የበሽታዎቹን መከሰት ከወዲሁ የሚጠቁሙ አስቀድመው የሚታዩ ምልክቶች ይኖሩ ይሆን? የስኳር ሕሙማን በራሳቸው ሊወስዱ የሚችሏቸው የጥንቃቄ እርምጃዎች ይኖሩ ይሆን? የስኳር በሽታን ተከትለው የሚከሰቱት አሳሳቢዎቹ የዓይን ሕመም ዓይነቶች የትኞቹ ናቸው? ተከታታይ ቅንብሮቹ የሕክምና አማራጮቹን ጨምረው ሕሙማንና የቤተሰብ አባላት ሊጠይቁና ሊመልሱ የሚሿቸውን ጭብጦች ይዳሳሳሉ።

ሚስትና ልጁን ያጣ፣ እናትና ወንድሞቹን ውሃ የበላበት፣ እህቱን እና 28 ጓደኞቹን ያጣ ናቸው። ስላሳለፉት ጉዞ አስቸጋሪነትና ለመሄድ ስለተዘጋጁ ስደተኖች የሚነግረን ወጣትም ከግብጽ አነጋግረናል። ባለፈው ሳምንት ማብቂያ በሜዲትራንያን ባህር ላይ ጀልባ ተገልብጦ 500 ስደተኞች ሰጥመው ሕይወታቸው ማለፉን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ኤጀንሲ …

ከመስመጥ የተርፉት ኢትዮጵያውያን 11 ብቻ ናቸው፤ ሦስቱን አነጋግረናቸዋል – VOA Read more »

በደቡብ ሱዳንና ኢትዮጵያ ድንበር አከባቢ የሕወሓት ሰራዊት እንቅስቃሴ ምንም እንዳሌለ ምንጮች ጠቆሙ:: ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎SouthSudan‬ ‪#‎Gambella‬ ‪#‎EUPF‬ ‪#‎MinilikSalsawi‬ Minilik Salsawi – Ethiopian DJ – የጋምቤላ ፖሊስ እና ልዩ ሃይል ወደ ካምፕ ሆን ተብሎ ሰብስቦ ማስገባትን መሳሪያ ማስፈታትን ወታደሩን ክፍል ከድንበር አከባቢ …

በደቡብ ሱዳንና ኢትዮጵያ ድንበር አከባቢ የሕወሓት ሰራዊት እንቅስቃሴ ምንም እንዳሌለ ምንጮች ጠቆሙ:: ‪ Read more »

ራሱን ‹‹የደቡብ ሱዳን ቡድን›› በማለት የሚጠራው የሙርሌ ጎሳ ታጣቂ ቡድን የደቡብ ሱዳንን ወታደራዊ ዩኒፎርም በመልበስና ዘመናዊ የጦር መሣሪያዎች በመታጠቅ መቼ እንደተነሳ እስካሁን ማረጋገጫ ባይገኝም፣ ዓርብ ሚያዚያ 7 ቀን 2008 ዓ.ም. ለቅዳሜ አጥቢያ ከንጋቱ 11፡00 ሰዓት ጋምቤላ ደረሰ፡፡ ታጣቂው ኃይል ከደቡብ …

አሰቃቂው የጋምቤላ ጭፍጨፋና የፀጥታ ኃይሎች አሠላለፍ Read more »

የደም ባንክ በመኪና አደጋ ብዛት የደም እጥረት ያጋጠመው መሆኑን አስታወቀ በኢትዮጵያ በየዕለቱ የሚሰቀጥጡ የመኪና አደጋዎችን መስማት እየተለመደ መጥቷል፡፡በአዲስ አበባ የሚገኙ የኤፍ ኤም ሬዲዩ ጣብያዎችም በየማለዳው ከተለያዩ አካባቢዎች መረጃዎችን በማጠናቀር የሚጠብቋቸውን የትራፊክ ባለሞያዎች በማስተናገድ የደረሱትን የመኪና አደጋዎች ለህዝብ ያስተላልፋሉ፡፡ የህክምና ባለሞያዎችና …

የደም ባንክ በመኪና አደጋ ብዛት የደም እጥረት ያጋጠመው መሆኑን አስታወቀ Read more »

የዓለም የጤና ድርጅት ሰነድ እንደሚለዉ በአሁኑ ወቅት የዓለማችን 37 ሚሊየን ሕዝብ HIV ተሐዋሲ በደሙ ዉስጥ ይገኛል። ባለፈዉ ጎርጎሪዮሳዊ ዓመት 2015 ላይ 16 ሚሊየኑ ፀረ ኤች አይቪ መድኃኒት እንደሚወስዱ ተመዝግቧል። በሽታዉ እስካሁን ከ34 ሚሊየን በላይ ሰዎችን ሕይወት ቀጥፏል። የመድኃኒቱ ስርጭት እና …

የፀረ ኤች አይቪ መድኃኒቶች – ዶይቸ ቬለ Read more »

የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ባለፈዉ ሳምንት በሰጠዉ ዉሳኔ ነጻ ያሰናበታቸዉ ሁለት ሰዎች እንዳልተፈቱ የቅርብ ምንጮች አስታወቁ። ፖሊስ ማእከላዊ የወንጀል ምርመራ እንደወሰዳቸዉም ተገልጿል። የፖሊስ እርምጃ ምክንያት ግን አልታወቀም። ዝርዝሩን ከመለስካቸዉ አመሃ ዘገባ ያድምጡ → listen

በተለያዩ ምክንያቶች ከአፍንጫ ደም ሊፈስ ይችላል። ነስር የምንለዉ ማለት ነዉ። ብዙዎች መንስኤዉ ምንድነዉ ብለዉ ይጨነቃሉ። ነስር ድንገተኛ እና አስደንጋጭ የመሆኑን ያህል አብዛኛዉን ጊዜ ቤት ዉስጥ ሊቆጣጠሩት የሚቻል እንደሆነ አንዳንድ የህክምና ጽሑፎች ይጠቁማሉ። ሆኖም አልፎ አልፎ ደግሞ ብዙ ደም የሚፈስበት ከባድ …

የአፍንጫ መድማት ወይም ነስር – ዶይቸ ቬለ Read more »

News #Ethiopia Wetatoch Dimts – መረጃ ሙሉ ያደርጋል ለዚህ ደግሞ የኢትዮጵያ ወጣቶች ድምፅ ሳምንታዊ ዜናዎችን እንዲሁም መጣጥፎችን ለስለስ ካሉ ሙዚቃዎች ጋር ይዘንላችሁ ቀርበናል አብራችሁን ሁኑ ። [youtube http://www.youtube.com/watch?v=afh4A-rNteM]

በ120ኛው የቦሰተን ማራቶን በሴቶቹ ተከታትለው በመግባት ያሸነፉት፥ አፀደ ባይሣና ትርፊ ነገሪ ናቸው። የወንዶቹን ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ያለውን ሥፍራ የወሰዱትና ታሪክ የሠሩት የኢትዮጵያ ሯጮች ደግሞ፥ ለሚ ብርሃኑ፥ ያለፉት ሁለት ዓመታት ሻምቲዮኑ ሌሊሣ ዴሢሣና ፀጋዬ ናቸው። listen

ማኅደረ ማርያም ሰሞኑን በደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት በፋርጣ ወረዳ፣ ከደብረ ታቦር 28 ኪሎ ሜት ርቀት ላይ፣ በ2450 ሜትር ከፍታ ከባሕር ወለል በላይ፣ በቧኢት ተራራ ላይ ወደተተከለቺው ማኅደረ ማርያም ደብር ተጉዤ ነበር፡፡ የጉዞዬ ዋና ዓላማ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን በተመለከተ ለምሠራው ጥናት …

ማኅደረ ማርያም – ማኅደረ ታሪክ Read more »

በኦሮሚያ ክልል አልፎ አልፎ በተማሪዎችና በነዋሪዎች የሚካሄደዉ ተቃዉሞና የጸጥታ ሃይሎች የሃይል እርምጃ ምላሽም ቀጥሏል። በጉጂ ዞን ኦዶሻኪሶ ወረዳ መጋደር በተባለ መንደር ባለፈዉ ማክሰኞ በዳዳ ጋልቹ የሚባል ወጣት በመንግስት ሃይሎች መገደሉን የአካባቢ ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ ገልጸዋል። በወረዳዉ የሻኪሶ ከተማ አስተዳዳሪዎች …

በጉጂ ዞን ኦዶ ሻኪሶ ወረዳ በዳዳ ገልቹ የሚባል ወጣት በመንግስት ታጣቂዎች መገደሉ ተነገረ – VOA Read more »

ሰሞኑን በአዲስ አበባ አንድ ትልቅ የስብሰባ አዳራሽ ውስጥ የአዲስ አበባ ደረጃ አንድ ሌቦች ስብሰባ አድርገው ነበር፡፡ የስብሰባው መሪ ቃል ‹የሕዝቡን ጥያቄ ለመመለስ ሌቦች ምን ሊያደርጉ ይችላሉ?› የሚል ነው፡፡ ስብሰባው እንደተጀመረ አንደኛው የታወቀ ሌባ እጁን አወጣና ‹መፈክሩ ላይ የተጠቀስንበት ስም ትክክል …

“የሰርቆ አደሮች” ስብሰባ ” – ዲ/ን ዳንኤል ክብረት Read more »

በምዕራብ ኢትዮጵያ ከደቡብ ሱዳን ድንበር የተሻገሩ ታጣቂዎች በዕለተ አርብ ማለዳ በፈጸሙት ጥቃት ህጻናት መታገታቸውን የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል-አቀባይ ተናገሩ። ቃል-አቀባዩ አቶ ተወልደ ሙሉጌታ በጥቃቱ ምን ያኽል ሰዎች ታግተው እንደተወሰዱ አለመናገራቸውን የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘግቧል።

በኦሮሚያ በየደረጃው የተካሄደውን ግምገማ ተከትሎ ሃላፊነታቸውን አልተወጡም የተባሉ ከ 800 በላይ አመራሮች ከደረጃ ዝቅ ብለው እንዲሰሩ የማድረግና ከሀላፊነት የማንሳት እርምጃ መወሰዱን የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት አስታወቀ። በክልሉ የተጀመረው የተቃውሞ እንቅስቃሴ መነሻ የመልካም አስተዳደር ችግር መሆኑን የኦሮሚያ ክልልና የፌደራሉ መንግስት ማስታወቃቸው ይታወሳል። ዘጋብያችን እስክንድር ፍሬው ከአዲስ አበባ የላከው ዘገባ ዝርዝሩን ይዟል።

በእንዳለ ጌታ ከበደ የካቲት 2008 ዓም ዋጋ፡- 120 ብር እንዳለ ጌታ ከበደ በዓሉ ግርማን እንደ ጌታ ነፍስ ዘርቶ እንደደአልዓዛር ከሞት አስነሥቶታል፡፡ ከትውልድ ቀየው ጀምሮ ‹እስከ መቃብሩ› ደረስ እየተከተለ፡፡ መዛግብቱን ያገላብጣል፣ እናውቃለን የሚሉትን ይጠይቃል፣ ያውቃሉ ብሎ የገመታቸውን ያናግራል፤ ሄዶበታል፣ ውሎበታል፣ ገብቶበታል፣ …

በዓሉ ግርማ – ሕይወቱና ሥራዎቹ (መጽሃፍ ግምገማ በዳንኤል ክብረት) Read more »

የቦሌ ደብረ ሳ ሌም መድኃኔዓለም ካቴድራል ካህናትና ሠራተኞች፤ለታላቁ ሕዳሴ ግድብ ያዋጣነው ከ400ሺሕ ብር በላይ ገንዘብ የገባበትን አናውቅም፤ አሉ፡፡  ገንዘቡ ከ4 ዓመት በፊት 160 ከሚሆኑ ሠራተኞች ደመወዝ የተሰበሰበ መሆኑን ምንጮች ለአዲስ አድማስ ጠቁመዋል፡፡ እንደ ምንጮቹ ገለፃ፤ ካህናቱ በወቅቱ በተደጋጋሚ ለካቴድራሉ አስተዳደር …

“ለሕዳሴ ግድብ ቦንድ ያዋጣነው 400ሺ ብር የገባበትን አናውቅም” የቦሌ መድኃኔዓለም ካህናት Read more »

–    አምስት ምእመናን ለእስር ተዳርገዋል –    የውጭ ጉዳይ ሓላፊው ተጠያቂ ተደርገዋል –    ሰበካ ጉባኤው በፕሪቶርያ ፍ/ቤት ክሥ መሥርቷል አለማየሁ አንበሴ በደቡብ አፍሪካ ጆሐንስበርግ ጽርሐ ጽዮን መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በአስተዳደር ሳቢያ የተፈጠረ አለመግባት ወደ ዐምባጓሮ አምርቶ 8 ምእመናን የተጎዱ ሲሆን ጉዳዩም …

በጆሐንስበርግ መድኃኔዓለም የተፈጠረ ውዝግብ ምዕመናንን ለዐምባጓሮ አደረሰ Read more »

በኩዌት በቤት ሰራተኛነት ተቀጥራ የምትሰራ ስሟ ያልተጠቀሰ ኢትዮጵያዊት፣ የአሰሪዎቿን  ቤተሰቦች የሰው ስጋ ይበላሉ ስትል መክሰሷን ገልፍ ዲጂታል ኒውስ የተባለው ድረገጽ ዘገበ፡፡ሳላዋ በተባለው የአገሪቱ አውራጃ በቤት ሰራተኛነት ተቀጥራ የምትሰራው ኢትዮጵያዊቷ፣ በአሰሪዎቿ   መኖሪያ ቤት ውስጥ የሰው ራስ ቅል ተደብቆ ማየቷን በመጥቀስ ለፖሊስ …

ኢትዮጵያዊቷ በኩዌት አሰሪዎቿን “በሰው በላነት” ከሰሰች Read more »

ጋምቤላ ኢትዮጵያ ውስጥ ከ140 በላይ ሰዎች ዐርብ ሚያዝያ 7 ቀን፣ 2008 ዓ.ም. ማንነታቸው ባልታወቀ ታጣቂዎች ተገደሉ። የኑዌር ጎሳ አባላት የመኖሪያ መንደሮች ላይ ባነጣጠረው ጥቃት የተገደሉት ሰዎች ቁጥር ከ221 በላይ መሆኑን ሱዳን ትሪቡዩን ዘግቧል። ሱዳን ትሪቢዩን የደቡብ ሱዳን ጦር መለዮ የለበሱ …

ጋምቤላ ኢትዮጵያ ውስጥ ከ140 በላይ ሰዎች ማንነታቸው ባልታወቀ ታጣቂዎች ተገደሉ። Read more »

ጋምቤላ ኢትዮጵያ ውስጥ ከ140 በላይ ሰዎች ዐርብ ሚያዝያ 7 ቀን፣ 2008 ዓ.ም. ማንነታቸው ባልታወቀ ታጣቂዎች ተገደሉ። የኑዌር ጎሳ አባላት የመኖሪያ መንደሮች ላይ ባነጣጠረው ጥቃት የተገደሉት ሰዎች ቁጥር ከ221 በላይ መሆኑን ሱዳን ትሪቡዩን ዘግቧል።

ጫት ለኢትዮጵያ የሚሰጠው ጥቅምና በጤና ላይ የሚያስከትለው ጉዳት በቅጡ እንዲጤን ስለ ጫት ጥናታዊ ጽሁፎች ያቀረቡ ምሁራን አሳሰቡ ። «ፎረም ፎር ሶሻል ስተዲስ» የተባለው መንግሥታዊ ያልሆነው ድርጅት ባዘጋጀው አዲስ አበባ ውስጥ ለሁለት ቀናት በተካሄደው ዐውደ ጥናት ላይ የጫት ኤኮኖሚያዊ እና ባህላዊ …

የጫት ጉዳትና ጥቅሞች በኢትዮጵያ – ዶይቸ ቬለ Read more »

በምስራቅ ወለጋ መነሲቡ ወረዳ ውስጥ ሰኞ እና ማክሰኞ በተማሪዎችና በመንግሥት ኃይሎች መካከል ግጭት መፈጠሩን ነዋሪዎች ገለጹ። ከግጭቱም በኋላ ከሰላሳ ሰው በላይ መታሰሩን ተናግረዋል። የከተማው ፖሊስ ምንም የተፈጠረ ነገር የለም ይላል። የአፋን ኦሮሞ ዝግጅት ባልደረባ ቱጁቤ ኩሳ ያጠናቀረችውን ዘገባ ጽዮን ግርማ …

በምስራቅ ወለጋ መነሲቡ ወረዳ ከ30 በላይ ሰዎች መታሠራቸውን ተማሪዎች ተናገሩ – VOA Read more »

ይድረስ ለኢትዮጵያ ደራስያን ማህበር
ሰሞኑን ሥርጭቱን በጀመረው “ቃና ቲቪ” ይዘት እና አሰራር ላይ ለመወያየት በደብዳቤ
ባሳወቅናችሁ መሰረት ተወካያችሁን መላካችሁ ይታወቃል፡፡  የኪነ ጥበብ ሞያ ማኅበር ተወካዮቹ (የእናንተም ባሉበት) በተጠቀሰው ጉዳይ ለሁለት የተለያዩ  ቀናት የጋራ ውይይት አካሂደው የጋራ የአቋም መግለጫ ማውጣታቸው ይታወቃል፡፡ ይህ የጋራ  አቋም በፅሁፍና በንባብ ለሚዲያ ከመቅረቡ በፊት የእናንተ ሁለት ተወካዮችን ጨምሮ የሁሉም   የሞያ ማኅበር ተወካዮች መስመር በመስመር በጥንቃቄ ተመልክተው ማሻሻያና ማረሚያ ካደረጉ  በኋላ በጋራ ጋዜጣዊ መግለጫው የተሰጠ መሆኑ አይዘነጋም፡፡ መግለጫ ከመሰጠቱ አንድ ቀን ቀደም  ብሎ (በ20/07/2008) የደራስያን ማኅበር ልሳን በሆነውና ዘወትር ማክሰኞ ምሽት በኤፍ ኤም አዲስ 97.1 በሚቀርበው ፕሮግራም ላይ የመግለጫውን ፍሬ ሃሳብ ለህዝብ በመግለፅ ሚዲያዎች እንዲገኙ መረጃ ስታደርሱ እንደነበርም ይታወቃል፡፡ይህ ጥሬ ሀቅ ባለበት ሁኔታ ባለፈው ቅዳሜ ሚያዚያ 1 ቀን 2003 ዓ.ም በወጣው የአዲስ አድማስ  ጋዜጣ ላይ የደራስያን ማኅበር ፕሬዝደንት ዶ/ር ሙሴ ያዕቆብ የሰጡት ከእውነት የራቀና የተዛባ  መግለጫ እጅግ የሚያሳፍርና የሚያሳዝን ሆኖ አግኝተነዋል፡፡ የመላው የደራስያን ማኅበር አመራርና አባላት እምነት እንዳልሆነም እናምናለን፡፡ የእሳቸው ማኅበር ተወካይና ሌሎች የጥበብ ማኅበራት በጋራ ተወያይተው ያወጡትን መግለጫ በምን ምክንያትና መነሳሳት ለመካድ እንዳነሳሳቸው ለጊዜው ያወቅነው ነገር የለም፡፡ በሂደቱ ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ሲሳተፍ የነበረውን የማኅበራቸውን ተወካይ፤ “መግለጫውን ለመከታተል የተገኘ ነው” በማለት ከደራሲያን ማኅበር ተወካይነት ወደ ሚዲያ ተወካይነት ለውጠው፣ ለጋዜጣው ለመግለፅ ለምን እንደተገደዱም አልተረዳንም፡፡ ከዚህም በላይ ማህበራቱ የቴሌቪዥን ጣቢያውን በሚመለከት እያቀረቡት ካለው አመክንዮና ለህዝብ ከገለፁት አቋም ፈፅሞ የራቀና የማናውቀውን ጉዳይ በመናገር አንባቢን ግራ ከማጋባታቸውም በላይ የማኅበራቱን ጥያቄ ያልተገባ ለማስመሰል መሞከራቸው ከምን በመነጨ አስተሳሰብና ዓላማ እንደሆነ ለጊዜው አልደረስንበትም፡፡ በእሳቸውና በመላው የጋዜጣዊ መግለጫው ተሳታፊ በነበሩ የሚዲያ አካላት እጅ በሚገኘው ባለ አምስት ገፁ የሞያ ማኅበራቱ የአቋም መግለጫ በየትኛው አንቀፅ ላይ ይሆን የሳንሱር ጉዳይ የተነሳው!? የኢትዮጵያ ደራስያንን እወክላለሁ የሚል
የማኅበር ፕሬዚደንት የተፃፈን ፅሑፍ አንብቦ መረዳት ተሳነው ቢባልስ ማን ያምን ይሆን!? የሆነስ
ሆነና “እነ በዓሉ ግርማን የመሳሰሉ ፀሐፍት በሳንሱር ምክንያት የሕይወት መስዋዕትነት ከፍለዋል”
ማለታቸውስ የደራስያን ጉዳይ ጉዳዬ ነው ብሎ የፕሬዚደንትነት ሥልጣን ከተቆናጠጠ ግለሰብ ይጠበቃል ወይ!? ሌላው ቢቀር የደራስያን ማኅበር የአመራር አባል በነበረው ደራሲ እንዳለጌታ  ከበደ ጥልቅ ጥናትና ምርምር የታተሙትን “ማዕቀብ” እና “የበዓሉ ግርማ ሕይወትና ሥራዎች” የተሰኙ በብዙዎች የተነበቡ መፃሕፍትን ቢያነቡ ኖሮ በዓሉ ግርማን ጨምሮ በኢትዮጵያ ውስጥ በሳንሱር ምክንያት የሕይወት መስዋዕትነት የከፈለ (የተገደለ) አንድም ደራሲ እንደሌለ በተረዱ ነበር፡፡ እንደሚታወቀው የኪነ ጥበብ ሞያ ማኅበራቱ በመግለጫቸው ያሉት ዋና ፍሬ ሀሳብ ዶ/ር ሙሴ በስህተት አልያም በችኮላ ተረድተው እንዳሉት ሳይሆን “ቃና” ቴሌቪዥን ለውጭ ሀገር ፕሮግራሞች የሰጠው (70%) ተገቢ አይደለም የሚል ነው፡፡ ይህ ሀሳብ የሳንሱር ሳይሆን በሀገር ውስጥ፣ በሀገር አቅም በሚሰሩ ፊልሞች ላይ ጫና ፈጥሮ ፍትሀዊ ተወዳዳሪነት እንዳይኖር በማድረግ፣ ዳዴ በማለት ላይ ያለውንና የብዙ ዓይነት ጥበቦችና ባለሙያዎች ውህደት ውጤት የሆነውን የኢትዮጵያ ሲኒማ አቀጭጮ ያጠፋል፣ አዲስ ለሚከፈቱ ጣቢያዎች በቀላሉና በውስን ሰዎች ሳይለፉ ገንዘብ እንደሚሰራ በማሳየት በመስኩ የተሰማሩ የኢትዮጵያ ዜጎች በሀገራቸው ስለ ሀገራቸው ጉዳይ የሚተርክ ፊልም በመስራት እንዳይጠቀሙና ሞያውን እንዳያሳድጉ እንቅፋት ይሆናል፣ ህዝብን የሚያረካ ሥራን የሰሩና ይሁንታን በማግኘት የተደነቁ ባለሙያዎችም ዝናቸውን በመጠቀም የደሀ
ህዝባቸውን ችግር ለመቅረፍ በሚደረጉ የማኅበራዊ አገልግሎቶች ላይ የሚያደርጉትን በጎ እንቅስቃሴና ቅስቀሳ ተፅዕኖ አልባ በማድረግ ያዳፍነዋል የሚል ነው፡፡ በእግረ መንገድም ፊልሞቹ በአብዛኛው ከምዕራባውያን የሚመጡ እንደመሆናቸውና የሚተላለፈው ለቤተሰብ ቅርብ በሆነው የቴሌቪዥን ሚዲያ በኩል ከመሆኑ አንፃር አጉል ባህል በቀላሉ ታዳጊ ህፃናትና ልጆች ላይ እንዳይሰርፅ ሥጋታችንን የገለፅንበት ነው፡፡ የኪነ ጥበብ ሞያ ማኅበራቱ በጋራ ባካሄዱት ውይይት ዶ/ር ሙሴ የእሳቸውን ማኅበር በመወከል በተገኘው ግለሰብ እምነት ከሌላቸው፣ ከቢሮአቸው በአራት እርምጃ ከሚርቀው የጋራ ማኅበራቱ
መሰብሰቢያ ቢሮ በመምጣት ጉዳዩን ማጣራት ይችሉ ነበር፡፡ አልያም በአሁን ሰዓት የደራስያን አመራር አባል የሆኑት የሥራ ባልደረባቸው በዚሁ ጋዜጣ ሚያዝያ 26 ቀን 2008 ዓ.ም የፃፉትን ጥልቅና ለብዙዎች ስለ ጉዳዩ የበለጠ ግንዛቤ ያስጨበጠ ፅሑፍ ቢቻል አንብበው ካልሆነም ካነበበ ሰምተው አስተያየታቸውን ቢሰጡ ኖሮ ትዝብት ላይ የሚጥል ስህተት ባልሰሩ፣ መልካም ሥም የነበረውን ማኅበራቸውንም ባላቀለሉ ነበር እንላለን፡፡
(ተፃፈ፡- ከ “የኢትዮጵያ  የኪነ ጥበብ ማኅበራት
ጊዜያዊ አስተባባሪ”)

 ከደቡብ ኦሞ ዞን ጂንካ ከተማ በሽብርተኝነት የፈጠራ ውንጀላ ታስረው በጠፍ ሌሊት ወደ አዋሳ የተወሰዱትና ከ20/07/08 ጀምሮ በአዋሳ ፖሊስ ኮሚሽን ግቢ ታስረው የሚገኙት የኦሞ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ኅብረት ም/ሊቀመንበርና የዞኑ ጽ/ቤት ኃላፊ መምህር ዓለማዬሁ መኮንን ፣ የኦህዲኅ አባል አቶ አብርሃም ብዙነህና የቀድሞ …

በሽብርተኝነት የፈጠራ ውንጀላ ታስረው በጠፍ ሌሊት ወደ አዋሳ የተወሰዱት እነ ዓለማዬሁ ለሳምንት ተቀጠሩ Read more »

በርካታ ኢትዮጵያዊያን ምሁራን በአገራዊ ጉዳዮች ላይ ችግሮች ሲፈጠሩ የአገሪቱን ፖሊሲ አውጭዎችና ህግ አስፈጻሚዎችን በድፍረት ከመተቸትም ሆነ መልካም ጎኖችን ከማበረታታት ታቅበው ይታያሉ። ቁጥራቸው በዛ ያሉ አይሁን እንጂ በገዥው ፓርቲ ጉያም ሆነ በተቃውሞው ጎራ የተሰለፉ ምሁራንም ምሁራዊ ግዴታቸውን ለመወጣት ሲንቀሳቀሱ እናያለን። ከተቃውሞውም …

“አቶ መለስ በታሪክ ሊጠየቁበት የሚችለው ነገር ቢኖር ኢትዮጵያን ወደብ አልባ ማድረጋቸው ነው” ዶክተር ፍሰሃ አሰፋው Read more »

በአምቦ ዩኒቨርስቲ አዋሮ ግቢ ካለፈው አርብ ጀምሮ ውሃ መቋረጡን፣ መብራት ከዕረቡ ጀምሮ መጥፋቱን እንዲሁም በምስራቅ ወለጋ መነሲቡ ወረዳ ከሠላሳ በላይ ሰዎች መታሠራቸው በዚህ ዘገባ ተካቷል።

በሕክምናው አጠራር “ኮሌስትሮል” በመባል በሚታወቀው፤ በአንድ በኩል ለጤና በእጅጉ አስፈላጊ፤ መጠንና ዓይነቱ ሲለወጥ ደግሞ ጎጂ በሚሆነው በደማችን ውስጥ የሚዘዋወረው ስብ መሠል ንጥረ ነገር ምንነትና የሕክምናው ዓለም ምልከታዎች ዙሪያ የሚያተኩር ተከታታይ ቅንብር ነው። ሞያዊ ትንታኔውን የሚሰጡን የልብና የውስጥ ደዌ ከፍተኛ አማካሪ …

ኮሌስትሮልን ተከትለው የሚመጡ የጤና ሁከቶችን መከላከያ ቅድመ ጥንቃቄ – VOA Read more »

አዲሱ “ቃና” ቴሌቭዥን የአርቲስቶችን መንደር አናወጠ

      የኢትዮጵያ ፊልም ሰሪዎች፣ የቲያትር ባለሙያዎች ፣ የሙዚቀኞችና  የሰአሊያን ማህበራት እንዲሁም አላቲኖስ የፊልም ሰሪዎች ማህበር ሰሞኑን በጋራ በሰጡት መግለጫ፤ አዲሱ የ“ቃና” ቴሌቪዥን የፕሮግራም ይዘት የአገሪቱን የሲኒማ ጥበብ አደጋ ላይ የሚጥል በመሆኑ ይዘቱን ሊያስተካክል ይገባል አሉ፡፡
“ቃና” ቴሌቪዥን በበኩሉ፤ የአገሪቱን የፊልም ኢንዱስትሪ ለማሳደግ እተጋለሁ ብሏል፡፡
“ቃና” 70 በመቶ የውጭ ሀገር ፊልሞችን፣ 30 በመቶ የአገር ውስጥ ፕሮግራሞችን ሊያቀርብ መዘጋጀቱን የጠቆሙት ማህበራቱ፤ የይዘት ምጣኔው የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ ያላገነዘበና የባህል ወረራን የሚያስፋፋ ነው ሲሉ ነቅፈዋል፡፡ የአደጋው ምንጭ በዋናነት የውጭ ሀገር ፊልሞችን ተርጉሞ በዳቢንግ (ድምጽ በመቅዳትና አስመስሎ በመለጠፍ) ማቅረቡ ነው ብለዋል፡፡
በቴሌቪዥን ጣቢያው የሚቀርቡት የውጭ ሀገር ፊልሞች ንግድ ተኮር በመሆናቸው ምንም አይነት ትምህርታዊና ሞራላዊ ይዘት የላቸውም ያሉት ማህበራቱ፤ የባህል ወረራን በማስፋፋት ትውልድን ከማጥፋታቸው በፊት መንግስት ህጋዊ እርምጃ እንዲወስድ ጠይቀዋል፡፡
ጣቢያው አጭር እድሜ ያለውን የተከታታይ ድራማ ታሪካችንን በማቀጨጭ የፊልም ኢንዱስትሪውን ዕድገት የሚያሰናክል በመሆኑ ፕሮግራሙን በድጋሚ ሊከልስ ይገባዋል ብለዋል፤ ማህበራቱ፡፡
ባለፈው ዓመት “ዳና” የቴሌቪዥን ድራማ 8 ሚሊዬን ብር ገቢ ለመንግስት ማስገኘቱን የጠቀሱት ማህበራቱ፤ “ቃና” በዚህ ይዘቱ የሚቀጥል ከሆነ ግን ትውልድ ከማጥፋቱ በተጨማሪ መንግስት ማግኘት የሚገባውን ጥቅም ያሳጣዋል ብለዋል፡፡
ባለፈው ረቡዕ በብሄራዊ ቲያትር በሰጡት በመግለጫ ላይ የቴሌቪዥን ጣቢያውን የሥራ ሐላፊዎች ለምን እንዳልጋበዙ የተጠየቁት ማህበራቱ፤ የተቻላቸውን ያህል ጥረት ቢያደርጉም ሊያገኙአቸው እንዳልቻሉ ተናግረዋል፡፡ የ“ቃና” ቴሌቪዥን የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ኃይሉ ተክለሃይማኖት በበኩላቸው፤ ጣቢያው በመግለጫው ላይ አለመጋበዙን ገልፀው፤ በይዘቱ ዙሪያም ቀርቦ ሊያናግራቸው የሞከረ ማህበርም ሆነ ግለሰብ አለመኖሩን ተናግረዋል፡፡ በፕሮግራሙ ይዘት ላይ ችግር አለ ብሎ የሚያምን አካል በማንኛውም ጊዜ ሊያነጋግራቸው እንደሚችልም ገልፀዋል – ሃላፊው፡፡
ባለፉት 50 ዓመታት የቴሌቭዥን ታሪክ በተለያዩ አገራት በራሳቸው ቋንቋ ተተርጉመው ባህልና እሴቶችን ሳይጋፉ የቀረቡና እየቀረቡ ያሉ የመዝናኛ ስራዎች፣ በየአገሩ ያሉትን የፊልምና የቴሌቪዥን ኢንዱስትሪ አሁን ላለበት ደረጃ አድርሰውታልም ሲሉ አስረድተዋል፡፡ ጣቢያው ከመቋቋሙ በፊት በአገሪቱ ያደረገው ጥናት እንደሚያሳየው፤ የቴሌቪዥን ፕሮግራሞችን ከሚመለከቱ ኢትዮጵያውያን ግማሽ ያህሉ የሚያዩት የውጭ አገር ይዘት ያላቸውንና  በሌላ ቋንቋ የተሰሩትን ሲሆን የሚያዩትም እንዲሁ እንደወረዱ መሆኑን የጠቆሙት  አቶ ኃይሉ፤ አሁን ጣቢያው ለእይታ የሚያበቃቸው ፊልሞች ግን የተመረጡና  ለማህበረሰቡ ትርጉም ሊሰጡ የሚችሉት ብቻ ናቸው፡፡
ፊልሞቹ በቀጥታ የተተረጐሙ ሳይሆኑ በእኛ ሀገር ባህል፣ አባባልና አስተሳሰብ የተቃኙ እንደሆኑም ጠቁመው፤ ያልተገቡ የተባሉ የፊልሙ ክፍሎችም ተቆርጠው እንደሚወጡ ኃላፊው ተናግረዋል፡፡
ጣቢያው በቲያትር ጥበባት የተመረቁ ከ100 በላይ ኢትዮጵያውያንን በፀሐፊነት፣ በዳይሬክቲንግ፣ በድምጽና በቪዲዮ ኤዲቲንግ ቀጥሮ እያሰራ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ኃይሉ፤ በቀጣይም የእራሱን አገራዊ ስራዎች ለመስራት በእንቅስቃሴ ላይ ነው ብለዋል። ለ“ቃና” ፕሮግራሞቹን የሚያቀርበው “ቢ. ሚዲያ” የተባለው ኢትዮጵያዊ ድርጅትም ፕሮግራሙን በዶላር በመሸጥ፣ የውጪ ምንዛሪ ወደ አገር ውስጥ እንደሚያስገባም የጣቢያው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አክለው ገልፀዋል፡፡
ደራሲያንና የፊልም ምሁራን በጉዳዩ ዙሪያ ያላቸውን አስተያየት ለማወቅ አዲስ አድማስ ሁለት አንጋፋ ባለሙያዎችን አነጋግሯል፡፡ የጣቢያው ይዘት ለኢትዮጵያዊው ተመልካች ያን ያህል ይጠቅማል ብዬ አላምንም፤ ጉዳቱ ግን ከፍተኛ ነው ያለው ደራሲ ኃይሉ ፀጋዬ፤ የፕሮግራሙ ይዘት የአገር ውስጥ 30፣ የውጪው 70 እጅ መሆኑ ለአገር ውስጥ እጅግ ዝቅተኛ ትኩረት መሰጠቱን ያሳያል፤ ይሄ ደግሞ እየተንገዳገደ ያለውን የፊልም ኢንዱስትሪ ያቀጭጨዋል ብሏል፡፡
የጣቢያው የፕሮግራም ይዘት ከፍተኛ የባህል ወረራን ከማስፋፋቱም በላይ ለጥቂት ሰዎች የስራ እድል በመፍጠር በመስኩ የተሰማሩ ከ10 ሺህ በላይ ሰዎችን ስራ እንደሚያሳጣም ደራሲው ገልጿል፡፡
ተቋሙ ገንዘብን መሰረት ያደረገ መሆኑን የገለፀው ኃይሉ ፀጋዬ፤ ይህ ደግሞ ኃላፊነት የጎደለው ስራ ነው ብሏል፡፡
የትያትር ባለሙያው ረዳት ፕሮፌሰር ሙሉጌታ ጀዋሬ በበኩሉ፤ “የጣቢያው መፈጠር ገንቢ ነገር አለው፤ ለምሳሌ የህብረተሰቡን የፊልም ማጣጣም አቅም ይጨምራል፡፡ ሆኖም ጣቢያው ለውጪ ፊልሞች የሚሰጠው ድርሻ ዝቅ ማለት አለበት” ሲል አስተያየቱን ሰንዝሯል፡፡
“ባህልን ባላገናዘበና ይህንን ለመቆጣጠር የሚያስችል ህግ ባልተረቀቀበት ሁኔታ በስፋት መልቀቁ ግን አደጋ አለው ያለው ፕሮፌሰሩ፤ መጀመሪያ ህግ መውጣት አለበት፤ ፊልሞቹ ባህልን፣ ስነ ልቦናንና፣ እምነትን ጠብቀው ተጣርተው የሚቀርቡና በህግ የሚመሩ መሆን አለባቸው ብሏል፡፡ “በርግጥ ውድድር መኖር አለበት፤ ውድድር መኖር ያለበት ግን በእኩል የመወዳደሪያ ሜዳ ላይ ነው፡፡ ካልሆነ ግን የውድድር አምዱን ኢ-ፍትሃዊ ያደርገዋል፡፡  ይህ ለኔ ወንጀል ነው” ሲልም አስረድቷል ሙሉጌታ ጀዋሬ፡፡
በሳተላይት የሚሰራጩ የቴሌቪዥን ጣቢያዎችን በተመለከተ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ባለስልጣን ተጠይቆ በሰጠው ምላሽ፤ “በሳተላይት ለሚሰራጩ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ፍቃድ አልሰጥም፤ እነዚህ ጣቢያዎች ከውጪ አገራት ፍቃድ አውጥተው የሚንቀሳቀሱ በመሆናቸው ከባለስልጣኑ እውቅና ውጪ ናቸው” ብሏል፡፡ ሆኖም ጣቢያዎቹ በኢትዮጵያ የሚያዘጋጁአቸው ፕሮግራሞች ሲኖሩ ባለስልጣን መ/ቤቱ የብቃት ማረጋገጫን እንደሚሰጥ ለማወቅ ተችሏል፡፡ የሳተላይት ቴሌቪዥን ጣቢያዎችን የፕሮግራሞች ይዘት የሚቆጣጠርበት አሰራር ግን እንደሌለው ለአዲስ አድማስ ተናግሯል፡፡   

ከትንሽ ጋር እንደመታገል ምን የሚያደክም ነገር አለ?!! ለኢትዮጵያውያን አብሮ መስራትና ሥርዓት መስርቶ መሄድ ከጊዜ ወደጊዜ ምን ያህል ከባድ እየሆነ እንደመጣ ለመረዳት ያለፉት አርባና ሃምሳ አመታትን ታሪካችንን ምስክር ነው፡፡ አለመተማመንና አምባጓሮ ሳይፈጥርበት ለረጅም ጊዜ የሚዘልቅ ተቋም ለመፍጠር ምን ያህል እየተቸገርን እንደሆነ …

ከትንሽ ጋር እንደመታገል ምን የሚያደክም ነገር አለ?!! ወረታው ዋሴ Read more »

በዓለም በፍጥነት በማደግ ላይ ከነበሩ አስራ ሀገሮች ሰባቱ የአፍሪካ ሀገሮች ሲሆኑ፤ ኢትዮጵያ ግንባር ቀደም ሆና ቆይታለች። የያዝንው የአውሮፓዊያን ዓመት ግን ይሄ ሁኔታ እንደሚቀየር ነው የዓለም የገንዘብ ድርጅት አይ ኤም ኤፍ (IMF)በየዓመቱ የሚያወጣው የዓለም ምጣኔ ሀብት ግምገማ ዘገባው አስታውቋል። ባለፈው ዓመት …

የኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት እድገት ለሚቀጥለው አንድ ዓመት እንደሚያሽቆለቁል የዓለም የገንዘብ ድርጅት IFM አስታወቀ – VOA Read more »

ብዙዎቻችን ቴዲ አፍሮን ከሙዚቃ ሥራውና ከሐገር ወዳድነቱ ባሻገር እምብዛም የግል ሕይወቱን እና ምን አይነት ሰው እንደሆነ አናውቀውም እርሱም ቢሆን ስለራሱ ማውራት ስለማይወድ እና ይህንን ፈፀምኩኝ ብሎ ስለማያወራ የቴዲን ማንነት በግልጽ ልናውቀው አልቻልንም ሆኖም ቴዲ አፍሮ እንደዚህም አይነት ሌላ ገፅታ አለው። ★ ሐምሌ 30,1998 ዓመተ ምሕረት በድሬዳዋ ደርሶ በነበረው የጎርፍ አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የ30 ሺህ ብር […]

ከአምዶም ገብረስላሴ ኣቶ መኮነን ኣስፋው በምርጫ 2007 ዓ/ም በተካሄደው ምርጫ ዓረና-መድረክን ወክለው በኣላማጣ ምርጫ ክልል ለክልል ምክር ቤት ተወዳድረው ህወሓትን ኣምበርክከዋል ዳሩ ድምፃቸው ተዘረፉ እንጂ። ኣቶ መኮንን በ1974 ዓም ወደ በረሃ ወጥቶ ያታገሉ ሲሆኑ ከነ ሓየሎም ኣርኣያና ገብሩ ኣስራት ጎን …

በካድሬዎች ስር የወደቀችው ቤተ ክርስትያን (አምዶም ገብረስላሴ) Read more »

ዛሬ ሚያዚያ 6, 2008ዓ.ም. ዐፄ ቴዎድሮስ የዛሬ 148 ዓመት “ተማርኬ የሐበሻ ንጉሥ ተማረከ! ተብሎ እራሴን ሀገሬንና ሕዝቤን ከማዋርድ ስም ከምሰብር ሞት ይሻለኛል!” ብለው ለሚወዷት ሀገራቸውና ሕዝቧ ክብርና ኩራት ሲሉ ተማርከው በጠላት እጅ ከመውደቅ እራሳቸውን አጥፍተው የጀግና እረፍትን ቢያርፉ መርጠው እራሳቸውን ያጠፉበት የሚታሰብበት ዕለት ነው፡፡ “ዐፄ ቴዎድሮስ ለምን ይተቻሉ! ፈጽሞ መተቸት የለባቸው!” ለማለት አይደለም አነሣሴ፡፡ ነገር […]

ወያኔና ትግሬ መስፍን ወልደ ማርያም ሚያዝያ 2008 አዳም በበደለ መድኃኔ ዓለም ካሠ፤ የተጠቀሰውን አባባል የማያውቅ ክርስቲያን ያለ አይመስለኝም፤ ለእስላሞችም ቢሆን አዲስ ነገር አይሆንባቸውም፤ አዳም ትእዛዝ ጥሶ ዕጸ በለስን በላና ተረግሞ ከገነት ወጣ፤ አዳም በደለ የሚባልበት ምክንያት ይህ ነው፤ አዳም በገነት …

ወያኔና ትግሬ – Pro.መስፍን ወልደ ማርያም Read more »

የኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት እድገት ለሚቀጥለው አንድ ዓመት እንደሚያሽቆለቁል የዓለም የገንዘብ ድርጅት አይ ኤም ኤፍ አስታወቀ::-( VOA)- ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎IMF‬ ‪#‎WorldBank‬ ‪#‎Economy‬ የኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት እድገት ለሚቀጥለው አንድ ዓመት እንደሚያሽቆለቁል የዓለም የገንዘብ ድርጅት አይ ኤም ኤፍ (IMF) አስታወቀ። በዚህ በያዝንው የአውሮፓዊያን ዓመት …

የኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት እድገት ለሚቀጥለው አንድ ዓመት እንደሚያሽቆለቁል የዓለም የገንዘብ ድርጅት አይ ኤም ኤፍ አስታወቀ Read more »

ኢንተርኔትን በመጠቀም የጽሁፍና የድምጽ መልእክቶች የምናስተላልፍባቸው አፕሊኬሽኖችን ጨምሮ ፌስ ቡክና ትዊተር በኢትዮጵያ የኦሮሚያና በአንዳንድ የደቡብ ክልሎች ካለፈው አንድ ወር ጀምሮ አገልግሎት መስጠት ማቆማቸውን ብሎምበርግ የአካባቢዎቹን ነዋሪዎች በመጥስ ዘግቧል፡፡ የስማርት ስልክ ተጠቃሚዎች በስልካቸው የጫኗቸውን አፕሊኬሽኖች በመጠቀም አገልግሎቶቹን ማግኘት አለመቻላቸውን በመጥቀስ የቴሌ …

በኢትዮጵያ የኦሮሚያና በአንዳንድ የደቡብ ክልሎች ካለፈው አንድ ወር ጀምሮ አገልግሎት መስጠት ማቆማቸውን ብሎምበርግ ዘግቧል፡፡ Read more »

ወጣቶች ትናንት ምሽት በተለያዩ የደሴ ከተማ አካባቢዎች የበተኑት ወረቀት የከተማው ህዝብ ትኩረት መሳቡን ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ ወጣቶች ተናግረዋል፡፡ የትግል ጥሪ ወረቀቶች፣ ህዝቡ ለመብቱ እንዲነሳ፣ በወልቃይት ጥያቄ ዙሪያ የደሴ ህዝብ ጥያቄውን ከሚያቀርቡ የወልቃይት ጠገዴ ተወላጆች ጋር በጋራ እንዲቆም የሚያሳስቡ ናቸው፡፡ በሁለተኛ …

በደሴ ከተማ በሺዎች የሚቆጠሩ የትግል ጥሪ ወረቀቶች ተበተኑ Read more »

የማያዛልቅ እያለማን ነው የወያኔ ጸሎት አደገኛ ቅጽፈት ይዞበት መምጣቱ አጣብቂኝ ውስጥ ከቶታል። ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎EPRDF‬ ‪#‎EthiopianOppositionparties‬ ‪#‎Miniliksalsawi‬ ‪#‎Change‬ Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – ወያኔ የጀመረው የስልጣን ማስረዘሚያ ስልት ራሱን እና በክሎኒግ ያባዛቸውን ጭፍሮቹን ወደ መቃብር እያወረደ መሆኑ ለአፍታ ቆም ብሎ ማስብ …

የማያዛልቅ እያለማን ነው የወያኔ ጸሎት አደገኛ ቅጽፈት ይዞበት መምጣቱ አጣብቂኝ ውስጥ ከቶታል። Read more »

አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከአቶ አባይ ወልዱ ጋር በወልቃይት ጉዳይ ጸብ ውስጥ ነኝ አሉ የወልቃይትን ማንነት በተመለከተ በተነሳው ጥያቄ ዙሪያ የአማራ ክልል ፕሬዚደንት፣ ከትግራይ ክልል ፕሬዚደንት ጋር ፀብ ውስጥ መሆናቸው ተገለጠ። ይህንን የተናገሩት ራሳቸው የአማራ ክልል ፕሬዚደንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ሲሆኑ፣ …

አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከአቶ አባይ ወልዱ ጋር በወልቃይት ጉዳይ ጸብ ውስጥ ነኝ አሉ Read more »

ምርጫ 2012 ሳይደርስ ዓረናን ማፍረስ! እንግድህ ወደድንም ጠላንም ሳልሳይ ወያነ (3rd Weyane)የሚባል ድብቅ ፓርቲ በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ ውስጥ ተመስርተዋል። የዚህ ፓርቲ የመጀመሪያው ድብቅ ኣላማው ዓረናን ማፍረስ ሲሆን፣ ሁለተኛ ኣላማው ደግሞ ትግራይ ውስጥ ብቻ የአስተዳደር ለውጥ በማምጣት የህውሃትን እድሜ ማራዘም …

ሳልሳይ ወያነ የሚባል ድብቅ ፓርቲ በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ ውስጥ ተመስርተዋል። Read more »

ሰሞኑን የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ለከፍተኛ የዉኃ እጥረት ተዳርገዋል። የአፍሪቃ ኅብረት ርዕሰ መዲና አዲስ አበባ በርካታ ዲፕሎማቶችን የምታስተናግድ ብትሆንም የመብራት ኃይልን ጨምሮ የዉኃ አቅርቦት እጥረት ችግር ላይ መዉደቅዋን አስመልክቶ የተለያዩ ዘገባዎች እየወጡ ነዉ።

የሰው ልጅ አራት የጠባይ እርከኖች አሉት ይላሉ ትውፊታውያን ሊቃውንት፡፡ በነባሩ የኢትዮጵያ ትምህርት መሠረት ጠባይና ባሕርይ ይለያያሉ፡፡ ‹ባሕርይ› ማንነት ነው፡፡ በፍጥረትህ ታገኘዋለህ፡፡ ይዘህው ትኖራለህ፡፡ አትለውጠውም፤ አታሻሽለውም፡፡ ለምሳሌ ሰውነት ባሕርይ ነው፡፡ ሰው መሆንን፣ እንስሳ ወይም ዛፍ ወይም ውኃ በመሆን አትለውጠውም፡፡ ‹ጠባይ› ደግሞ …

አራቱ የጠባይ እርከኖች – ዳንኤል ክብረት Read more »

ዓለም አቀፍ አዉቅና ያተረፉት እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ ያረፉት ከዓራት ዓመት በፊት ነበር።አዲስ አበባ ዉስጥ በመንበረ ፅባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቅፅር ግቢ የቆመዉን ሐዉልት ያስቀረፀዉ የኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለሥልጣን ነዉ

የሙስሊሞች ጉዳይ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ጋዜጠኛ ሰለሞን ከበደ በዛሬው ዕለት ከዕስር ተፈታ!! ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎Journalist‬ ‪#‎EthioMuslims‬ ‪#‎SolomonKebede‬ ‪#‎MinilikSalsawi‬ በነ አማን አሰፋ መዝገብ በ24ኛነት የተከሰሰው እና ላለፉት ከ3አመት በላይ በግፍ በማዕከላዊ፣ ቃሊቲ፣ ቂሊንጦ በጋዜጠኛነት ሞያው በመንቀሳቀሱ ብቻ ሲንገላታ የነበረው የሙስሊሞች ጉዳይ ማኔጂንግ ዳይሬክተር …

የሙስሊሞች ጉዳይ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ጋዜጠኛ ሰለሞን ከበደ በዛሬው ዕለት ከዕስር ተፈታ!! Read more »

ከጅቡቲ ወደ ኢትዮጵያ የሚጓጓዘው የእርዳታ እህል እና ማዳበሪያ ጭነት መብዛት በአገሪቱ የትራንስፖርት ዋጋ ንረት ፈጥሯል። የኢትዮጵያ መንግስት ጅቡቲ ወደብ ላይ የተፈጠረውን መጨናነቅ ለመቀነስ የበርበራ ወደብን ለመጠቀም ስምምነት ፈርሟል። ለመሆኑ የሶማሌላንድ የበርበራ ወደብ ምን ያክል ለአጠቃቀም ምቹ ነው?

በኢሕኣዴግ ማእከላዊ ኮሚቴ የሕወሓት ተሰሚነት እያሽቆለቆለ ነው::ለጄኔራሎች እና ለደህንነት ሹሞች ተማጽኖ ቀርቧል:: የኢህኣዴግ ውጥረትና የኣቦይ ስብሓት ጭንቅ ።።።።።።።።።።።።። ሰሞኑን ኢህኣዴግ በኣዲስ ኣበባ ስብሰባ ማካሄድ ጀምሮ ነበር። ስብሰባው ከተጠበቀው በላይ ውጥረት የተሞላበትና የድርጅቶች ሞቧደን የታየበት ነበር። ቡዱኖቹ ህወሓትና ደህዴን በኣንድ በኩል፤ …

በኢሕኣዴግ ማእከላዊ ኮሚቴ የሕወሓት ተሰሚነት እያሽቆለቆለ ነው::ለጄኔራሎች እና ለደህንነት ሹሞች ተማጽኖ ቀርቧል:: Read more »