አፍ በፈቱበት ቋንቋ ስደተኞች መረጃ ሲያገኙ

ኢትዮ -ኮሎኝ የተባለው የስፖርት እና የባህል ማህበር በኮሎኝ ከተማ ከአንድ የስደተኞች ምክር መስጫ ማዕከል ጋር በመተባበር የብዙ ስደተኞችን ጥያቄ የሚመልስ ድረ ገፅ በአማርኛ ተርጉሞ ለስደተኞች አቅርቧል። ስለዚሁ ድረ ገፅ በዛሬው የወጣቶች ዓለም እናወራለን።