ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በመምህር የኔሰው ገብሬ አስደንጋጭ መስዕዋትነት ምክንያት የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን ይገልፃል። የመምህር የኔሰው ገብሬ መሰዋት ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጆቹና ለዳውሮ ዞን ነዋሪዎች ብቻ ሳይሆን ለኢትዮጵያዊያን ሁሉ መሪር ሃዘን ነው። በደቡብ ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግሥት በዳውሮ ዞን የሚገኘው የዋካ ከተማና አካባቢው ህዝብ በአስተዳደር በደል፣ በኑሮ ውድነትና በወረዳ አከላለል መነሻነት ከወር በላይ የዘለቀ […]

ላለፉት 20 አመታት በአገራችንና በህዝባችን ላይ በፈጸመው ወንጀል ተረብሾ ህዝብ በማሸበር ላይ የሚገኘው የመለስ ዜናዊ አገዛዝ የአንድነት ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበርና የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ በሆነው አንዷለም አራጌ የክስ መዝገብ በሽብርተኝነት ወንጀል የከሰሳቸው 24 የፖለቲካ ፓርቲ የአመራር አባላት፣ ጋዜጠኞች እና የፖለቲካ አክቲቪስቶች የክስ ቻርጅ በመለስ ዜናዊ ቀጭን ት ዕዛዝ በሚዘወረው የከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሦስተኛ ወንጀል […]

ዘረኛውና አምባገነኑ የወያኔ አገዛዝ በህዝብ ላይ እያደረሰ ያለው ግፍና በደል ልኩን አልፎ ከሚሸከመው አቅም በላይ እየሆነ በመምጣቱ ራሱን በቤንዚን አርከፍክፎ ህይወቱን የሰዋውን መምህር የኔሰው ገብሬን የህይወት መስዋዕትነት ለማድበስበስ ወያኔ ሆን ብሎ የፈጠረው ”አይምሮው ጤናማ አልነበረም” የሚለው ሃሰተኛ ማስተባቢያ አገዛዝ ያለበትን የወረደ የዝቅጠት ደረጃ በግልጽ የሚያመላክት ነው በማለት አስተያየት ሰጪዎች ተናገሩ። በዳውሮና አካባቢው የሚገኙና ስማቸው ፍጹም […]

የኢትዮጵያ ጦር ወደሶማሊያ ግዛት ዘልቆ መግባቱን ተከትሎ በአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት የአፍሪካ ተጠሪ የሆኑት ጆኒ ካርሰን ኢትዮጵያ ሶማሊያን ዳግም መውረሯ ፍጹም ትክክል አይደለም ሲሉ ተናገሩ። ጆኒ ካርሰን ይህን የተናገሩት ማክላቺ ከተባለው ጋዜጣ ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ነው። ካርሰን ኢትዮጵያ ከአራት አመት በፊት ሶማሊያን በመውረር ለሁለት አመታት ያክል በአገሪቱ ውስጥ ብትቆይም፣ በመጨረሻ አልሸባብን ከመፍጠር በስተቀር ያመጣቸው […]

ህወሃት ለሁለት በተከፈለበት ወቅት ከነ አቶ ተወልደ ቡድን ጋር በመወገኑ ከሥልጣን ተባሮ የነበረውና ቦኋላ ንሰሃ ገብቶ የመለስ ዜናዊን ቡድን በመቀላቀል ድህረ ምርጫ 97 የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ሆኖ ለመሾም የበቃው ኩማ ደመቅሳ በከተማው ውስጥ እየታየ ያለው የኑሮ ውድነት ከባድ ፈተና ሆኖብናል በማለት ከትናንት በስቲያ ማክሰኞ ለተሰበሰበው የወያኔ ፓርላማ አስታወቀ። እንደ ኩማ ደመቅሳ አነጋገር ከተማውን ለከባድ […]

የአረመኔውን የወያኔ አገዛዝ ግፍና በደል በመቃወም ራሱን በቤንዚን አርከፍክፎ በማቃጠሉ ኢትዮጵያዊው ቡአዚ የሚል ቅጽል ስም እየተሰጠው ያለው አርበኛው መምህር የኔሰው ገብሬ በተለይም በሃገር ውስጥና ከሃገር ውጭ ባሉት ኢትዮጵያዊያን ከፍተኛ የመወያያ አጀንዳ ሆኖ ሲሰነብት በርካታ የሬዲዮ ፕሮግራሞችና የመረጃ ድረገጾች ሰፊ ሽፋን ሰጥተው ሲዘክሩት ሰንብተዋል። በሃገር ውስጥ በተለይም በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ በርካታ ወጣቶች የመምህር የኔሰው ገብሬ […]

የዘረኛውና አረመኔው የወያኔ አገዛዝ የሚያደርስባቸውን ግልጽና ስውር አፈና ተቋቁመው ህትመት ላይ ቀርተው ከነበሩ ጋዜጦች መካከል የአውራ አምባ ታየምስ ጋዜጣ ዋና መስራችና አዘጋጅ የነበረው ዳዊት ከበደ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በጋዜጠኞች ላይ የተከፈተው አዲስ ዙር መንግሥታዊ ሽብርና ዛቻ ለህይወቱ አስግቶት አገር ጥሎ መኮብለሉን ኢሳት በትናትናው የዜና እወጃ ፕሮግራሙ ዘግቦአል። የጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ አገር ጥሎ መሰደድ ካለፈው ሳምንት […]

በአገራችን የተዘረጋው የስልክና የኢንተርኔት አቅርቦት ወያኔ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ለመገደብና ዜጎች ስለአገራቸውና ስለሚያስተዳድራቸው መንግሥት በቂ መረጃ እንዳያገኙ ለመከላከል እንዲያስችል ተደርጎ የተዋቀረ በመሆኑ ፤ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ የሆኑ ተቀማጭነታቸው በአዲስ አበባ የሆነ አለም አቀፍ ድርጅቶችና ዲፕሎማቲክ ሚሽኖች ጭምር እያስመረረ መምጣቱን ባለፈው ሳምንት ይፋ የሆነ ዜና አረጋገጠ። በወያኔ አገዛዝ ቁጥጥር ሥር የሆነው የኢትዮ ቴሌኮም ኮርፖሬሽን ከደንበኞቹ ጋር […]

ይህ የመጨረሻው ክፍል ነው። የመጨረሻውን ክፍል ከማቅረቤ በፊት የጽሁፌን አሃድ በምስጋና ልጀምር። ሁልጊዜ በህሊናዬ የነበረውን… ነገር ግን ለመጻፍ ጊዜ አጥቼ በነበረበት ወቅት ብርታት ለሆነኝ የእውነት እና የፍቅር አምላክ ምስጋና ይጋባው። ምንም እንኳን ባላነበውም ስለጽሁፉ በሰማሁ ጊዜ… ይህንን ታሪክ ለመጻፍ ምክንያት የሆነኝን የኢትዮ ሚዲያ ባለቤት አብርሃ በላይን በንፁህ ልቤ አመሰግነዋለሁ። ይህንን ጽሁፍ በነጻ ህሊና በድረ ገጾቻችሁና […]

የአውራምባ ታይምስ ጋዜጣ ባለ አክስዮን ድርሻና የጋዜጣው ማኔጂንግ ኢዲተር ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ ከሀገር መሰደዱን የመረጃ ምንጮቻችን ገለጹ፡፡ እንደ መረጃ ምንጮቻችን ገለጻ ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ ሊሰደድ የቻለው “ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ገጥሞት እንደሆነ” ይገልጻሉ፡፡ ምንጮቻችን እንደሚሉት “ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ ምርጫ 97 ተከትሎ ከታሠሩት ጋዜጠኞች መካከል አንዱ ነበር፡፡ እድሜልክ ተፈርዶበት በይቅርታ ተፈቶ ነበር፡፡ በጋዜጣ በሚጽፋቸው ጽሑፎች ይቅርታው […]

“ፍትህና ዲሞክራሲ በሌለበት አገር አልኖርም” በሚል ምክንያት ራሱን በእሳት አቃጥሎ በገደለው ጀግናዉ መምህር የኔሰው ገብሬ ላይ የመለስ መንግሰት የከፈተዉ የስም ማጥፋት ዘመቻ የህዝብ ቀልብ አልሳበም። ክህደት፤ ዉሸትና ንቀት የአምባገነኑ መንግስት ተብዬዉ መለያ ጠባይ መሆኑ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ዘንድ የተሰወረ አይደለም። ከዚህ አሳፋሪና አስነዋሪ ባህሪይ ጋር ከጠ/ሚር መለስ ጀምሮ እገሌ ከእገሌ ሳይል ሁለት አስርተ አመታትን ያስቆጠረ፤ እጅግ […]

“ፍትህና ዲሞክራሲ በሌለበት አገር አልኖርም” በሚል ምክንያት ራሱን በእሳት አቃጥሎ በገደለው ጀግናዉ መምህር የኔሰው ገብሬ ላይ የመለስ መንግሰት የከፈተዉ የስም ማጥፋት ዘመቻ የህዝብ ቀልብ አልሳበም። ክህደት፤ ዉሸትና ንቀት የአምባገነኑ መንግስት ተብዬዉ መለያ ጠባይ መሆኑ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ዘንድ የተሰወረ አይደለም። ከዚህ አሳፋሪና አስነዋሪ ባህሪይ ጋር ከጠ/ሚር መለስ ጀምሮ እገሌ ከእገሌ ሳይል ሁለት አስርተ አመታትን ያስቆጠረ፤ እጅግ […]