ዘ ኢስት አፍሪካን የተሰኘ ድረ ገጽ 50 የሚሆኑ በከፍተኛ ሁኔታ የታጠቁ የኢትዮጵያ ወታደሮች የኬንያን ድንበር በማቋረጣቸው ምክንያት፣ የኬንያ የፀጥታ አካላት በከፍተኛ ተጠንቀቅ ላይ መሆናቸውን ዘገበ፡፡ መንግሥት ግን አስተያየት ከመስጠት ተቆጥቧል፡፡

በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጡ የተጠየቁት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ተወልደ ሙሉጌታ ‹‹ብዙም የተጠናከረ መረጃ የለኝም፤›› በማለት ለሪፖርተር ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

በኬንያ ሰሜናዊ ሁር ግዛት የሚገኘውን ኢለሬት ፖሊስ ጣቢያን የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት አባላት የተቆጣጠሩት የሁለቱ አገሮች ድንበር ለማካለል የቅየሳ ሥራ ከተጠናቀቀ ከአንድ ሳምንት በኋላ እንደሆነ፣ የኬንያ ፖሊስን ጠቅሶ ድረ ገጹ አስነብቧል፡፡

ክላሺንኮቭ መሣሪያዎችን የታጠቁ የኢትዮጵያ ወታደሮች በአሥር ተሽከርካሪዎች ተጭነው የኬንያን ድንበር 16 ኪሎ ሜትሮችን ያህል አቋርጠው በመግባት ገዥ ቦታዎችን በመያዝ፣ የፖሊስ ጣቢያውን የከበቡ መሆናቸውና በአካባቢው ቅኝት ማድረጋቸውን፣ እንዲሁም ፎቶግራፎችን ማንሳታቸውንም እንዲሁ ድረ ገጹ አስነብቧል፡፡

በድረ ገጹ ዘገባ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላት ሥፍራውን እንደሚለቁ ቃል መግባታቸውን ተገልጿል፡፡

የኢትዮጵያ ሠራዊት ድንበሩን ያቋረጠበትን ምክንያት ያልጠቀሰው ድረ ገጹ፣ የኢትዮጵያ ጦር ዘንድሮ ለሦስተኛ ጊዜ የኬንያን ድንበር ማቋረጡን አስታውሶ ዘግቧል፡፡

የኬንያ መከላከያ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኮሎኔል ዴቪድ ኦቦነዬ ስለክስተቱ የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ገልጸው፣ ‹‹ኢትዮጵያና ኬንያ ዘለግ ያለ ዕድሜ ያስቆጠረ ግንኙነት ያላቸውና ወዳጆች ከመሆናቸው አንፃር ኢትዮጵያውያኑ የከፋ ነገር ያደርሳሉ የሚል እምነት የለኝም፤›› በማለት መግለጻቸውን ድረ ገጹ አስነብቧል፡፡

ጉዳዩን አስመልክቶ በማኅበራዊ ድረ ገጾች አስተያየታቸውን ያሰፈሩ ሰዎች፣ የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት አባላት የኬንያን ድንበር በማለፍ የገባው በመጪው እሑድ የሚካሄደው ምርጫ ያለምንም የፀጥታ ሥጋት እንዲካሄድ አስተማማኝ ለማድረግ ነው ብለዋል፡፡ በተለይ አልሸባብን የመሳሰሉ ሰርጎ ገቦች የፀጥታ ሥጋት እንዳይሆኑ ለማድረግ የተከናወነ ድርጊት መሆኑንም አክለዋል፡፡ 

 

ብረታ ብረት ኮርፖሬሽን ተርባይን ማምረቻ ፋብሪካ ሊገነባ ነው

በ350 ሚሊዮን ብር ያስገነባውን ትራንስፎርመር ፋብሪካ አስመርቋል

በግዙፉ መንግሥታዊ የኢንዱስትሪ ተቋም የኢትዮጵያ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ሥር የሚገኘው የኢትዮጵያ ፓወር ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ፣ የተርባይን ፋብሪካ ሊገነባ መሆኑን አስታወቀ፡፡ 

በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ መጀመሪያ ላይ ማለትም በ2008 ዓ.ም. የመጀመሪያ ወራት የተርባይንና የጄኔሬተሮች ማምረቻ ፋብሪካ ለመገንባት በዝግጅት ላይ መሆኑን፣ የኢትዮጵያ ፓወር ኢንጂነሪንግ የኢንዱስትሪ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሻለቃ አሰፋ ዮሐንስ ገልጸዋል፡፡ 

በአሁኑ ወቅት ኢንዱስትሪው ለኃይድሮ ፓወር ማመንጫነት የሚያገለግሉ ተርባይኖችና ጄኔሬተሮች ዲዛይን የማድረግ አቅም መፍጠሩን የገለጹት ሻለቃ አሰፋ፣ በቀጣዩ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን መርሐ ግብር መጀመሪያ ላይ የተፈጠረውን አቅም ወደ ማምረት፣ መትከልና ሥራ ማስጀመር ይቀየራል ብለዋል፡፡ 

ፋብሪካውን ለማቋቋም ምን ያህል ወጪ ያስፈልጋል የሚለውና ሌሎች የአዋጭነት ጥናቶች በመካሄድ ላይ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ የኢትዮጵያ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን በ2002 ዓ.ም. በአሥር ቢሊዮን ብር ካፒታል ሲመሠረት፣ የ200 ሺሕ ብር መንቀሳቀሻ ካፒታል ተፈቅዶለት በኮርፖሬሽኑ ሥር የተደራጀው የኢትዮጵያ ፓወር ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ በአሁኑ ወቅት ከ1.3 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል እንደሚያንቀሳቅስና በሥሩም ሰባት ፋብሪካዎች መቋቋማቸውን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ 

በቅርቡ በ350 ሚሊዮን ብር ካፒታል ከአዲስ አበባ በ20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው ታጠቅ የኢንዱስትሪ ዞን ያስገነባውን የትራንስፎርመር ፋብሪካ ግንቦት 9 ቀን 2007 ዓ.ም. አስመርቋል፡፡ 

የኢትዮጵያ ፓወር ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ይህንን ፋብሪካ ከመገንባቱ ቀደም ብሎ የተለያዩ ትራንስፎርመሮችን ምርትና ዕድሳት በማድረግ፣ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ያቀርብ የነበረ መሆኑ ይታወሳል፡፡ 

ከዚህ በተጨማሪም የተለያዩ መጠን ያላቸው ትራንስፎርመሮችን ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ማቅረቡን የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ 

ነገር ግን ቀደም ሲል የሚያመርትበት ወርክሾፕና የአገሪቱ የትራንስፎርመር ፍላጎት መጨመር ራሱን የቻለ ፋብሪካ እንዲያቋቁም አስገድዶታል፡፡ በመሆኑም በቡራዩ ታጠቅ የኢንዱስትሪ መንደር በ28 ሔክታር ላይ ያረፈ ፋብሪካ በቻይናው ፖሊ ግሩፕ አማካሪነት ገንብቶ በይፋ አስመርቋል፡፡ 

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የኢኮኖሚ ዘርፍ አስተባባሪና የኢንፎርሜሽንና ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል የአገሪቱ የትራንስፎርመር ፍላጎት በዚህ ፋብሪካ እንደሚሸፈን ገልጸዋል፡፡ 

‹‹ኢትዮጵያውያን አይችሉትም›› የሚል አስተሳሰብ የነበራቸው ወዳጅ አገሮችን ያሳመኑ ፕሮጀክቶችን የኢትዮጵያ ብረታ ብረት ኮርፖሬሽን ማረጋገጡን ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ፓወር ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ከትራንስፎርመር ማምረቻ ፋብሪካው በተጨማሪ በ300 ሚሊዮን ብር ካፒታል ያስገነባው የኬብልና ዋየር ማምረቻ፣ የፓወር ፋክተር ኮሬክተርና የኮምፓክት ሰብስቴሽን ማምረቻ፣ በ350 ሚሊዮን ብር ካፒታል የተገነባ የኢንጂን ማምረቻ ፋብሪካ፣ በ300 ሚሊዮን ብር ካፒታል የተገነባ የሶላር ፓናል ማምረቻ ፋብሪካ፣ በ200 ሺሕ ብር የተገነባ የሞተርና ጄኔሬተር ፋብሪካ በሥሩ ይገኛሉ፡፡ 

 

የፊታችን እሑድ በሚደረገው ጠቅላላ ምርጫ ተሳታፊ የሆነው የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) በዘንድሮ የምርጫ ተሳትፎው ላይ በርካታ ችግሮች እየገጠሙት ቢሆንም፣ በምርጫው እስከ መጨረሻው ድረስ ተሳትፎው እንደሚቀጥል አስታወቀ፡፡ 

‹‹ለመርሆዋችን ተገዥ በመሆን የምርጫ ተሳትፎአችን እስከ መጨረሻው ይቀጥላል፤›› በሚል ርዕስ ለሪፖርተር በላከው መግለጫ፣ በምርጫ ተሳትፎው ላይ እየደረሱ ነው ያላቸውን ችግሮች ኢዴፓ ገልጿል፡፡

ፓርቲው ያገኛቸውን ነፃ የአየር ሰዓቶች በመጠቀም አማራጮቹን ለሕዝብ እንዳያደርስ በሚዲያ ተቋማት የደረሰበትን ሳንሱር፣ በየክልሉ በሚወዳደሩ ዕጩዎቹ ላይ የማዋከብ፣ የማስፈራራት፣ ስም የማጥፋትና የመደብደብ ዕርምጃዎች ተጠናክረው መቀጠላቸው፣ ዕጩዎቹና ደጋፊዎቹ ቅስቀሳ እንዳያደርጉ መከልከላቸው፣ የፖስተር መቀደድ እንደ ገጠመው፣ ባነሮችን ከቦታቸው ላይ መሰወርና ዕጩዎቹን ከሥራ ማባረር፣ ደመወዝ መከልከል፣ ከአገልግሎት ማግለልና የመሳሰሉት እየደረሱበት ካሉ ችግሮች መካከል ተጠቃሽ እንደሆኑ አስታውቋል፡፡

ኢዴፓ በዚህ መጠኑ ያለፈ ተፅዕኖ ምክንያት በክልል የሚገኙ ጥቂት ዕጩዎቹ ራሳቸውን ከምርጫ እንቅስቃሴ ለማግለል የሚያስገድዳቸው ሁኔታ እንደተፈጠረ በመግለጫው የጠቆመ ቢሆንም፣ የፓርቲው የጥናትና ምርምር ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ዋሲሁን ተስፋዬ ግን ችግሩ በድርድር ተፈቶ አሁን ዕጩዎቹ ሥራዎቻቸውን በአግባቡ እያናወኑ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡

አቶ ዋሲሁን፣ ‹‹ቁጫና ወላይታ ላይ አባሎቻችን ከሌሎች ፓርቲ አባላት ጋር በመሆን ከምርጫው ራሳቸውን እንደሚያገሉ ገልጸው የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ግን ችግሩ በመፈታቱ ሥራቸውን ቀጥለዋል፡፡ የምርጫ ቅስቀሳውንም ሲያከናውኑ ነበር፤›› በማለትም አክለዋል፡፡

‹‹ፓርቲያችን እነዚህ ከመጠን ያለፉ ጫናዎች ቢኖሩም፣ አባሎቻችንና መዋቅሮቻችን ችግሩን ተቋቁመው በምርጫው ውስጥ የሚያደርጉትን ተሳትፎ እስከ መጨረሻው እንዲዘልቁበት ጥረት እየተደረገ ይገኛል፤›› በማለት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆኖም በምርጫው ተሳታፊነቱን እንደሚያረጋግጥ ኢዴፓ በመግለጫው አስታውቋል፡፡

በዚህ አገር የምርጫ ሥርዓቱ ጠንካራ መሠረት ላይ ሊቆም የሚችለው በማኩረፍና ራስን ከምርጫ ሒደት በማግለል ሳይሆን፣ በሒደቱ ውስጥ በመቆየት ችግሮችንና ጫናዎችን በመቋቋም፣ በማጋለጥና ችግሮች እንዲፈቱ ጥረት በማድረግ ነው ብሎ እንደሚያምንም ኢዴፓ አትቷል፡፡

በዘንድሮ ምርጫ ከሚሳተፉ 58 የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል አንዱ የሆነው ኢዴፓ፣ 165 ዕጩዎችን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በማቅረብ 501 ዕጩዎችን ካቀረበው የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢሕአዴግ) እና 270 ዕጩዎችን ካስመዘገበው የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) በመቀጠል፣ በርካታ ዕጩዎችን በማስመዝገብ ሦስተኛ ፓርቲ መሆኑን የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መረጃ ያመለክታል፡፡ በቦርዱ መረጃ መሠረት 139 ዕጩዎችን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በማቅረብ በአራተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ሰማያዊ ፓርቲ ነው፡፡   

 

በርካታ የውጭ ኩባንያዎች ከንፋስ ኃይል ለማመንጨት ፍላጎት አሳዩ

በሰኔ 2007 ዓ.ም. መጨረሻ በሚጠናቀቀው የአምስት ዓመቱ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን፣ ከንፋስ ከሚገኝ የኤሌክትሪክ ኃይል 894 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ለማመንጨት ቢታሰብም፣ ማሳካት የተቻለው 324 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ብቻ መሆኑ ተገለጸ፡፡ 

 

ይህ 324 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ሊገኝ የቻለው ከአዳማ አንድ 51 ሜጋ ዋት፣ ከአሸጎዳ 120 ሜጋ ዋትና ግንቦት 10 ቀን 2007 ዓ.ም. ከተመረቀው አዳማ ሁለት 153 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ድምር ነው፡፡ 

ሌሎች ፕሮጀክቶች በሚፈለገው ፍጥነት መሄድ ባለመቻላቸው ዕቅዱ ወደሚቀጥለው አምስት ዓመት መሸጋገር ግድ ሆኖበታል፡፡ በዕቅድ ዘመኑ ግንባታቸው ተጀምሮ ይጠናቀቃሉ ተብሎ ይጠበቁ የነበሩት አይሻ 300 ሜጋ ዋት፣ መሶቦ-ሐረና 42 ሜጋ ዋት፣ አሰላ 100 ሜጋ ዋትና ደብረ ብርሃን 100 ሜጋ ዋት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ናቸው፡፡ 

እነዚህ ፕሮጀክቶች ግን እስካሁን ፋይናንስም ሆነ ኮንትራክተር አላገኙም፡፡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት፣ እነዚህን የንፋስ ኃይል ኤሌክትሪክ ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ለማግኘት በርካታ ኩባንያዎች ፍላጎት እያሳዩ ነው፡፡ 

ምንጮች እንደገለጹት የአይሻን ፕሮጀክት የቻይናው ዲዶንግ ፎንግና የጀርመኑ ላፍቶ ኩባንያዎች ለማልማት ፍላጎት አሳይተዋል፡፡ ከእነዚህ ኩባንያዎች በተጨማሪ የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የፕሮጀክቱ ተሳታፊ እንዲሆን መንግሥት ፍላጎት አሳይቶ በድርድር ሒደት ላይ ይገኛል፡፡ 

አዳማ ሁለትን የገነቡት ኃይድሮ ቻይናና ሲጂሲ ኦቨርሲስ አሰላ ላይ ይገነባል ተብሎ የሚጠበቀውን የንፋስ ኃይል ፕሮጀክት በአዳማ ሦስት ስም ለመረከብ ድርድር እያካሄዱ ነው፡፡ 

ነገር ግን የአሜሪካው ዲሴንቴ ኩባንያን ጨምሮ የቱርክ፣ የቻይናና የአውሮፓ ኩባንያዎች የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ለማግኘት ፍላጎት እያሳዩ በመሆናቸው ውድድሩ መካረሩን መረጃዎች አመልክተዋል፡፡ 

እነዚህ የውጭ ኩባንያዎች ይዘው የመጡት በዓለም አቀፍ ደረጃ የወቅቱ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ከመሆኑም ባሻገር፣ አንድ ተርባይን ያለው የማመንጨት አቅም አሁን ካለው 1.5 ሜጋ ዋት የበለጠ በመሆኑ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ድርጅት በሩን ለድርድር እንዲከፍት እንዳደረገው ታውቋል፡፡ 

ከአዲስ አበባ ከተማ 95 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የተገነባው አዳማ ሁለት ንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በተመረቀበት ወቅት የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ አቶ ዓለማየሁ ተገኑ እንደተናገሩት፣ የአዳማ ሁለት ፕሮጀክት ሥራ መጀመር በአገሪቱ ከንፋስ ኃይል ይመረት የነበረውን 171 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ወደ 324 ሜጋ ዋት አሸጋግሮታል፡፡ 

‹‹እነዚህ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ከውኃ ማመንጫ ጣቢያዎች ጋር የተጣጣመ የኃይል ስብጥር ለመፍጠር ጠቀሜታ አላቸው፤›› ያሉት አቶ ዓለማየሁ፣ ‹‹የዝናብ እጥረት በሚያጋጥምበት ወቅት የንፋስ ኃይል የሚጨምር በመሆኑ፣ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ከመዘርጋት አንፃር ጉልህ ሚና ይጫወታል፤›› በማለትም የፕሮጀክቱን ጠቀሜታ አብራርተዋል፡፡ 

በአሁኑ ወቅት ከውኃና ከንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች 2,368 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት መቻሉን፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መረጃ ያመለክታል፡፡ 

ኢትዮጵያ ከውኃ 50 ሺሕ ሜጋ ዋት፣ ከንፋስ 1.3 ሚሊዮን ሜጋ ዋት፣ ከእንፋሎት ከአሥር ሺሕ ሜጋ ዋት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ 

በሰኔ 2005 ዓ.ም. ተጀምሮ በግንቦት 2007 ዓ.ም. የተጠናቀቀው አዳማ ሁለት 102 ተርባይኖች አሉት፡፡ አንዱ ተርባይን 1.5 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም አለው፡፡ ይህ ፕሮጀክት 345 ሚሊዮን ዶላር ሲወጣበት፣ 85 በመቶ በቻይናው ኤግዚም ባንክ፣ ቀሪው 15 በመቶ ደግሞ በኢትዮጵያ መንግሥት የተሸፈነ መሆኑ ታውቋል፡፡ 

 

አወዛጋቢ በነበረው የባዮ ሴፍቲ ወይም የደኅንነት ሕይወት ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ፣ የፓርላማው የተፈጥሮ ሀብትና የአካባቢ ጥበቃ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ለመጀመርያ ጊዜ ጥልቅ የተባለ ውይይት ካደረገበት በኋላ፣ በረቂቁ ላይ ማሻሻያዎችን በማከል ማክሰኞ ግንቦት 11 ቀን 2007 ዓ.ም. ፓርላማው አፀደቀው፡፡

በ2001 ዓ.ም. በጄኔቲክ ምሕንድስና የተለወጠ ህያው ወደ ኢትዮጵያ በሚገባበት ወቅት፣ በኢትዮጵያ ብዝኃ ሕይወት ደህንነት ላይ ጉዳት እንዳያደርስ የሚያስችል እጅግ ጥብቅ የተባለ የኢትዮጵያ የደኅንነት ሕይወት አዋጅ ፀድቆ ነበር፡፡

የዚህ አዋጅ መፅደቅ በወቅቱ ተከስቶ ለነበረ ድርቅ በጄኔቲክ ምሕንድስና የተለወጠ የስንዴ ዕርዳታ ወደ አገር እንዳይገባ ተፅዕኖ ፈጥሮ እንደነበር መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ 

ይህ አዋጅ በጄኔቲክ ምሕንድስና የተለወጡ ዘሮች ወይም ህያዋን ለጥቅም እንዳይውሉ ይከልክል እንጂ ለምርምር፣ ለትምህርትና ለሙከራ በዝግ ላብራቶሪ መከናወን የሚቻልበትን ሁኔታ አመቻችቷል፡፡ ይሁን እንጂ ይህንን በዝግ ላብራቶሪ የተፈቀዱ ምርምሮችን ለማድረግ የተቀመጡት መሥፈርቶች አስቸጋሪነትና የአዋጁ ዓላማም ወደ መከልከል ያመዘነ በመሆኑ፣ ረቂቅ ማሻሻያ አዋጅ ጥቅምት 13 ቀን 2007 ዓ.ም. ለፓርላማ ቀርቦ ነበር፡፡ 

ረቂቅ አዋጁ የተመራለት የተፈጥሮ ሀብት ልማትና የአካባቢ ጥበቃ ጉዳዮች ከጥቅምት 19 ቀን 2007 ዓ.ም. ጀምሮ አምስት መድረኮችን በማዘጋጀት ከተለያዩ የአገር ውስጥ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አድርጐ፣ የውሳኔ ሐሳቡን ግንቦት 11 ቀን 2007 ዓ.ም. ለምክር ቤቱ አቅርቧል፡፡

በማሻሻያ ረቂቅ አዋጁ አንቀጽ ሁለት ንዑስ አንቀጽ 1(5) ላይ የሰፈረውን ድንጋጌ ሙሉ በሙሉ ሰርዞታል፡፡ 

የተሰረዘው አንቀጽ ‹‹የተጤነ ልቀት›› ማለት ከግንዛቤ በመነጨ ስምምነት ልውጥ ህያውን ለንግድ፣ ለምግብ፣ ለዕርዳታ ምግብ፣ አካባቢን ለማፅዳት፣ ለማስተማሪያነት፣ ለምርምር፣ ለመስተዋት ቤት፣ ለውኃ ውስጥ እርባታ፣ ለእንስሳት መኖ፣ ወይም ለሌላ የእንስሳት ግብዓት፣ ለሰው ወይም ለእንስሳት ሕክምና ወይም ለማስወገድ ወደ አካባቢ መልቀቅ እንደሆነ ያስቀምጥ ነበር፡፡ 

ይህ ማሻሻያ ረቂቅ አንቀጽ ላይ በኢትዮጵያ የሚገኙ የአካባቢ ጥበቃ አቀንቃኞች እንዲሰረዝ ከፍተኛ ግፊት ሲያደርጉ ነበር፡፡ ለዚህ የሚሰጡት ምክንያት ደግሞ የተለወጠ ህያው ወደ አካባቢ መለቀቁ በኅብረተሰብ ጤና ላይ ጠንቅ እንደሚኖረውና የኢትዮጵያን ብዝኃ ሕይወት ይበርዛል የሚል ነው፡፡

ይህንን ሥጋት ከግምት ውስጥ ያስገባው የፓርላማው ቋሚ ኮሚቴ አንቀጹን ሙሉ በሙሉ ሰርዞታል፡፡ ቋሚ ኮሚቴው ብሔራዊ የደኅንነት ሕይወት አማካሪ ኮሚቴ በሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚወጣ ደንብ በሕግ እንዲቋቋምና የኮሚቴው ተግባርም ደኅንነተ ሕይወትን በተመለከተ መንግሥትን ማማከር ነው፡፡ 

ቋሚ ኮሚቴው የአካባቢ ጥበቃ ተሟጋቾች ያቀረቡት ሐሳብን ሙሉ በሙሉ ባይቀበልም፣ የተደረጉት ሁለት ማሻሻያዎችና ብሔራዊ አማካሪ ኮሚቴ በሕግ እንዲቋቋም መደረጉን ሪፖርተር  ያነጋገራቸው ባለሙያዎች ተቀብለዋል፡፡

ሁለተኛ የተባለው ማሻሻያ ‹‹በግንዛቤ የመነጨ ስምምነት እንዲሰጠው ለሚኒስቴሩ ማመልከቻ የሚያቀርብ ማንኛውም ሰው በላከው አገር ሕግ ዕውቅና ያለው መሆን አለበት፤›› ይላል፡፡ 

በረቂቁ ተቀምጦ የነበረው ግን ‹‹ከግንዛቤ የመነጨ ስምምነት እንዲሰጠው የሚጠይቅ የውጭ ላኪ፣ በላኪው አገር ሕግ ኃላፊነት እንዲወስድ የሚፈቀድለት መሆኑን የሚገልጽ በራሱ በላኪው የተፈረመ ሰነድ ማቅረብ አለበት፤›› የሚል ነው፡፡

የአካባቢ አቀንቃኞቹ ይህ አንቀጽ መሻሻል እንዳለበት፣ ምክንያቱም ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች በአገራቸው ኃላፊነት እንዲወስዱ የሚገልጽ ደብዳቤ መጻፋቸው ተጠያቂ ስለሚያደርጋቸው፣ በአገራቸው ሕግ ራሳቸው ዕውቅና ያላቸው መሆን ይገባቸዋል ሲሉ አቤቱታቸውን ሲያሰሙ ነበር፡፡ 

ከግንዛቤ የመነጨ ስምምነት የሚል ስያሜ ያለው ፈቃድ ማግኘት ማለት፣ የተለወጠ ህያውን ወደ አካባቢ የመልቀቅ እንቅስቃሴን ለማካሄድ የሚያስችል ብቻ ነው፡፡ ፓርላማው በቋሚ ኮሚቴው የቀረበለትን የውሳኔ ሐሳብ በሙሉ ድምፅ በመቀበል ረቂቁን አፅድቆታል፡፡     

 

የግድብና የመስኖ ፕሮጀክቶች አፈጻጸማቸው ዝቅተኛ ነው ተባለ

የኢትዮጵያ የውኃ ሥራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅት ከውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ጋር ውል ፈጽሞ እያከናወናቸው ያሉ ፕሮጀክቶች አፈጻጸማቸው ዝቅተኛ ነው ተባለ፡፡

የውኃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር በሚኒስትሩ አቶ ዓለማየሁ ተገኑ ለሚመራው የድርጅቱ ሥራ አመራር ቦርድ አስቸኳይ ማስተካከያ እንዲያደርግ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ተጻፈለት፡፡ 

ለሥራ አመራር ቦርዱ የማሳሰቢያው ደብዳቤ የተጻፈው የርብ የመገጭና  የጊዳቦ ግድቦች፣ የከሰም መስኖ መሠረተ ልማት ግንባታና የተንዳሆ የኅብረተሰብና የስኳር ልማትና መጠጥ ውኃ ግንባታን ለማከናወን ውል የገባው የውኃ ሥራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅት፣ ፕሮጀክቶቹን በማጓተቱና አፈጻጸሙ ዝቅተኛ በመሆኑ ምክንያት ነው ለቦርድ ማስጠንቀቂያ የተጻፈው፡፡

በውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ወንድሙ ተክሌ ሚያዝያ 21 ቀን 2007 ዓ.ም. የተጻፈው ደብዳቤ ውኃ ሥራዎች ድርጅት ከሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ጋር በገባው ውል መሠረት በአማራ ክልል የሚገኙትን የርብና የመገጭ ግድቦች ግንባታን፣ በኦሮሚያ ክልል የጊደቦ ግድብ ግንባታን፣ በአፋር ብሔራዊ ክልል የከሰም መስኖ መሠረተ ልማት ግንባታና የተንዳሆ የኅብረተሰብና የስኳር ልማትና የመጠጥ ውኃ ግንባታ ለማካሄድ ኮንትራት የወሰደ ቢሆንም፣ ፕሮጀክቶቹ በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ሊጠናቅቁ አለመቻላቸው ደብዳቤው ያስረዳል፡፡ ሚኒስቴሩ በተደጋጋሚ የቀረቡለትን የማራዘሚያ ጥያቄዎችም በመቀበል የውል ጊዜን ያራዘመ ቢሆንም፣ አንዳንዶቹ ፕሮጀክቶች ወደ ኪሳራ ሊገቡ መገደዳቸውንም ያክላል፡፡

የርብ ግድብ እ.ኤ.አ. ጥቅምት 2 ቀን 2007 ተጀምሮ እ.ኤ.አ. ሚያዝያ 30 ቀን 2011 የሚጠናቀቅ ቢሆንም፣ በተያዘው ዓመት እ.ኤ.አ. 2015 አፈጻጸሙ 76.5 በመቶ ነው ተብሏል፡፡ ነገር ግን እ.ኤ.አ. ከግንቦት 2011 እስከ ሰኔ 2014 ድረስ እንዲራዘም መደረጉን ለውኃ ሥራዎች ድርጅት ሥራ አመራር ቦርድ የተላከው የማሳሰቢያ ደብዳቤ ይገልጻል፡፡ የመገጭ ግድብ ግንባታም እ.ኤ.አ. መጋቢት 22 ቀን 2012 ዓ.ም. የተጀመረ ሲሆን፣ መጠናቀቅ ያለበት እ.ኤ.አ. ነሐሴ 30 ቀን 2016 ነው፡፡ በዚህ ዓመት ያለው የአፈጻጸም መጠን ግን 26.05 በመቶ ብቻ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

የጊዳቦ ግንባታ ግንባታ የተጀመረው ጥር 3 ቀን 2002 ዓ.ም. ሲሆን፣ ይጠናቀቃል የተባለው ጥር 3 ቀን 2004 ዓ.ም. መሆኑ ተገልጿል፡፡ ነገር ግን አራት ጊዜ ውሉ እንዲሻሻል ተደርጎ አሁን ያለበት አፈጻጸም 63.86 ብቻ መሆኑን ሚኒስቴሩ አስታውቋል፡፡ በሌሎቹም ፕሮጀክቶች የሚታየው አፈጻጸም ተመሳሳይ መሆኑን የሚያብራራው የሚኒስቴሩ ደብዳቤ፣ ባለድርሻ አካላቱ ማለትም ሚኒስቴሩ የውኃ ሥራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅትና አማካሪው የውኃ ሥራዎች ዲዛይንና ቁጥጥር ድርጅት ተመካክረው ቦርዱ እንዲያውቀው ያደረጉ ቢሆንም ሊሻሻል አለመቻሉን ያብራራል፡፡

ሦስቱ ባለድርሻ አካላት ባደረጉት ምክክር ድርጅቱ አጠቃላይ ያለበትን ሁኔታ ቦርዱ እንዲያውቀው ተደርጎ ለማበረታታት መሞከሩን፣ ድርጅቱ ያጋጠመውን የፋይናንስ ችግር በመረዳት ከክፍያ ተመላሽ የሚደረግ 250 ሚሊዮን ብር በብድር መልክ እንዲሰጠው መደረጉን ደብዳቤው ያስረዳል፡፡

ከመንግሥት ጋርም በመነጋገር ለርብና ለመገጭ ግድቦች ግንባታ ከሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን አዲስ የዋጋ ማሻሻያ መደረጉን፣ እንዲሁም መንግሥት የድርጅቱ ካፒታል እንዲያድግ በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር በኩል የተወሰነ ክፍያ መፈጸሙንም ደብዳቤው ያብራራል፡፡ ነገር ግን ከላይ የተገለጹት ድጋፎች የተደረጉለት ቢሆንም የፕሮጀክቶቹ አፈጻጸም ሊሻሻል አለመቻሉንም ጠቁሟል፡፡ ፕሮጀክቶቹ ከጊዜ ወደ ጊዜ መሻሻል ከማሳየት ይልቅ ዝቅተኛ አፈጻጸም ላይ መሆናቸውን ገልጾ፣ የውኃ ሥራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅት ሥራ አመራር ቦርድ ልዩ ትኩረት በመስጠትና ችግሮቹን በመፈተሽ በቀሪው ጊዜ አፈጻጸሙ የሚሻሻልበትን  የበኩሉን ሚና እንዲጫወት የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር በደብዳቤው አሳስቧል፡፡

የሥራ አመራር ቦርዱ ከሚኒስቴሩ በደረሰው ማሳሰቢያ መሠረት ምን እያደረገ እንደሚገኝ ማብራሪያ ለማግኘት የተደረገው ጥረት አልተሳካም፡፡

 

 

አስተዳደሩ የኮንዶሚኒየም ቤቶችን ዋጋ የሚያጠና ልዩ ኮሚቴ ማቋቋሙ ተሰማ

ጭማሪው በካሬ ሜትር ከ27 እስከ 45 በመቶ መሆኑ ተጠቁሟል

‹‹አስተዳደሩ ያደረገው ጭማሪ 15 በመቶ ብቻ ነው›› የቤቶች ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መጋቢት 13 ቀን 2007 ዓ.ም. ለአሥረኛ ጊዜ ዕጣ ያወጣባቸው 41 ሺሕ የጋራ መኖሪያ ቤቶች (ሰባት ሺሕ ለልማት ተነሽዎች ናቸው)፣ በዋጋቸው ላይ ከፍተኛ ጭማሪ መደረጉን ካቢኔው ሊቀበለው ባለመቻሉ፣ ልዩ ኮሚቴ ተቋቁሞ የዋጋ ጥናት እየተደረገ መሆኑ ተሰማ፡፡

 

የተወሰኑ የካቢኔ አባላት ሚያዝያ 26 ቀን 2007 ዓ.ም. በከንቲባው ጽሕፈት ቤት ስብሰባ አድርገው በኮንዶሚኒየሙ ወጪ ላይ መግባባት ባለመደረሱ፣ ልዩ ኮሚቴ ተቋቁሞ የዋጋ ጥናት እንዲደረግ ስምምነት ላይ መደረሱን ምንጮች ገልጸዋል፡፡

ቀደም ብሎ ተቋቁሞ የነበረው ኮሚቴ ስለ ኮንዶሚኒየም ቤቶች ያጠናው ጥናት ከመጠን በላይ የተጋነነ በመሆኑ፣ ከሁሉም ዘርፍ የተወጣጣ ልዩ ኮሚቴ ተቋቁሞ ዋጋው እንደገና መጠናት እንዳለበት ውሳኔ ላይ መደረሱን ምንጮች አስረድተዋል፡፡  አዲስ የተቋቋመው ኮሚቴ የመጀመርያ ስብሰባውን ግንቦት 3 ቀን 2007 ዓ.ም. ማድረጉንም አክለዋል፡፡

የከተማ አስተዳሩ ለቤቶች ልማት ፕሮግራም ከስድስት ቢሊዮን ብር በላይ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መበደሩን የሚያስታውሱት ምንጮቹ፣ ለቤቶች ግንባታ የወጣው ወጪና በባንክ ያለው ገንዘብ ሊጣጣም ባለመቻሉ ሁለቱን አጣጥሞ ለመቀጠል በቤቶቹ ላይ ዋጋ መጨመር እንዳለበት የፕሮጀክት ጽሕፈት ቤቱ እምነት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በተለይ የቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት የተወሰኑ ሠራተኞች የአሥረኛው ዙር ዕድል ተጋሪ በመሆናቸው፣ ጽሕፈት ቤቱ ሥራውን እንዴት እየሠራና ምን ዓይነት ወጪ ለምንና እንዴት እየወጣ እንደሚገኝ በቅርበት ስለሚያውቁ፣ ጠንከር ያሉ ጥያቄዎችን  ያቀረቡ መሆኑንም ምንጮች ገልጸዋል፡፡ 

በቤቶቹ ላይ መደመር የሌለባቸው የተለያዩ ወጪዎች በብክነት ወይም በሌላ ወጪ መመዝገብ ሲገባቸው በቤቶቹ ላይ በመደመራቸው፣ ለግንባታና ለዲዛይን ወጪ ተገምቶ ሥራውን ለምርምር ብድር የተወሰደ ቢሆንም፣ ከባንክ ጋር የተገባውን ብድር ማፋለሱን ገልጸዋል፡፡ ካቢኔውም በተሠራው የግንባታና የዲዛይን ዋጋ መሠረት ጽሕፈት ቤቱ መሥራት ሲገባው፣ የተጋነነ ዋጋ መቅረቡ ትክክል አለመሆኑን መግለጹን  ምንጮቹ ገልጸዋል፡፡ የጽፈሕት ቤቱም ሠራተኞች ወጪው ለብቻ መያዝ እንዳለበት በመግለጽ የካቢኔውን አቋም እየደገፉ መሆኑም  ተጠቁሟል፡፡ 

የካይዘን ኢንስቲትዩት ባደረገው ጥናት መሠረት በቤቶች ግንባታ ላይ 33 በመቶ ብክነት መኖሩን ለካቢኔው ማሳወቁን የገለጹት ምንጮች፣ ብክነቱን በተለያዩ ነገሮች ማወራረድ ሲቻል በቤቶቹ ዋጋ ላይ መደመር አግባብ አለመሆኑን ካቢኔውም ሆነ የዕጣው ዕድለኞች የሚስማሙበት ሐሳብ መሆኑንም ምንጮች አስረድተዋል፡፡

የቤቶች ልማት ፕሮጀክት ማንኛውም ዓይነት ክትትልና ጥንቃቄ ቢደረግበት እንኳ እጅግ በጣም አስቸጋሪና ለምዝበራ የተጋለጠ መሆኑን፣ የቤቶች ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስትሩ አቶ መኩሪያ ኃይሌ በቅርቡ በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የከተማ ልማትን በተመለከተ ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር ባደረጉት ክርክር ላይ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ቢሮ ኃላፊ በሚያዝያ ወር የመጀመርያ ሳምንት አካባቢ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ በአሥረኛው ዙር ዕጣ በወጣባቸው ቤቶች ላይ የተደረገው ጭማሪ እንደሚባለው የተጋነነ ሳይሆን፣ 15 በመቶ ብቻ እንደሆነ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡ ነገር ግን አስተዳደሩ የነባር 20/80 ባለ አንድ፣ ሁለትና ሦስት መኝታ ቤቶችና እንዲሁም የስቱዲዮ ቤቶችን ለመሸጥ ካስቀመጠው ዋጋ ላይ ከ27 እስከ 45 በመቶ ጭማሪ ማድረጉን የዋጋውን ልዩነት ያሰሉ ነዋሪዎች እየገለጹ ነው፡፡

የ10/90 ተመዝጋቢዎች ዝቅተኛ ክፍያ በካሬ ሜትር 1,310 ብር የሚከፍሉ መሆኑን በምዝገባ ወቅት የተነገረ ቢሆንም፣ በአሥረኛው ዙር ግን በካሬ ሜትር 1,910 ብር እንዲከፍሉ ተደርጓል፡፡ ልዩነቱ 600 ብር ወይም 45 በመቶ መሆኑን ነዋሪዎቹ ይናገራሉ፡፡ ዝቅተኛው የስቱዲዮ ስፋት 29 ካሬ ሜትር ነበር፡፡ 

በተመሳሳይ ሁኔታ ነባር የ20/80 ባለሁለት መኝታ ቤት ተመዝጋቢ በካሬ ሜትር የሚከፍለው 3,452 ብር የነበረ ቢሆንም፣ በአሥረኛው ዙር ዕድለኛ የሆነ ግን በካሬ ሜትር 4,394 ብር ይከፍላል፡፡ ሲመዘገብ ከሚያውቀው ዋጋ ጋር ያለው ልዩነት 942 ብር ወይም 27 በመቶ መሆኑን ነዋሪዎቹ አሥልተዋል፡፡ ዝቅተኛው ባለሁለት መኝታ ቤት ስፋቱ 65 ካሬ ሜትር ነው፡፡ 

በመሆኑም የዕጣው ባለቤቶች መንግሥት መሬት በነፃ፣ ሁሉንም የግንባታ ግብዓቶች ከአገር ውስጥ ባደረገበት ጊዜ ዋጋው ይኼንን ያህል ሊጋነን እንደማይገባ እየገለጹ ባሉበት ወቅት፣ አስተዳደሩ ዋጋው በልዩ ኮሚቴ እንዲጠና ማድረጉ ተገቢና ዕድለኞቹንም ያሰበ ሊሆን ይችላል በሚል ተስፋ ላይ መሆናቸውን ምንጮች አስረድተዋል፡፡ ነዋሪዎች የሠሩት ሥሌት ትክክል መሆን አለመሆኑንና አዲስ ስለተቋቋመው ኮሚቴም ማብራሪያ እንዲሰጡ የአስተዳደሩት ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎችንና የከንቲባ ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎችን ለማግኘት የተደረገው ጥረት አልተሳካም፡፡

 

የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽ በኢትዮጵያ የመጀመርያውን የብረት ማዕድን ማውጫና ማቅለጫ ፋብሪካ ሊገነባ ነው፡፡ ፋብሪካው የሚገነባው በምሥራቅ ወለጋ ዞን ነቀምት ከተማ ሲሆን፣ የብረት ክምችቱም በምዕራብ ወለጋ ዞን ቢቅላል አካባቢ እንደሚገኝ ታውቋል፡፡

ለዚህ ግዙፍና ለአገሪቱ የመጀመርያ ለሆነው ፋብሪካና የብረት ማዕድን ማውጪያ ከሦስት ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደሚደረግ፣ ግንቦት 6 ቀን 2007 ዓ.ም. የፋብሪካው የመሠረት ድንጋይ በነቀምት ከተማ በተቀመጠበት ወቅት ተገልጿል፡፡

የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብርጋዴር ጄኔራል ጠና ቁሩንዴ እንደተናገሩት፣ የሚገነባው የብረታ ብረት ፋብሪካ በዓመት ከሦስት መቶ ሺሕ ሜትሪክ ቶን በላይ የተለያዩ ብረቶችን ማምረት ያስችላል፡፡

በቀድሞው ንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ባለቤትነት በኢትዮጵያ መሠረታዊ ለውጥ ማምጣት ያስችላሉ የተባሉትን የድንጋይ ከሰልና የብረት ማዕድን መገኛ ለማወቅ ጥናት ተካሂዶ ነበር፡፡ በሚኒስቴሩ በተቋቋመው ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤትና የቻይና ኩባንያዎች በተሳተፉበት ጥናት፣ በምዕራብ ኢትዮጵያ ኢሉአባቦራ ዞን ያዩ አካባቢ ከፍተኛ የድንጋይ ከሰል መኖሩን፣ በዚሁ ቀጣና ውስጥ ምዕራብ ወለጋ ቢቅላል አካባቢ ደግሞ የብረት ማዕድን ክምችት (አይረን ኦር) ከሌሎች ማዕድናት ጋር መኖሩን አመልክቷል፡፡

በወቅቱ እነዚህን ማዕድናት ማውጣትና ማምረት የሚያስችል ፋብሪካ ለማቋቋም የሚፈለገው ካፒታል ከፍተኛ በመሆኑ ሳይሞከር እንደቀረ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

ነገር ግን ከመከላከያ ተገንጥሎ በኢትዮጵያ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ለውጥ እንዲያመጣ የተቋቋመው የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን፣ በሒደት በሁለቱም ዘርፎች በጥልቀት መግባት ችሏል፡፡

ኮርፖሬሽኑ በአሁኑ ወቅት ያዩ አካባቢ የሚገኘውን የድንጋይ ከሰል በማውጣት ማዳበሪያ ፋብሪካ ለመገንባት ተግባራዊ እንቅስቃሴ ከጀመረ ዓመት አስቆጥሯል፡፡ ባለፈው ሳምንት አጋማሽ ደግሞ የብረት ማዕድን አውጥቶ የሚያቀልጥበት ፋብሪካ ለመገንባት የመሠረት ድንጋይ አስቀምጧል፡፡

በብረታ ብረት ኢንዱስትሪ ዘርፍ ግዙፍ ኩባንያ የሆነው ስቲሊ አርኤምአይ  የኦፕሬሽንና የፖሊሲ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ተፈራ ለማ የፋብሪካውን መገንባት አስመልክተው ለሪፖርተር በሰጡት አስተያየት፣ ከውጭ ይገባ የነበረው ቢሌት (ጥቅል ፌሮ ብረት) አገር ውስጥ ማምረት መቻል ትልቅ ትርጉም አለው፡፡

አቶ ተፈራ ጨምረው እንደገለጹት፣ አገር ውስጥ ሲመረት የቆየው ብረት ከወዳደቁ ብረታ ብረት (ስክራፕ) እና ከውጭ በሚገባ ቢሌት ነው፡፡ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ወደዚህ ዘርፍ ከገባ ዩክሬን፣ ቻይናና አውስትራሊያ የሚታወቁበት የብረት ምርት በኢትዮጵያ እንዲመረት ያስችላል፡፡

‹‹ይህ ለአገሪቱ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ወሳኝ ነው፤›› በማለት አቶ ተፈራ የፕሮጀክቱን ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ አብራርተዋል፡፡

የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ይኼን አዲስ ፕሮጀክት በሁለተኛው የአምስት ዓመት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ውስጥ ያካተተ ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ተገልጿል፡፡

የፕሮጀክቱ ዕውን መሆን ለምዕራብ ኢትዮጵያ አካባቢዎች ኢኮኖሚያዊ መነቃቃት ከመፍጠሩም ባሻገር፣ በሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች የሥራ ዕድል ይፈጥራልም ተብሏል፡፡ 

 

የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ችግር በሲሚንቶ ገበያ ውስጥ ችግር ፈጥሯል

የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ በገበያ ውስጥ ለተከሰተው የሲሚንቶ እጥረት ዋነኛ ምክንያት መሆኑ ታወቀ፡፡ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጡ የሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ ሦስተኛውን መስመር ከጥቅም ውጪ ሲያደርግ፣ ደርባ ሚድሮክ

ሲሚንቶ ፋብሪካን ደግሞ የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረቱ የማምረት አቅሙን እንዳይጠቀም እንዳደረገበት ተገልጿል፡፡

ሁለቱ ሲሚንቶ ፋብሪካዎች በሙሉ አቅም ማምረት ባለመቻላቸው፣ የሲሚንቶ አቅርቦት ጫና በዋነኛነት መሰቦና ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካዎች ላይ ማረፉን ለማወቅ ተችሏል፡፡

ሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ ከሳምንታት በፊት በዓመት 1.2 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ማምረት የሚያስችለው መስመር ቁጥር ሦስት መቆጣጠርያ መሣሪያ ተቃጥሎበታል፡፡ ይኼንን መሣሪያ ከውጭ ለማስገባት ልዩ ፈቃድ የሚያስፈልግ በመሆኑ፣ በአፋጣኝ ማስገባትና ፋብሪካውን ሥራ ማስጀመር አልተቻለም ተብሏል፡፡

የኬሚካልና የኮንስትራክሽን ግብዓት ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳሙኤል ሀላላ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጡ የሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ ሦስተኛውን መስመር ከጥቅሙ ውጪ ቢያደርገውም፣ ከአንድ ሳምንት በኋላ ሙገር የሚፈልገው መሣሪያ አገር ውስጥ የሚገባ በመሆኑ የፋብሪካው ቁጥር ሦስት መስመር ሥራ ይጀምራል፡፡

ደርባ ሚድሮክ ደግሞ የገጠመው ችግር የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረት ነው፡፡ የደርባ ሚድሮክ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ኃይሌ አሰግዴ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ደርባ ሚድሮክ ሲሚንቶ ፋብሪካ በመሉ አቅሙ ለማምረት 45 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ይፈልጋል፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ወቅት ፋብሪካው እያገኘ ያለው ከስድስት ሜጋ ዋት አይበልጥም ብለዋል፡፡

‹‹የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረቱ በሙሉ አቅማችን ሥራ እንዳንሠራ አድርጎናል፤›› በማለት አቶ ኃይሌ የችግሩን ክብደት ይናገራሉ፡፡

የእነዚህ ሁለት ፋብሪካዎች ችግር ውስጥ መግባት የሲሚንቶ ገበያውን ችግር ውስጥ ከቶታል፡፡ በእርግጥ በሥራ ላይ ያሉት የሲሚንቶ ፋብሪካዎች የመሸጫ ዋጋቸው ላይ ጭማሪ ባያደርጉም ነጋዴዎች ግን በመሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ አድርገዋል፡፡

መሰቦ ሲሚንቶ ሦስት ዓይነት ሲሚንቶዎች ለገበያ ያቀርባል፡፡ የሲሚንቶ መሸጫ ዋጋውም በኩንታል 250 ብር፣ 190 ብርና 165 ብር ነው፡፡ ነገር ግን በገበያ ውስጥ የመሰቦ ሲሚንቶ አንድ ኩንታል ከ350 ብር በላይ እየተሸጠ ነው፡፡

በሲሚንቶ ንግድ የተሰማሩ ነጋዴዎች እንደሚሉት፣ ማንኛውም ሰው ከፋብሪካው የፈለገውን መጠን ሲሚንቶ መግዛት ይችላል፡፡ በተለይ ደላሎች ክፍያ ተፈጽሞ ሲሚንቶውን ለማግኘት እስከ ሦስት ወራት የሚወስድ በመሆኑ ወረፋቸውን በመሸጥ ብቻ ከአንድ ኩንታል እስከ አንድ መቶ ብር እያተረፉ ነው፡፡ በዚህ ምክንያት በአሁኑ ጊዜ ፕሮጀክት ላለውና ንግድ ፈቃድ ላለው ቅድሚያ የሚሰጥ ባለመሆኑ የሲሚንቶ ገበያው ከፍተኛ ችግር ውስጥ እየገባ መሆኑን እየተናገሩ ነው፡፡ በዚህ ምክንያት የሲሚንቶ ዋጋ በኩንታል ከ350 ብር እስከ 410 ብር ድረስ እየናረ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡

የመሰቦ ሲሚንቶ ፕሮሞሽን ክፍል ኃላፊ አቶ ኢሳያስ ሐጎስ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በሙገርና በደርባ ሲሚንቶ ፋብሪካዎች ችግር የገበያው ጫና ወደ መሰቦ ዞሯል፡፡ መሰቦ ይህ ነው የሚባል ችግር የገጠመው ባለመሆኑ ከሰባት ሺሕ እስከ ስምንት ሺሕ ሜትሪክ ቶን ሲሚንቶ በቀን ለገበያ እያቀረበ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች የማምረት አቅም፣ ካለው ፍላጎት ከአምስት ሚሊዮን ቶን በላይ ትርፍ መሆኑ ይነገራል፡፡ ነገር ግን ፋብሪካዎቹ በተለያዩ ችግሮች ምክንያት የማምረት አቅማቸውን ሙሉ በመሉ መጠቀም ባለመቻላቸው ችግር እየተፈጠረ መሆኑን ይናገራሉ፡፡

በሲሚንቶ ዘርፍ ያለውን ችግር ለመፍታት ግንቦት 7 ቀን 2007 ዓ.ም. ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ስብሰባ ጠርቷል፡፡ በዋንኛነት በዘርፉ ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ችግርን ለመፍታት የተመከረ ሲሆን፣ በተለይ የደርባ ሲሚንቶ ፋብሪካን ችግር ለመፍታት በገፈርሳ ኃይል ማመንጫ የማሻሻያ ሥራዎች እየተከናወኑ በመሆናቸው፣ በአጭር ጊዜ ችግሩ እንደሚፈታ መግባባት ላይ ተደርሷል ሲሉ አቶ ሳሙኤል ተናግረዋል፡፡

ከወራት በፊት በአገሪቱ ለተከሰተው የሲሚንቶ ገበያ ችግር የትራንስፖርት እጥረት በምክንያትነት ይቀርብ ነበር፡፡ ይኼም የሆነበት ትራንስፖርት ባለሥልጣን በአገሪቱ የሚገኙ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎች በጂቡቲ ወደብ የተራገፉ መሠረታዊ ሸቀጦችን እንዲያነሱ በግዳጅ በማሰማራቱ ነበር፡፡ በአሁኑ ወቅት የትራንስፖርት ችግሩ የተቃለለ ቢሆንም፣ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ዋነኛ ምክንያት ሆኖ ቀርቧል፡፡

 

ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. በሚካሄደው አምስተኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ ተሳታፊ የሆኑ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ለማሸነፍ ተስፋ የሚያደርጉባቸውን አካባቢዎች ለሪፖርተር ገለጹ፡፡ 

በዚህም መሠረት ተቃዋሚ ፓርቲዎች የተለያዩ ሥፍራዎችን ለማሸነፍ ተስፋ እንዳደረጉባቸው የገለጹ ሲሆን፣ ገዢው ፓርቲ ኢሕአዴግ ግን በሁሉም ሥፍራዎች ለማሸነፍ እንደሠራ አስታውቋል፡፡ 

የኢሕአዴግ የሕዝብና የውጭ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ደስታ ተስፋው፣ ‹‹በሁሉም የምርጫ ክልሎች እናሸንፋለን በሚል ነው እየሠራን ያለነው፡፡ ምርጫ ውድድር ነው፡፡ ውጤቱ የሚታወቀውም በመጨረሻ ሕዝቡ በሚሰጠው ውሳኔ ነው፤›› ብለዋል፡፡

ሕዝቡ ገና ድምፁን ሳይሰጥ እዚህ አሸንፋለሁ እዚህ ደግሞ እሸነፋለሁ ማለት ትክክል አይደለም በማለት፣ ትንበያ ከምርጫ ሥነ ምግባር መርሆዎች ጋር የሚጣጣም አለመሆኑን አስገንዝበዋል፡፡ 

በዚህ ሐሳብ የሚስማሙት የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሐሪ፣ ‹‹ጠንካራ ቦታዎች የሚባሉትን የሚወስነው ሕዝቡ ነው፡፡ እዚህ ላይ ነው ብለን ለማለት ያስቸግረናል፤›› ብለዋል፡፡ ነገር ግን ከክልል ከተሞች ይልቅ በአዲስ አበባ ተስፋ እንደሚያደርጉ ጠቁመዋል፡፡ 

ከዚህ በተቃራኒ ደግሞ የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) የምርምር ጉዳይ ኃላፊ አቶ ዋሲሁን ተስፋዬ፣ ፓርቲያቸው በሦስት የተወሰኑ ቦታዎች ላይ ተስፋ እንደሚያደርግ ገልጸዋል፡፡ 

በዚህም መሠረት የፓርቲው ፕሬዚዳንት የሚወዳደሩበት የዘንዘልማና የጢስ ዓባይ የምርጫ ክልል፣ ደብረ ማርቆስና ወላይታ ፓርቲው ለማሸነፍ ተስፋ የሚያደርግባቸው ሥፍራዎች መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡ 

አዲስ አበባ በፓርቲው ከፍተኛ የቅስቀሳ ሥራ የሚሠራበት እንደሆነ የገለጹት አቶ ዋሲሁን ‹‹ነገር ግን በከተማው 11 ተቃዋሚ ፓርቲዎችና ገዢው ፓርቲ በመኖራቸው ድምፅ የመከፋፈል ዕድሉ ከፍተኛ ነው፤›› በማለት በክልል ከተሞች ያተኮሩበትን ምክንያት አብራርተዋል፡፡ 

አዲስ አበባ ላይ በእርግጠኝነት እንደሚያሸንፉ የገለጹት ደግሞ የሰማያዊ ፓርቲ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ሲሆኑ፣ በክልልም እንዲሁ ፓርቲው ተስፋ የሚያደርጋቸውን ከተሞች አስታውቀዋል፡፡ 

በዚህም መሠረት ጅማ፣ ኢሉአባቦርና የባሌ አካባቢዎች ከኦሮሚያ፣ ኮንሶና ሆሳዕና ደግሞ ከደቡብ ክልል ለማሸነፍ ተስፋ የሚያደርጉባቸው ናቸው፡፡ ከአማራ ክልል ደግሞ ባህር ዳር፣ ደብረ ማርቆስ፣ ደሴና ወልድያ ፓርቲው ጠንካራ እምነት አግኝቼባቸዋለሁ የሚላቸው ከተሞች ናቸው፡፡ 

‹‹ደቡብ ውስጥ በሁሉም ቦታዎች ለማሸነፍ እየሠራን የነበረ ቢሆንም፣ ባለው ሁኔታ ከፍተኛ ቅስቀሳ ማድረግ ባለመቻላችን ዕቅዳችን ሊያንስ ችሏል፤›› በማለት በደቡብ ተስፋ ያደረጉትና አሁን የሚጠብቁት የተለያዩ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡ 

በአብዛኛው የኦሮሚያ ክልል በተወሰኑ የደቡብና የትግራይ ክልሎች የማሸነፍ ተስፋ እንዳለባቸው የገለጹት ደግሞ የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፌዴራላዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) የውጭ ግንኙነት ኃላፊ ዶ/ር መረራ ጉዲና ናቸው፡፡ በዚህም መሠረት የትግራይ ክልል ርዕሰ ከተማ በሆነችው መቐለ፣ እንዲሁም ከደቡብ ከንባታና ሀድያ አካባቢዎች፣ ጋሞ ጐፋ፣ እንዲሁም ቡርጂ ዞን ውጤት የሚጠብቅባቸው ቦታዎች ናቸው፡፡ 

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ፕሬዚዳንት አቶ ትዕግሥቱ አወሉ በበኩላቸው፣ በተወሰኑ የአዲስ አበባ የምርጫ ክልሎች እንዲሁም በደቡብ ሐዋሳና ዳውሮ፣ በኦሮሚያ ክልል ደግሞ በአዲስ አበባ ዙሪያ ባሉ የኦሮሚያ ልዩ ዞን ከተሞችና ጅማ፣ በአማራና በአፋር ክልሎች ተስፋ አለን ብለዋል፡፡

 

ሐና ላላንጐን አስገድዶ በመድፈር ሕይወቷ እንዲያልፍ አድርገዋል የተባሉ ተከሳሾች ጥፋተኛ ተባሉ

የጥፋተኝነት ውሳኔ የተሰጠው በልዩነት ነው 

በመስከረም ወር 2007 ዓ.ም. የ16 ዓመት ታዳጊ መሆኗ የተገለጸውን ሐና ላላንጐ፣ በታክሲ አፍነው ወደ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቀራኒዮ አካባቢ በመውሰድ፣ ተፈራርቀው በመድፈር ሕይወቷ እንዲያልፍ አድርገዋል በሚል ክስ

የተመሠረተባቸው አምስት ወጣቶች፣ ግንቦት 7 ቀን 2007 ዓ.ም. ጥፋተኛ ተባሉ፡፡ የጥፋተኝነት ውሳኔው የተሰጠው በልዩነት ነው፡፡

ተከሳሾቹ ሳምሶን ስለሺ፣ በዛብህ ገብረ ማርያም፣ በቃሉ ገብረ መድኅን፣ ኤፍሬም አየለና ተመስገን ዘገዬ የተባሉ ከ19 እስከ 31 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ወጣቶች ሲሆኑ፣ የታክሲ ሾፌርና ረዳት መሆናቸው በክሱ መገለጹ ይታወሳል፡፡

ዓቃቤ ሕግ የወንጀል ሕግ 32(1ሀ) ማለትም በዋና ወንጀል ተካፋይነት፣ የወንጀል ሕግ 539(1ሀ)ን ማለትም ከባድ የሰው ግድያና የወንጀል ሕግ 626 (1)ን፣ ማለትም ዕድሜያቸው 13 በሆነና 18 ዓመት ባልሞላቸው ልጆች ላይ የሚፈጸም የግብረ ሥጋ ግንኙነትን በሚመለከት የተደነገገውን አዋጅ መተላለፋቸውን ጠቅሶ ክስ መሥርቶ ነበር፡፡ 

የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ የመሠረተውን ክስ ሲመረምር የከረመው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 3ኛ ወንጀል ችሎት (የክስ ሒደቱ የተካሄደው በዝግ ችሎት ነው)፣ ግንቦት 7 ቀን 2007 ዓ.ም. ሁሉንም ተከሳሾች በልዩነት ጥፋተኛ ብሎ ለቅጣት፣ አስተያየትና የቅጣት ውሳኔ ለመስጠት ለግንቦት 14 ቀን 2007 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

የተለዩት ዳኛ ከአንድ እስከ ሦስት ያሉት ተከሳሾች ላይ ከሌሎቹ ዳኞች ጋር ተመሳሳይ ሐሳብ ያላቸው ቢሆኑም፣ በአብላጫ የወንጀል ሕግ አንቀጾችን በልዩነት ያስቀመጡት፣ ተከሳሾቹ ማለትም ከአንድ እስከ ሦስት ያሉት ተከሳሾች ላይ የወንጀል ሕግ 539 (1ሀ) [ያገዳደል ሁኔታው ክብደት] እና የወንጀል ሕግ 620(3) [የአስገድዶ መድፈሩ ክብደት] ተገቢ ሆኖ ሳለ፣ በወንጀል ሕግ 620 (2መ) [ጭካኔና ስቃይ መፍጠር] ጥፋተኛ መባል የለባቸውም በሚል ነው፡፡ በአብላጫ ድምፅ በተደራቢነት የተጠቀሰውን የወንጀል ሕግ 620(4)ን [ጠለፋ] የተለዩትም ዳኛ ደግፈው፣ ነገር ግን ይኼ አንቀጽ ወደ ወንጀል ሕግ 585(1) [ከሕግ ውጭ ይዞ መቀመጥ] ስለሚወስድ በእሱ መሠረት ከአንድ እስከ ሦስተኛ ያሉት ተከሳሾች ጥፋተኛ ሊባሉ እንደሚገባ በመግለጽ ተለይተዋል፡፡ 4ኛና 5ኛ ተከሳሾች ግን በዓቃቤ ሕግ ስላልተመሰከረባቸው በነፃ ሊሰናበቱ እንደሚገባ ገልጸው ተለይተዋል፡፡

 

 

የሆላንድ ካር ባለቤት ኩባንያቸውን ለመታደግ ወደ አገር ቤት ተመለሱ

የኩባንያው ንብረት እንዳይሸጥ በድጋሚ ታገደ

በሆላንድ ካር የመኪና መገጣጠሚያ ኩባንያ በተፈጠረ ቀውስ ከሦስት ዓመት በፊት ኪሳራ በማሳወጅ አገር ጥለው የተሰደዱት ኢንጂነር ታደሰ ተሰማ፣ ኩባንያቸውን ለመታደግ ግንቦት 4 ቀን 2007 ዓ.ም. ወደ አዲስ አበባ ተመለሱ፡፡ 

ኢንጂነር ታደሰ ግንቦት 6 ቀን 2007 ዓ.ም. በኢንተር ኮንቲኔንታል ሆቴል ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ ኩባንያውን ለመታደግ የሚያስችል ዕቅድ ነድፈውና ለመንግሥት አቅርበው ተቀባይነት በማግኘታቸው የሕግ ከለላ ተሰጥቷቸው ወደ አገር ቤት መመለሳቸውን ተናግረዋል፡፡ 

ከ200 በላይ የሚሆኑ ደንበኞች መኪና ለመግዛት ለሆላንድ ካር ክፍያ ፈጽመው ኩባንያው መኪኖቻቸውን ለማስረከብ ሳይችል መቅረቱ ይታወሳል፡፡ ለኩባንያው ብድር የሰጠው ዘመን ባንክ በመያዣነት የያዛቸውን የኩባንያውን ንብረቶች ለመሸጥ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ መኪኖቻቸውን ያልተረከቡት ደንበኞችም በፍርድ ቤት ሲሟገቱ ቆይተዋል፡፡ 

በሆላንድ ካር መክሰር ምክንያት የኩባንያው ባለቤትና ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ታደሰ በ2004 ዓ.ም. ወደ ኔዘርላንድ ተሰደዋል፡፡ ኩባንያው በየካቲት 2005 ዓ.ም. በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት መክሰሩ በይፋ ታውጇል፡፡ 

አቶ ታደሰ ኩባንያቸው ወደ ኪሳራ ሊገባ የቻለው በመሥሪያ ካፒታል እጥረት እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ ‹‹ከሦስት ዓመት በፊት አገሬን ለቅቄ ወጥቼ ነበር፡፡ የወጣሁበት ምክንያት ሆላንድ ካር ውስጥ በተፈጠረ ችግር ምክንያት ሥራ መሥራት ስላልተቻለ ነው፡፡ ለገጠሙን ችግሮች መፍትሔ ማግኘት ስላልቻልኩኝ ምናልባት ለጊዜው ዞር ማለት ይሻላል በማለት ወጥቼ ነበር፤›› ብለዋል፡፡ 

ከአገር ከወጡ በኋላ የተቋረጠውን የኩባንያውን ሥራ ለማስቀጠል በተለይ መኪና የገዙ ደንበኞች ንብረታቸውን የሚያገኙበት ዘዴ ከመፈለግ ወደኋላ እንዳላሉ አስረድተዋል፡፡ ‹‹ብዙ ጥረት አድርጌያለሁ፡፡ በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ ፕሮፖዛሎች አስገብቻለሁ፤›› ያሉት ኢንጂነር ታደሰ፣ በመጨረሻ ለመንግሥት ያስገቡት ፕሮፖዛል በቤልጂየም የኢትዮጵያ ኤምባሲ በኩል ቀርቦ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤትና በፍትሕ ሚኒስቴር በተደረገላቸው ድጋፍ የሕግ ከለላ ተሰጥቷቸው አገራቸው ገብተው እንዲሠሩ መደረጉን ተናግረዋል፡፡ 

ሆላንድ ካር የከሰረበት ምክንያት ንብረት በማጣት እንዳልሆነ ገልጸዋል፡፡ ኢንጂነር ታደሰ አበዳሪያቸውን ዘመን ባንክን ወቅሰዋል፡፡ ‹‹በዚያን ጊዜ ባንኩ የኩባንያውን ንብረቶች የመሸጥ አቋም ነበረው፡፡ ያ ቢሆን የአንድ ቡድን ጥቅም ብቻ ነው የሚጠበቀው፡፡ ባንኩ ንብረቶቹን ሽጦ ገንዘቡን ይወስዳል፡፡ የቀሩት ደንበኞች ምንም የሚያገኙት ነገር አይኖርም፡፡ ከባንኩ ጋር ስንነጋገር የነበረው ወደ ሐራጅ ከተገባ ደንበኞች ስለሚጎዱ ወደዚያ አንግባ ብዬ ብዙ ተከራክሬያለሁ፤›› ብለዋል፡፡ 

ዘመን ባንክ በሠራው የፋይናንስ ዕቅድ ኩባንያውን ለመታደግ በወቅቱ ለሦስት ወራት 17 ሚሊዮን ብር ያስፈልግ እንደነበር ጠቁሞ፣ ከሦስት ወራት በኋላ ያለ ዕዳ መንቀሳቀስ ይችላል የሚል ነበር፡፡ ‹‹ነገር ግን ባንኩ ቶሎ ብሎ ወደ ሐራጅ ማውጣት ስለፈለገ ያንን ለመከላከል የምችለው ኪሳራ በማወጅ ብቻ ነው፡፡ ወደ ኪሳራ በማስገባበት ጊዜ ባንኩ እንደ ሌሎች ደንበኞች ተሰልፎ ይጠብቃል፡፡ እኔ ብቻ ሸጬ ልውሰድ የሚለው አይኖርም፡፡ ይህን ደግመን ደጋግመን ተናግረናል፡፡ እዚያ ውስጥ አንግባ በሚል ተነጋግረናል፡፡ እስከ መጨረሻው ቀን ጠብቄ ወደ ኪሳራ እንዲገባ አድርጌያለሁ፤›› ብለዋል፡፡ 

ሪፖርተር ዘመን ባንክን ለማነጋገር ተደጋጋሚ ጥረት ያደረገ ቢሆንም፣ ማኔጅመንቱ አስተያየት ከመስጠት ተቆጥቧል፡፡ ‹‹አስተያየት የለንም፤›› ብለዋል አንድ የባንኩ ከፍተኛ ኃላፊ፡፡ 

ሆላንድ ካር የዘመን ባንክ 34 ሚሊዮን ብር ዕዳ አለበት፡፡ ባንኩ የኩባንያውን ንብረቶች በ83 ሚሊዮን ብር የመነሻ ዋጋ ለጨረታ አቅርቧል፡፡ ሞጆ ከተማ የሚገኘው በ20,000 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈው የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ፣ መጋዘንና የቢሮ ሕንፃ 22.3 ሚሊዮን ብር የተገመተ ሲሆን፣ 236 ያልተገጣጠሙና 70 የተገጣጠሙ መኪኖች 51.7 ሚሊዮን ብር ተተምነዋል፡፡ 

ዘመን ባንክ የጨረታ ማስታወቂያውን ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ያስነገረ ሲሆን፣ የጨረታ መዝጊያው ግንቦት 8 ቀን 2007 ዓ.ም. ነበር፡፡ ኢንጂነር ታደሰ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ግንቦት 7 ቀን 2007 ዓ.ም. የኩባንያው ንብረቶች እንዳይሸጡ አግዷል፡፡ እንደ ኢንጂነር ታደሰ ገለጻ ኩባንያው ያለበት የባንክ፣ የደንበኞችና የመንግሥት (ግብር) ዕዳ በአጠቃላይ 63 ሚሊዮን ብር ሲሆን፣ የኩባንያው ጠቅላላ ንብረት ግምት 180 ሚሊዮን ብር ነው፡፡ ኢንጂነር ታደሰ በአውሮፓ ቆይታቸው የገንዘብ ምንጭ ሲያፈላልጉ እንደነበር ገልጸው፣ የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት በቤልጂየም ከኢትዮጵያ አምባሳደር አቶ ተሾመ ቶጋ ጋር ረዥም ጊዜ ሲወያዩ እንደነበር፣ አምባሳደር ተሾመ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዳደረጉላቸው ተናግረዋል፡፡ 

አዲስ የነደፉትን ሆላንድ ካርን ካለበት ችግር አውጥቶ ወደፊት ሊያስኬድ የሚያስችል ያሉትን ዕቅድ፣ ቤልጂየም ለሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ አቅርበው ኤምባሲው ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ማቅረቡን፣ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽንና የፍትሕ ሚኒስቴር አስተያየት እንዲሰጡበት ተጠይቀው ዕቅዱ ተቀባይነት በማግኘቱ፣ አስፈላጊው የሕግ ከለላ ተደርጎላቸው ወደ አገር ቤት ተመልሰው ችግሮቹን በውይይት እንዲፈቱ እንደተፈቀደላቸው አስረድተዋል፡፡ 

ኢንጂነር ታደሰ ያቀረቡት ዕቅድ በመጀመርያ በፋብሪካ ውስጥ የሚገኙትን መኪኖች ገጣጥሞ ክፍያ ለፈጸሙ ደንበኞች ማቅረብ፣ በመቀጠል የተቀሩትን መኪኖች ገጣጥሞ በመሸጥ ኩባንያው ያለበትን የባንክ ዕዳ መክፈል የሚል ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት 150 ያልተገጣጠሙ መኪኖች በፋብሪካው ውስጥ እንደሚገኙ ጠቅሰው፣ እነዚህን መኪኖች ለመገጣጠም አምስት ሚሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡ ስድስት ሚሊዮን ብር ከአውሮፓ የገንዘብ ምንጮች ይዘው እንደመጡ ለማወቅ ተችሏል፡፡ 

ሆላንድ ካር ከገባበት ማጥ ውስጥ ለማውጣት አንድ ዓመት እንደሚፈጅም ተናግረዋል፡፡ ‹‹ያልተገጣጠመ መኪና ብረት ነው፡፡ አይሸጥም፡፡ ገጣጥመን እሴት ጨምረን ብንሸጠው ሁሉም ተጠቃሚ ይሆናል፡፡ ደንበኞች ንብረታቸውን ያገኛሉ፡፡ ከዚያም ተርፎ ድርጅቱ መቀጠል የሚችልበት ሁኔታ ይኖራል፤›› ብለዋል፡፡ 

ኢንጂነር ታደሰ 115 ደንበኞች ክፍያ ፈጽመው መኪኖቻቸውን አለመረከባቸውን፣ 40 ያህል ደግሞ ቀረጥ ከፍለው መኪኖቹን መውሰዳቸውን አረጋግጠዋል፡፡ የጀመሩት ጥረት ከሰመረ ወደ ሌሎች ኢንቨስትመንቶች ለመግባት ዕቅድ እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡

 ከሆላንድ ካር መኪና ከገዙ ግለሰቦች መካከል በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ብቸኛው የተቃዋሚ ፓርቲ አባል የሆኑት አቶ ግርማ ሰይፉ አንዱ ናቸው፡፡ በሆላንድ ካር ቀውስ ከተፈጠረ በኋላ መኪናቸውን የተረከቡ የመጀመርያው ደንበኛ መሆናቸውን ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ 

‹‹መኪናዬን ከተረከብኩ በኋላ ሌሎች ግለሰቦች መኪናቸውን እንዲያገኙ ጊዜዬንና ገንዘቤን በመሰዋት ብዙ ጥረት አድርጌያለሁ፡፡ ሆኖም እጃችን አመድ አፋሽ ሆነና ባልሠራነው ኃጢያት ተከሰን ጠበቃ ቀጥረን ተከራክረን ነፃ ወጥተናል፤›› በማለት በወቅቱ የነበረውን ሁኔታ አስታውሰዋል፡፡ ‹‹አሁን ባለሀብቱ ያሉትን ችግሮች ፈትቼ ከባንኩ ጋር ተነጋግሬ ለደንበኞች መኪኖቹን አስረክባለሁ ካሉ በእውነቱ ይህ መልካም ዜና ነው፡፡ የሚደገፍ ተግባር ነው፤›› ብለዋል አቶ ግርማ፡፡ 

 

በምርጫው ሁከት ቢፈጠር እንኳን ከአቅም በላይ እንደማይሆን መንግሥት አስታወቀ

ምርጫውን ተጠቅመው ሰላም ለማወክ የሚንቀሳቀሱ አካላትን መንግሥት የሚታገስበት ምክንያት እንደሌለና ችግር ከተፈጠረም ከአቅም በላይ ሊሆን እንደማይችል፣ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትሩ አቶ ሬድዋን ሁሴን አስታወቁ፡፡

ሚኒስትሩ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ግንቦት 6 ቀን 2007 ዓ.ም. በሰጡት መግለጫ፣ አጠቃላይ የቅድመ ምርጫ ዝግጅት ከጥቃቅን ችግሮች ባሻገር ሰላማዊ እንደነበር ባለፈው ሳምንት ከምሁራንና ከፓርቲዎች ጋር በተደረገ ውይይት መረጋገጡን ገልጸዋል፡፡

ቀጣዩ ምዕራፍም ተመሳሳይና ሰፋ ያለ ተሳትፎ የሚደረግበትና ምርጫው በአጠቃላይ እጅግ ሰላማዊ ሆኖ ይጠናቀቃል የሚል እምነት መያዙን ተናግረዋል፡፡

በዚህም መሠረት ሁከትም ሆነ ችግር ለመፍጠር የሚያስችል ምክንያት አለመኖሩን፣ ተቃዋሚ ፓርቲዎችም ሆኑ ገዥው ፓርቲ በጋራ ባካሄዱት ግምገማ ከሞላ ጎደል ማረጋገጣቸውን ጠቅሰዋል፡፡

‹‹ይህ ማለት ግን ምርጫውን ተጠቅመው ሰላም ለማወክ የሚንቀሳቀሱ አካላት አይኖሩም ማለት አይደለም፤›› ያሉት ሚኒስትሩ፣ ‹‹ይህንን የሚሸከም የሕዝብ ትከሻ የለም፡፡ በመንግሥት በኩልም ለፀጥታ ኃይሎች ሥልጠናና የቁሳቁስ ዝግጅት የተደረገ በመሆኑ ችግር ከተፈጠረ ከአቅም በላይ ሊሆን እንደማይችል መንግሥት እርግጠኛ ነው፤›› ብለዋል፡፡

ለፀጥታ ኃይሉ በቅርቡ የተሰጠው ሥልጠናና የአቅም ግንባታ ማዳበሪያ የተከናወነው የተለየ ሥጋት በመኖሩ እንዳልሆነም አስታውቀዋል፡፡ ከምርጫ 97 በኋላ የተደረገ ቀጣይነት ያለው የአቅም ግንባታ ለፀጥታ ኃይሉ መስጠት መደበኛ ተግባር መሆኑን ጠቅሰው፣ ከቁጥጥር ውጪ የሚወጣ ነገር አይኖርም ብለዋል፡፡ የአቅም ግንባታ ሥራውም ከምርጫ በኋላ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡

የግንቦት ሰባት ዋና ጸሐፊ የነበሩትና በኢትዮጵያ የደኅንነት ኃይል የመን ሰንዓ አውሮፕላን ማረፊያ በቁጥጥር ሥር የዋሉት የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ፣ ከአዲስ አበባ አዳማ የሚወስደውን የፍጥነት መንገድ ሲጐበኙ የሚያሳይ ፎቶግራፍ በተለያዩ ማኅበራዊ ድረ ገጾች መታየቱን አስመልክቶ የተጠየቁት አቶ ሬድዋን፣ ‹‹ምሥሉን አይቼዋለሁ፡፡ ነገር ግን ዝርዝር መረጃ አልጠየቅኩም፡፡ በመሆኑም በጉዳዩ ላይ የምሰጠው መረጃ የለም፤›› ብለዋል፡፡  

 

በካሩቱሪ ላይ ዕርምጃ ለመውሰድ ከኤጀንሲው አቅም በላይ ሆኗል

ሳዑዲ ስታር ግብርና ልማት ኩባንያ አንድ መቶ ሺሕ ሔክታር መሬት እንዲሰጠው፣ ለግብርና ሚኒስቴር አዲስ ጥያቄ ማቅረቡን መረጃዎች አመለከቱ፡፡ 

ሳዑዲ ስታር የመሬት ጥያቄውን ከሦስት ዓመት በፊት ያቀረበ ቢሆንም፣ ሚኒስቴሩ ቀደም ብሎ የወሰደውን መሬት ማልማት ባለመቻሉ፣ በፍጥነት ወደ ልማት እንዲገባ ማሳሰቢያ በመስጠት ጥያቄውን አልተቀበለም ነበር፡፡ ነገር ግን ሳዑዲ ስታር በዚህ የበጀት ዓመት ቀደም ሲል ከተሰጠው አሥር ሺሕ ሔክታር መሬት ሰባት ሺሕ ሔክታሩን በማልማቱ፣ የተጨማሪ መሬት ጥያቄውን በድጋሚ ማቅረቡን ምንጮች ገልጸዋል፡፡

የሼክ መሐመድ ሁሴን አል አሙዲ ግዙፍ የእርሻ ኩባንያ የሆነው ሳዑዲ ስታር፣ በጋምቤላ ክልላዊ መንግሥት አሥር ሺሕ ሔክታር መሬት የተረከበው የሩዝ ልማት ለማካሄድ እንደነበረ ይታወቃል፡፡ የኩባንያው የረጅም ጊዜ ዕቅድ በጋምቤላ፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝና በአማራ ክልሎች እስከ 500 ሺሕ ሔክታር መሬት ድረስ ማልማት ነው፡፡

ኩባንያው ከዕቅዱ ውስጥ በአብዛኛው ልማት በጋምቤላ ክልል ማካሄድ እንደሚፈልግ የኩባንያው መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ በዚህ ዕቅድ መሠረት አሥር ሺሕ ሔክታር መሬት በመረከብ ወደ ሥራ ገብቷል፡፡

ሰፋፊ የገጠር መሬቶችን ከክልሎች በውክልና እየተረከበ የሚያስተዳድረው የኢትዮጵያ የግብርና ኢንቨስትመንትና መሬት አስተዳደር ኤጀንሲ የሚመሩት አቶ አበራ ሙላት ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ሳዑዲ ስታር በዚህ የበጀት ዓመት የተሻለ የሥራ አፈጻጸም አሳይቷል፡፡ ‹‹ከዚህ ቀደም የተሰጠውን አሥር ሺሕ ሔክታር መሬት ሳያለማ ተጨማሪ መሬት በመጠየቁ የቦታ ጥያቄው አልተስተናገደም፡፡ ነገር ግን ዘንድሮ ሰባት ሺሕ ሔክታር መሬት በማልማቱ የሳዑዲ ስታር ተጨማሪ መሬት ጥያቄ ሊታይ ይችላል፤›› በማለት አቶ አበራ ኩባንያው የጠየቀው መሬት ሊሰጠው እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡ 

በ500 ሚሊዮን ብር ካፒታል የተቋቋመው ሳዑዲ ስታር፣ ከሦስት እስከ አምስት ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስት በማድረግ በአሥር ዓመት ውስጥ በ500 ሺሕ ሔክታር መሬት ላይ ሩዝን ጨምሮ የተለያዩ ሰብሎችን የማልማት ዕቅድ እንዳለው ማስታወቁ ይታወሳል፡፡ ነገር ግን በተሰጠው መሬት ላይ የሚፈለገውን ልማት ባለማካሄዱ ምክንያት ዕቅዱ የይስሙላ ነው ተብሎ ሲተች ነበር፡፡

የሚያመርተውን ምርት ለአገር ውስጥ ገበያ ከማቅረብ ባሻገር በተለይ ለሳዑዲ ዓረቢያ ገበያ በስፋት እንደሚያቀርብ ሲገልጽ ቆይቷል፡፡ 80 ሚሊዮን ዶላር ወጭ በማድረግ ዘመናዊ የእርሻ መሣሪያዎች ገዝቶ ወደ ሥራ የገባው ሳዑዲ ስታር በቅርቡ የጠየቀው መሬት ሊሰጠው እንደሚችል የግብርና ሚኒስቴር ምንጮች ያስረዳሉ፡፡

በኢትዮጵያ ሰፋፊ እርሻ ውስጥ በመግባታቸው ድጋፍና ውግዘት ካስተናገዱ ኩባንያዎች መካከል ሳዑዲ ስታርና ካሩቱሪ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ አቶ አበራ እንዳሉት ሳዑዲ ስታርና ሌሎች የህንድ ኩባንያዎች አሁን በጥሩ ሁኔታ  ላይ የሚገኙ ቢሆንም፣ ካሩቱሪ ግን በችግር ውስጥ ይገኛል፡፡ 

አንድ መቶ ሺሕ ሔክታር መሬት ተረክቦ ወደ ሥራ የገባው ካሩቱሪ እስካሁን ማልማት የቻለው 1,340 ሔክታር መሬት ብቻ መሆኑን አቶ አበራ ገልጸዋል፡፡ ‹‹ኩባንያው የውስጥ ችግር ያለበት በመሆኑ መሬቱን ያለማል ብለን አንጠብቅም፡፡ መሬቱን በመንጠቅ ለሚያለማ አካል ማስተላለፍ ቢኖርብንም፣ በእኛ ደረጃ ዕርምጃ መውሰድ አንችልም፤›› በማለት የሚናገሩት አቶ አበራ ጉዳዩ በመንግሥት ደረጃ በሚወሰድ አቋም የሚፈታ ነው ብለዋል፡፡

ካሩቱሪ ከአምስት ዓመት በፊት ከጋምቤላ ክልል 300 ሺሕ ሔክታር መሬት ተረክቦ ነበር፡፡ የክልሎችን ሰፋፊ መሬት የፌዴራል መንግሥት በውክልና ተረክቦ ማስተዳደር ሲጀምር ካሩቱሪ ይዞት ከነበረው መሬት ሁለት መቶ ሺሕ ሔክታር ተነጥቆ፣ አንድ መቶ ሺሕ ሔክታሩን እንዲያለማ ተወስኖ ነበር፡፡

ነገር ግን ከአንድ መቶ ሺሕ ሔክታር መሬቱም ቢሆን ማልማት የቻለው 1,340 ሔክታር ብቻ በመሆኑ፣ ለግብርና ሚኒስቴር ባለሥልጣናት ተስፋ አስቆራጭ ሆኗል፡፡

ግብርና ሚኒስቴር ለ86 የአገር ውስጥና የውጭ ኩባንያዎች 2.3 ሚሊዮን ሔክታር መሬት ሰጥቷል፡፡ ነገር ግን መልማት የቻለው 840 ሺሕ ሔክታር ብቻ በመሆኑ በዝቅተኛ የሥራ አፈጻጸም ተመዝግቧል፡፡  

ነገር ግን በቅርቡ በግብርና ፖሊሲ ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች ባደረጉት የቴሌቪዥን ክርክር በውጭ ባለሀብቶች የግብርና ልማት ላይ የተጠየቁት የግብርና ሚኒስትሩ አቶ ተፈራ ደርበው፣ ‹‹የውጭ ባለሀብቶች የካፒታል እጥረታችንን በሚያቃልል፣ ቴክኖሎጂ በሚያሸጋግር፣ የገበያ ትስስር በሚፈጥር መንገድ እስከ 300,000 ሔክታር የሚደርስ መሬት ይዘው ለማልማት ጥረት እያደረጉ ነው፡፡ 50 ሚሊዮን ሔክታር ገና የሚለማ መሬት አለን፤›› ብለዋል፡፡ በአገር ውስጥ ባለሀብቶች 2.2 ሚሊዮን ሔክታር መልማቱንም አክለዋል፡፡

 

መኢአድ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው የት እንደሚገኙ አላውቅም አለ

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ወደ ቢሮ አለመምጣታቸውን አስታወቀ፡፡ በአሁኑ ወቅት የት እንዳሉ አላውቅም ብሏል፡፡

በተለያዩ ማኅበራዊ ድረ ገጾች ዘገባዎች ደግሞ የትጥቅ ትግል ለማድረግ ወደ ኤርትራ ማምራታቸው እየተነገረ ነው፡፡ በትክክል የት እንደሄዱ ግን አልተረጋገጠም፡፡

ካለፈው ሳምንት አጋማሽ ጀምሮ በፌስቡክ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ተስፋሁን አለምነህ የትጥቅ ትግል ለማድረግ ወደ ኤርትራ ሄደዋል የሚሉ ዘገባዎች የወጡ ቢሆንም፣ የመኢአድ ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሐሪ ግን፣ ‹‹የት እንደሄደ አላውቅም፡፡ ጉዳዩን በተመለከተ ግን እንደ ማንኛውም ሰው በማኅበራዊ ድረ ገጽ አይቻለሁ፤›› በማለት ከሪፖርተር ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

አቶ ተስፋሁን ለመጨረሻ ጊዜ መኢአድ ቢሮ የታዩት ድርጅቱ ባዘጋጀው ስብሰባ ላይ ለመካፈል ከሁለት ሳምንት በፊት ቅዳሜ እንደነበር ያስታወሱት አቶ አበባው፣ በመሀል የተፈጠረውን ነገርና ወዴት እንደሄዱ እንደማያውቁ ገልጸዋል፡፡

የፊታችን እሑድ በሚካሄደው አምስተኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ መኢአድን ወክለው እንደማይወዳደሩ የገለጹት አቶ አበባው፣ አቶ ተስፋሁን ፓርቲውን የተቀላቀሉት ከአሥር ዓመታት በፊት እንደነበረ አክለው ገልጸዋል፡፡

‹‹ፓርቲውን የተቀላቀለው ከጐጃም ነው፡፡ ከዚህ ቀደም ብሎ ደግሞ የምዕራብ ጐጃም የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ ነበር፤›› ብለዋል፡፡ 

አቶ አበባው ‹‹የድርጅታዊ ጉዳይ አይደለም፡፡ የመኢአድ አባልነት መሥፈርት በፈቃደኝነት ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ በዚህም መሠረት በፈቃደኝነት አባል ይሆናል፡፡ ለመውጣት ሲፈልግ ደግሞ ይለቃል እንጂ በግድ የሚያዝ ነገር የለም፤›› በማለት ውሳኔው ግለሰቡን ብቻ የሚመለከት እንደሆነና ከፓርቲው ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት እንደሌለው አስረድተዋል፡፡

አቶ ተስፋሁን በፓርቲ እንቅስቃሴ ውስጥ ጥሩ ተሳትፎ እንደነበራቸው ያስታወሱት አቶ አበባው፣ ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በእንግሊዝኛ ቋንቋ መመረቃቸውንም አመልክተዋል፡፡

በኢትዮጵያ መንግሥት በአሸባሪነት የተፈረጁ ድርጅቶች ኤርትራ ውስጥ እንደሚንቀሳቀሱ፣ ከእነዚህ ድርጅቶች መካከል ግንቦት 7፣ ኦነግ እና ኦብነግ ነፍጥ አንግበው መንግሥትን ለመጣል አቅደው እንደሚሠሩ ይነገራል፡፡ 

በቅርቡ መንግሥት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት የሆኑት ብርሃኑ ተክለ ያሬድ፣ ፍቅረ ማርያም አስማማውና እየሩሳሌም አስፋው ወደ ኤርትራ ሊገቡ ሲሉ በቁጥጥር ሥር እንዳዋላቸውና ክስ እንደመሠረተባቸው መዘገባችን የሚታወስ ነው፡፡  

አቶ ተስፋሁን በፌስቡክ ገጻቸው ላይ የፕሮፋይል ፎቶአቸውን በመለወጥ ታጣፊ ክላሽኒኮቭ አንግተው የሚታዩ ሲሆን፣ ከሰላማዊው ትግል በመውጣት ለትጥቅ ትግል መዘጋጀታቸውን ማሳያ ነው እየተባለ ነው፡፡ በፌስቡክ ገጻቸው ላይ ከዚህ ቀደም የተለያዩ የፉከራና የሽለላ ግጥሞችን በማስፈር የሚታወቁት አቶ ተስፋሁን፣ ኤርትራ ወይም ሌላ ሥፍራ ለትጥቅ ትግል መሄዳቸውን ያረጋገጠ አካል የለም፡፡ 

 

እውነቱን እንነጋገር ከተባለ የኢኮኖሚውና የንግዱ እንቅስቃሴ ቀዝቀዝ እያለ ነው፡፡ ልዩ ጥናትና ምርምርም አያስፈልገውም፤ በግልጽ የሚታይ ነውና፡፡

•    አዲሱ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ነገ ርክክብ ይፈጽማሉ
በዳዊት ታዬ
በአገሪቱ ከሚገኙ የግል ባንኮች መካከል በቀዳሚነት የሚጠቀሰው ንብ ኢንተርናሽናል ባ

ተሰናባቹ የንብ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አመርጋ ካሳ
በኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ ከአርባ ዓመታት በላይ በመቆየት ከሚታወቁ የባንክ ባለሙያዎች መካ

በውድነህ ዘነበ
የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ትላልቅ የመንግሥት ፕሮጀክቶችን ለመመርመር የያዘውን ዕቅድ ለማሳካት፣ ከብሔራዊ ደኅንነት ኤጀንሲ ጋር…

ለፖለቲካ ተፅዕኖ የተጋለጡ ግለሰቦች ሀብት ምንጭ እንዲመረመር ያስገድዳል
በዮሐንስ አንበርብር
በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብ ወይም ንብረትን ሕጋዊ

በዮናስ አብይ
በደቡብ ክልል የፖለቲካ እንቅስቃሴ ውስጥ ረጅም ጊዜ ያሳለፉትና ከደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢሕዴን) መሥራቾች አንዱ የ…

በዮሐንስ አንበርብር
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (ፓርላማ) በቅርቡ ከሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትርነታቸው የተነሱትን የአቶ ጁነዲን ሳዶ ያለመከሰስ መብት ሊያነ

‹‹ድርጅቱ ኪራይ ሊጨምርብን እንጂ ሊያስወጣን አይችልም›› ተከራይ ነጋዴዎች‹‹ግንኙነታችን በውል ላይ የተመሠተና ነፃ በመሆኑ ከሌላው ጋር መወዳደር አ

በየማነ ናግሽ
ኢትዮጵያ በመጪው ሚያዝያ ወር የአካባቢና የአዲስ አበባ መስተዳደር ምርጫ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ነች፡፡ ባለፉት አራት የአካባቢ ምርጫዎች

የኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በቅርቡ ባካሄደው ስብሰባ ልዩና አንገብጋቢ ትኩረት ያስፈልጋቸዋል ብሎ ውሳኔ ካስተላለፈባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ በመል

–    አሠልጣኝ ሰውነት ቢሻው ሊፋን መኪና ተሸለሙ
በደረጀ ጠገናውትናንት ማምሻውን በኢንተርኮንትኔንታል ሆቴል በተካሄደው ሥነ ሥርዓት የኢትዮጵያ እግር

“ድርጊቱን አልፈጸምኩም ጥፋተኛም አይደለሁም” ተጠርጣሪ የወንድወሰን ይልማ
በታምሩ ጽጌጥቅምት 10 ቀን 2005 ዓ.ም. ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት አካባቢ በቂርቆስ ክፍለ…

በየማነ ናግሽከጥቂት ወራት በፊት በኦጋዴን ብሔራዊ ነፃነት ግንባር (ኦብነግ) እና በኢትዮጵያ መንግሥት መካከል ሊካሄድ የታሰበው ድርድር ከተቋረጠ በኋላ አ

በታምሩ ጽጌየፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ዓቃቤ ሕግ ሥልጣናቸውን አላግባብ በመጠቀም ሙስና ፈጽመዋል በሚል በተጠረጠሩበት የሙስና ወንጀል

–    አሥር ሰዎች መሞታቸው ይነገራል-    የክልሉ ፕሬዚዳንት የሞተ ሰው የለም ብለዋል
በዮሐንስ አንበርብርበጋምቤላ ክልል አኝዋ ዞን በአቦህ ወረዳ በተከሰ…

በውድነህ ዘነበየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ያልተመለሱ የኅብረተሰብ ጥያቄዎችን እስከ ጥር 15 ቀን 2005 ዓ.ም. ድረስ ለመመለስ ጥብቅ ውሳኔ ባሳለፈበት ሳምን…

በውድነህ ዘነበኢትዮጵያ ከሱዳን ጋር በሚያዋስናት ጠረፍ በኩል ሕገወጥ የገቢና ወጪ ንግድ መስፋፋቱን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ገለጹ፡፡

በውድነህ ዘነበመንግሥት የግብርናውን ክፍለ ኢኮኖሚ በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ የያዘውን ዕቅድ ለማሳካት፣ የግብርና ኢኮኖሚ ዞን ለማቋቋም እየተዘጋጀ መሆ

–    ‹‹ምርጫ ቦርድ ከኢሕአዴግም በላይ ኢሕአዴግ ሆኗል›› ቅሬታ አቅራቢ ተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች
በየማነ ናግሽየኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ በመጪ

–    የፈረንሳዩ ቦሎሬ አፍሪካ ሎጂስቲክስ ለመንግሥት ጥያቄ አቀረበ
በዮሐንስ አንበርብር ሦስት የተለያዩ መንግሥታዊ ተቋማትን በማዋሀድ ግዙፉ የኢትዮጵያ…

በአገራችን የሙስና አደጋ  በእጅጉ አሳሳቢ እየሆነ መጥቷል፡፡ ሥርም እየሰደደ ነው፡፡ እየተስፋፋም ነው፡፡ ቀስ በቀስም ወደ ብሔራዊ ባህልነት እየተቀየረ

–    ውጤታማ የአንድ ለአምስት ተዋናዮች የሚሸለሙበት መመርያ ተዘጋጀ
በውድነህ ዘነበየሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር በ22 ሚኒስቴር መሥርያ ቤቶችና ኤጀንሲዎች ላ…

አቶ አስመላሽ ወልደ ሥላሴ፣ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግ፣ የፍትሕና የአስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ

በታምሩ ጽጌ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሦስተኛ ወንጀል ችሎት በሽብርተኝነት ወንጀል ክስ ተመሥርቶባቸው በ18፣ በ25 ዓመታትና በዕድሜ ልክ እስራ…

በብርሃኑ ፈቃደ በአዲስ አበባ ብቅ ብቅ እያሉ ስላሉ ሕንፃዎች ከውስጥና ከውጭ ቅሬታዎች ቢነሱም፣ የሚመለከተው አካል ጆሮ ያለው አይመስልም፡፡ ሕንፃዎቹ መ

በዮሐንስ አንበርብርበኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ ምሁራንና ሌሎችንም የሚያካትት መንግሥትን በተለያዩ ፖሊሲ ጉዳዮችና አፈጻጸሞች ላይ የሚያማክር ‹‹የኢትዮ

–    አራት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር አልዋሉም
በታምሩ ጽጌየተሰጣቸውን ሥልጣን ያላግባብ በመጠቀምና በመመሳጠር ለመንግሥት ገቢ መሆን የሚገባውን ከ1.7

በውድነህ ዘነበበዓለም ገበያ ውስጥ የግብርና ምርቶች ዋጋ እየቀነሰ በመምጣቱ ምክንያት ንግድ ሚኒስቴር የአገሪቱ ኤክስፖርተሮች የሚልኩትን የምርት መጠን

–    ስዊስ ባንክ በታምራት ላይኔ ስም የተቀመጠ ስምንት ሚሊዮን ዶላር መለሰ
በውድነህ ዘነበበኢትዮጵያ እየተካሄዱ ያሉ ግዙፍ የመንግሥት ፕሮጀክቶች ከሚያ

በጋዜጣው ሪፖርተርለረዥም ጊዜ የቆየና ሥር የሰደደ የፖለቲካ ፍጥጫ ውስጥ የሚገኙት እስራኤልና ኢራን የቀይ ባህር አካባቢን ለመቆጣጠር የሚያደርጉት ፉክክ

–    ዶክተር ኃይሉ አርዓያ ከኃላፊነታቸው ተነሱ
በታምሩ ጽጌበአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ልዩ አስተባባሪ ኮ…

–    ከቀረቡት ስምንት የክስ መቃወሚያዎች ሁለቱ ተቀባይነት አገኙ
በታምሩ ጽጌከጄነራል ዊንጌት ቴክኒክና ሙያ ማሠልጠኛ ኮሌጅ ወደ አስኮ በሚወስደው መንገ…

በዳዊት ታዬየኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤትን በቦርድ አባልነት በማገልገል ላይ የሚገኙት አቶ ሸዋዬ ገብሩ፣ እርሳቸው አባል የሆኑበትና  በአ

በውድነህ ዘነበከትናንት በስቲያ ረፋድ ላይ በኦሮሚያ ክልል ከምዕራብ ወለጋ ዞን ደምቢዶሎ ከተማ ወደ ጋምቤላ ከተማ በመጓዝ ላይ በነበረ አይሱዙ የጭነት ተሽ

በምዕራፍ ብርሃኔ አገሪቷ ከጨርቃ ጨርቅ ኢንዱትሪ እንድታስገባ የታቀደላትን የአንድ ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማሳካትና በዘርፉ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንድትሆ