ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ለባለሙያዎች ከፍተኛ ክብር አለው። ሆኖም ግንቦት 7 ነፃነት በሌለበት ሃገር ውስጥ ሙያም ሆነ ባለሙያ ክብር የማይሰጣቸው፤ በክፍያም ሆነ በማስገደድ የአምባገነኑ ፈቃድ ፈፃሚዎች እንደሚሆኑ ይገነዘባል። ነፃነት በሌለበት ሃገር ባለሙያዎች ተገደው አሊያም ለመኖር በሚል ሰበብ ገንዘብ ለሚከፍል የጊዜው አምባገነን ሥርዓት በሎሌለነት ያድራሉ። ግንቦት 7  እንዲህ ያለው ሁኔታ በሀገር ላይ የሚያደርሰውን ከፍተኛ […]

በቱኒዚያ ተቀጣጥሎ የሰሜን አፍሪቃ ሃገራት አምባገነኖችን እየጠራረገ ያለው የህዝብ አመጽ በሊቢያ ከተቀሰቀሰ ሰባት ወራት ቦኋላ ተቃዋሚዎቻቸውን አንዴ ሽብርተኞች፤ ሌላ ጊዜ ደግሞ የውጪ ቅጥረኞች ከማለት አልፈው አይጦች እያሉ ሲሳደቡ የነበሩት ሙአመር ጋዳፊ ለተቃዋሚዎቻቸው በተመኙት የአይጥ ጉድጓድ ውስጥ ለ2 ወራት ያህል ከመሸጉ ቦኋላ ከትናንት ወዲያ የሚያሳፍር ሞት መሞታቸው መላውን የአለም ህዝብ እያነጋገረ መሆኑ ታወቀ። ሙአመር ጋዳፊ በሥልጣን […]

ዘረኛውና ፋሽስቱ የመለስ ዜናዊ አገዛዝ በህዝባችን ላይ እያደረሰ ያለው  አፈናና ጭቆና ባስመረረው የአርባምንጭና አካባቢዋ ነዋሪዎችና በአገዛዙ መካከል በተነሳው ውዝግብ እስካሁን ወደ 65 የሚጠጉ ሰዎች መታሰራቸውን የኢትዮጵያ ሳታላይት ቴለቪዥን ኢሳት የዘገበ ሲሆን፤ አካባቢው በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሎአል። ኢሳት በአካባቢው ያሉትን ወኪሎቹን ዋቢ አድርጎ እንዳጠናቀረው መረጃ ከሆነ፤ውጥረቱ ይበልጥ እየተባባሰ የመጣው፤ ከሁለት ሳምንት በፊት በወረዳቸው፣ በዞናቸውና […]

“ዘረኛው የወያኔ አገዛዝ በአገራችንንና በህዝባችን ላይ እያደረሰ ያለው ሰቆቃ ሰልባ ነኝ “በሚል ሽፋን የሃሰት ማስረጃ በማቅረብ በአውሮጳና በሰሜን አሜሪካ የፖለቲካ ጥገኝነት ካገኙ ቦኋላ መልሰው በአገር ቤት ውስጥ የሚፈጸመውን የመብት አፈናና የሰብአዊ መብት ጥሰት ለማጋለጥ የሚንቀሳቀሱትን ኢትዮጵያዊያንን፣ በመሰለል ለአገዛዙ መረጃ የሚያቀብሉ ኢትዮጵያዊያንን ተከታትሎ የሚመዘግብና እንደአስፈላግነቱ ለየሚኖሩበት አገራት መንግሥታት የሚያጋልጥ  አንድ ኮሚቴ ተቋቁሞ  ከሰሞኑ እንቅስቃሴ መጀመሩን  ለዝግጅት […]

በተለያዩ አንስተኛ ጥቅማጥቅሞች በመደለል በአገራቸውና በወገናቸው ላይ ታሪክ ይቅር የማይል ወንጀል በመሥራት  የዘረኛውን አምባገነን ስርአት አገዛዝ እድሜ ለማራዘም ከፍተኛ አስተዋጽኦ ሲያደርጉ ከነበሩ በርካታ የወያኔ ሆድ አደሮች መካከል አንዱ የሆነው ያረጋል አይሸሹም ከሰሞኑ ከሥራ እንደታገደና በቁም እስር ላይ እንደሚገኝ ለዝግጅት ክፍላችን የደረሰ መረጃ አጋለጠ። ያረጋል አይሸሹም ቀደም ሲል የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፕሬዚዳንት ሆኖ ሲያገለግል ከቆየ ቦኋላ […]

ባለፈው አንድ ሳምንት ብቻ በተለያዩ ቦታዎች ተመድበው የነበሩ 14 ወጣት የኢትዮጲያ ሠራዊት አባላት የዘረኛና አፋኙን  የመለስ አገዛዝ በመቃወም ከትግራይ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ ጋር መቀላቀላቸውን የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን ኢሳት ዘገበ። እንደ ኢሳት ዘገባ  በምህፃረ-ቃል “ትህዴን” በመባል የሚታወቀው የትግራይ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ የወጣቶቹንና የወታደሮች ፎቶ አያይዞ ለኢሳት መግለጫ መላኩ የታወቀ ሲሆን በመግለጫው፤ የዘረኛው መለስን ሥርዓት ከድተው ወደ […]

በተፈጥሩአዊ መስህብነቱ በአለማችን የሚታወቀው የራሽ ደጀን ተራራ በሚገኝበት በዬዳ ወረዳ አካባቢ የሚኖሩ የሏሪ ቀበሌ ነዋሪዎችን፣ በትግራይ ክልል ውስጥ እንዲካተቱ ለማሳመን ለ7 ተከታታይ ቀናት የተደረገው ውይይት ሳይሳካ መቅረቱን ስማቸው እንዳይገለጥ የፈለጉ የአካባቢው ነዋሪዎች መግለጻቸውን የኢትዮጵያ ሳተካይት ቴሌቪዥን ኢሳት ዘገበ። እንደ ኢሳት ዘገባ የትግራይ ክልል ባለስልጣናት የቀበሌው ነዋሪዎች ወደ ትግራይ ክልል እንዲዛወሩ ተደጋጋሚ ሙከራ ቢያደርጉም፣ ህዝቡ ግን […]

የፋሽስቱ መለስ ዜናዊ አገዛዝ ከጊዜ ወደ ጊዜ በህዝብ ላይ እየፈጸመ ስላለው የሰብኣዊ መብት ረገጣ በሰፊው የተነጋገረ አንድ ታላቅ ሀዝባዊ ስብሰባ ከትናንትና ወዲያ እሁድ (16/10/2011) በእንግሊዝ አገር በሎንደ ከተማ በፍሬንድ ሃዉስ አዳራሽ ውስጥ መካሄዱን ከስፍራው የደረሰን ዜና አመለከተ። ቁጥራቸው ወደ ሁለት መቶዎች የሚገመቱ ኢትዮጵያዊያን  በተገኙበት በተካሄደው በዚህ ታላቅ ስብሰባ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የ3ኛዉ አለም […]

ወያኔ መላውን አገራችንን በመሳሪያ ሃይል በመቆጣጠር ከዛሬ 20 ዓመት በፊት ስልጣን ሲቆጣጠር የኢትዮጵያን ህዝብ በመጀመሪያው 10 አመት ቢያንስ በቀን ሶስት ጊዜ እንዲበላ እናደርገዋለን በማለት የሃሰት ተስፋ የሰጠ ሲሆን መለስ ዜናዊና ጥቂት ግብረአበሮቹ በተከተሉት የአገር ሃብት ምዝበራና ዘረፋ ምክንያት ከ20 ዓመታት የወያኔ የስልጣን ዘመናት ቦኋላ ዛሬ አገራችን ታይቶ በማይታወቅበት የድህነት አረንቋ ውስጥ እንደገባችና በቀን አንድ ጊዜ […]

እየሮጠ ጊዜው ለእኛም ሊነጋጋ፤ ታየኝ ከጋዳፊ ነፃነት ተጠጋ። ሞት ይመርጣል እንጂ ሕዝቡማ አይምርም?? የራበው ነፃነት፦ ህልም ሆኖም አይቀርም። ቃዠን ሃያ ዓመታት፦ራዕይ ጥበቃ፤ መለስ ነው ተረኛ ጋዳፊም አበቃ:: እኛም አልን በቃ፤ ብርጥቆ ከነቃ፡ አይሆንም ለዕቃ:: እናም ገዬ በቃ!!!! እንነሳ በቃ!!! ሕዝብ አይታለልም ባመፁ አይምርም፤ እንንቃ ከቅዠት ህልም ሆኖ አይቀርም። በሰበብ እንውጣ ይህ አጋጣሚ ነው ፤ መጥቷል […]

ያ ያልደረቀ ደም በመላክ ታትሞ ኢሐደግ ሸንቁሮት ደጋግሞ አሁንም በኢትዮጵያ ምድር ሰሜን ሆነ ደቩቭ ወይንም በጎንደር እሪታው አልጠፋም ያ ያልደረቀ ደም መላክ ሥለሆነ ያተመው ያነን ደም ቅን ፍርድ የማያውቀው ኢሀደግ አይሠጥም ኢትዮጵያ ባንድነት ለእግዚር አቬት ትቨል ደም መላሽ ነውና መላክ ይሁን ሌላም ለዚያ ላልደረቀ ደም ለምለም ጸጋው ደራሲ፣ ጥቅምት 12፣2004 (October 19, 2011)in objection to […]

የኢትዮጵያ የምርት ገበያ ሥራ ከጀመረ ከሦስት ዓመታት በላይ ተቆጥረዋል፡፡ በዚህ ዘመናዊ የግብይት ሥራዎች ውስጥ ግብይቱን በማስፈጸም በዋና ተዋናይነት የ…