የልጆቹን እናት በጥይት ደብድቦ ገድሏል የተባለው ተጠርጣሪ ክስ ተመሠረተበት

“ድርጊቱን አልፈጸምኩም ጥፋተኛም አይደለሁም” ተጠርጣሪ የወንድወሰን ይልማ

በታምሩ ጽጌ

ጥቅምት 10 ቀን 2005 ዓ.ም. ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት አካባቢ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 20/20 ልዩ ሥፍራው ካርቱም ሬስቶራንት ኦሎምፒያ አካባቢ የልጆቹን እናት ከ10 በላይ ጥይቶች ተኩሶ ግፍ በተሞላበትና በአሰቃቂ ሁኔታ ገድሏል የተባለው ተጠርጣሪ የወንድወሰን ይልማ፣ በከባድ የሰው መግደል ወንጀልና የሰው መግደል ሙከራ ወንጀል ክስ ተመሠረተበት፡፡