በኢትዮጵያ ጉዳይ ሰፊ ጥናት ያካሄዱና የተለያዩ መጽሃፎችን የጻፉ ታዋቂው የፖለቲካና ታሪክ ምሁር ጆን ማርካኪስ ፣ ህወሀት መራሹ አገዛዝ ከደርግና የሀይለስላሴ ስርአቶች ውድቀት ለመማር ባለመቻሉ፣ እሱም በተራው ወደ ውደቀት እየተጓዘ ነው አሉ
ለረጅም ጊዜ በአገራችን ፖለቲካ ሰፊ ጥናት ያካሄዱት ጆን ማርካኪስ “ኢትዮጵያ፣ ዘ ላስት ቱ ፍሮንቲየርስ” የሚለውን አዲሱን መጽሀፋቸውን ለማስተዋወቅ በለንደን ቻትሀም ሀውስ በተገኙበት ወቅት ህወሃት መራሹ የመለስ ዜናዊ አገዛዝ ስልጣን በበቂና ተጨባጭ በሆነ መልኩ ወደ ክልሎችና ወደ ወረዳዎች ለማስተላለፍ ባለመቻሉ፣ የመፈረካከስ አደጋ ተጋርጦበታል ብለዋል። በዚህ ስነሥርዓት ላይ ተመሳሳይ ንግግር ያደረጉት ሌላው ታዋቂ ምሁር ፕሮፌሰር ክርስቶፈር ክላፋም […]