙ ቀርተዋል። ይሄን ሰነድ በሚከተለው ሊንክ ልታገኙት ትችላላሁ፡

http://www.un.org/ga/search/view_doc.as … S/2014/727

አስገራሚ መረጃዎችን ያካተተ ሰነድ ነው። ሰነዱ አልፎ አልፎ አንዳንድ ጥቃቅን ግድፈቶች አሉት። ለምሳሌ ግንቦት ሰባትን የአማራ ድርጅት እንደሆነ የገለጹበት ሁኔታ አለ። ከዚያ ዉጭ ከሞላ ጎደል በሰነዱ የተካተተው ዝርዝር፣ የሚታመን ነው ብዬ አስባለሁ። በዚህ ሪፖርት ላይ በስፋትና በቅርብ ጊዜ ትንታኔ እንሰጥበታለን። ግን ለአሁን በግርድፉ አንብቤ ከሰነዱ ያገኙኋቸውን ጥቂት አንኰ ነጥቦች እንዳስቀመጥ ይፈቀድልኝ፡

1) ኦ.ኤን.ኤል፣ኤፍ ከአልሻባብ ጋር እንደሚሰራና ማእከሉን ከኤርትራ ወደ ሶማሊያ እንደወሰደና አሁን ኤርትራ ከበስተጀርባ ሆና መደገፏን እንደቀጠለች

2) ኦነግ የሚባል ነገር እንደሌለ

3) የግንቦት ሰባት ጦር ከ50 እስከ 70 እንደሆነ

4) ደሚት የሚባለው ድርጅት ትልቁና ጠንካራው እንደሆነ፣ ከሕወሃት ተቃዋሚነት አልፎ የኢሳያስ ክብር ዘበኛና ቅልብ ጦር እንደሆነና ከባባድ መሳሪያዎች ከኤርትራ ጦር እየተወሰደ ወደ ደሚት እየተሰጠ እንደሆነ

5) ሻእቢያ ለግንቦት ሰባት ሆነ ለሌሎች ድርጅቶች የሚያደርገው እርዳታ የተባበሩት መንግስታትን ዉሳኔ የሚያፈርስ እንደሆነና ግንቦት ሰባት በተባበሩት መንግስታት ራዳር ዉስጥ እንደወደቀ

በቅርቡ ኢትዮጵያያ ሪቪው የተለያዩ ሪፖርቶች ሲያቀርብ እንደነበረ የሚታወቅ ነው። የዚህ ሞኒተሪንግ ቡድን ሪፖርት በአብዛኛው ኢትዮጵያ ሪቪው ካቀረበው ጋር የሚዛመድ ነው።

በተያያዘ ዜና ደግሞ በኤርትራ ዉስጥ ከፍተኛ ተቃዉሞ በኢሳያስ አፈርቂ አገዛዝ ላይ እየተነሳ እንደሆነ ነው። ሃርነር አርቢ የሚባለው ሰላማዊ እንቅስቃሴ ከፍተኛ ድጋፍ እያገኘ ነው። በጦር ሰራዊቱ ዉስጥ ሁሉ ዘልቆ ስለገባ ፣ ኢሳያስ ፊቷን ወደ ደሚት ለማዞር እስኪገደድ ድረስ።
በ ኤርትራ ያለው ሁኔታ ይህ ሆኖ እያለ የተከበሩ ዶር ብርሃኑ ነጋ፣ ከአሜሪካን አገር ሳይወጡ ለምን የግፈኛው አቶ ኢሳያስ ተሟጋች እንደሆኑ አልገባኝም ? እርሳቸውስ እሺ ሌሎች የግንቦት አባላትና ደጋፊዎች፣ እንደ አበበ ገላው፣ መቼ ይሆን አንድ ግለሰብን ማምለክና መከተል አቁመው ለሕዝቡና ለትግሉ የሚጠቅም ነገር የማያደርጉት ?

የግንቢት ሰባት ንቅናቄ የተሳሳተ መንገዱን በአስቸኳይ መመርመር አለበት። ኢሳያስ ሊገነደስ ጥቂት ጊዜ የቀረው የበሰበሰ ዛፍ ነው። እስከመቼ ነው በበሰበሰ ዛፍ ላይ ተንጠልጥለው ትግሉን ብለው ወደነርሱ የመጡትን ለጋ ኢትዮጵያዉያን የሚያስበሉት ?

Image

የሕገ ቤተ ክርስቲያን ማሻሻያው የቅዱስ ሲኖዶሱን ልዕልና በማጽናት ተጠናቀቀ ::

+ የፓትርያርኩ ምሬትና ብስጭት ያሳሰባቸው ብፁዓን አባቶች ሲያረጋጓቸው አመሹ::
+ አቡነ ማትያስ አማካሪዎችን በከፍተኛ ድምፅ ‹‹ውጡልኝ›› በማለት ከፊታቸው አበረሯቸው፡፡

‹‹ከሕዝብ አጋጫችኹኝ፤ ከወንድሞቼ አንድነት ለያችኹኝ፤ ከነገራችኹኝ አንዱንም የተቀበለኝ የለም›› በሚል የተመረሩት አቡነ ማትያስ ምክራቸው ያልሠመረላቸውን ሦስት አማሳኝ አማካሪዎችን በከፍተኛ ድምፅ ‹‹ውጡልኝ›› በማለት ከፊታቸው አበረሯቸው፡፡

ከትላንትናው የስብሰባ ውሎ መጠናቀቅ በኋላ ፓትርያርኩ የነበሩበት የምሬትና የብስጭት ኹኔታ ተነግሯቸው ወደማረፊያቸው የተጠሩት በሹመት ቅድምና ያላቸው ብፁዓን አባቶች÷ አቡነ ማትያስ በተጠሪነት ጉዳይ የተሟገቱለት አቋም የቤተ ክርስቲያን እንዳልኾነ፣ ለአጭር ዕድሜ የኖረው የቤተ ክርስቲያን ሕግ መለወጥ እንደሌለበት ይልቁንም የአማሳኞችንና የባዕዳንን ምክር ከመስማትና ከመቀበል ተጠብቀው ትላንት ከቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ጋራ ኹነው የተከላከሉለትን ሕገ ቤተ ክርስቲያን ማስከበራቸውን ቢቀጥሉ በእርሳቸውና በአባቶች መካከል ያለው ውጥረት ሊረግብና ሊተራረቅ እንደሚችል አመልክተዋቸዋል፡፡

ፓትርያርኩ በትላትናው ምሽት አማሳኞቹን በብስጭትና በምሬትም ቢኾን ከአበረሯቸውና በብፁዓን አባቶች ምክር ከተጽናኑ በኋላ በዛሬው የምልአተ ጉባኤው ውሎ ስብሰባውን በተረጋጋና በመግባባት መንፈስ ሲመሩና ‹‹እናንተ ካላችኁት አልወጣም›› እያሉ በጋራ ሲወስኑ ውለዋል፡፡
የቅዱስ ሲኖዶሱን የበላይነት(ልዕልና) በማረጋገጥ በተጠናቀቀው የሕገ ቤተ ክርስቲያን ማሻሻያ ረቂቅ አጀንዳ፣ ከፓትርያርኩ ጀምሮ እያንዳንዱ ሊቀ ጳጳስና ኤጲስ ቆጶስ(ጳጳስ) ተጠሪነቱ ለቅዱስ ሲኖዶሱ እንደኾነ ጸንቷል፤ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የፓትርያርኩ ልዩ ሀገረ ስብከት ኾኖ ሲሠራበት የቆየው ልምድ በማሻሻያው ተካትቶ እንዲደነገግ ተወስኗል፡፡ በልዩነት ነጥቦቹ ላይ በተላለፉት ውሳኔዎች መሠረት ረቂቁ ተስተካክሎ ሲቀርብ በምልአተ ጉባኤው አባላት ፊርማ እንደሚጸድቅ ይጠበቃል፡፡

በደቡብ አፍሪቃ በሊቀ ጳጳሱ ብፁዕ አቡነ ያዕቆብና በምእመናን መካከል ለተፈጠረው አለመግባባት መፍትሔ ለመስጠት በቀረበው የአጣሪ ልኡክ ሪፖርት ላይ የመከረው ምልአተ ጉባኤው÷ ብፁዕነታቸው ለጊዜው መንበረ ጵጵስናቸውን በናይሮቢ አድርገው በኬንያ፣ በጅቡቲና በሱዳን ተወስነው እንዲሠሩ፤ በደቡብ አፍሪቃ ደግሞ አገልግሎቱ በአድባራት አለቆችና በሰባክያነ ወንጌል ላይ ተመሥርቶ እንዲቀጥል ተወስኗል፡፡ ምልአተ ጉባኤው በሰሜን አሜሪካ በሚገኙት ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ጉዳይ መምከር ጀምሯል፡፡

ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ራሱን የቻለ ሊቀ ጳጳስ ስለመመደብና በሀገረ ስብከቱ የተፈጠሩ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ዙሪያ በነገው ዕለት በመምከር ውሳኔ እንደሚያሳልፍ ይጠበቃል፡፡

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

‹‹ከሕዝብ አጋጫችኹኝ፤ ከወንድሞቼ አንድነት ለያችኹኝ፤ ከነገራችኹኝ አንዱንም የተቀበለኝ የለም›› በሚል የተመረሩት አቡነ ማትያስ ምክራቸው ያልሠመረላቸውን ሦስት አማሳኝ አማካሪዎችን በከፍተኛ ድምፅ ‹‹ውጡልኝ›› በማለት ከፊታቸው አበረሯቸው፡፡ ከትላንትናው የስብሰባ ውሎ መጠናቀቅ በኋላ ፓትርያርኩ የነበሩበት የምሬትና የብስጭት ኹኔታ ተነግሯቸው ወደማረፊያቸው የተጠሩት በሹመት ቅድምና ያላቸው ብፁዓን አባቶች÷ አቡነ ማትያስ በተጠሪነት ጉዳይ የተሟገቱለት አቋም የቤተ ክርስቲያን እንዳልኾነ፣ ለአጭር ዕድሜ የኖረው የቤተ …


 ጸሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
—–
“ሀረር ጌይ” በተሰኘው መጽሐፌ ውስጥ “ሀረር የባግዳድ እህት ናት” የሚል የረጅም ጊዜ ልማድ እንዳለ አጫውአችኋለሁ፡፡ ይህም አመለካከት የመጣው ሁለቱ ከተሞች የሚመሳሰሉ በመሆናቸው ነው፡፡ ከተሞቹን ከሚያመሳስሏቸው የህይወት ዘርፎች መካከል አንዱ እምቅ የስነ-ቃል ሀብታቸው ነው፡፡ ከነዚህ የስነ-ቃል ሀብቶች ቀዳሚ ሆኖ የሚጠቀሰው ተረት ነው፡፡ የባግዳድ ተረቶችን በ“አንድ ሺህ አንድ ሌሊት” በኩል አንብበናቸዋል፡፡ የሀረር ተረቶች ግን በመጽሐፍ ያልተሰበሰቡ በመሆናቸው ከብዙኃኑ አንባቢ ዘንድ ሊደርሱ አልቻሉም፡፡ ስለዚህ እነርሱንም በመጽሐፍ የሚሰበስብ የብዕር ጀግና ያስፈልገናል፡፡
በዚህ ጽሑፍ ሁለት የሀረር ተረቶችን አጋራችኋለሁ፡፡ ሁለቱንም ተረቶች በልጅነቴ የማውቃቸው ቢሆንም በሀረር ከተማ ቆይታዬ በአዲስ መልክ ሰምቼአቸዋለሁ፡፡  
የሓኪም ጋራ መሰንጠቅ
በጥንት ዘመን ሀረር በድርቅ ተመታች፡፡ በድርቁ ሳቢያም ምንጮቿና ወንዞቿ ደረቁ፡፡ አንድ “ኤላ” (የውሃ ጉድጓድ) ግን በተአምራዊ መንገድ ከመጥፋት ተረፈ፡፡ ይሁንና መገኛው ያልታወቀ ትልቅ ዘንዶ ከጉድጓዱ አፋፍ ተቀምጦ “ኤላው የኔ ነው” በማለቱ ከኤላው ውሃ መቅዳት አስቸጋሪ ሆነ፡፡ የሀረር ህዝብ ከኤላው ውሃ መቅዳት ከፈለገ በየዓመቱ አንዲት ቆንጆ ወጣት መገበር እንዳለበት ዘንዶው በአዋጅ አስታወቀ፡፡ የመጠጥ ውሃ ማግኘት የቸገረው የሀረር ህዝብም አማራጭ ሲያጣ ለዘንዶው በመገበር ከኤላው ውሃ ለመቅዳት ተገደደ፡፡
ለዘንዶው የምትሰጠው ልጅ በእጣ ነው የምትወሰነው፡፡ እጣው የሚወጣበት ሁኔታ ግን ፍትሐዊ አልነበረም፡፡ የሀብታምና የባለስልጣናት ልጆች በስውር ዘዴ ከእጣው ውጪ እንዲሆኑ ይደረግና የድሃ ልጆች ብቻ እየተመረጡ ለዘንዶው ይሰጣሉ፡፡ ድሆቹ ይህንን በደል ቢያውቁትም ከሀብታሞቹ ጋር መፎካከር ስለማይችሉ ልጆቻቸውን ለዘንዶው እየገበሩ እምባቸውን መርጨት ግዴታ ሆነባቸው፡፡
ታዲያ በአንድ ዓመት ልጅ የመገበሩ እጣ የደረሰው ለአንዲት “ተቂይ” (አላህን የምትፈራ) ሴት ነው፡፡ ያቺ ሴት አንዲት ልጅ ብቻ ነበራት፡፡ ልጅቷንም ያገኘችው በስተእርጅና ሲሆን ባለቤቷ ከልጅቷ መወለድ በኋላ ሞቶባታል፡፡ በመሆኑም ሴትዮዋ አንድዬ ልጇን እንደ እናትና እንደ አባት ሆና ነው ያሳደገቻት፡፡  እንግዲህ እነዚያ እጣ አውጪዎች ሴትዮዋ በስተእርጅና ያገኛትንና በድህነት ያሳደጋችትን ያቺኑ ልጅ ለዘንዶው እንድትገብር ነው የፈረዱት፡፡
   ይሁንና ሴትዮዋ ልጇን ለዘንዶው አላስረክብም አለች፡፡ የሰፈሯ ሰዎች “እምቢ ካልሽ እኮ ዘንዶው አንቺንም ጨምሮ ይበላሻል” እያሉ ቢያስፈራሯትም ሴትዮዋ ወይ ፍንክች በማለት በቃሏ ጸናች፡፡ ሰዎቹም “በቃ! ውርድ ከራሳችን!! ዘንዶው ቢበላሽ ተጠያቂ አይደለንም” በማለት ብቻዋን ተዋት፡፡ ወደ ዘንዶው ሄደውም ስለሴትዮዋ እምቢተኝነት ነገሩት፡፡ ከዚያም በየቤታቸው ሆነው ተከታዩን ነገር መጠባበቅ ጀመሩ፡፡ ሴትዮዋም ልጇን ከምታስረክብበት ዕለት በፊት ባለው ምሽት የዘንዶውን ጭካኔና የእጣ አውጪዎቹን አሻጥር እያነሳች ፈጣሪዋን ስትለምን አደረች፡፡ በማግስቱም ከቤቷ ቁጭ ብላ ዘንዶው የሚያመጣውን መቅሰፍት መጠባበቅ ጀመረች፡፡
 ሴትዮዋ ልጇን የምታስረክበው ከጧቱ በሶስት ሰዓት ገደማ የነበረ ቢሆንም ዘንዶው በሰዓቱ ግብሩን አላገኘም፡፡ በዚህም የተናደደው ዘንዶ ሴትዮዋን ከነልጅቷ ሊውጣት እጅግ በሚያስፈራ ግርማ ወደ ቤቷ መጓዝ ጀመረ፡፡ የሰፈሩ ሰዎችም “ሊበላት ነው፤ ሴትዮዋ አለቀላት!” እያሉ በአድናቆትና በተመስጦ ትርዒቱን ይመለከቱ ገቡ፡፡
ዘንዶው አቧራውን እያቦነነ ከሴትዮዋ ቤት አጠገብ ደረሰ፡፡ ሴትዮዋንም ሊውጣት መንደርደር ጀመረ፡፡ ፍላጎቱን ከመፈጸሙ በፊት ግን ፈጣሪ ውጥኑን አከሸፈበት!! እጅግ ግዙፍ የሆነ ንስር (አሞራ) ከሀረር በስተሰሜን አቅጣጫ በመምጣት ዘንዶውን ከመሬት ላይ “ላጥ” አድርጎ አነሳው፡፡ ንስሩ ዘንዶውን ወደ ሰማይ በማውጣት ላይ ሳለም የዘንዶው ጭራ ሀረርን በደቡብ በኩል የከበበውን የሀኪም ጋራን በሁለት ቦታ ከፈለው፡፡
 
  ያ ከይሲ ዘንዶ ፈጣሪዋን የምትፈራው ሴትዮ ባደረገችው ጸሎት ተወገደ፡፡ በሀረር ከተማ ላይ የተጣለው ልጅን የመገበር ግዴታም ለዘልዓለሙ ተነሳ!! ይሁንና ያኔ በዘንዶው ጭራ የተከፈሉት ሁለቱ የሐኪም ጋራ ኮረብቶች በአንድ ላይ ሳይመለሱ እስከዚህ ዘመን ድረስ ዘለቁ፡፡
አሚር ሆይ! አንተ “ኸይሩ”ን ብቻ አስብ፤ “ለሸሩ” ባለቤት አለውና!!
——
በጥንት ዘመን አንድ ቅን ሰውዬ በሀረር ከተማ ይኖር ነበር፡፡ ይህ ሰው ሁለት ልጆች ነበሩት፡፡ የመጀመሪያው ልጁ ርህሩህና የዋህ የነበረ ሲሆን ሁለተኛው ልጁ ግን ተንኮል እየፈጠረ ሰዎችን ማሞኘትና መሳቅ ይወድ ነበረ፡፡ አባትዬው ትንሹን ልጅ ቢመክረው አልሰማ እያለ አስቸገረው፡፡ ስለዚህ በትንሹ ልጅ ተስፋ የቆረጠው አባት ዘወትር ትልቁን ልጅ እየጠራው “ልጄ ሆይ! አንተ ደጉን ብቻ አስብ፡፡ ለተንኮል ባለቤት አለውና” የሚል ምክር ይሰጠው ነበር፡፡ አባት በዚህም ሳያበቃ ለትልቁ ልጅ “ዓሊ ኸይሮ” (ቅን አሳቢው ዓሊ) የሚል ቅጽል አወጣለት፡፡ ትንሽየውን ግን “ዓሊ ሸርሮ” (ተንኮለኛው ዓሊ) በማለት ሰየመው፡፡
 
   ከጊዜ በኋላ አባት የአዱኛውን ዓለም ተሰናበተ፡፡ በዚህም የተነሳ ልጆቹ ተቸገሩ፡፡ ኑሮ በጣም ከበዳቸው፡፡ በመሆኑም ወደ ሀረሩ አሚር ሄደው በችግር መቆራመዳቸውን ነገሩት፡፡ አሚሩ በአጋጣሚ የቤተ መንግሥት ከብቶችን የሚጠብቅ ሰው ይፈልግ ነበርና ወንድማማቾቹ ለእረኝነት እንዲቀጠሩ ጠየቃቸው፡፡ ወንድማማቾቹ ለስራው የሚሰጣቸውን ምንዳ ሲጠይቁት ከሚበሉት ምግብና ከሚለብሱት ልብስ በተጨማሪ በዓመቱ መጨረሻ ላይ አንዲት ጊደር እንደሚያገኙ አሳወቃቸው፡፡ ወንድማማቾቹም ከአሚሩ የቀረበላቸውን ጥያቄ በደስታ ተቀበሉትና ስራቸውን ጀመሩ፡፡
ወንድማማቾቹ በመቶዎች የሚቆጠሩትን የአሚሩን ከብቶች “አው-ሓኪም”፣ “አቦከር” እና “ሸድዳ ዋ መድዳ” ወደሚባሉት ተራሮች እያሰማሩ በትጋት ማገዱን ተያያዙት፡፡ ስራቸውን በደህና ሁኔታ እያከናወኑ ዓመቱን አገባደዱት፡፡ የዓመቱ መጨረሻ እየተቃረበ ሲመጣ ግን የ“አሊ ሸርሮ” ልብ በግለኝነት መመታት ጀመረች፡፡ ለምንዳ የምትሰጣቸውን ጊደር ጉዳይ ሲያስብ አዕምሮው በስስት ተወጠረ፡፡ በመሆኑም “ወንድሜን ገድዬው ጊደሪቱን የግሌ ማድረግ አለብኝ” በማለት ወሰነ፡፡ እቅዱንም በአው ሓኪም ተራራ ላይ ለመፈጸም ቆረጠ፡፡
ወንድማማቾቹ ከብቶቹን ወደ “ሓኪም” ተራራ በወሰዱበት በአንደኛው ቀን “አሊ ሸርሮ” ለወንድሙ “አንተ ከዚህ ሆነህ ከብቶቹን ጠብቅ፤ እኔ ተራራው ላይ ወጥቼ ለምለም ሳር እንዳለ ልይና ልመስ” አለው፡፡ “አሊ ኸይሮ”ም በቀረበለት ሃሳብ ተስማምቶ ከብቶቹን ለብቻው መጠበቅ ጀመረ፡፡ “አሊ ሸርሮ” ከተራራው ላይ እንደ ወጣ ትልቅ ድንጋይ አንቀሳቅሶ ወንድሙ ወዳለበት አቅጣጫ ቁልቁል ለቀቀው፡፡ ድንጋዩ ከተራራው ላይ እየተንከባለለ ወረደ፡፡ ከ“አሊ ኸይሮ” አጠገብ ሲደርስ ግን ወደ ወርቅነት ተቀየረ፡፡ “አሊ ኸይሮ” በዚህ ተአምር ተገረመ፡፡ “ወደ ወርቅነት የተቀየረው ድንጋይ እኔና ወንድሜ ሀብታም እንድንሆን ዘንድ ከአላህ የተሰጠን ነው” በማለት በደስታ ፈጣሪውን አመሰገነ፡፡ የተፈጠረውንም ተአምር ለወንድሙ ለመንገር በጉጉት ይጠባበቅ ጀመር፡፡
 
 “አሊ ሸርሮ” በበኩሉ “አሊ ኸይሮ በድንጋይ በመገደሉ “ጊደሪቱ የኔ ብቸኛ ሀብት ትሆናለች” እያለ በደስታ ከተራራው ወረደ፡፡ ወንድሙ ወደነበረበት ቦታ ሲደርስ ግን ያልጠበቀውን ነገር አየ፡፡ “ይህ ወርቅ ከየት ነው የመጣው?” በማለትም ወንድሙን ጠየቀው፡፡ አሊ ኸይሮም “አንድ ትልቅ ድንጋይ ከተራራው ላይ እየተንከባለለ መጥቶ እኔ ጋ ሲደርስ ይህንን ወርቅ ሆነ” በማለት መለሰለት፡፡ “አሊ ሸርሮም “ድንጋዩ የተንከባለለው ከስሩ የነበረውን ለምለም ሳር ለማየት ብዬ ስላንቀሳቀስኩት ነው፤ እዚህ ደርሶ ወደ ወርቅ ከተቀየረ እኔም የራሴ ወርቅ ሊኖረኝ ይገባል፡፡ ስለዚህ አንተም በተራህ ወደ ተራራው ውጣና ሌላ ድንጋይ አንከባልልኝ” አለው፡፡
“አሊ ኸይሮ”ም ከወንድሙ የሰማውን ሳይጠራጠር ወደ ተራራው ወጥቶ ትልቅ ድንጋይ አነሳና “አሊ ሸርሮ” ወደነበረበት አቅጣጫ አንከባለለው፡፡ ይሁንና ድንጋዩ ወደ ወርቅነት ሳይቀየር “አሊ ሸርሮ”ን ጭፍልቅ አድርጎ ገደለው፡፡ “አሊ ኸይሮ” ከተራራው ወርዶ ወንድሙ ወደነበረበት ስፍራ ሲሄድ ወንድሙ ሞቶ አገኘው፡፡ በዚህም በጣም ደነገጠ፡፡ ወደ ሀረሩ አሚር ሄዶም የተከሰተውን ሁሉ አንድ በአንድ ነገረው፡፡ ሆኖም አሚሩ ሊያምነው አልቻለም፡፡ “ወንድምህን ራስህ ነህ የገደልከው” በማለትም ከሰሰው፡፡ በመሆኑም “ነፍስ ያጠፋ ሰው ይገደል” በሚለው የሀረር ከተማ ጥንታዊ ህግ መሰረት በድንጋይ ተጨፍልቆ እንዲሞት ተፈረደበት፡፡
 
“አሊ ኸይሮ”ም ፍርዱ ሊፈጸምበት ወደ “ሐኪም” ተራራ ግርጌ ተወሰደ፡፡ ከተራራው ላይ ትልቅ ድንጋይ ተንዶ ቁልቁል ተወረወረበት፡፡ ይሁንና ድንጋዩ “አሊ ኸይሮ” አጠገብ ሲደርስ እንደገና ወርቅ ሆኖ ቁጭ አለ፡፡ የቅጣቱን አፈጻጻም ለማየት በስፍራው ተሰብስቦ የነበረው የሀረር ህዝብም በተፈጠረው ነገር በጣም ተገረመ፡፡ “ይህ ተአምር ልጁ ወንድሙን እንዳልገደለ በሐቅ ይመሰክራል” በማለትም ደመደመ፡፡ የሀረሩ አሚር በበኩሉ “የዓሊ ኸይሮ”ን ተአምር ሲያይ “በህይወቴ ስፈልገው የነበረውን ሐቀኛ ሰው ዛሬ አገኘሁት” የሚል ቃል ተናገረ፡፡ “አሊ ኸይሮ”ንም የዙፋኑ ወራሽ በማድረግ ሾመው፡፡
—–
ወደ ሀረር ከተማ ከመጣችሁ “Amiroo! Kheyruma yaadi, Sharriin abbuma eeydii” የሚል አባባል ትሰማላችሁ፡፡ “አሚር ሆይ! አንተ ኸይሩን ብቻ አስብ፤ ለሸርሩ ባለቤት አለውና” እንደማለት ነው፡፡ ከአባባሉ ጀርባ ብዙ ታሪኮች ይነገራሉ፡፡ ከነዚያ ታሪኮች መካከል አንዱ ከላይ የቀረበው ተረት ነው፡፡
 በተረቱ እንደተገለጸው ተንኮለኛ ሰው በለስ የቀናው መስሎት ብዙ የሸር ትብታቦችን ሊተበትብ ይችላል፡፡ ይሁንና እንደዚህ ዓይነቱ ሰው አጓጉል ሆኖ ነው የሚቀረው፡፡ የማታ ማታ ራሱ በሸረበው የተንኮል ድር መታሰሩ የማይቀር ነው፡፡ ስለዚህ በህይወት እያለ ደግ ደጉን ብቻ አስብ!! ለተንኮሉ ባለቤት አለውና!!
በድጋሚ Amiroo kheyruma yaadi, Sharriin abuma eeydi ብለናል፡፡
—-
አፈንዲ ሙተቂ
ጥቅምት 20/2007
—–
The writer, Afendi Muteki, is a researcher and author of the ethnography and history of the peoples of East Ethiopia.  You may like his facebook page and stay in touch with his articles and analysis: Just click the following link to go to his page.
አፈንዲ ሙተቂ
ጥቅምት 8/2007
ሀረር-ምስራቅ ኢትዮጵያ

የግብፅ መንግሥት በሀገሩ ሙሥሊሞች አኳያ የሚከተለውን ፖሊሲ ካልቀየረ በስተቀር በሲና በረኃ የአክራሪዎች ጥቃት እየተጠናከረ ሊሄድ እንደሚችል የፖለቲካ ታዛቢዎች አስጠነቀቁ። እንደሚታወሰው ፣ አንድ አጥፍቶ ጠፊ በዚሁ አካባቢ

ጥቅምት ፲፱(አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በርካታ ቁጥር ያላቸው የመከላከያ ሰራዊት አባላት በቴፒ ከተማ በብዛት መታየታቸውን ተከትሎ መንግስት   የከተማውን ህዝብ አርብ ጥቅምት 20፣ በትልቁ አዳራሽ በመሰብሰብ፣ በአካባቢው የሚታየውን ችግር በጋራ እንፍታ በማለት ጥሪ አቅርቧል። ለግማሽ ቀን በተካሄደው ስብሰባ ነዋሪዎችና የመንግስት ባለስልጣናት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ሲወዛገቡ አርፍደው ሳይግባቡ መለያየታቸውን በስብሰባው የተሳተፈው ወኪላችን ገልጿል። …

የአሸባሪ ቡድን ድርጅቶች በመካከለኛዉ ምሥራቅ የሚገኙ ጥንታዊና ታሪካዊ ቅርሶችን በመዝረፍና በከፍተኛ ገንዘብ በማግኘት ላይ መሆናቸዉ ተመልክቶአል። ይህን ጥንታዊ ቅርስ ከሚገዙት ጥንታዊና ታሪካዊ ቅርስ አድናቂዎች እና ሰብሳቢዎች መካከል ደግሞ ጀርመናዉያንም እንደሚገኙበት ተመልክቶአል።

ጥቅምት ፲፱(አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው ለአንድ ሳምንት ያክል በታሰረበት ክፍል ውስጥ እንዲጸዳዳ መደረጉን፣ ለ3 ቀናት በጨላ ክፍል ውስጥ ታስሮ የበቀል እርምጃ እንደተወሰደበት ፓርቲው በሰጠው መግለጫ አስታውቋል። ምክትል የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ የሆነው አቶ ዳንኤል ሽበሺ ደግሞ በታፈነ ክፍል ውስጥ እንዲቀመጥ መደረጉን፣ በተቅማጥና በሌሎች በሽታዎች እየተሰቃየ …

ጥቅምት ፲፱(አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-  በምዕራብ ሸዋ በሆለታ ገነት የሚገኘው የሼክ ሙሃመድ አላሙዲጅ ንብረት በሆነው ” ኢትዮ ድሪም” ድሪም የአበባ እርሻ ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች ላለፉት ሁለት ወራት ደሞዝ ያልተከፈላቸው በመሆኑ እነሱና ቤተሰቦቻቸው ለከፍተኛ ችግር ተዳርገዋል። ሰራተኞች አቤቱታቸውን ለድርጅቱ ሃላፊዎች ቢያቀርቡም መልስ ማጣታቸውን ገልጸዋል። አብዛኛው ሰራተኛ 600 ብር እንደሚከፈለው የሚናገሩት ሰራተኞች፣ ከዚህ …

ጥቅምት ፲፱(አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በሪክ ማቻር የሚመራው የተቃዋሚ ቡድን ቤንቲዩና ሮቡክና የተባሉ ቦታዎችን መቆጣጠሩን መረጃዎች አመለክተዋል። ሁለቱን ተፋላሚ ሃይሎች ለማስታረቅ በኢትዮጵያ በኩል ሲደረግ የነበረው ድርድር ውጤት አለማምጣቱን ታዛቢዎች ይናገራሉ። የሪክ ማቻር ሃይሎች ሃይላቸውን እያጠናከሩ በመሆናቸው ሌሎች ከተሞችንም ለመያዝ ተከታታይ ጥቃት ሊፈጽሙ ይችላሉ ሲሉ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት ገልጸዋል።

የጀርመን ድምፅ ራድዮ፣ ዶይቸ ቬለ በአሜሪካ የሚኖሩት አድማጩች ስርጭቱን በስልክ የሚያደምጥበት አገልግሎት መጀመሩ ከፍተኛ ተቀባይነት ማግኘቱ ተገለጸ። ይህንኑ አገልግሎት ተግባራዊ ያደረገው በዩኤስ አሜሪካ የሚገኘው «አውዲዮ ናው » የተሰኘው ድርጅት የራድዮ ስርጭት በስልክ የማድመጡ አገልግሎት

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የግንቦት 2007 ምርጫን የጊዜ ሰሌዳ አፀድቆ ይፋ አደረገ። የቦርዱ ስራ ኃላፊዎች ዛሬ በሂልተን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የጊዜው ሰሌዳ ከመፀደቁ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት በማድርግ እና ማሻሻያዎችን በማከል የፀደቀ መሆኑን አመልክተዋል።

ወያኔ/ህወሓት ያደራጃቸው ምሊሽያዎች በአፋር ነዋሪዎች ላይ ተኩስ ከፈቱ

አኩ ኢብን አፋር ለዘ-ሐበሻ እንደዘገበው፦

ትናንት ማክሰኞ 18/02/2007 በአፋር ክልል በሰሜናዊ ዞን በኮናባ ወረዳ በትግራይ ታጥቂ ሚሊሻዎች በኮናባ ፈራስዳገ ቀበሌ ነዋሪዎች ላይ ጦርነት የከፈቱ ሲሆን ቦታውን በቶክስ እሩምታ ሲያምሱት ማርፈዳቸውን ከቦታው የሚወጡ መረጃዎች ጠቁመዋል። ይሁን እንጂ ለጊዜው ከአፋር ነዋሪዎች በኩል የቶክስ ምላሽ አላገኙም! ከቀኑ 8:00 ሰዓት ሲሆን የተጀመረው ይህ ቶክስን ተከትሎ ከኮናባ ወረዳ ብዙ ወጣቶች ተሰብሰበው በፍጥነት ወደ ቦታው የደረሱ ሲሆን በዛን ጊዜ የኔትዎርክ አገልግሎት ወዲያው ተቋርጧል። እስካሁን ከአፋር ነዋሪዎች በኩል የተተኮሰ አንድ ጥይት የለም።

የቦታው ምንጮች አያይዘውም «ይህ ደግሞ የአፋር ወጣቶች ለሰላም ካላቸው ፍላጎት የተነሳ ነው። ነገር ግን አስገዳጅ ነገር ከተፈጠረ የሚደርስባቸውን ጥቃት ለመከላከል ከየቦታው ተሰብስበው ዝግጅት ላይ ናቸው።» ብለዋል። ከኮናባ አንድ ስሙን ሊናገር ያልፈለገ ወጣት እንደነገረኝ «ይሄ በህወሓት ሆን ተበሎ የሚደረግ ትንኮሳ በመሆኑ የአፋር ወጣቶች በበሰለ አስተሳሰብ ለሰላም ያላቸው ፈለጎት በትዕግስት አሳይተዋል።» ብሏል። አያይዞም «ኔትወርክ ራሱ የጠፋው ለሌሎች መረጃ እንዳይደርስና የአፋር ህዝብ እንዳይነሳ በመፍራት ነው» ሲል አክሏል። አሁንም ቦታው ውጥረት እንዳለ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

በዚህ ጉዳይ ላይ የኮናባ ወረዳ የፀጥታ ቢሮ ኃላፊን አስተያየት ለማካተት ያደረኩት ተደጋጋሚ ሙከራ አልተሳካም።

ምንጭ ዘሃበሻ አማርኛ ገጽ

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ እ.ኤ.አ በ2014 በአሁኑ ወቅትም በኢትዮጵያ ረኃብ አለ፣ ሆኖም ግን የሌለ ለማስመሰል ስሙ የሚጠራው በሌሎች የመቀባቢያ፣ የመሸፋፈኛ፣ የማስመሰያ እና የማደናገሪያ ተቀጽላ ስሞች አማካይነት ነው፡፡  በኢትዮጵያ ረኃብ የሚያስደነግጠኝ ርዕሰ ጉዳይ ነው፡፡ እራሱን ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ እያለ …

እ.ኤ.አ በ1984 የተከሰተው የኢትዮጵያ ታላቁ ረኃብ ሲታወስ፣ Read more »

አቡነ ማትያስ÷ የሊቃነ ጳጳሳትንና ኤጲስ ቆጶሳትን ተጠሪነት ለፓትርያርኩ በማድረግ በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖት ሕገ ቤተ ክርስቲያን የመጨረሻው ከፍተኛ ሥልጣን ባለቤት የኾነውን የቅዱስ ሲኖዶሱን የበላይነት በፓትርያርኩ የበላይነት ለመተካት ከምልአተ ጉባኤው ጋራ መሟገታቸውን አጠናክረው ውለዋል፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስ አመራር ያላትን ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን በፓትርያርኩ ዐምባገነናዊ አመራር ሰጪነት በመርገጥ በስም እንጂ በግብር የሥልጣን ልዕልና የሌለው ሲኖዶስ ለመፍጠር እየተጣጣሩ ነው፡፡ …

የፊታችን ማክሰኞ በዩናይትድ ስቴትስ በሚካሄዱ ምርጫዎች፥ ድምጽ ሰጪዎች በፕሬዘዳንት ባራክ ኦባማ የመጨረሻዎቹ ሁለት አመታት የትኛው ፓርቲ የኮንግሬሱን የሕግ መወሰኛና የተወካዮች ምክር ቤት እንደሚቆጣጠር ለመወሰን ድምጽ ይሰጣሉ።

በአንድ አገር ዴሞክራሲ እንዲጸናና ስር እንዲሰድ ሶስት አስፈላጊ ነጻነቶች እነርሱም የመጻፍ የመናገር ሃሳብ የመቀያየር፣ የተደራጀና ነጻ የሆነ የፓለቲካ ተቃዋሚ፣ እንዲሁም ገለልተኛና ነጻ የሆኑ ፍርደ ቤቶችና ዳኞች መኖር አለባቸዉ ይላሉ ፕሬፌሰር አድኖ አዲስ።

ጥቅምት ፲፰(አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፌደራል ዋና ኦዲተር፣ አባካኝ የመንግስት ተቋማት በሚል ለጠቅላይ ሚ/ር ጽ/ቤት እና ለተወካዮች ም/ክር ቤት አፈ ጉባኤ ያቀረበው ሪፖርት ለህዝብ ይፋ ይሁን አይሁን የሚለው ጉዳይ  ሚኒስትሮችን አወዛግቧል። አቶ አባዱላ ገመዳ፣ አቶ ደመቀ መኮንን፣ አቶ አዲሱ ለገሰና አቶ ጸጋየ በርሄ፣ የፌደራል ኦዲተሩ ሪፖርት ለህዝብ በፍጹም ሪፖርት መደረግ የለበትም ብለው …

ጥቅምት ፲፰(አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፓርቲው ባወጣው መግለጫ የሀገራችን አስተዳደራዊና ፖለቲካዊ ችግሮች ከግዜ ወደ ግዜ እየተባባሱና እየከፉ የመምጣታቸውን ያህል ገዢው ፓርቲ ቆም ብሎ ከማሰብ ይልቅ ወደ ማይወጣው አዘቅት ውስጥ ሀገሪቷን ጭምር እያንደረደራት ይገኛል ብሎአል። ኢህአዲግከዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ሂደት ፍፁም በማይጣጣም መለኩ ዜጎችን ለአንድ ሀሳብ ብቻ እንዲገዙ አስገዳጅ መንገዶችን ጭምር በመጠቀም አፋኝ መዋቅሩን …