የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

የምርጫዉን ውጤት የገመገሙልን በባልቲሞር ሞርጋን ስቴት ዮኒቨርሲቲ የፓለቲካ ሳይንስ መምህር ዶክተር ጌታቸዉ መታፈሪያ የፕሬዚደንት ኦባማ የአገርና የዉጪ ፓሊሲዎች ላይ ከፍተኛ እንድምታ ይኖረዋል ብለዋል። ከፊታችን ጥር ወር ጀምሮ በሁለቱም ምክር ቤቶች ማለትም በመምሪያዉና በመወሰኛዉና ክፍሎች የአብላጫ ድምጽ የሚኖራቸዉ ሬፑብሊካዉያን ሲቃወሙዋቸዉ የነበሩ ለምሳሌ እንደ ፕሬዚደንት ኦባማ የጤና ጥበቃ ሕግ ያሉትን ሊሽሩ እንደሚችሉ ተናግረዋል። የሆነ ሆኖ ፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ ድምጽን በድምጽ የመሻር ስልጣን እንዳላቸዉ ይታወቃል።

 

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም  ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ እውነታው ከልብወለድ በላይ እንግዳ ነገር ነው!   እ.ኤ.አ ሴፕቴምበር 7/2014 “ድፍረት፡ የፊልም ጠለፋ በኢትዮጵያ” በሚል ርዕስ ባወጣሁት ትችት ድፍረት በሚለው ፊልም ላይ የኢትዮጵያ መሪ ተዋንያን ሆና በሰራችው የውርጃ ድርጊት ላይ የነበረኝን ቁጣ ገልጨ ነበር፡፡ በአበራሽ በቀለ እውነተኛ ታሪክ ላይ …

የጠለፋ ጋብቻ በኢትዮጵያ ፡ በሴቶች ላይ የሚፈጸም ወንጀል Read more »

በሕዋ ለመመራመርም ሆነ ለመንሸራሸር፣ የሚደረግ ጉዞ፣ በምድር ላይ እንደምናውቀው የተለያየ የማጓጓዣ ዘዴ ፍጹም ቀላል አይደለም። በሕዋ ጎዞ የማይታሰብ የተለያየ ችግር ሊያጥም እንደሚችል በማሰብ ማሰላሰል ፤ አማራጭ መላዎችን ሁሉ መሻቱ ተገቢ ነው።

በቻይና የመጠጥ ዉኃ ምንጭ በደንብ በተመጣጠነ ሁኔታ ለኅብረተሰቡ አልተከፋፈለም። በሰሜናዊ የሀገሪቱ ክፍል ከሚገኘዉ የመጠጥ ዉኃ አገልግሎት ይልቅ በደቡባዊ የሀገሪቱ ክፍል በብዛት ተዳርሷል።

በዩኤስ አሜሪካ ትናንት በተካሄደው አጋማሽ የምክር ቤት ምርጫ ሬፓብሊካውያን በሁለቱም የምክር ቤት ክፍሎች አሸነፉ። በሕግ መምሪያው ምክር ቤት አብላጫውን ድምፅ የያዙት ሬፓብሊካውያን 100 መንበሮች ባሉት በሕግ መወሰኛው ምክር ቤትም ውስጥ 52 መንበሮችን በማግኘት አብላጫውን ድምፅ መያዝ ችለዋል።

በብዙ የኢትዮጵያ ከተሞች እየታየ ያለው የኤሌክትሪክ መቆራረጥ በዕለት ተዕለት ኑሮው እና ስራ ላይ ከፍተኛ ችግር እንዳስከተለባቸው ዜጎች በምሬት ገልጸዋል። በሕዝቡ ኑሮ ላይ አሉታዊ ጫና የፈጠረውን የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ችግር ለመቀነስ መንግሥት ባለፉት ዓመታት ብዙ ስራ መሰራቱንና ይህንኑ ጥረቱን መቀጠሉን የኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ገልጾዋል።

የአፍሪቃን ኤኮኖሚ ዕድገት ይበልጥ አጠናክሮ መቀጠል እንዲቻል በተለይ ትኩረቱ በከፍተኛው ትምህርት ዘርፍ ላይ ማረፍ እንደሚገባው በአዲስ አበባ የተመ የአፍሪቃ ኤኮኖሚ ኮሚሽን ውስጥ ለአራት ቀናት የተካሄደው ጉባዔ አሳሰበ።

ጥቅምት ፳፭ (ሃያ አምት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የቀድሞው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባዔ  የአሁኑ የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ( ሰመጉ) ባወጣው 132ኛ ልዩ መግለጫ በክልሉ በመንገሽና ጎደሬ ወረዳዎች ተፈጥሮ በነበረው ግጭት የተገደሉ የ60 ሰዎች ስም ዝርዝር ይፋ አድርጓል። በሪፖርቱ እንደቀረበው 27 የአማራ፣ 27 የመዠንገር፣ 2 የከፋና 4 የኦሮሞ ተወላጆች ተገድለዋል። እንዲሁም 16 የአማራና 6 የመዠንገር ተወላጆች …

ጥቅምት ፳፭ (ሃያ አምት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ካለፉት ሁለት ቀናት ጀምሮ መንግስት በተለያዩ አካባቢዎች ያሉ የተቃዋሚ አመራሮችን በመያዝ እያሰረ ነው::  በትግራይ ክልል በምዕራባዊያን ዞን ቃፍታ ሁመራ ወረዳ ዳንሻ ከተማ የአረና ፓርቲ የማእከላዊ ኮሚቴ አባል አቶ ዘነበ ሲሳይ ጥቅምት 25፣ 2007 ዓም ከቤታቸው ተነጥለው በመወሰድ ሲታሰሩ፣  በተመሳሳይ ቀን በሁመራ የአረና የቁጥጥር ኮሚቴ አባል የሆኑት …

ጥቅምት ፳፭ (ሃያ አምት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፌዴራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ክስ በመሰረተባቸው አቶ ዘላለም ወርቅነህ፣  ሃብታሙ አያሌው፣ አብርሃ ደስታ ፣ ዳንኤል ሺበሺ፣ የሽዋስ አሰፋና በሌሎች 5 ተካሳሾች ላይ ዋስትናን በተመለከተ ሊሰጥ የነበረውን ውሳኔ አራዘመ። ፍርድ ቤቱ የሁሉም ጠበቆች ተዘጋጅተው ባለመቅረባቸው ውሳኔውን ለህዳር 2 ፣ 2007 ማራዘሙን አስታውቋል። እስረኞቹ በሽብር …

ኢሕአዴግ በጭራሽ እራሱን ነፃ ለሆነ የምርጫ ውድድር እያዘጋጀ አይደለም !የፖለቲካ ሊቃውንት እንደሚያስገነዝቡት እና ዓለም አቀፍ ነባሪዊ ሁኔታ የሚያመላክተው ለምርጫ መሰረታዊ ከሆኑት ውስጥ ፤በእኩል ደረጃ ባይወንም እንኳን በአንፃራዊነት የተወዳዳሪ ፓርቲዎች ነፃነት እና እኩል ተሣትፎ ሊኖር ይገባል፣ፓርቲዎችን ሊያወዳደሩ የሚችል ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ምርጫ ቦርድ እና ጉዳዩን ሙያዊ ስነምግባር መሠረት በማድረግ ለህዝብ መረጃ የሚያደርስ ነፃ ሚዲያ ያስፈልጋል፡፡እነዚህ መሰል ዋንኛ መስፈርቶች ባልተሟሉበት በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ፣ በመጪው ግንቦት ወር ነፃ ምርጫ ማካሄድ የሚታሰብ አይደለም፡፡

እንደ መግቢያ፡- በመዝገበ ቃላት አተረጓጎም መሠረት “ዲሞክራሲ ማላት በሕዝብ የተመረጠ መንግሥት ማለት ሲሆን የመጨረሻውም ሥልጣን በሕዝብ ቁጥጥር ስር ያለ፣በቀጥታ በራሳቸው ወይም እነርሱ በወከሉት ወገን ብቻ በሥራ የሚተረጐምና በነፃ ምርጫ ስርዓት የተመረኮዘ ነው” ይላል፡፡ በአብርሃም ሊንከን አባባል “ዲሞክራሲ ከሕዝብ የወጣ ፣በሕዝብ የተመረጠና ለሕዝብ የሚያገልግል መንግስት ነው፡፡”በማለት የሰጠው ትርጓሜ በአብዛኛው ተቀባይነት ያገኝ ሃሳብ ነው፡ሦስቱ መሠረታዊ የመንግስት ምሶሶዎች ተብለው የሚታወቁት ማለትም ሕግ አውጪ፣ሕግ አስፈጻሚ እና ሕግ ተርጓሚ በሁለት መንገድ ሥራቸውን ያከናውናሉ፡፡እነኚኽም አካሄዶች ቀጥተኛ እና የተወካይ ዲሞክራሲ ተብለው ተለይተው ይታወቃሉ ፡፡
ቀጥተኛ ዲሞክራሲ ዜጎች የሚመርጧቸው ምንም ዓይነት ተወካይ አይኖራቸውም፡፡ይህ ማላት ግን አስተዳዳሪ ወይም መሪ የላቸውም ማለት አይደለም፡፡በማናቸውም ጉዳዮች ውሳኔ የሚወስነው በቀጥተኛ የህዝብ ተሳትፎ ነው፡፡ለየትኛውም የህዝበ ውሳኔ ጉዳዮች ፣ዜጎች በጋራ ተሰባስበው በመመክር በአንድ ዓይነት ስምምነት፣ ውይም በድምፅ ብልጫ ውሳኔ የሚያስተላልፉበት ስርዓት ነው፡፡የዲሞክራሲ እናት በመባል የምትታውቀው አቴንስ ከ4 ሺህ እስከ 7ሺህ የሚደርሱ ሰዎች ስብሰባ በማካሄድ ነበር ቀጥተኛ የሆነ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን ተግባራዊ ታደርግ የነበረችው፡፡ይሁን እንጂ ከሕብረተሰብ ብዛት እና ከውስብስብነቱ አኳያ ለቀጥተኛ ዲሞክራሲ ተግባራዊነት የሚሰጠው ጥቅም ውስን በመሆኑ ብዙም ሳይጓዝ እንዲቀር ተደርጓል፡፡በአሁን ወቅት በዓለማችን በአብዛኛው ተግባራዊ እየተደረገ ያለው የዲሞክራሲ ዓይነት የተወካዮች ዲሞክራሲ ነው፡፡እንዲህ ዓይነቱ ዲሞክራሲ ዜጎች የፖለቲካ ውሳኔዎችን የሚወስንላቸው ተወካዮቻቸውን በመምረጥ ነው፡፡ተመራጮችሁም በበኩላቸው የመረጣቸውን ሕዝብ ወክለው ውስብስብ መንግስታዊ ሥራዎችን እውቀታቸውን፣ጊዜያቸውን እና ጎልበታቸውን ሰውተው ግልጋሎት ይሰጣሉ፡፡
በአገራችን ኢትዮጵያ፡- ከቀጥተኛ ዲሞክራሲ ይልቅ የተወካዮች ዲሞክራሲ ውጤቱ አጥጋቢ ባይሆንም፣ ተግባራዊ ለማድረግ ሙከራዎች ከዚህ ቀደም ተደርጓአል፡፡በተለይ በቀዳማዊ ንጉሳችን ኃይለ ስላሴ የተወካዮች ዲሞክራሲ ወደ አገራችን በማስገባት የዲሞክራሲ በዓላችን እንዲዳብር የተደረገው ጥረት እና ውጤት በታሪክ በአውንታዊ ጎን ተፅፎ የሚኖር ነው፡፡ይሁን እንጂ የተወካዮቹ አመራረጥ እና የሥራ ሂደታቸው ሲለካ ውጤቱ ምን እንደነበር ለታሪክ አዋቂዎች ቢተዉ የተሻለ ይሆናል፡፡ከዚህ ባለፈ በደርግ የተካሄደው የብሔራዊ ሸንጎ እና የኢሕአዴግ የ4 ዙር አገር አቀፍ ምርጫ ለዜጎች ከሰጠው ፋይዳ ይልቅ የአምባገነን ሥርዓት ለማስቀጠል የሰጠው ጥቅም የበዛ ነው፡፡
ከምርጫ 1997 ዓ.ም ወዲህ፣ ገዥው መንግሰት የምርጫን መቃረብ ተከትሎ መንገዶችን ይሰራል፣ የጋራ መኖራይ ቤት ገንብቶ በዱቢ እና በረጅም ወራት ክፍያ ለተጠቃሚዎች ያስተላልፋል፣ለመንግሰት ሠራተኞች የደሞዝ ጭማሪ ያደርጋል፣በአንድ ለአምስት አደረጃጀት በመጠቀም የምረጡኝ ዘመቻ ይጀምራል፣አብዮታዊ ዲሞክራሲ ስልጠናና ጥምቀትን ያካሂዳል፣ዘላቂነት የሌላቸው ጊዚያዊ የሥራ እድሎችን በመፍጠር የሥራ አጦችን ካርድ ይነጥቃል፤ይህ ሣይሆን ሲቀር ኢ-ፍህታዊ ጥቅማ-ጥቅምን በመስጠት ደጋፊን ያበዛል፡፡ በተጨማሪም መቼም የማይፈፀሙ ትልልቅ ፕሮጀክቶችን በየቦታው የመሠረት ድንጋይ በመጣል ዳንኪራ ያስጨፍራል፣ከዚህም በላይ የሆነበትን ደግሞ ቃል ይገባል ፡፡እነዚህና መሰል የሆኑ ሁሉ ነገሮችን ማከናወኑ ለምርጫ ካርድ እንጂ ለዘለቂታዊ ልማት አይደልም፡፡የምርጫ ወቅት ሲቃረብ መንግስት ደፋ ቀና ደፈ ቀና የሚለበት ሥራ ሁሉ ለይስሙላ እንጂ ዘለቄታዊ ጠቀሜታ እንደሌለው ላለፉት አራት ዙር በተደረጉ ምርጫዎች ለማረጋገጥ ይቻላል ፡፡ በይበልጥ ደግሞ የፊታችን ግንቦት ወር ይካሄዳል የሚባለው ምርጭ በገዥው መንግሰት ቀጥተኛ ተፅኖ ስር በወደቀው ምርጫ ቦርድ እና ፣በመንግስት በኩል መንገስት ስል ኢሕአዴግ ወይም ወያኔ ለማለት እንደተፈለገ ግንዛቤ ይወሰድልኝ፡፡ምክንያቱ ደግሞ ገዥው ፓርቲ እና መንግስት ባልተለያዩበት ሥርዓት ውስጥ በመሆናችን ነው፡፡ስለሀኖም በእነዚህ ሁለት ሃይሎች ተፎካካሪ ወይንም አማራጭ በሆኑ በተቃዋሚ ፓርቲዎች ላይ ይህ-ቀረሽ የማይባል ጫና እየደረሰባቸው ይገኛል፡፡ችግሩ ደግሞ ቀጥተኛ በሆነ መንግድ የሚፈፀም ስለመሆኑ ከዚህ በታች በመጠኑ ለማመላከት ይሞከራል፡፡
የገዥው መንገስት ቀጥተኛ ጫና በፓርቲዎች፡-
በዓለም አቀፍ የተባበሩት መግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ጉባሄ ባፀደቀው መግለጫ ኢትዮጵያም በፈረመችው ስለ መሰብሰብ እና መደራጀት መብቶች በሚከተሉው መልኩ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ “ የዜጎች የመሰብሰብ እና የመደራጀት መብቶች ተግባራዊ ሂደት ገደብ በማይጣልበት ሁኔታ መከበር ሲኖርበት ነገር ግን ገደብ ቢደረግ እንኳን ገደቡ የዓለም ዓቀፍ ህግና ሰብዓዊ መብቶችን መሰረት ያደረገ እና የእነዚህን መብቶች ሁለንተናዊ ጥበቃ እዉን የሚያደርግ መሆን አለበት፡፡በተለይም ዜጎች የፖለቲካ እና የአይማኖት ለማስከበር የሚያደርጓቸው ተቃውሞዎች መደገፍ አለባቸው፡፡”የሚል ነው ፡፡
ይህ እጅግ በጣም ጠንካራ የሆነ ዜጎች በፖለቲካ የመደራጀት መብታቸውን የሚያስከበር ዓለም አቀፍ ሕግ ነው፡፡አሁን በሥራ ላይ ያለው ሕገመንገስት ይህን ህግ በመቀበል አካቶ ይገኛል፡፡እርግጥ ነው ህገመንግስቱ በራሱ ማሻሻይን የሚፈልጉ በርካታ አንቀፆች አሉት፡፡በዚህ አጋጣሚ ሰማያዊ ፓርቲ ዜጎችን በጋራ አግባብቶ በዘላቂነት ሊያገለግል የሚችል እና ለሕገመንግሰት መሠረት ወይም ምሶሶ የሚሆን “የዜጎች ቃል-ኪዳን ሰነድ ለዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ”የተሰኘ ሠነድ በማዘጋጀት ለህዝብ ይፋ ማድረጉ የሚታወቅ ነው፡፡ለዚህም መልካም ጅማሮ ለሰማያዊ ፓርቲ አድናቆት ሊቸረው ይገባል፡፡ወደጉዳያችን ስንመለስ በዓለም አቀፍ እዲሁም በኢትዮጵያ ሕግ የፖለቲካን ዓላማ ለማስፈፀም ሕግን መሠረት ያደረገ አደረጃጀት የተፈቀደ ነው፡፡ይሁን እንጂ ይህን መሰረት ያደረገ አደረጃጀት ኖራቸው በአገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የተቃወሚ ፓርቲዎች፤ ሰብዓዊና ዲሞክራሳዊ መብቶች ይከበሩ፣የሕግ የበላይነት ይረጋገጥ፣ህዛባዊ መንግሰት ይመስረት በማለታቸው እና ለተግባራዊነቱ በመንቀሳቀሳቸው ብቻ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ለሞት፣ለእስራት፣ለስደት እና ለእንግልት እየተዳረጉ ይገኛሉ፡፡
ይህም በመሆኑ አብዛኛው የተቃዋሚ ፓርቲ አባላቶቺ ታስረዋል፣የመንግሰት ታጣቂ ሃይሎች በግልፅ እና በስውር በፓርቲ አባላት ወከባና እንግልት እየፈፀሙ ይገኛሉ፣ጠንካራ የሚባሉ የተቃዋሚ ሃይሎች የቀን-ተቀን ሥራቸውን የሚያከናውኑበት ቢሮ መከራየት እንዳይችሉ አከራዩች በቀበሌ ካድሬዎች ማስፈራሪያ እና ዛቻ ይደርስባቸዋል፣ከብዙ ልፋት እና እንግልት በኋላ በሚያገኙት ቢሮ የፓርቲ አባላቶች ወደ ቢሮ ሲገብ እና ሲወጡ እየጠበቁ የመንግሰት ደንነቶች ወከባ ከፍ ሲልም ትንኮስ እየፈፀሙ ይገኛሉ፣ ፓርቲዎች ዋንኛ የተቋቋሙለትን ዓላማ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችላቸውን ማናቸውም እንቅስቃሴዎች ከደጋፊዎቻቸው ጋር በመሆን በነፃነት አደባባይ ወጥተው ቅስቀሳ እንዲሁም ተቃውሞ ማድረግ የሞት ሽረት ትግል ነው፡፡በተለይ ደግሞ አዲስ ተመዝጋቢ አባላት የአባልነታው የእጩ ቀናት መቁጠር ከመጀመራቸው በፊት በመንግሰት ታጣቂ እና በካድሬዎች የሚደርስባቸው ማስፈራሪያ እና ዛቻ ልጉድ ነው፡፡ከምንም በላይ ደግሞ የአባላትን ወራዊ መዋጮ እና ድጋፍ የፓርቲዎች የፋይናስ አቅም አይነተኛ መንግድ ነው፡፡ሆኖም ግን ይህ ገንዘብ በራሱ በቂ አይደለም፡፡ይህም በመሆኑ የፓርቲ አባላት ሣይሆኑ ደግፍ መስጠት ለሚፈልግ ለማንኛውም ኢትዮጵያዊ በልብ ሙሉነት ገንዘባቸውን እንዳይለግሱ ጫና ይደረግባቸዋል፡፡የጉዳዩ አሳሳቢነት ምን ያኸል እነደሆነ ለማሳያ አነድ ምሣሌ መጥቀስ ይቻልል፤አቶ የሺዋስ አሰፋ፣አቶ አብታሙ አያሌው፣አቶ ደንኤል ሽበሺ እና አቶ አብርሃ ደስታ በማእከላዊ እስር ቤት በዋንኛነት የሚደረግባቸው ምርመራ “የፓርቲያችሁ የገንዘብ ምንጭ ምንድነው ? ማነው በቋሚነት ድጋፍ የሚያደርግላችሁ ?ገንዘቡ የት ነው የሚቀመጠው” የሚሉት ዘወትር የተለያየ የምርመራ ዘዴዎች በመጠቀም የሚጠየቁት ጥያቄ ነው፡፡ነገሩን ይበልጥ አስገራሚ የሚያደርገው ከላይ የተገለፁት የፓርቲ አባለት የተያዙት “በሽብር ወንጀል በመጠርጠር ነው”በማለት ገዥው መንግስት ገልፆአል ሆኖም በምርመራ ወቅት ግን የሚጠየቁት የፓርቲ ገንዘብ ወጪና ገቢ ነው፡፡ በአጠቃላይ የተቃዋሚ ፓርቲ አባል በመሆን ብቻ ነጋዴው ከንግዱ፣ተማሪው ከት/ት፣ሰራተኛው ከስራው፣ገበሬው ከእርሻው፣አርብቶ አደሩ ከከብቶችሁ እየተፈናቀለ ይገኛል፡፡
ስለዚህም ተፈካካሪን የተቃወሚ ፓርቲን በእንዲህ መልኩ እያዳከመ እና አንዳንዶችን በጭራሽ ከወደቁበት እንዳይነሱ እያደረገ ይገኛል፡፡በእንዲህ መልኩ ከሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች ጋር ኢሕአዴግ ተፎካካሪ በመሆን ለመርጫ እራሱን እያዘጋጀ ነው እንዴት ሊባል ይቻላል ?
የገዥው መንገስት ቀጥተኛ ጫና በምርጫ ቦርድ ፡-
በየደረጃው ትክክለኛ ምርጫ እንዲካሄድ ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ይቋቋማል፡፡የሚለው በህገመንግስቱ አንቀፅ 102 ላይ ይገኛል፡፡ይሁን እንጂ የምርጫ ቦርድ ሃላፊዎች ሹመታቸው ከመንግስት መልካም ፍቃድ የመነጨ ሲሆን አሰራራቸውም ለገዥው መንግስ በእጅጉ በጣም ያደላ ነው፡፡ስለዚህም ምርጫ ቦርድ ህገመንግስቱን መሠረት አድርጎ ነጻ እና ገለልተኛ ነው ለማለት ከበድ ድፍረትን የሚጠይቅ ነው፡፡የስከዛሬውም የምርጫ ቦርድ የሥራ አንቅስቃሴ ለገዥው መንግስት ያለው ታማኝነት እና አገልጋይነት በድብቅ ሣይሆን በአደባባይ “እዩልኝ፣ስሙልኝ” እያለ በራሱ ላይ መስክሮ የእኛን መስክርነት ከሰጠን አመታት ተቆጠሩ፡፡ከወረዳ የምርጫ አስፈፃሚ ጀምሮ እስከላይ ያለው የምርጫ ቦርድ ሃላፊ፣ በገዥው መንግሰት ቀጥተኛ ተፅእኖ ስር መሆናቸው ግልፅ እና አሻሚ ያልሆነ ጉዳይ ነው፡፡ በዚህ ላይ ከዘህ በላይ ማሣያዎችን ለማመላከት መሄድ ዉሃ ቅዳ ዉሃ መልስ ይሆናል ነገሩ፡፡
በመሆኑም ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ በአገራችን የለም፡፡ ሃቁ ይህ ሆኖ ሣለ ከተፈካካሪ የተቃወሚ ፓርቲዎች ጋር ኢሕአዴግ ለመርጫ እራሱን እያዘጋጀ ነው ማለት እንዴት ይቻላል ?
የገዥው መንገስት ቀጥተኛ ጫና በነፃ በጋዜጠኛ ላይ ፡-
ማንኛውም ሰው ያለማንም ጣልቃ ገብነት የአመለካከት እና ሐሳብን በነፃ የመያዝና በማንኛውም የማሰራጫ ዘዴ የመግለፅ ነፃነት አለው፡፡የሚለው በህገመንግስቱ አንቀፅ 29 ተፅፎ ይገኛል፡፡ በእርግጥ ይህ መብት ገደብ ሊጣልበት እንደሚችል በህገ መንግስቱ ላይ ተገልፆ የተቀመጠ ሲሆን ገደብ ግን መሠረታዊ የሆነውን መረጃን የመስጠት እና የማግኘት እንዲሁም አስተሳሰብ ላይ ወይም አመለካከት ላይ ውጤት እንደማይኖረው በህገመንግስቱ ተገልፆ ይገኛል፡፡
ይሁን እንጂ አሳብን በነፃ ማሰብና ማንሸራሸር በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ እጅግ አዳጋች ነው፡፡ አሳብን ለመግለፅ ይቅርና ከገዥው መንግስት ፍላጎት እና አሳብ ውጪ ማሰብ በራሱ ለእስራት እና ለእንግልት ይዳርጋል፡፡ጋዜጠኞችን በማሰቃየት፣በማሰር እና እንዲሰደዱ በማደረግ ኢትዮጵያ በዓለማችን መጥፎ ሪከረድ አስመዝግባለች፡፡በአሁን ወቅት ከ17 የማያንሱ ጋዜጠኞች በእስር ቤት እየተሰቃዩ ይገኛሉ፡፡21 የሚሆኑ ጋዜጠኖች በስደት መከራን እየተቀበሉ ነው፡፡መንግስትን ተችቶ የፃፈና ፁሁፉ የወጣበት ጋዜጣ ወይም መፅሔት ጨምሮ ሁሉም ተጠራርጎ ቃሊቲ የሚገባበት ወይም አደገኛ ዛቻና መስጠንቀቂያ የሚሰጥበት ደረጃ ላይ ተደርሷል፡፡በውጪ አገር የሚገኙ የተለያዩ ሚዲያዎችም ቢሆኑ፣በአገር ውስጥ ተደማጭ እና ተነባቢ እንዳይሆኑ ከፍተኛ ገንዘብ በመመደብ አፈና እየተደረገባቸው ይገኛል፡፡
ስለዚህም ነፃ አሳብ የሚንሸራሸርባቸው ነፃ ጋዜጦችና መፅሔቶች ምን ያህል አሉ ? በመጪው ግንቦት ወር ለሚካሄደው አገራዊ ምርጫ ተፈካካሪ ፓርቲዎች የምረጡኝ ዘመቻ ቅስቀሳ የሚያደርጉት በይትኛው ነፃ ጋዜጣ እና መፅሔት ነው ? ህሊናውን እና ሙያውን ብቻ መሠረት አድርጎ የሚሰራ ጋዜጠኛ ምን ያህል አለ ? እርግጥ ይህ ፁሑፍ የቀረበበት ሚዲያ ጋዜጣ በቀጣይ የሌሎች ጋዜጣ እና ጋዜጠኞች እጣ ፈንታ እንደማይደረሰው በምንም እርግጠኛ መሆን ይቻላል፡፡በምንም!!
እናም ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ጋዜጠኛ እና የእትመት ውጤት ሣይኖር መርጫ እንዴት ይታሰባል፡፡አገራችን በጋዜጠኛ ድርቅ እንድትመታ ገዥው መንግሰት ሆነ ብሎ ያደረገው መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡ይህ በሆነበት ሁኔታ ኢሕአዴግ ለመርጫ እራሱን እያዘጋጀ ነው ማለት በራስ ላይ እንደመተኮስ ይቆጠራል ፡፡

ከላይ በመጠኑ የዚህ ፁሑፍ አቅራቢ ለመዳሰስ የሞከራቸው እና ሌሎች ተመሳሳይ ምክንያቶችን ግምት ውስጥ በማስገባት፣ ኢሕአዴግ በጭራሽ እራሱን ነፃ ለሆነ የምርጫ ውድድር እያዘጋጀ አይደለም !የፖለቲካ ሊቃውንት እንደሚያስገነዝቡት እና ዓለም አቀፍ ነባሪዊ ሁኔታ የሚያመላክተው ለምርጫ መሰረታዊ ከሆኑት ውስጥ ፤በእኩል ደረጃ ባይወንም እንኳን በአንፃራዊነት የተወዳዳሪ ፓርቲዎች ነፃነት እና እኩል ተሣትፎ ሊኖር ይገባል፣ፓርቲዎችን ሊያወዳደሩ የሚችል ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ምርጫ ቦርድ እና ጉዳዩን ሙያዊ ስነምግባር መሠረት በማድረግ ለህዝብ መረጃ የሚያደርስ ነፃ ሚዲያ ያስፈልጋል፡፡እነዚህ መሰል ዋንኛ መስፈርቶች ባልተሟሉበት በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ፣ በመጪው ግንቦት ወር ነፃ ምርጫ ማካሄድ የሚታሰብ አይደለም፡፡

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር !

ጎንደር ፦ የህዝቦችን መብቶች የማይወክሉ የወያኔ ሰንደቅ አላማዎች ከሚውለበለቡበት ወረዱ ::
#Ethiopia #Gonder #Kimant #ESAT #MinilikSalsawi #Freedom

– በሰሜን ጎንደር ከ80 በላይ ትምህርት ቤቶች ተዘጉ:: ESAT
– በሰሜን ጎንደር ዞን 130 ሺህ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው አልተገኙም።
– በአድማው የመንግስት መስሪያ ቤቶች ይካተታሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የቅማንት ተወላጆች ያነሱትን ጥያቄ ተከትሎ በተጠራ የስራ ማቆም አድማ በዞኑ የሚገኙ ከ80 በላይ ትምህርት ቤቶች ካለፈው አርብ ጀምሮ የተዘጉ ሲሆን፣ መንግስት እስከ መስከረም 30 መልስ የማይሰጥ ከሆነ፣ ተቃውሞው ግብር ባለመክፈል እንደሚቀጥል አስተባባሪዎቹ ለኢሳት ገልጸዋል።
ከዚህ ቀደም በርካታ አስተባባሪዎች ተይዘው የታሰሩ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን መንግስት ለጥያቄው እስከ መስከረም መጨረሻ መልስ እንደሚሰጥ አስታውቆ ነበር።

እስካሁን ከ130 ሺ ያላናሱ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው የቀሩ ሲሆን፣ ሌሎች ትምህርት ቤቶችና የመንግስት መስሪያ ቤቶችም በአድማው ይቀጥላሉተብሎ ይጠበቃል። በተዘጉት ትምህርት ቤቶች ውስጥ የሚውለበለቡ ሰንደቃላማዎች እንዲወርዱ ተደርጓል። ሰንደቃላማዎች እንዲወርዱ የተደረገበት ምክንያት የህዝቦችን መብቶች የሚወክሉ አይደሉም በሚል ነው።

Image

ትናንትና ምሽት አካባቢ ወደ አልታወቀ ቦታ ታፍኖ የተወሰደው የዞኑ አስተባባሪ እስከአሁን ሰዓት ድረስ ያለበትን ቦታ ማወቅ አልተቻለም፡፡ ትናንት ማምሻውን በሲቪል እና መሳሪያ በታጠቁ የገዢው ፓርቲ ሀይሎች ቤቱ ተበርብሮ ወደ አልታወቀ ቦታ ታፍኖ መወሰዱን በዞኑ ያሉ የፓርቲው አካላት አረጋግጠዋል፡፡

ከሰማያዊ ፓርቲ የጎንደር ዞን አስተባባሪ አቶ አግባው ሰጠኝ በተጨማሪም ወደ ስድስት(6) የሚደርሱ የአንድነት እና መኢአድ ፓርቲ አባላትም ወደ አልታወቀ ቦታ ታፍነው መወሰዳቸው ተረጋግጧል፡፡

በሌላ በኩል በጎንደር ባሉ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ከፍተኛ ክትትልና ወከባ እየደረሰባቸው እንደሆነ የዞኑ ተጠሪዎች አመልክተዋል፡፡

ጋዜጠኛ አንተነህ መርዕድ

በዙህ ጉዳይ ላይ ለመጻፍ በሁለት ምክንያቶች ከራሴ ጋር ብዙ ታግያለሁ። መጀመርያ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም አይደለም ለራሳቸው፤ ለሌላም የሚተርፍ አንደበት አላቸውና ራሳቸው መልስ  ይስጡ በማለት ሲሆን ሁለተኛው ምክንያቴ ደግሞ ትልልቅ አገራዊ ጉዳይ እያለ በዚህ ጠባብ ነገር መጠመድ ለማን ይበጃል በሚል ነበር።በሁለቱም ትክክል አልነበርሁም።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም 9 ተቃዋሚ ፓርቲዎች የመሰረቱት ትብብር ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል ለአንድ ወር የሚቆይ የመጀመሪያ ዙር የህዝባዊ ትግል ፕሮግራሙን ዛሬ ጥቅምት 25/2007 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ይፋ አደረገ፡፡ ‹‹ነጻነት በሌለበት ፍትሃዊ ምርጫ የማይታሰብ በመሆኑ የተዘጋውን በር ለመክፈት የ‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ› በሚል የፕሮግራም መርሃ ግብር ለመክፈት ወስኖ የመጀመሪያው ዙር እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ ከተማ […]

የአንድነት ፓርቲ በተለያዩ የአገሪቷ ክፍሎች መዋቅሩን የዘረጋ ድርጅት ነው። ወደ አምስት ሚሊዮን የሚጠጋ ሕዝብ በሚኖርባት አዲስ አበባ ፣ ፓርቲው እስከታች በመዝለቅ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ድርጅታዊ መዋቅሩን ዘርግቶ የሚንቀሳቀስ ነው። – የአዲስ አበባ ምክር ቤት የተቋቋመው በአዲስ አበባ ከሚገኙ 23 የምርጫ ወረዳዎች በተወከሉ ስድስት ስድስት አባላት ነው። በአጠቃላይ 138 አባላት አሉት። – በ23ቱም የምርጫ ወረዳዎች ፣ […]

“በሽብር” ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙት የፓርቲ አመራሮች ሀብታሙ አያሌው የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት፣ ዳንኤል ሺበሺ የአንድነት ፓርቲ ም/የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ፣ የሺዋስ አሰፋ የሰማያዊ ፓርቲ ም/አፈ ጉባኤ፣ መምህርና የአረና ፓርቲ የአመራር አባል አብርሃ ደስታ እንዲሁም የአ/አ ዩኒቨርስቲ የማስትሬት ተማሪ ዘላለም እና ተመሳሳይ መዝገብ የተከሰሱ ሌሎች 5 ግለሰቦች ነገ ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ልደታ በሚገኘው ፍርድ ቤት ይቀርባሉ፡፡ […]

የምስራቅ ሸዋ ዞን አዳማ የአንድነት ለዲሞክራሲና ፍትህ ፓርቲ የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊ የነበረው አቶ ደረጀ ክበበው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ፡፡ አቶ ደረጀ በጠና ታሞ በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ትላንት ጠዋት በአዳማ ከተማ ቀበሌ 07 በሚገኘው መኖሪያ ቤቱ ያረፈ ሲሆን የቀብር ስነስርዓቱ በትላንትናው ዕለት ከቀኑ በ 7፡00 ሰዓት አዳማ በሚገኘው መድኃኒአለም ቤ/ክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡ ፓርቲው በአቶ ደረጀ ክበበው ሞት […]

– የመከላከያ እና ፖሊስ ሰራዊቱ ላይ አለመተማመኑ እየጨመረ መጥቷል። – የደህንነት አባላቱ መረጃን በግል ጥቅም በመለወጥ እየሰሩ ነው የሚል ግምገማ ቀርቦባቸው ተንጠዋል። – የሃገሪቱን ጉዳይ በተመለከተ ለበታች “ተከታይ ” ባለስልጣናት መረጃ መስጠት ቆሟል። – የሕወሓት ታጣቂዎች ከምቾት ኑሮ ተነስተው ለመሸሽ እንጂ ታጥቀው ደም ለመፋሰስ ዝግጁ አይደሉም ። በኢትዮጵያ ውስጥ መጭው ጊዜ በህዝቡ ዝምታ ተከትሎ በስርአቱ […]

በደቡብ ጎንደር የፎገራ ወረዳ የአንድነት ሰብሳቢ የሆኑት አቶ አለበል ዘለቀ በዛሬው ዕለት ከሚሰሩበት የእርሻ ቦታቸው ላይ በፌዴራል በፖሊስ ተይዘው ወዳልታወቀ ቦታ መወሰዳቸውን እንዲሁም በአማራ ክልል ምዕ/ጎጃም ደጋ ዳሞት ወረዳ የወረዳው አንድነት ፓርቲ ሰብሳቢ አቶ ጥላሁን አበበ በተጨማሪም በወረዳው ያሉ 3 የአንድነት አባላት ከቤታቸው በፌዴራል ፖሊስ ተይዘው ወዳልታወቀ ቦታ መወሰዳቸው ከስፍራው ለፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ የደረሰው ዜና […]

የኢትዮጵያ መንግስት ባለፉት ቅርብ ወራት ያሰራቸውን የኢንተርኔት አምደኞችና ጋዜጠኞች፤ ጉዳይ ጨምሮ በተለያዩ ጊዜያት የወሰዳቸው እርምጃዎች ተከትሎ የተለያዩ ትችቶች ለመገናኛ ብዙኃን መብት የቆሙ ወገኖችን ጨምሮ ከተለያዩ አቅጣጫዎች እየተሰሙ ነው።

ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ በቅርቡ ለአገሪቱ ፓርላማ ባሰሙት ንግግራቸው የግል ጋዜጦችንና ሞያውን አስመልክቶ የሰጡትን አስተያየት ተከትሎ፤ ”የኢትዮጵያ መንግስት ጋዜጠኞችንና ጋዜጠኝነትን አስመልክቶ እያራመደ ያለው ፖሊሲ ለአገሪቱ የንግግርና የፕሬስ ነጻነት አይበጅም፤” ሲል ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት CPJ ተችቷል።

በሰሞንኛው የመንግስቱ እርምጃዎችና በንግግር ነጻነት መብት ላይ አንድምታ ባላቸው የተለያዩ የአገሪቱ ሕጎች ዙሪያ ከኅግ ባለሞያ ጋር የተካሄዱ ተከታታይ ቃለ ምልልሶች ከዚህ…

ውጥረት በተመላበት ኹኔታ ተጀምሮ ተጋግሎ የሰነበተውና በመጨረሻም ወደ መግባባትና አንድነት የመጣው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ÷ ለኹለት ሱባዔ ያኽል ሲያካሒድ የቆየውን የመጀመሪያ ዓመታዊ መደበኛ ስብሰባውን ነገ፣ ጥቅምት ፳፮ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም. ከቀትር በፊት ያጠናቅቃል፡፡ በስብሰባው ማጠናቀቂያ÷ ቅዱስ ሲኖዶስ መሰንበቻውን ስለተነጋገረባቸው ጉዳዮች፣ ስላሳለፋቸው ውሳኔዎችና ስለወሰዳቸው አቋሞች የምልአተ ጉባኤው ርእሰ መንበር ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ በንባብ የሚያሰሙት ጋዜጣዊ መግለጫ …

ጥቅምት ፳፬(ሃያ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከአዲስ አበባ የተላኩ የፌደራል ፖሊስ አባላትና ደህንነቶች፣ ወደ ፓርቲው መሪዎች ቤት ከንጋቱ አስራ አንድ ሰአት ላይ በመሄድ፣ መኖሪያ ቤቶቻቸውን ሰብረው በመግባትና አንዳንዶችንም ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ በመደብደብ አፍነው ወዳልታወቀ ቦታ ወስደዋቸዋል። የመተማ ወረዳ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ በላይነህ ሲሳይ፣ የምእራብ አርማጭሆ ወረዳ ሰብሳቢ አቶ አንጋው ተገኝ እንዲሁም የስራ አስፈጻሚ …

ጥቅምት ፳፬(ሃያ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በቅርቡ ትብብር የመሰረቱ 9 ተቃዋሚ ፓርቲዎች ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል ለአንድ ወር የሚቆይ የመጀመሪያ ዙር የህዝባዊ ትግል ፕሮግራሙን ጥቅምት 25/2007 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ይፋ አድርገዋል። ‹‹ነጻነት በሌለበት ፍትሃዊ ምርጫ የማይታሰብ በመሆኑ የተዘጋውን በር ለመክፈት የ‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ› በሚል የዝግጅት መርሃ ግብር አዘጋጅቷል። ‹‹ምርጫ ቦርድ ለገዥው ፓርቲ …

ጥቅምት ፳፬(ሃያ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የቅማንት ተወላጆች ያነሱትን ጥያቄ ተከትሎ በተጠራ የስራ ማቆም አድማ በዞኑ የሚገኙ ከ80 በላይ ትምህርት ቤቶች ካለፈው አርብ ጀምሮ የተዘጉ ሲሆን፣ መንግስት እስከ መስከረም 30 መልስ የማይሰጥ ከሆነ፣ ተቃውሞው ግብር ባለመክፈል እንደሚቀጥል አስተባባሪዎቹ ለኢሳት ገልጸዋል። ከዚህ ቀደም በርካታ አስተባባሪዎች ተይዘው የታሰሩ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን መንግስት ለጥያቄው እስከ መስከረም …

ጥቅምት ፳፬(ሃያ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፌደራል ፍርድ ቤቱ ከአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጋር በተያያዘ ተይዘው በነበሩት ተማሪዎች ላይ ከ1 እስከ 5 በሚደርስ እስር እንዲቀጡ ውሳኔ አሳልፏል። በሌላ ዜና ደግሞ በአዳማ ቤታቸው የሚፈርስባቸው ሰዎች ባስነሱት ተቃውሞ ፖሊሶች ተጎዱ። የአከባቢው ነዋሪዎች እንደገለጹት  ከከተማ አስተዳደሩ ቤት አፍራሽ ግብረ ሀይል  ህገወጥ የተባሉ ቤቶችን ለማፍረስ ወደ ስፍራው …

#FreeZone9bloggers #FreeEdom #FreeTesfalem #FreeAsemamaw #Ethiopia 
ዛሬ ከጠዋቱ ሶስት ሰአት ጀምሮ ይሰየማል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው የጦማርያኑ እና የጋዜጠኞቹ ችሎት ከወትሮው በተለየ ጥብቅ ጥበቃ ለአጭር ደቂቃዎች ተከናውኗል፡፡ 

በነሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ ከተከሰሱት 10 ተከሳሾች ( አንድ በሌለችበት) ዘጠኙ ፍርድ ቤት የቀረቡ ሲሆን ሲሆን በእለቱ ፍርድ ቤቱ የክሱ ላይ የተከሳሽ ጠበቆች ያቀረቡትን የመጀመሪያ ደረጃ የክስ መቃወሚያ እና የአቃቤ ሀግን መልስ አይቶ ብይን ይሰጣል ተብሎ ተጠብቆ ነበር፡፡ 

ችሎቱ ከተለመደው አዳራሽ ይከናወናል በሚል እሳቤ ወዳጅና ቤተሰቦች ቢገኙም መጀመሪያ በደፈናው ወደ ችሎት አዳራሽ መግባትን በመከልከል በማስከተል ደግሞ የተወሰኑ የቤተሰብ አባላት ችሎት ውስጥ አንዲገቡ ተደርጎ ነበር፡፡ ከአፍታ ቆይታ በኋላ ግን ችሎቱ ውስጥ ያለው የድምጽ ማጎያ ስለማይሰራ ይበልጥ አነስተኛ ወደሆነ ክፍል ችሎቱ አንዲዘዋወር ተደርጓል፡፡ በመሆኑም የተከሳሽ ወዳጅና ቤተሰቡ ባልታደሙት አጭር ችሎት ሁለት የግራ እና የቀኝ ዳኞች አዲስ የተለመወጡ በመሆናቸውና ኬዙን ስላልመረመሩት ለህዳር ሶስት ( ኖቬምበር 12) ተለዋጭ ቀጠሮ በመስጠት የዛሬው ቀጠሮ በአጭሩ ተዘግቷል፡፡ 

እስር ላይ የሚገኙት ሴት ተከሳሾች ጉብኝት መብትን አስመልክቶ ፍርድ ቤቱ ባለፈው ቢሰየምም ለውጥ አለመኖሩን በመጥቀስ አቤቱታቸው ያሰሙ ሲሆን የማረሚያ ቤት ሃላፌው በሚቀጥለው ቀጠሮ መጥተው አንዲያስረዱ ፍርድ ቤቱ ትእዛዝ ሰጥቷል፡፡ 

ዛሬ ከፍተኛ ግርግር እና የቦታ እጥረት አንዲሁም ወላጆች መንገላታት የታየ ሲሆን ጦማርያኑ እና ጋዜጠኞቹ እነደቀድሞው ችሎት ነጭ ልብስ በመልበስ በመልካም ሁኔታ ላይ አንደሚገኙ ታይቷል፡፡ 

በተያዘ ዜና የጦማርያኑን የዋስትና ጥያቄ አስመልክቶ ጠበቃቸው ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ የተባለ ሲሆን ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ነገ ጠዋት በሚሰየመው ችሎት ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ( አጋርነታችሁን የምታሳዩ የዞን 9 ነዋሪያን ነገ ስድስት ኪሎ በሚገኘው የጠቅላይ ፍርድ ቤት ችሎት በመገኘት አጋርነታችሁን እነድታሳዩ ጥሪ እናቀርባለን)

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

በሶማልያ ፕሬዝደንት ሃሰን ሼኪ ሞሃመድ እና በጠቅላይ ሚኒስትሩ አብዱዊሊ ሺካህ አህመድ መካከል የተፈጠረዉ የስልጣን ሽኩቻ ከሁለት አስርተ ዓመታት በላይ በጦርነት ስትታመስ የቆየችዉን ሀገር ዳግም እንዳያንኮታኩታት ማስጋቱን የአዉሮጳ ሕብረት እና የተመድ አሳሰቡ።

በጣሊያኒኛዉ«ማሬ ኖስትሩም» ወይም ባህራችን በሚል መጠሪያው ለአንድ ዓመት ያህል ሜዲትራኒያን ባህል ላይ ችግር የሚገጥማቸውን በተለይም ስደተኞችን ባህር ሰምጠው እንዳይቀሩ የማዳን ተግባር ሲያከናዉን የነበረው የኢጣልያ ባህር ኃይል ካለፈው ቅዳሜ ጀምሮ በትሪቶን ተተክቷል።

የዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ፒተር ማዉረር ኢትዮጵያን ሰሞኑን ለሶስት ቀናት ጎብኝተዋል። ፒተር ማዉረር በቆይታቸዉም ከአፍሪቃ ሕብረት ከፍተኛ ባለስልጣናት እና ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ተገናኝተዉ፤

ለአቶ ዛይድ መነሳት ምክንያት የሆነው ጉዳይ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ደብዳቤ ላይ ባይተነተንም፣ የትራንስፖርት ሚኒስቴር ባቀረበው ጥያቄ ላይ ተመሥርቶ ውሳኔውን እንዳሳለፈ ደብዳቤው አትቷል፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ለትራንስፖርት ሚኒስቴር ሪፖርት ያቀርባል፡፡ የትራንስፖርት ሚኒስትሩ አቶ ወርቅነህ ገበየው የመንገድ ባለሥልጣን ቦርድም ሰብሳቢ ናቸው፡፡ ሰሞኑን አቶ …

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ዛይድ ወልደ ገብርኤል ከሥልጣናቸው ተነሱ Read more »

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር – ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም 9 ተቃዋሚ ፓርቲዎች የመሰረቱት ትብብር ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል ለአንድ ወር የሚቆይ የመጀመሪያ ዙር የህዝባዊ ትግል ፕሮግራሙን ዛሬ ጥቅምት 25/2007 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ይፋ አደረገ፡፡
‹‹ነጻነት በሌለበት ፍትሃዊ ምርጫ የማይታሰብ በመሆኑ የተዘጋውን በር ለመክፈት የ‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ› በሚል የፕሮግራም መርሃ ግብር ለመክፈት ወስኖ የመጀመሪያው ዙር እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ ከተማ ለማድረግ›› እንዳዘጋጀ ያሳወቀው ትብብሩ የትግሉ ዓላማ ፍትሃዊ ምርጫ እንዲኖር የሚያስችል መሆኑን ገልጾአል፡፡
‹‹ምርጫ ቦርድ ለገዥው ፓርቲ ያለውን ወገናዊነትና ጉዳይ አስፈጻሚነት ፍንትው አድርጎ አሳይቷል›› ያለው መግለጫው በመጀመሪያ ዙር የአንድ ወር ፕሮግራሙ 6 ዋና ዋና ተግባራትን ለመፈጸም ዝርዝር እቅዶችን አውጥቶ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል፡፡

phpBB [video]

በህዳር ወር የሚያከናውናቸው ተግባራትም፡-
1. በቤተ እምነት ጸሎት እንዲደረግና ጥሪ ማቅረብና አማኞች እንደየ እምነታቸው ተሳትፎ እንዲያደርጉ ማድረግ
2. የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባዎችን ማድረግ
3. የተቃውሞ ድምጽ ማሰማት (ሰላማዊ ሰልፍ)
4. ለመንግስት ተቋማት ደብዳቤ ማስገባት
5. በምርጫ ዙሪያ የፓናል ውይይቶችን ማድረግና
6. የህዝብን ተሳትፎ ማበረታታትና ድጋፍ ማሰባሰብ እንደሆኑ በመግለጫው አሳውቋል፡፡
ከእቅዶቹ መካከልም በሶስት ተከታታይ እሁዶች በተለያዩ የአዲስ አበባ ክፍሎች 3 የአደባባይ ስብሰባዎች እንደሚኖሩ፣ በመጨረሻው መርሃ ግብርም ህዳር 27ና 28 በፕሮግራሙ ማጠቃለያነት የ24 ሰዓት (የውሎና የአዳር) የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚደረግ የትብብሩ ሊቀመንበር ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ገልጸዋል፡፡

በገዥው ፓርቲና በምርጫ ቦርድ ጥምረት ይፈጸማል ያለውን ህገ ወጥ ተግባር በመታገል ለሰላማዊ ትግሉ አወንታዊ አስተዋጽኦ ለማበርከት እስከመጨረሻው በፅናት ለመቆም መዘጋጀቱን የገለጸው ትብብሩ በአገር ቤትና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን፣ በትብብሩ ሂደት ቆይተው እስካሁን ያልፈረሙና ሌሎች ፓርቲዎች እና የዓለም አቀፉ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ከጎኑ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርቧል፡፡
Image
Image
Image
Image

የበፍቃዱ ሃይሉ ወንድም በፎቶ ማንሳት ሙከራ ተይዟል።የዋስትና ጉዳይ ለነገ ተቀጥሯል።
Minilik Salsawi

193 ቀናት ካለምንም ማስረጃ ሃሳባቸውን በነጻነት በመግለጻቸው ብቻ ለእስር የተዳረጉት የዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ሶስት ጋዜጠኞች በዛሬው እለት በልደታ ፍርድ ቤት ተገኝተዋል ። ነጭ በመልበስ ሰላማዊነታቸውን ያሳዩት ጦማርያኑ እና ጋዜጠኞቹ በልደታ ፍርድ ቤት ሲደርሱ ፎቶግራፍ ለማንሳት ሞክሯል የተባለ የጦማሪ በፍቃዱ ሃይሉ ወንድም በወያኔ ፖሊሶች ቁጥጥር ስር ውሏል።

ፍርድ ቤቱ ለህዳር 3 2007 ቀጠሮ የሰጠ ሲሆን ማህሌት እና ኤዶም ያቀረቡትን የማረሚያ ቤቱ የሚደርስባቸውን በደል በተመለከተ ሃላፊዎቹ ቀርበው እንዲያስረዱ ት እዛዝ ሰቷል።ዛሬ ጥቅምት 25 ቀን 2007 ዓ.ም በልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ለ10ኛ ጊዜ ችሎት የቀረቡት የዞን ዘጠኝ ጦማርያንና ሶስቱ ጋዜጠኞች ለሳምንት (ህዳር 3/2007 ዓ.ም) ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠባቸው፡፡
ፍርድ ቤቱ ዛሬ በጦማርያንና በጋዜጠኞቹ ቀደም ሲል የቀረበውን የክስ ማሻሻያ አቤቱታ መርምሮ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ የተጠበቀ ቢሆንም፣ ምርመራው አላለቀም በሚል ምክንያት አጭር ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
በዛሬው ችሎት ላይ ከተሰየሙት ዳኞች መካከል ሁለቱ አዲሶች በመሆናቸው ምክንያት ተለዋጭ ቀጠሮ መሰጠቱን ጠበቃ አምሃ መኮንን ገልጸዋል፡፡ ዳኞች ብቻ ሳይሆን ችሎት ክፍሉም በመቀየሩ ክፍሉ ጠባብ ነው በሚል፣ የተከሳሽ ቤተሰቦችና ጋዜጠኞች ችሎት መግባት አለመቻላቸውም ታውቋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ በነገው ዕለት ጠቅላይ ፍርድ ቤት በተከሳሾች ዋስትና ጉዳይ ውሳኔ ለመስጠት ቀጠሮ መያዙን አቶ አምሃ ጨምረው አስረድተዋል፡፡
በተከሳሾች በኩል ደግሞ፣ ሁለቱ ሴት ተከሳሾች (ኤዶም ካሳዬ እና ማህሌት ፋንታሁን) በቃሊቲ ማረሚያ ላይ ያነሱትን የመብት ጥሰት አቤቱታ በተመለከተ የማረሚያ ቤቱ አስተዳደር በቀጣይ ቀጠሮ ድጋሚ ቀርቦ እንዲያስረዳ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ ሁለቱ ተከሳሾች በቀን ለ10 ደቂቃ ብቻ ስማቸው ቀድሞ በተመዘገቡ ሰዎች ብቻ እየተጎበኙ እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡

– የወያኔ ልማታዊ ዲሞክራሲ የህዝብን መጉላላት እንደጨመረ ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች አማረሩ።
– አዳማ ናዝሬት ውጥረቱ የነገሰ ሲሆን ሕዝባዊ ተቃውሞ ይፈነዳል ተብሎ ተፈርቷል።
– ሕዝቡ ለታክሲዎች የስራ ማቆም አድማ በመተባበር ለህግ የበላይነት እና ልእልና እንዲነሳ ተጠይቋል ።
– በአዳማ ናዝሬት የባጃጅ ባለቤቶች ሊያደርጉት የነበረው የስራ ማቆም አድማ አስተላለፉት። – የታክሲ ባለንብረቶች ከትላንትና ጀምረው ቁጣቸውን እየገለጹ ነው።
Minilik Salsawi

በወያኔው መንግስት አዲሱ የልማት ስታራቴጂ በሚል በታክሲዎች እና በሕብረተሰቡ ላይ ከፍተኛ እንግልት እየደረሰ እንደሆን ነዋሪዎች በመግለጽ ላይ መሆናቸው ታወቀ ። ከትላንትና ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ላይ በከተማው ትራፊኮች እየተካሄዱ ያሉ ድርጊቶች በከፍተኛ ሁኔታ ህዝብን ወደ ተቃውሞ የታክሲ ባለንብረቶችንም ወደ ስራ ማቆም አድማ የሚመራ ነው ሲሉ ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።

በአዲስ አበባ ከተማ የታክሲዎች የስራ ማቆም አድማ ልንጠራ እንችላለን ሲሉ አንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የታክሲዎች ባለንብረቶች ማህበር አባል የገለጹ ሲሆን የታክሲዎች የስራ ማቆም አድማ ከበፊትም የታሰበበትና በሂደት የጊዜ ሰሌዳ ወጥቶበት እንደሚካሄድ ሲገልጹ ሕዝቡም ለዚሁ ያለውን ትብብር እንዲገልጽ በማለት ሲናገሩ ሕዝቡ ለታክሲዎች የስራ ማቆም አድማ በመተባበር ለህግ የበላይነት እና ልእልና እንዲነሳ ጠይቀዋል ።

የታክሲዎች የስራ ማቆም አድማ መታየት አለበት በሚለው ሃሳብ የሚስማሙ ሹፌሮች እንዳሉት ከዚህ ቀደም በተለያዩ የከተማዋ ቦታዎች የነበሩት የታክሲ መጫኛዎች እንዲቀሩ የተደረጉ ሲሆን ወደተለያዩ ቦታዎች በመበታተናቸው የህዝቡ እንግልት ከመጨመሩም በላይ ሹፌሮችም ይህንን ተከትሎ በመንገድ ላይ እንዳይጭኑ ከጫኑ ከባድ ቅጣት እየተጣለባቸው ስለሆነ ከልማታዊው የትራፊክ ህግ ጋር ተስማምተው ሊሄዱ እንዳልቻሉ ገልጸዋል። የታክሲ ባለንብረቶችም ይሁኑ ሹፌሮች እና ረዳቶቻቸው በልማታዊው የትራፊክ እኩይ ህግ የተበሳጩ ሲሆን ቁጣቸውን በመግለጽ ወደ ስራ ማቆም አድማ ጥሪ ለማድርግ እያመሩ መሆኑን ታውቋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በአዳማ ከትላንትና ጀምሮ ከፍተኛ ውጥረት እንደተከሰተ ነዋሪዎች ተናግረዋል። ሕዝባዊ ተቃውሞ ይፈነዳል በሚል በነገሰው ውጥረት የባጃጅ ባለንብረቶች ባጃጆቻቸው ወደ ከተማው እንዳይወጡ ይዘዋቸው የነበረ ቢሆንም ፖሊስ ውጥረት እንዳሌለ እና ስራwቸን እንዲጀምሩ ሲያስገዲዳቸው ውሏል።

ስራቸውን እንዲጀምሩ ቢያስገድዳቸውም የባጃጅ ሹፌሮች ስራ ለማቆም ያስነሱት ተቃውሞ በፖሊስ የከሸ መሆኑንም ተያይዞ የመጣው ዜና ይገልጻል። ሹፌሮቹ በመንግስት ትራፊኮች ከፍተኛ የአስተዳደር በደል እና ዘረፋ ይፈጸምብናል በማለት ሲናገሩ የነበረ ሲሆን ከትላንት ጀምረው አዳማን ፖሊሶች በአጥለቅልቀዋታል ሲሉ ምንጮቹ ገልጸዋል።በአዳማ ናዝሬት ከሁለት አመት በፊት በተደረገ የስራ ማቆም አድማ ባጃጆች እና ሹፌሮቻቸው በመንግስት ላይ ተቃውሞ አሰምተው እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው ሲሉ ምንጮቹ አስታውስዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ዜና በቅርብ ቀናቶች ውስጥ ህዝቡ በንቃት እንዲከታተል እና በአዳማ ናዝሪት የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ሁሉ የስራ ማቆም ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል ሲሉ የባጃጅ ሹፌሮች በላኩት ቃላቸው ገልጸዋል።

– የመከላከያ እና ፖሊስ ሰራዊቱ ላይ አለመተማመኑ እየጨመረ መጥቷል።
– የደህንነት አባላቱ መረጃን በግል ጥቅም በመለወጥ እየሰሩ ነው የሚል ግምገማ ቀርቦባቸው ተንጠዋል።
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
– የሃገሪቱን ጉዳይ በተመለከተ ለበታች “ተከታይ ” ባለስልጣናት መረጃ መስጠት ቆሟል።
– የሕወሓት ታጣቂዎች ከምቾት ኑሮ ተነስተው ለመሸሽ እንጂ ታጥቀው ደም ለመፋሰስ ዝግጁ አይደሉም ።

በኢትዮጵያ ውስጥ መጭው ጊዜ በህዝቡ ዝምታ ተከትሎ በስርአቱ ላይ ከፍተኛ ቀውስ ይከተላል የሚል መረጃ መሰማት ከጀመረ ጀምሮ በወያኔ ባለስልጣናት እና በቅርብ ሰዎቻቸው ዘንድ ከፍተኛ የሆነ ድንጋጤ መኖሩን ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ ገልጸዋል።የአስመራ ተቃዋሚዎች እንቅስቃሴ ሪሞት ኮንትሮል ወያኔ እጅ ነው ስለዚህ የትጥቅ ትግል ወያኔን አያስፈራውም ያሉት ምንጮች የሃገር ውስጥ ተቃዋሚ ፓርቲዎች እና ወያኔ ልሙጥ የሚላቸው የተቃዋሚ ፓርቲዎቹ አጋር ዲያስፖራዎች በለውጥ እንቅስቃሴ ውስጥ ህዝቡን በማንቃት ረገድ እያደረጉት ያለው ርብርብ ትልቅ ስጋት እንደፈጠረባቸው እንዳስደነገጣቸው ሲታወቅ በድንጋጤ የመጣ ለኢሕአዴግ አንዳንድ ወቅታዊ ጥያቄዎችን እያቀረቡ ያሉ ባለስልጣናት ከሃገር እንዳይወጡ እና ምንም አይነት እንቅስቃሴ እንዳያደርጉ ፓስፖርታቸውን ከመነጠቅ ጀምሮ በአይነቁራኛ እንደሚጠበቁ ታውቋል። የሕወሓት ታጣቂዎች ከምቾት ኑሮ ተነስተው ለመሸሽ እንጂ ታጥቀው ደም ለመፋሰስ ዝግጁ እንዳልሆኑ ከምንጮቹ ተሰምቷል።
Image
በመከላከያ ሰራዊቱ ውስጥ አዳዲስ የሆኑ ውስጣዊ እርምጃዎችን በመውሰድ በተጠናከረ መልኩ በሰራዊቱ መካከል እየተከሰተ ያለውን አለመተማመን ለመቆጣተር የሚረዱ ስብሰባዎች በስፋት ከባለፈው ሳምንት ጀምሮ መካሄድ የጀመሩ ሲሆን በፖሊስ ሰራዊቱም ውስጥ በተለይ በቡድን የሚያሴሩ ሰዎች አሉ እየተባለ ስለሚነገር የወያኔ አንድ ብሄር ሰዎችን በስፋት በመመደብ እንዲሁም ከዚህ ቀደም እንደተሰረገው የቢሮ ሰራተኛውን ከደህንነት ቢሮ በሚመደቡ የሕወሓት ደህንነቶች ለመተካት የታቀደ ሲሆን ቀሪውን ከቢሮ ውጭ የሚሰራውን የፖሊስ አካል ለመቆጣጠር አዲስ ሃይል እንደሚመደብ ታውቋል።የመከላከያ እና የፖሊስ ሰራዊቱ ከሃገሪቱ የተቃዋሚ ሃይሎች ጋር በማበር አደጋ ሊፈጥር ይችላል ሲል መፈራቱ እንዲሁም ሰራዊቱን እየከዱ የሚሄዱ መበራከታቸው አለመተማመኑን ከማስፋቱም በላይ ጥያቄዎች እንዲነሱ አድርጓል።

በኢትዮጵያ ውስጥ እየተደረገ ያለውን የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ መንግስት አቀፍ እንቅስቃሴ በተመለከተ ከሕወሓት ባለስልጣናት ውጪ ለበታች ተከታይ ባለስልጣናት ምንም አይነት መረጃ መስጠት እንደቆመ ሲታወቅ ማንኛውም ሃገራዊ ጉዳይ አልቆ እና በአፈጻጸም ደረጃ ላይ ሆኖ እንደማንኛውም ሰራተኛ እንደሚሰሙ ባለስልጣኖቹ በመናገር ላይ መሆናቸው ታውቋል ። በደህንነት ቢሮ ውስጥ በተደረገ ግምገማ የደህንነት አባላት መረጃዎችን በግል ጥቅም በመለወጥ አሳልፋቹ እየሸጣችሁ ናቸው በሚል መገምገማቸውን የውስጥ ምንጮች ተናግረዋል።እንደ ምንጮቹ ከሆነ መረጃን ያለምንም ርሕራሔ መረጃው በአምስት ደኢቃ ውስጥ ጠላት እጅ ገብቶ ያገኘነው ነው ሲሉ የአዲስ አበባው ደህንነት ሹም አቶ ጸጋዬ ተናግረዋል።በዚህ ግምገማ የተከፉት የደህንነት አባላት በመንግስት ባለስልጣናቱ እየተናጡ ቢወረፉም ዝምታን መርጠዋል።#ምንሊክሳልሳዊ