አዲሱ የኢትዮጵያ ፓርላማ ሰኞ ስራ ይጀምራል
ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ መቶ በመቶ የሚቆጣጠረው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መሪዎቹን ይመርጣል
ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ መቶ በመቶ የሚቆጣጠረው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መሪዎቹን ይመርጣል
ቦታውን እና መልኩን እየቀያየረ የሃይማኖት ነጻነት የሚጋፋው የወያኔው አስተዳደር የሕዝበ ሙስሊሙን መስኪድ ሲዳፈር እና እየቀማ ለመጤ የአህበሽ እምነት ሲሰጥ በኢርቶዶክስ ተዋህዶ ውስጥ ገብቶ በዘረኝነት እና በሙስና ቤተክርስቲያኒን ሲበጠብጥ አሁን ደሞ ባለተራዎቹ የሆኑት የፕሮቴስታንት አማኞች ጋር በመዝመት ላይ ሲገኝ በልማት ስም …
በሐረር አማኑኤል ባፕቲስት ቤተክርስትያን መሪዎች ላይ የመብት ጥሰት ተደረገ:: Read more »
ታካሚዎች የሰውነት መከላከያ እንክብል (ARV) የሚሰጣቸው የበሽታ መከላከያ ቁጥር ከተወሰነ ድረጃ በታች ሲወርድ ነው። በአዲሱ አሰራር በቫይረሱ መያዛቸው የታወቀ ሰዎች በፍጥነት የመከላከያ ህክምና ያስፈልጋቸዋል።
የሳኡዲን ንጉስ ሰልማንን ልክ እንደ ግብፁ ሙርሲ ከስልጣን ለማሶገድ ምዕራባውያን እና ጀሌዎቻቸውን እያሴሩ ነው Muslim Wedaje ይህን ፅሁፍ ለመፃፍ ያነሳሳይ ኢነዲፔንደንት የተሰኘው የእግሊዙ ጋዜጣ ንጉስ ሰልማን ከስልጣን እንዲወገዱ መፈንቅለ ስልጣን ለማድረግ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን መዘገቡን ተከትሎ ነው፡፡ ጋዜጣው ስማቸው እንዲጠቀስ …
የሳኡዲን ንጉስ ሰልማንን ልክ እንደ ግብፁ ሙርሲ ከስልጣን ለማሶገድ ምዕራባውያን እና ጀሌዎቻቸውን እያሴሩ ነው Read more »
በሀገራችን የዘመን አቆጣጠር መሠረት ሕዝባችን 2007 ዓ.ም. ዘመነ ሉቃስን አሳልፎ ወደ አዲሱ 2008 ዓ.ም. ዘመነ ዮሃንስ ከተሸጋገረ ጥቂት ቀኖችን አሳልፏል። የሰው ፍጡር በህይወት እስከኖረ ድረስ ማንኛውም ዜጋ እንደ አቅሙና ችሎታው፤ መድረስ ከሚፈልገው ሁለንተናዊ የኑሮ መሻሻል አንፃር ባለፈው ዓመት በክፉም ሆነ …
አሮጌው 2007 ዓ.ም. ተገባዶ አዲሱ ሲተካ! የት ላይ ነን? ምንስ ይጠብቀናል? ዴሞ (የኢሕአፓ ልሳን) Read more »
በኢትዮጵያ ትከሻ ላይ የተቆለፈውን ቀምበር ለማላቀቅ ቍልፉ የትጥቅ ትግል መሆኑ በተነሣ ቍጥር ከአንዳንድ ሰዎች የሚሰጠው አስተያየት ግራ የሚያገባ ነው። ገዢዎቹና ደጋፊዎቻቸው ቢቃወሙ ይገባኛል። የሚሰጡት አስተያየት ግን ሕፃንን ሳይቀር የሚያሥቅ ነው። “ጦርነት በቃን” ይላሉ። “አትንኩን” ማለታቸውን የማናውቅ ይመስላቸዋል። ጦርነት ካላስፈለገ፥ ለምን …
ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል በማፈራረስና ኦሮሚያ ክልልን የመገንጠል ፖለቲካዊ ዓላማ በመያዝ፣ ዓላማውን ለማስፈጸም ሲንቀሳቀሱ ተደርሶባቸዋል የተባሉ ሦስት ተጠርጣሪዎች ተከሰሱ፡፡
በመንግሥት ላይ ተፅዕኖ በማሳደር፣ ኅብረተሰቡን በማስፈራራትና የአገሪቱን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ተቋማትን ለማናጋት፣ ራሱን የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ብሎ ከሚጠራው ድርጅት ተልዕኮ ተቀብለው ሲንቀሳቀሱ ተደርሶባቸዋል የተባሉት ተከሳሾች ቶሎሳ በየነ፣ ቱሉ ሞኦ አቤቱና መገርሳ መሸሻ የሚባሉ መሆናቸውን የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ችሎት ያቀረበው ክስ ያብራራል፡፡
ተከሳሾቹ በኦነግ አማካይነት ‹‹የኦሮሞን ብሔር ከመንግሥት ጫና ለማላቀቅና ነፃ ለማውጣት መታገል አለብህ፤›› ተብሎ የቀረበላቸውን ጥያቄ በመቀበል አባል መሆናቸውን ክሱ ይጠቁማል፡፡
ተከሳሾቹ ከ2000 ዓ.ም. ጀምሮ በኦሮሚያ ክልል በምሥራቅ ወለጋ ዞን በነቀምት ከተማ በሚገኙ የተለያዩ የንግድ ቤቶች ከኦነግ አባላት ጋር በመገናኘት፣ ድርጅቱ የሚሰጠውን ወታደራዊና ፖለቲካዊ ሥልጠና ለመውሰድ ወደ ኤርትራ መጓዛቸውንም ክሱ ያክላል፡፡ ኤርትራ አገር ከደረሱ በኋላ ኢን ተብሎ በሚጠራው ማሠልጠኛ ካምፕ፣ ከሌሎቹ የድርጅቱ አባላት ጋር በመሆን ወታደራዊ የአካል ብቃት ሥልጠና መውሰዳቸውም በክሱ ተገልጿል፡፡ የጦር መሣሪያ አገጣጠም፣ ዒላማ ተኩስ፣ ቦምብ አፈታት፣ አገጣጠምና አወራወር ያካተተ ወታደራዊ ሥልጠና ለተከታታይ ሦስት ወራት መውሰዳቸውን ክሱ ይገልጻል፡፡
በቁጥጥር ሥር ካልዋሉት ግብረ አበሮቻቸው ጋር በመሆን ኢትዮጵያ ውስጥ የኤሌክትሪክና የውኃ መስመሮችን መቁረጥ፣ የመኪና መንገዶችን በድንጋይ መዝጋትና የኦሮሞ ገበሬዎች እህል ወደ ገበያ እንዳያወጡ ለማድረግ ተልዕኮ በመቀበል፣ በተለይ ቶሎሳ በየነ የተባለው ተከሳሽ ሲንቀሳቀስ እንደነበር ክሱ ያስረዳል፡፡ ተልዕኮ ማስፈጸሚያ ተብሎ 8,000 ብር ተቀብሎ ከኤርትራ በጂቡቲ በኩል ወደ ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት መስከረም ወር 2007 ዓ.ም. መግባቱንም ጠቁሟል፡፡
ተከሳሾቹ ቁጥሩን በማያሳይ ‹‹UN KNOWN›› በሚል ስልክ በመደዋወል የጦር መሣሪያ ይቀባበሉ እንደነበርና ጥይቶቹን በፍራሽ ጠቅልለው በትራንስፖርት ሲያሳልፉ እንደነበሩ የዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡
ቱሉ ሞኦ አቤቱ የተባለው ተከሳሽ ከኤርትራ ወደ ጂቡቲ ከዚያም በሚሌ አድርጐ ወደ ኮምቦልቻ ከሄደ በኋላ፣ ወደ አዲስ አበባ ከዚያም ወደ ነቀምት በመሄድ አንደኛ ተከሳሽ አባት ቤት ውስጥ ክላሽኒኮቭ ጠመንጃውን ከ60 ጥይቶች ጋር መደበቁን ክሱ ይገልጻል፡፡ ካልተያዙ ግብረ አበሮቹ ጋር ተቀብሎት የነበረው ተልዕኮ፣ ኦሮሚያ ውስጥ የሚኖሩ የአማራ ተወላጆችን ለመግደል እንደነበር የዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡
ተከሳሾቹ በአጠቃላይ የወንጀል ሕግ ቁጥር 32(1ሀን) እና የፀረ ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652 አንቀጽ 7(1)ን በመተላለፍ በፈጸሙት በሽብርተኛ ድርጅት ተግባር ውስጥ በመሳተፍ ወንጀል መከሰሳቸውን ዓቃቤ ሕግ በክሱ አስረድቷል፡፡ ተከሳሾቹ በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ትዕዛዝ ተሰጥቶ የቀረበባቸውን ክስ ለመስማት ለጥቅምት 2 ቀን 2008 ዓ.ም. ተረኛ ችሎቱ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

በከባድ የሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ክስ በተመሠረተባቸው በእነ አቶ መላኩ ፈንታ የክስ መዝገብ የተካተቱትን የልብ ሕክምና ስፔሻሊስት ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ ወርዶፋን መንግሥት ትብብር እንዲያደርግላቸው፣ የግል ሆስፒታሎች ማኅበር ጠየቀ፡፡
በማኅበሩ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሲሳይ ማሩ ጆፋ ፊርማ በቀጥታ ክስ ለመሠረተው ለፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ተጽፎ በግልባጭ ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፣ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ለፍትሕ ሚኒስቴር፣ ለጤና ጥበቃ ሚኒስቴርና ለዳያስፖራ ዴስክ እንዲደርስ የተደረገው ደብዳቤ ማኅበሩ ለምን የመንግሥት ትብብር እንደተፈለገ ያብራራል፡፡
ደብዳቤው እንደሚገልጸው፣ በሙስና ወንጀል ክስ ተመሥርቶባቸው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት በመታየት ላይ የሚገኙት ዶ/ር ፍቅሩ፣ በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን አዲስ የልብ ሕክምና ማዕከልን የከፈቱ ፈር ቀዳጅ የልብ ሕክምና ባለሙያ ናቸው፡፡
በሆስፒታሉ የተዘጉ የልብ የደም ሥሮች ማየት የሚችል ሕክምና፣ የልብ ምታቸው ለቀነሰ ሕሙማን የልብ ምት ማስተካከል፣ ድንገተኛ የልብ መቆም መከላከል ሕክምናና ሌሎችም በርካታ ከልብ ጋር የሚገናኙ ሕክምናዎች እንደሚሰጡ ማኅበሩ፣ በደብዳቤው ጠቁሟል፡፡
የነፍስ አድን መሣሪያዎች በሰውነታቸው የተገጠመላቸው ታካሚዎች በየሦስት ወራት እየተከታተሉ በሕይወት የመቆየት ተስፋ እንደነበረባቸው የሚገልጸው ማኅበሩ ዶ/ር ፍቅሩ በመታሰራቸው ይሰጥ የነበረው ሕክምና በመቋረጡ የልብ ታካሚዎቹ ለከፋ ችግር እየተጋለጡ መሆኑን አስረድቷል፡፡
ዶ/ር ፍቅሩ ኢትዮጵያውያን ሐኪሞችን ወደ ስዊድን በመላክ የልብ ሕክምና ስፔሻሊስት እንዲሆኑ ማድረጋቸውን ማኅበሩ በደብዳቤው ጠቁሞ፣ ከስዊድን ከሚመጡ ሐኪሞች ጋር በሚደረግ የሕክምና ሒደት ደግሞ የዕውቀት ሽግግርም ይካሄድ የነበረ ቢሆንም፣ እሳቸው በመታሰራቸው መቋረጡን አስረድቷል፡፡
በመሆኑም ዶ/ር ፍቅሩ በመታሰራቸው ምክንያት በእሳቸው ክትትል ይደረግላቸው የነበሩ ሕሙማን ለከፋ ችግር መጋለጣቸውን፣ በጤና አገልግሎቱም ክፍተት እየተፈጠረ መሆኑን፣ መንግሥት የእሳቸውን አስተዋጽኦ ከግምት ውስጥ በማስገባትና ኅብረተሰቡ የደረሰበትን የሕክምና ዕጦትና መንገላታት ታሳቢ በማድረግ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግላቸው ጠይቋል፡፡
ማኅበሩ ለሚመለከታቸው አካላት ደብዳቤ የጻፈው ጳጉሜን 2 ቀን 2007 ዓ.ም. ቢሆንም፣ እስከ መስከረም 18 ቀን 2008 ዓ.ም. ድረስ ከማናቸውም አካላት ምንም ዓይነት ምላሽ አለማግኘቱ ታውቋል፡፡
የግንቦት 7 ድርጅትን ተልዕኮ በመቀበል የሽብር ተግባር ለመፈጸም የፌዴራል ፖሊስ አባል በመሆን መረጃ ሲያስተላልፉ ተደርሶባቸዋል ተብለው የተጠረጠሩ ሁለት ፖሊሶች በቁጥጥር ሥር ውለው ክስ ተመሠረተባቸው፡፡
በፌደራል ፖሊስ ተቋም ውስጥ ተመድበው ሕገ መንግሥቱን ለመጠበቅ የተጣለባቸውን አደራ በመተው፣ የግንቦት 7 ጥምረት ነው የተባለውን የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች የሰጣቸውን ተልዕኮ በመቀበል ሲንቀሳቀሱ ነበር የተባሉት፣ ኮንስታብል ነገደ ሸዋ ቀናና ረዳት ሳጅን እንዳለ ዘየደ የሚባሉ መሆናቸውን፣ የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ችሎት መስከረም 10 ቀን 2008 ዓ.ም. ያቀረበው ክስ ይገልጻል፡፡
ኮንስታብል ነገደ የተባለው ተጠርጣሪ ኤርትራ ከሚኖርና የግንቦት 7 ድርጅት አባል ጋር በስልክ በመገናኘት፣ ለመንግሥት ጥሩ አመለካከት የሌላቸውን እየመለመለ አድራሻቸውን እንዲሰጠው መስማማታቸውን ክሱ ይገልጻል፡፡ በፌዴራል ፖሊስ ተመሳሳይ የሥራ ድርሻ የነበረው ተከሳሽ ረዳት ሳጅን እንዳለ ተመሳሳይ ድርጊት መፈጸሙን የሚገልጸው የዓቃቤ ሕግ ክስ፣ ሁለቱም ተከሳሾች በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በሽብርተኛ ድርጅት ውስጥ በማናቸውም መልኩ መሳተፍ ወንጀል ክስ መሥርቶባቸዋል፡፡ ክሱን ተቀብሎ ያየው ተረኛ ችሎትም ተከሳሾቹ በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ በማዘዝ፣ ክሱን ለመስማት ለጥቅምት 2 ቀን 2008 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
ሌላው የመከላከያ ሠራዊት አባል መሆኑ የተጠቀሰውና የኦነግ አባል በመሆን አባላትን በመመልመልና መረጃ በማስተላለፍ ተጠርጥሮ ክስ የተመሠረተበት ወታደር አማኑኤል ደስታ ጅማ ይባላል፡፡
ተከሳሹ ኅብረተሰቡን አደጋ ላይ ለመጣል፣ ሕይወት ለማጥፋትና ንብረት ለማውደምና በመንግሥት ላይ ተፅዕኖ ለመፍጠር፣ ከመስከረም ወር 2007 ዓ.ም. ጀምሮ በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን ሻኪሶ አካባቢ ከድርጅቱ አባላት ጋር ይገናኝ እንደነበር የዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡
ተከሳሹ የኦነግን ተልዕኮ ለማሳካት በጥር ወር 2007 ዓ.ም. በአገር መከላከያ ሠራዊት በመቀጠርና ለአራት ወራት ሁርሶ ወታደራዊ ሥልጠና በመውሰድ፣ ሠራዊቱን ተቀላቅሎ መመደቡን ክሱ ያብራራል፡፡
በሠራዊቱ ውስጥ ከተመደበ በኋላ አባላትን በመመልመልና በማደራጀት በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን፣ ሻኪሶ ወረዳ፣ ሻኪሶ ከተማ ከሚገኘውና የኦነግ አባል ከሆነው ደበበ ሚደቅሳ ከተባለው የድርጅቱ አባል ጋር ግንኙነት ሲያደርግ መቆየቱ በክሱ ተጠቅሷል፡፡
የመለመላቸውን ሻምበል ባሻ ስንታየሁና ሃምሳ አለቃ ሸለመ ሞቱማ የተባሉ የመከላከያ ሠራዊት አባላትንና ሌሎች ወታደሮችን አስከድቶ፣ ወደ ኤርትራ ሄደው ለመቀላቀል በዝግጅት ላይ እያሉ በቁጥጥር ሥር መዋሉን ክሱ ይገልጻል፡፡ ክሱን ለመስማት ፍርድ ቤቱ ለጥቅምት 22 ቀን 2008 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
በትግራይ መንስኤው በውል ባልታወቀ የጉበት በሽታ ብዙዎች ለሞትና ለአልጋ ቁራኛነት እየተዳረጉ እንደሚገኙ በምስል የተደገፉ መረጃዎች ጠቁመዋል፡፡በ1997 በሰሜናዊ ትግራይ በታችኛው ቆራሮ ቀላቕል በተባለ ወረዳ መከሰቱ የሚነገርለት በሽታው ዛና በተባለ አካባቢ በሚገኙ 20 የወረዳው ጣብያዎች 430 የሚደርሱ ሰዎችን በማጥቃት 101 ያህሉን …
https://www.youtube.com/watch?v=ApjiJqFnVwc
መስከረም ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ መራሹ ገዥው ፓርቲ በመንግስት ቁጥጥር ስር የሚገኙ መገናኛ ብዙሃን የመልካም አስተዳደር፣ የሙስናና ኪራይ ሰብሳቢነት ችግሮችን አጋልጡ በሚል ከፍተኛ ግፊት ማድረጉን ተከትሎ ትርምስ መፈጠሩ ተሰማ፡፡ የመገናኛ ብዙሃኑን መሪዎች ጨምሮ አንዳንድ ጋዜጠኞች በሙስናና ብልሹ አሠራር የሚጠረጠሩ መሆናቸው ይበልጥ ነገሩን አወሳስቦታል፡፡ ኢህአዴግ በቅርቡ በመቀሌ ከተማ ባካሄደው ድርጅታዊ ጉባዔ …
መስከረም ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የህወሃት ነባር ታጋይና በሁዋላም የአፋር ብሄራዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ( አብዴፓን) መስርተው ክልሉን ላለፉት 24 ዓመታት ሲመሩት የቆዩት አቶ እስማኤል አሊ ሴሮ፣ ከስልጣን ተነስተው ወደ ፌደራል ሲዛወሩ እርሳቸውን ለመተካት በተፈጠረው የስልጣን ሽኩቻ፣ ህወሃት የደገፋቸው ቡድኖች አሸናፊዎች ሆነው መውጣታቸውን የደረሰን መረጃ ይጠቁማል። ቀድም ብለው ፓርቲውን እንዲመሩ የተመረጡት ወጣቱ …
መስከረም ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኤልኒኖ የአየር መዛባት ምክንያት በተፈጠረው ድርቅ ሳቢያ በኢትዮጵያ ውስጥ ሕፃናትን ጨምሮ ከ4.5 ሚሊዮን ሕዝብ በላይ ከፍተኛ በሆነ የምግብ እጥረት እየተሰቃዩ መሆኑንና አፋጣኝ የሆነ የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው የአውስትራሊያው ቻይልድ ፈንድ በሪፖርቱ አስታውቋል። በኢትዮጵያ ያለው የርሃብ ሁኔታ እጅግ አስጊ መሆኑንና በተለይ በአፋር፣ በአማራ፣ በኦሮሚያ፣ በትግራይ፣ በደቡብና በሶማሌ ክልሎች …
መስከረም ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአምስት ዓመቱ የጣሊያን ፍሽስት ወረራ ወቅት ለተፈጸሙት ዘግናኝ ግፎች የጣሊያን መንግስትና ቫቲካን የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ እንዲጠይቁና የተዘረፉት ቅርሶችና ንብረቶች ለኢትዮጵያ እንዲመለሱ በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ በተካሄደ ዓለም አቀፍ ጉባኤ ላይ ዓለምአቀፍ ሕብረት ለፍትሕ ጥያቄውን አቀረበ። በጣሊያን ወረራ ወቅት የጣሊያን ወራሪዎች በዓለም ላይ የተከለከለውን ካለስተር ቦንብ ተጠቅመው ንፁሃን …
መስከረም ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በየመን የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ችግር በማጋለጥ እንዲሁም የተለያዩ የሰብአዊ ድጋፎችን በማድረግ የሚታወቀው ጋዜጠኛ ግሩም ተክለሃይማኖት ፣ በየመን የጸጥታ ሃይሎች መታሰሩ ታውቋል። ጋዜጠኛ ግሩም በምን ምክንያት እንደታሰረ የታወቀ ነገር የለም። ኢሳት ባለቤቱን ለማነጋገር ተደጋጋሚ ሙከራ ቢያደርግም አልተሳካለትም። በየመን በመካሄድ ላይ ያለውን አስከፊ ጦርነት ተከትሎ በኢትዮጵያውያን ላይ የሚደርሰውን ግፍ …
የወያኔው መንግስት እና መጅሊስ ሳኡድ አረቢያ ውስጥ በተከሰተው አደጋ የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት አልተወጡም:: የሚለውን የመረጃ Mereja.com ዘገባ http://www.mereja.com/amharic/archives/468473 ተከትሎ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የሃጂ ጉዞ ጉዳይ ቢሮ መግለጫ አውጥቷል::በሳኡድ አረቢያ በሚና በሃጅ ጸሎት ላይ በተፈጠረው መጨናነቅ በተከሰተው አደጋ አስራሶስት ኢትዮጵያውያን …
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የሃጂ ጉዞ ጉዳይ ቢሮ መግለጫ አውጥቷል:: አስራሶስት ኢትዮጵያውያን ሲሞቱ ሃያስድስት ቆስለዋል:: Read more »
ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።
ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና
የአሜሪካ ፕሬዘዳንት ባራክ ኦባማና የሩሲያው ፕሬዘዳንት ቭላዲሚር ፑቲን ትላንት የዓለሙን መድረክ ስለ ሦሪያና ዩክሬን ግጭቶች ሃሳባቸውን ገልጸዋል።
የመን የሚገኘው ጋዜጠኛ ግሩም ተ/ሃይማኖት በየመን ወታደሮች ቁጥጥር ስራ መዋሉን ከታማኝ ምንጮች ማረጋገጥ ችያለሁ ። ጋዜጠኛ ግሩም ላለፉት ሶስት ቀናት ሲታደን መቆየቱን የጠቁሙኝ ምንጮች ዛሬ ማለዳ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን አረጋግጠውልኛል ! የጋዘጠኛ ግሩም መታሰር እንደሰማሁ ወደ የመን ስልክ በመደዎል …
ለሃጂ ጸሎት ወደ መካ መዲና ሳኡድ አረቢያ ተጉዘው ሰሞኑን በደረሱ አደጋዎች የሞቱ እና የት እንደገቡ የአልታወቁ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንን በተመለከተ የወያኔው አገዛዝ የተጓዦችን ስም ዝርዝር ከመለጠፍ እና ሰበብ ከመፍጠር ውጪ ካለበት ሳይንቀሳቀስ ዝምታም መምረጡን በሃገሪቱ ያለው መንግስት ለዜጎች ደህንነት ያለውን አቋም …
የወያኔው መንግስት እና መጅሊስ ሳኡድ አረቢያ ውስጥ በተከሰተው አደጋ የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት አልተወጡም: Read more »
የዛሬ አንድ መቶ ሃምሳ አንድ ዓመት በ1857 ዓ.ም በዐፄ ቴዎድሮስ ዘመን እንዲህ ሆኖ ነበር፡፡ የመስቀል በዓል በዋለ በሁለተኛው ቀን በዓሉን ምክንያት በማድረግ ምናልባት በኢትዮጰያ የመጀመርያው የቁንጅና ውድድር በጎንደር ከተማ ተደርጎ ነበር፡፡ ከልደታ ምሥራቅ ለአበራ ጊዮርጊስ ሰሜን ከሆነችው በቀሃ ወንዝ አጠገብ …
በ1857 ዓ.ም በዐፄ ቴዎድሮስ ዘመን በኢትዮጰያ የመጀመርያው የቁንጅና ውድድር በጎንደር ከተማ ተደርጎ ነበር፡፡ Read more »
ሰንደቅ አላማ የአንድ ሀገር ህዝቦች ተስማምተውበት ይወክለናል ቢውለበለብ ይገልፀናል ብለው ለቀለማቱ ትርጉም በመስጠት ከምንም በላይ ክብራቸውን የሚገለፀበት የሀገር ውክልና የሚወስድ ወይም የሚገልፅ የሀገር ንብረት ወይም መግለጫ ነው ። ሰንደቅ ሀገራት ከሀገራት የሚለዮበት ትልቅ ምልክት ነው። ሀገራት ወይም ሰንደቅ አላማ ትልቅ …
በዚህ የህዝብ ምርጫ በሚከበርበት ዓለም ሰንደቅ አላማ ያህል ነገር አንድ ገዥ ቡድን ‹‹ከአሁን በኋላ ሰንደቅ አላማው ይኼ ነው›› ብሎ አንዳች ምልክት ሊለጥፍበት አይገባም ነበር፡፡ በአሁኑ ወቅት ያለው ሰንደቅ አላማ የመጣው ግን በዚህ መንገድ ነው፡፡ ለዚህ ሰንደቅ አላማ በቅርቡ አዋጅ ወጥቶለታል፡፡ …
አርባ ምንጭ የነበረው የዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ መንግስት የመከላከያ ኃይል ቡድን ከባለፈው ሳምንት ሐሙስ ጀምሮ አካባቢውን ለቆ እየወጣ እንደሆነ ታወቀ፡፡በአርባ ምንጭ እና አካባቢው ሲንቀሳቀስ እና ሰው አልባ አውሮፕላኖችን ከዚያ እያስነሳ ወደ ሚፈልገው አቅጣጫ ለጥቃት ሲያሰማራ ለረጅም ጊዜ የቆየው የአሜሪካ የመከላከያ ኃይል …
አርባ ምንጭ የነበረው የአሜሪካ መንግስት የመከላከያ ኃይል አካባቢውን ለቆ እየወጣ እንደሆነ ታወቀ፡፡ Read more »
በሃዋሳ የተካሄደው የህገ ወጡ መጅሊስ ጠቅላላ ጉባኤ ሙሉ ቪዲዬ እንደሚከተለው ይቀርባል [youtube http://www.youtube.com/watch?v=VCDt_10fELo] ቢቢኤን በዛሬው መስከረም 17 ዝግጅታችን http://goo.gl/ktgu70 መደመጥ ያለበት ልዩ ዝግጅት ያልተቋረጠው የመንግስትና የመጅሊስ አስነዋሪ ጋብቻ በመጅሊሶች አንደበት ሲጋለጥ ክፍል አንድ 12ተኛው የህገወጡ አህባሽ መጅሊስ ጉባኤ የ2 …
ያልተቋረጠው የመንግስትና የመጅሊስ አስነዋሪ ጋብቻ በመጅሊሶች አንደበት ሲጋለጥ (FULL VIDEO ሙሉ ቪዲዬ) Read more »
ይህ የኢትዮጵያ ወጣቶች ድምፅ ነው። የተለመደው የአክብሮት ሰላምታችን በያላችሁበት ይድረሳችሁ። ሳምንታዊ ዜናዎችን እና ቃለመጠይቆችን እንዲሁም መጣጥፎችን ለስለስ ካሉ ሙዚቃዎች ጋር ይዘንላችሁ ቀርበናል አብራችሁን ሁኑ ። [youtube http://www.youtube.com/watch?v=m2B6UT6c6MY]
መስከረም ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአጼ ሃይለስላሴ ዘመን ስራውን የጀመረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ በትርፋማነቱ በተለያዩ አለማቀፍ የንግድ ተቋማት እየተመሰገነ ቢመጣም፣ የድርጅቱ ሰራተኞች ” ከዘረኝነት ጋር በተያያዘ ክሶችን እያቀረቡ ነው። አየር መንገዱ ጀምሮት ከነበረው የቁልቁለት ጉዞ የታደጉት አቶ ግርማ ዋቄ ስራቸውን ከለቀቁ በሁዋላ፣ በምትካቸው የተሾሙት አቶ ተወልደ ገብረማርያም ፣ ድርጅቱን ሙሉ በሙሉ …
መስከረም ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በባህርዳር ከተማ የ1997ቱን ምርጫ ውጤት ተከትሎ በከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ ገብቶ የነበረው ኢህአዴግ የህዝቡን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመቅረፍ በሚል የቤት ፈላጊዎችን በማህበር ካደራጀ በሗላ ፣ ከ1998 ዓ.ም ጀምሮ በየወሩ እንዲቆጥቡ በማድረግ ከ9 ዓመታት በሗላ የቤት መስሪያ ቦታቸውን ለቤት ሰሪዎች ሰጥቷል፡፡ ይሁን እንጅ ቤቱን መስራት የሚችሉት መንግስት ባወጣላቸው …
መስከረም ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን ለአዲስ አመት ዋዜማ በላፍቶ ሊያዘጋጀው የነበረው ኮንሰርት በመሰረዙ በአድናቂዎቹ ዘንድ የፈጠረው ቅሬታ ሳይረሳ ፣ አሁን ደግሞ ለመስቀል በአል ያዘጋጀው ኮንሰርት በድጋሚ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እንዳይካሄድ መከልከሉን የፎርቺን ሳምንታዊ ጋዜጣ ዘገባ ያመለክታል። የአዲስ አበባ መስተዳድር የካቢኔ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት አቶ ፈለቀ ነጋሽ የ አዲስ …
መስከረም ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ካሜሩን እንዳስታወቁት ወታደሮቺ የሚላኩት አልሸባብን እየተዋጉ ላሉት የ አፍሪካ ህብረት ሰላም አስከባሪ ልዑክ ድጋፍ ለመስጠት ነው። በመሆኑም እስከ 70 የሚደርሱ የ እንግሊዝ ወታደሮች በቅርቡ የሰላም አስከባሪ ልኡኩን ይቀላቀላሉ ተብሎ ይጠበቃል። ብሪታኒያ ከዚህም በተጨማሪ እስከ 300 የሚደርሱ ወታደሮቿን በደቡብ ሱዳን እንደምታሰፍር የቢቢሲ ዘገባ …
ሑመራ የገበያ ማእከሏ በእሳት ጋይቷል…ቃጠለው ሓሙስ 13/ 01 / 2008 ዓ/ም ሌሊት ያጋጠመ ሲሆን የ150 ነጋዴዎች ንብረት የሆነ ከ50 ሚልዮን ብር በላይ ንብረት በቃጠለው መውደሙ ታውቋል። ህብረተሰቡ ቃጠለው ለማጥፋት የተቻለው ቢጥርም ሊሳካ እንዳልቻለ ኑዋሪዋሪዎች ገልፀዋል። ከሁሉም በላይ ሒመራን የምታክል ትልቅ …
ሑመራ ከተማ የ150 ነጋዴዎች ንብረት የሆነው የገበያ ማእከል በእሳት ቃጠሎ ወድሟል። Read more »
በተለያዩ የብር ኖቶች ላይ ግራፊቲ ጽሁፎች ተጠናክረው መቀጠላቸው ታውቋል:: Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)ላለፉት አመታቶች በተለያየ ሰላማዊ የትግል እንቅስቃሴ ሃይማኖታዊ ነጻነታቸውን ለማስከበር የሚታገሉት ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች በገዛ አገራቸው በወያኔ አገዛዝ የሚደርስባቸውን ግፍ እና መከራ እስር እንግልት እና ግድያ በመቃወም ለሃይማኖት ነጻነት የሚያደርጉትን …
በተለያዩ የብር ኖቶች ላይ ግራፊቲ ጽሁፎች ተጠናክረው መቀጠላቸው ታውቋል:: (ምንሊክ ሳልሳዊ) Read more »
የባላገሩ ምርጥ አሸናፊ ዳዊት ፅጌ ሆኗል። እንኳን ደስ ያለህ! 2. ኢሳያስ ታምራት 3. ሜላት መንገሻ የባላገሩ ምርጥ የመጨረሻው ውድድር ዳዊት ፅጌ በሁለተኝነት ያቀረበው ሙዚቃ [youtube http://www.youtube.com/watch?v=XNMwIpBtRvo] ባላገሩ ምርጥ በነጠላ ውዝዋዜ ዘርፍ አሸናፊ ያሬድ ኬኔ ሆኗል። ባላገሩ ምርጥ በቡድን ውዝዋዜ ዘርፍ …
ድምጻዊ ዳዊት ጽጌ የባላገሩ ምርጥ አሸናፊ ሲሆን ኢሳያስ እና ሜላት 2ኛና 3ኛ ወጥተዋል Read more »
[youtube http://www.youtube.com/watch?v=61ixYcjl43s]
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – ይህን ሰሞን እያየን ያለነው ጉዳይ አጅግ የሚገርም እና የለውጥ ሃይል ነን የሚሉ ኣማሳኞች ሳይቀሩ አየተራወጡ ያሉበት የዘረኝነት መነባነብ በኣገሪቱ ስር አንዳይሰድ ትውልዱ እንዳይበከል የሚያስፈራ ጉዳይ መሆኑ ውሎ ኣድርዋል፥፥የሚደርሱኝ መረጃዎች አንደሚጠቁሙት ዘረኝነትን ለማስፋፋት የተለያዩ ኣካላት ገንዘብ …
ዘረኝነት መድሃኒቱ ያልተገኘለት ትልቁ በሽታ እና የበታችነት አባዜ (ምንሊክ ሳልሳዊ) Read more »
በማይጨው ከተማ ያሉት 11 ሉኳንዳ ቤቶች ለከተማዋ ኑዋሪ የሚያቀርቡት ስጋ ለማሳረድ ወደ ማይጨው ቄራ የተዘጋጁት ከብቶች ይዘው እንዲመለሱ ተደርገዋል። የመታገዱ ምክንያ በቄራው የከብቶች ምርመራ የሚያካሂድ ዶክተር “ለእርዱ የሚበቃ ውሃ ስለ ሌለ ከብቶቻቹ ይዛቹ ተመለሱ” የሚል ትእዛዝ መስጠቱን ተከትሎ መሆኑ ባለሉኳንዳዎች ገልፀዋል። በመስቀል በዓል የማጨው ህዝብ የሚቀመስ ስጋ ማግኘት ኣልቻለም። በውሃ እጥረት ምክንያት ማይጨው በኣለ መስቀሉ […]![]()
1437ኛው የኢድ አል አድኻ ( አረፋ) በአል በአዲስ አበባ ስታዲየም ሲከበር ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ አስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት በሽብር ወንጀል ተከሰው ከተፈረደባቸው የሙስሊሙ ማህበረሰብ ችግሮች መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት መካከል ስድስቱ በቅርቡ የተለቀቁት በእነርሱ ጥያቄና ጥረት አንደሆነ፤ ጥያቄአቸው ምላሽ በማግኘቱና ጥረታቸው በመሳካቱ መደሰታቸውን ገልጸው ለመንግሥት ምሥጋና ማቅረባቸውን የጀርመን ድምጽ ራዲዮ ዘጋቢ ከስፍራው ባስተላላፈው […]
The post ይቅርታ- የወያኔ ካርታ (ይገረም አለሙ) appeared first on ሳተናው (Satenaw)-Latest Ethiopian News & Breaking News.
በዋሽንግተን ዲሲ ከተማ ውስጥ በምትገኘው ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም ቤተክስቲያን ውስጥ በእነ ዶክተር አክሊሉ ሐብቴ የሚመራው ህገወጥ ቡድን (mob) ተቆልፎ የነበረውን በር ሰብረው በመግባት ቤተክርስቲያኑን በዛሬው ዕለት መቆጣጠራቸውን ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል። ይህንን የውንብድና ድርጊት በመምራት ላይ ያሉት …
በዶክተር አክሊሉ ሐብቴ የሚመሩት ጋጠወጦች የተዘጋ ቤተክርስቲያን ሰብረው ገቡ Read more »
በዋሽንግተን ዲሲ ከተማ ውስጥ በምትገኘው ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም ቤተክስቲያን ውስጥ በዶክተር አክሊሉ ሐብቴ መሪነትና በጥቂት ግብረ አበሮቻቸው ተባባሪነት ባለፈው ዕሁድ ቅጽረ ቤተክርስቲያን ውስጥ የተነሳው እረብሻና ብጥብጥ ተባብሶ በምዕመናን ህይወትና ንብረት ላይ ጉዳት እንዳይደርስ ለመከላከል የደብሩ ባለአደራዎች ቦርድ ሁኔታዎች እስኪስተካከሉ …
በዋሺንግተን ዲሲ ርዕሰ አድባራት ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተዳዳሪ ሊቀ ማዕምራን ዶ/ር አማረ ካሣዬ ሰሞኑን በቤተክርስቲያኑቷ ላይ በተደራጀ ሁኔታ በመድረስ ላይ ስላለው ጥቃት ምዕመናን ቤተክርስቲያናቸውን ነቅተው መጠበቅ እንዳለባቸው በማሳሰብ መልዕክት አስተላልፈዋል። “”አትሸበሩ ጸንታችሁ ቁሙ” በሚል ርዕስ የቀረበው መልዕክት ብዙ …
የመጽሐፉ ርእስ፣ አብዮቱና ትዝታዬ ደራሲ፣ ፍሥሓ ደስታ (ኮ/ል) አሳታሚ፣ ፀሐይ አሳታሚ ድርጅት የገጽ ብዛት፣ 598 ገጾች ዋጋ፣ $44.95 (ቅኝት ክንፉ አሰፋ) ፀሐይ አሳታሚ ድርጅት ከዚህ ቀደም ሁለት የአብዮቱ መጽሃፍቶችን አበርክቶልናል። የኮ/ል መንግስቱ ኃ/ማርያም – “ትግላችን” እና ሻምበል ፍቅረ …
አብዮቱና ትዝታዬ (ኮ/ል ፍሥሓ ደስታ)-አዲስ መጽሃፍ – አዲስ ምስጢር (ቅኝት ክንፉ አሰፋ) Read more »
ትላንት 26/09/2015 ማምሻውን በውቢቷ ፖርት ኤልዛቤት ከተማ በተካሄደው አስራ አንደኛው የ አፍሪካ ፊልም አካዳሚ አዋርድ ላይ፣ በ ስምንት ዘርፎች እጩ ሆኖ የቀረበው የ ቴዎድሮስ ተሾመ “ሦስት ማዕዘን” ፊልም በ ሦስት ዘርፎች አሸናፊ በመሆን ታሪክ ሰራ Triangle going to America …
የቴዎድሮስ ተሾመ “ሦስት ማዕዘን” ፊልም በ ሦስት ዘርፎች አሸናፊ በመሆን ታሪክ ሰራ:: Read more »
በኦሮሚያ ክልል በምትገኘው አዳማ ከተማ ማክሰኞ ነሃሴ 26/2007 በተጻፈው የግራፊቲ ፅሁፍ ተከትሎ የከተማዋ ደህንነት ሃይሎች እና የኦሮሚያ ፖሊሶች ሙስሊሞችን እያሰሩ እና እያንገላቱ መሆናቸው ታውቋል። የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ከደህንነት ሃይሎች ጋር በመቀናጀት በአዳማ ከተማ አሰሳውን በማጠናከር ሙስሊሙን እያሸበሩ ሲሆን ይፈለጋሉ በተባሉት …
ፖፕ አቡነ ቴዎድሮስ፣ የደመራ በዓልን በመስቀል ዐደባባይ ያከብራሉ አክሱም ጽዮንን፣ ጎንደርን፣ ላሊበላንና የደብረ ሊባኖስ ገዳምን ይጎበኛሉ የግብጽ ኮፕት ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የሃይማኖት አባቶች፣ በሃይማኖታዊ ጉዳዮችና በማኅበራዊ ግንኙነቶች ዙሪያ በአዲስ አበባ …
ኦሮሚፋ በቢቢሲ ስርጭት አድማስ እንዲያገኝ የተጀመረው ዘመቻ የሁላችንም የጋራ ጉዳይ እንጂ ከዜጎቻችን መካከል ለአንዱ የኦሮሞ ማኀበረሰብ አሊያም ደጋፊ ብቻ ተብሎ የሚተው አይመስለኝም፤ መሆንም የለበትም፡፡ ምክንያቱም በዚህ አንዱ ብቻ ተጠቃሚ ሌላው ዝም ብሎ ለሌላው ሲል በወገናዊነት ድጋፍ ያደረገ ያስመስለዋል፡፡ ቢቢሲ በኦሮሚፋ …
BBC በኦሮሚፋም ስርጭት እንዲጀምር የሚደረገው ዘመቻ ሊደገፍና ሊበረታታ ይገባዋል:: Read more »
• ኢቢሲ፣ ይሄን ዘገባ ሰሞኑን ያሰራጨው የት ከርሞ ነው? 1. ወጪው ከ1 ቢ. ብር በታች ነው የተባለው ግንባታ፣ ከ5 ቢ. ብር በላይ ፈጅቶም አላለቀም። 2. ቢበዛ በ3 ዓመት ውስጥ ግንባታው ይጠናቀቃል የተባለው ግድብ፣ 10 ዓመት አልበቃውም። 3. ግድቡ እየተጓተተ ወጪው …
ዘረፋ እና ፕሮፓጋንዳ – “ለዓመታት የተጓተተ ዘገባ” – ‘የተንዳሆ ግድብ ለዓመታት ተጓተተ” የሚለው የኢቢሲ ዘገባ… Read more »