በሽብር ወንጀል የተከሰሱት የስዊድን ጋዜጠኞች ክስ ሳይሰማ ቀረ

•  የአሜሪካ፣ የጀርመንና የፊንላንድ አምባሳደሮችና በርካታ ዲፕሎማቶች ተገኝተዋል

በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር ከዋሉ ሁለት ወራት በኋላ ጳጉሜን 1 ቀን 2003 ዓ.ም. ክስ እንደተመሰረተባቸው የፍትሕ ሚኒስቴር ካስታወቀ በኋላ፣ ክሳቸው በትናንትናው ዕለት እንደሚሰማ ቢገለጽም ሳይሰማ ቀርቷል፡፡