በማለዳው አነሳሴ እንደለመድኩት በስደቱ ዙሪያ ገብ የሆነውንና እየሆነ ስላለው ልሞነጫጭር ፣ ልብተከተክ አልነበረም … ከትናንት ከትናንት በስቲያ ጠዋት ፣ረፋድና ተሲያት ፣ ምሽት ፣ በደረቁ ሌሊት እያቅበጠበጠኝ ስልኬን አንስቸ ወደ ሊቢያ ዋና ከተማ ትሪፒሊ ወደ ማትረጋው ቢንጋዚና ሚስራታ የደዋወልኳቸውን ስልኮች ተመለከትኩ ። ከወዳጆቸ የደረሱኝን ሁለት ሶስት አድራሻዎችና እዚህ ጅዳ ያለ ሊቢያዊ ጓኛየ አድራሻቸውን አፈላልጎ የሰጠኝን ሌሎች […]

በነገው እለት በመስቀል አደባባይ የሚደረገው ሰልፍ ላይ ከአንድ ሚሊዮን ህዝብ በላይ ይወጣል ተብሎ ይገመታል። ከአዲስ አበባ እና አካባቢው ያለ ህዝብ በነቂስ እንደሚወጣ የሚደርሱን መረጃዎች ይተቁማሉ። ይህንን ሰላማዊ ሰልፍ ሰማያዊ ፓርቲ እና አንድነት ፓርቲንን ጨምሮ በርካታ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ደግፈውታል። አላማው በኢትዮጵያውያን ላይ አይሲስ የፈጸመውን ግድያ ለመቃወም ነው ተብሏል። በዛሬው እለት የታፈነው የአኢትዮጵያ ህዝብ አደባባይ ወጥቶ ድምጹን […]

‹‹. . . ዓይኔ በእንባ ደከመ፣ አንጀቴም ታወከ፡፡ ስለ ወገኔ ሴት ልጅ ቅጥቃጤ አንጀቴ በምድር ላይ ተዘረገፈ፡፡ አቤቱ የሆነብንን አስብ፣ ተመልከት ስድባችንንም እይ . . .፡፡›› ሰቆ. ፪፣፲፩ ፤ ፭፣፩ ፡፡ ይህን ቃል የተናገረው በመጽሐፍ ቅዱስ ምሁራን ዘንድ ‹‹አልቃሻው፣ ባለ ሙሾው ነቢይ›› በመባል የሚታወቀው አይሁዳዊው ነቢዩ ኤርምያስ ነው፡፡ ይህንን ነቢይ እንዲህ እንደ ርኁሩኋ እናት አንጀቱን […]

ዛሬ ሚያዚያ 13 ቀን በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዉያን በአዲስ አበባ ሰልፍ አድርገዋል። ህዝቡ በራሱ አነሳሽነት ነበር ሰልፍ የወጣው። የተወሰኑ ቦታዎች የወያኔ ታጣቂዎች ሰልፈኛዉን ደብድበዋል። በብዙ ቦታዎች መንገድ እየዘጉ ሰልፈኛው እንዳያልፍ ያከላከሉበትም ሁኔታ ነበር። ያው የታወቀ ነው። እነሱ የሚበረቱት ሁልጊዜ ሰላማዊ ሰዎች ላይ ነው። የሕዝቡን ስሜት፣ ሐዘን እና ንዴት የተረዳው ወያኔ፣ ነገ «በበመስቀል አደባባይ ሰልፍ ይደረጋል» ብሎ […]

በጎንደር ከተማ የሚገኙ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች፣ የመንፈሳውያን ወጣቶች ማኅበራትና የማኅበረ ቅዱሳን የጎንደር ማዕከል አባላት በላኩት መግለጫ በአሸባሪውና አረመኔው አይሲስ በኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች ላይ የተፈጸመውን ጭካኔ አውግዘዋል፡፡ በመግለጫው ላይ እንደተገለጠው ‹‹‹‹ISIS›› የሽብር ቡድን 30 ኢትዮጵያውያንን ክርስቲያን በመሆናቸውና ሃይማኖታችንን አንቀይርም በማለታቸው ርህራሄ በጎደለው ሁኔታ አንገታቸውን በሰይፍ በመቅላትና በጥይት በመደብደብ የፈጸመው ዘግናኝ ተግባር ኢትዮጵያዊነትን የሚፈታተን፣ ታላቅ ኀዘንን በክርስቲያኖች ላይ ፈጥሯል፡፡›› ብሏል፡፡ በማያያዝም እንደ ቤተ ክርስቲያን ልጅነታቸው ሊደረጉ ይገባል ያሏቸውን አራት ሐሳቦች ለሀገረ ስብከቱ አቅርበዋል፡፡ የመግለጫውን ሙሉ ቃል ቀጥሎ መመልከት ይቻላል፡፡ ይህንን በመጫን መግለጫውን ያንብቡ

ክንፉ አሰፋ

Eyassu Yukunualem and Balecha Belete, ISIS massacred them in Libya. የአይሲስ ሰለባዎቹ እያሱ ይኩኑዓምላክ እና ባልቻ በለጠ

ወጣት እየሩሳሌም አስፋው እንደወትሮው ቴሌቭዥን ከፍታ እየተመለከተች ነው። ብርቱካንማ ቱታ የለበሱና፣ እጆቻቸው የፍጢኝ የታሰሩ ወጣቶች በአሸባሪዎች ታጅበው ሲጓዙ ያሳያል ቴሌቭዥኑ። ለእርድ ከተሰለፉት ወገኖች ፊት ለፊት ላይ ያለው የእየሩሳሌም ወንድም ነበር። ሌላኛው ወንድሟም ከበስተኋላ ተሰልፏል። እያሱ ይኩኑዓምላክ እና ባልቻ በለጠ፤ ሁለቱም በዚያች ቅጽበት ክቡር ነብሳቸውን በግፈኞች ተነጠቁ። ከሁሉም የከፋ የሚያደርገው ደግሞ ወዳጅ ዘመዶች የነዚህን ወገኖች አስከሬን አግኝተው ለመቅበር እድል እንኳን ባለማግኘታቸው ነው። የሁሉንም ልብ የሚሰብር ክስተት!

ሙሉውን አስነብበኝ …

Senakriem Mekonnen. ሰናክሬም መኮንንክንፉ አሰፋ

“አሜሪካ ይዞን ከሄደ በኋላ በዋሽንግተን ዲሲ አንድ የገበያ አዳራሽ (ሞል) ውስጥ ጥሎን ጠፋ … ፖሊስ ሁለት ግዜ ይዞን ነበር … በርሃብ ተቀጣን፣ ርሃብ ጸንቶበት ሆስፒታል የገባም ልጅ አለ። … በየሬስቶራንቱ እየዞርን ለምነናል።” ይላል አንድ የ11 ዓመት ሕጻን ሳይንቲስት። ሂውስተን ቴክሳስ ያሚገኘውን ናሳ የጠፈር ምርምር ተቋም ለመጎብኘት ከአዲስ አበባ ሄደው ነው አስሩ ሕጻናት ዲሲ ላይ የሚሰቃዩት።

ሙሉውን አስነብበኝ …

በእኔ ዲ/ን አብርሃም ወርቁና ዲ/ን ዮሴፍ አባይ አስተባባሪነት ስድስት ብፁአን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን ይዘን በሰማዕታቱ በነኢያሱንና ባልቻ መኖርያቤት ከቀኑ 10:45 ሄደን አፅናንተን ተመልሰናል ቅዱስ ፓትርያርኩን ይዘን ለመሄድ ያደረግነው ሙከራ በኘሮግራም መደራረብ ምክንያት አልተሳካም ነገር ግን ልጆች ናቸው ብለው ሰሰይንቁን ማፅናናት ኃላፊነት አለብን ብለው ጥሪአችንን አክብረው 1ኛ/ብፁዕ አብነ ሉቃስ የሲኖዶሱ ዋና ፀሐፊና የሁመራ ሀ/ስ ሊቀ ጳጳስ […]

ሚያዝያ ፲፫(አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሊቢያ በአሸባሪዎች ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ ለተገደሉት ወጣቶች ኢያሱ ይኩኖአምላክና ባልቻ በለጠ ቤተሰቦች ሀዘናቸውን ለመግለጽ ከተለያዩ አቅጣጫዎች  በማምራት ላይ የነበሩ ወጣቶች ስሜታቸውን መቆጣጠር ተስኖአቸው ተቃውሞአቸውን ሲያሰሙ ውለዋል። በሺ የሚቆጠሩ ወጣቶች መንግስትን የሚያወግዙ መፈክሮችን እያሰሙ ወደ ቤተመንግስት በማቅናት ላይ እያሉ ሂልተን ሆቴል አካባቢ በብዛት የተሰባሰቡት የፌደራል ፖሊሶች አስቁመዋቸዋል። ወጣቶች …

ሚያዝያ ፲፫(አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ድምጻችን ይሰማ፦”ኢ–ሰብአዊነትንና ሽብርን ደግመን እናውግዝ! ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንን እንታደግ!”በሚል ርእስ ባወጣው መግለጫ በደቡብ አፍሪካ ኢትዮጵያውያን እና ሌሎችም አፍሪካውያን ዜጎች ላይ አሰቃቂ የግድያ ወንጀል እየተፈጸመባቸው እንደሚገኝ በመጥቀስ፤ ሰቅጣጩ የጭካኔ ምግባር አፍሪካዊያን ላይ በአፍሪካዊያን የሚፈፀም መሆኑ ደግሞ ይበልጥ አሳዛኝ ያደርገዋል ብሏል። ከአስርት ዓመታት በፊት ምእራባዊያን ደቡብ አፍሪካዊያን የሚያደርጉትን የፀረ-አፓርታይድ ትግልና …

አንዱዓለም ተፈራ

Revolution. መማር እንችላለን ወይ?

ከ፲፱፻፷፮ ዓመተ ምህረቱ የየካቲት ሕዝባዊ መነሳሳት ጀምሮ፤ ለመብት፣ ለነፃነትና በሰላም ሠርቶ ለመኖር ያለው ትግል፤ ሳያርፍ በተከታታይ አሁንም እየተካሄደ ነው። በነዚህ ባለፉት ፵ ዓመታት፤ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን፤ በትግሉ ከሕዝብ ጎን ተሰልፈው ሕይወታቸውን ሠጥተዋል። ቆራጥ የሕዝብ ጠበቃዎች ወጥተዋል፤ ሕይወታቸውን ላመኑበት ዓላማ በቆራጥነት በመሥጠት በጀግንነት ተቆጥረዋል። ትውልድ አልፎ ትውልድ ተተክቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ሚያዝያ ፲፫(አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ቢቢሲ የአለማቀፍ የስደተኞች ኮምሽነር ቃል አቀባይን  ጠቅሶ እንደዘገበው ሰሞኑን በሜዲትራኒያን ባህር በሰጠመችው ጀልባ ከነበሩ ከ800 በላይ የተለያዩ አገር ዜጎች መካከል 350 ኤርትራውያን ናቸው ተብሎ እንደሚገመት ገልጾ፣ ቀሪዎቹ ደግሞ ከኢትዮጵያ፣ ሶሪያ፣ ሶማሊያ፣ ሴራሊዮን፣ ማሊ፣ ሴኔጋል፣ ጋምቢያ፣ አይቮሪኮስት እና ባንግላዲሽ የመጡ መሆናቸውን ዘግቧል። አይ ኦ ኤም የተባለው አለማቀፍ የስደተኞች …

Donald N. Levine. ፕሮፌሰር ዶናልድ ሌቪን ፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም ነጻነት ለሀገሬ)

ፕሮፌሰር ዶናልድ ሌቪን፡ የልሂቃን ሁሉ ልሂቅ

ፕሮፌሰር ዶናልድ ሌቪን በዚህ ባሳለፍው ጥር ወር ኢትዮጵያን ለመጎብኘት የነበራቸው የረዥም ጊዜ ዕቅድ በህመማቸው ምክንያት የተጨናገፈ መሆኑን በኢሜይል መልዕክት ልከውልኝ ነበር። በዚያ አስበውት በነበረው ጉብኝት የሚከተሉትን ሶስት ዓላማዎች የማሳካት ዕቅድ ነበራቸው። እነርሱም፣

ሙሉውን አስነብበኝ …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

በነገው የአ/አበባ ነዋሪዎች የመስቀል ዐደባባይ ሰልፍ ቤተ ክርስቲያን መልእክቷን ታስላልፋለች ራሱን አይ ኤስ እያለ የሚጠራው አሸባሪ ቡድን፣ በንጹሐን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልጆች ላይ በፈጸመው ግፍ ለገደላቸው ወገኖቻችን በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጸሎተ ፍትሐት እና ጸሎተ ወንጌል ለማድረግ ለነገ ከጠዋቱ 2፡30 – 4፡30 የወጣው መርሐ ግብር ለኀሙስ ጠዋት፣ ሚያዝያ 15 ቀን 2007 ዓ.ም. […]

የኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሊቢያና ደቡብ አፍሪቃ ዉስጥ ሰሞኑን በግፍ የተገደሉ ኢትዮጵያዉያንን ለማሰብ የሠወስት ቀን ብሕራዊ ሐዘን አወጀ።ምክር ቤቱ ዛሬ ባደረገዉ ሥብሰባዉ በሁለቱም ሥፍራዎች የተፈፀሙትን ግድያዎች አጥብቆ አዉግዟል።

ራሱን እስላማዊ መንግስት «አይ ሲስ» ብሎ በሚጠራው አክራሪ ቡድን ሊቢያ ላይ ከተገደሉት ኢትዮጵያውያን መካከል የእያሱ ይኩኖአምላክ እና ባልቻ በለጠ ቤተሰቦች አዲስ አበባ በተለምዶ ቂርቆስ በሚባለው ሰፈር ድንኳን ጥለው ሃዘን ላይ ናቸው።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስትያን ሲኖዶስ ዛሬ ሚያዝያ 13/2007 ባወጣው ባለ9 ነጥብ መግለጫ፡- በሊቢያ ውስጥ በተደረገው አሰቃቂ ድርጊት ቤተ ክርስቲያንኒቱ እጅግ ያዘነች መሆኗን ገልጾ በዚህ ግድያ ውስጥ ግን ሟቾቹ ሰማዕት በመሆን የተጠቀሙ ጀግኖች እንጂ ተጐጂዎች እንዳልሆኑም ጭምር ማሰብ እንደሚገባ ገልጿል፡፡ በነገው ዕለት በአዲስ አበባ የሚገኙ ገዳማት እና አድባራት በአጠቃላይ ከጠዋቱ 2 ሰዓት ጀምሮ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በመገኘት ጸሎተ ፍትሐት እንዲያደርሱ ጥሪ አስተላለፏል፡፡ በመላው ዓለም የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናትም ሁሉ ከሚያዚያ 14 ጀምሮ ለ7 ተከታታይ ቀናት በሁሉም አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ምህላ እንዲያረግ ቅዱስ ሲኖዶስ አያይዞ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ አክሎም ለሟቾቹ የሰማዕትነት ክብርን በቀኖናው መሠረት መስጠት እንዲቻል ቤተሰቦቻቸውን የሚያውቁ ምዕመናን ፎቶአቸውንና ስማቸውን አሰባስባው ለቅዱስ ሲኖዶስ እንዲያቀርቡ አዝዟል፡፡ ሙሉ የሲኖዶስን ሙሉ መግለጫ ለማንበብ ከሥር ካለው ምስል ያንብቡ ወይም እዚህ ጋር በመጫን (link) ዳውንሎድ ያድርጉ፡፡ *********** — More from Horn Affairs AmharicSendek | የጁነዲን ሳዶ ባለቤትን ጨምሮ 29 ሰዎች በሽበርተኝነት ተከሰሱETV | የግንቦት 7ቱ አንዳርጋቸው ፅጌ በየመን ተይዞ ለኢትዮጵያ ተላልፎ ተሰጥቷልማዕተብም መስቀልም በግለሰቦች ነፃነት ውስጥ የሚካተት ነው – ዶ/ር ሺፈራው ተክለማርያምየዩኒቨርስቲዎች ሃይማኖታዊ ስነስርአትና አለባበስ ደንብን በመቃወም በሽብር የተሳተፉ ግለሰቦች ጥፋተኛ ተባሉሕገ-መንግስት እንዲያከብሩ ሲመከሩ – በሃይማኖታችን ጣልቃ ተገባ ይላሉ (ሚ/ር እውነቱ ብላታ)ማዕተብ ከሂጃብ

http://www.eaglewingss.com/
እስከመቼ ነው?
ዛሬ ውስጤን የሚያናውጠው ማዕበል፡ ከጥቂት ግለሰቦች በስተቀር የአብዛኛውን ኢትዮጵያዊ አእምሮ እንደ ትንሽ ታንኳ እያናጋ፡ አንዴ ከራሱ ምናብ የሃሳብ ቋጥኝ ጋር፡ አንዴም ከአምላክ ምስጢራዊ ፈቃድ ዓለት ጋር እያጋጨው እንዳለ ይገባኛል። ታዲያ፥ ስሜት በቀላሉ ሰብረው በማያመልጡት የምሬት ሠራዊት ሲከበብ፣ ተስፋ በድቅድቅ የሞት ጭጋግ ውስጥ ሲደበቅ፣ ለነፍስና – ለስጋ፡ ለአእምሮና – ለእጅ፡ እንደ መፃፍ ያለ ከባድ ህመም የለም። ልብ ብርቱ በሆነ የሀዘን ጦር ሲቆፈር፡ ጉልበትን ሰብስቦ ሃሳብን አምጦ መውለድ አይደለም፡ እውነታንም ቁጭ ብሎ መታዘብ ይከብዳል። ያኔ፥ እፅፋለሁ ላለ ጣት፡ ብዕር እንደ ብረት ለሽክም ይከብዳል። ቢሆንም ግን፡ የቆሰለው አእምሮዪ በተደጋጋሚ አንድ ጥያቄ ይጠይቀኛልና፡ በዝምታ ከማስታምመው – ይኸው ተንፍሼ ልገላገለው ሞከርኩ።

የማከብርህ ኢትዮጵያዊ ወገኔ፥ ተፈጥሮ ሳትሰስት፡ ከዓለም ሁሉ አብልጣና አድልታ የሰጠችንን የዘፍጥረት እና የስልጣኔ ብኩርና፡ እንደ ኤሳው ለሆዳችን – ለምስር ወጥ – ሸጠን፡ እስከመቼ ነው እንደ ዝቃጭ እንደ አተላ፡ ህይወታችን ክብር፣ ሞታችን ዝክር የሚያጣው? እስከመቼ ነው ዘረኞች የዘሩልንን አዝመራ ስናጭድ – ስንውቃ ውለን፡ ሲመሽ ምርት ሳይሆን ምሬት ሰብስበን ወደ ቤታችን የምንገባው? እስከመቼ ነው ሰሜን ጫፍ ተቀምጠው፡ ከደቡብ ጫፍ የተወረወረ ጠጠር ሊስታቸው እስከሚሳነው ድረስ እየሰፉ እና እየሰቡ ያሉት የፖለቲካ መሪዎቻችን፡ ከአፍንጫችን በላይ ያንጠለጠሉልንን የነፃነት ካሮት ላንደርስበት-ላንበላው አህያ ሆነን ስንጋልብ እና ስን’ጋለብ ዘመን የሚያልፈው? እስከመቼስ ነው ምስኪኑ ወገናችን ደረቱ ላይ ተደግኖ የተተኮሰበት የመሳሪያ ጥይት እስኪስተው ድረስ በየሰከንዱ-በየደቂቃው በረሃብ እየከሳ እና እያነሰ፡ በየበራሃው በኖ ተኖ፣ በየባህሩ ዝሎ ሰጥሞ የሚያልቀው?

በወንደሞችህ የግፍ ሞት ልብህ የተሰበረው ኢትዮጵያዊ ወገኔየነፃነት ትግል እኮ ዓላማ እንጂ ባህል አይደለም። ተጀምሮ ማለቅ፤ መነሻ አምድ፣ መደምደሚያ ግብ ሊኖረው ይገባል። የባርነት ሰንሰለት አልበጠስ ብሎ ከከረረ፡ አልቋጭ ብሎ ከረዘመ፡ እንደ ወግ-ባህል ከዘመን ዘመን፣ ከትውልድ ወደ ትውልድ ከተሻገረ፡ ቆም ብሎ ማስተዋል፤ መሪ ተመሪን መቃኘት ግድ ይላል።

ዛሬ በኣራቱም የዓለም ማዕዘናት ህዝባችን እየቆጠረ ላለው ፍዳና ሰቆቃ መነሻ ምክንያቱ ፖቲካዊ እንጂ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ አንዳልሆነ ለመረዳት፡ ማንም የርዕዮተ ዓለም ፈላስፋ አሊያም የምጣኔ ሃብት ሊቅ መሆን አይጠበቅበትም። ፖለቲካዊ ችግር ደግሞ ከምንም በላይ ፖለቲካዊ መፍትሔን ይሻልና፡ ፖለቲካችን እንዴት እና ወዴት ነው? ዜጎቻችን ትላንት- ሳውድ ዓረቢያ፡ ዛሬ- የመንደቡብ ኣፍሪካሊቢያ ላይ እየተጋቱ ያሉትን መከራ ከምንጩ ለማድረቅ፣ ነገም ተመሳሳይ ጥፋት ካይሮ ላይ ከመከሰቱ በፊት ችግሩን ከችካሉ ለመንቀል ልምን ተሳነን? ጉድለታችን የመሪ? የተመሪ? ወይንስ አጠቃላይ የድርጀታዊ መዋቅር እንከን ነው የሚለውን መጠየቅ እና በአፋጣኝ መመለስ ወቅቱ ይመስለኛል። እርግጥ ነው ዛሬም ቢሆን፡ ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጀቶች ከብሉይ ኪዳን የመማፀኛ ግንብ በተለየ መልኩ መዋቀርና ተቀዳሚ ዓላማቸው ተገዳዩን ማትረፍ እንጂ ገዳዩን ማቀፍ መሆን የለበትም ብዪ አምናለሁ። ዘራፊው ዘርፎ፣ ገዳዩም ገድሎ እጁ ሲዝል እና ሲደከም፡ ሀጢያቱን ለማስተሰረይ፣ ከህዝብ ለመታረቅ ዘሎ የሚቀላቀለው እና የሚያንቀላፋበት ጎራ – እንደ እኔ ግለሰባዊ እምነት- ወህኒ-ቤት እንጂ አንድነት፣ መድረክ፣ ሸንጎ ወይንም ግንቦት ሰባት መሆን ያለበት አይመስለኝም።

አምላክህ እግዚአብሔር ርስት አድርጎ በሚሰጥህ በምድርህ መካከል ሦስት ከተሞችን ለራስህ ትለያለህ። ነፍሰ ገዳይ ይሸሽባቸው ዘንድ ወደ እነርሱ የሚወስደውን መንገድ ታዘጋጃለህ … (ኦሪት ዘዳግም / ምዕራፍ 19 : 2)

ላለፉት በርካታ አመታት እንደታዘብነው ግን፦ ሀገር እንደ ቡሄ ሙልሙል ገምሶ፣ ህዝብ እንደ አክርማ ቀጭቶ፣ ዘርፎ እና አዘርፎ የበቃው ባለስልጣን መሽሽጊያው አንድም ቤተ-መቅደስ ኣለበለዚያም የተቃዋሚው ድርጅት ነው። ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች፡ ወንጀለኞች ሰይጣናዊ ባህሪያቸውን በሃይማኖታዊ ጠበል አርጥበው፣ በተቃዋሚ ፎጣ አድርቀው በአዲስ ካባ ብቅ ሲሉ እንደ ቅዱስ መላዕክት የሚሰገድላቸው የአይሁዳውያኑ የመማፀኛ ቅጥር መሆናቸው እስካላበቃ ድረስ፡ የነፃነት ኣላማችን ዕውን የሚሆነው፣ የመከራችን ቋጠሮ በዘላቂነት የሚፈታው – በዕድል እንጂ በትግል እንዳልሆነ መጠርጠር የለብንም።

ከረሃብ ወደ ስድብና ውርደት ተመሳሌነት ያሻገሩህ ኢትዮጵያዊ ወገኔ፥ ጽሁፌን ከማጠቃለሌ በፊት ዛሬም እንደ ትላንቱ የማሰምርበት እውነት ቢኖር፦ ህዝባችን ከእንሰሳ ባነሰ ክብር በየመንገዱ ተቀጥቅጦ ሲገደል ዝም ብሎ ከማየት የከፋ የወገን በደል የለምና፡ እንደ ዜጋ የሚጠበቅብንን ሁሉ በማድረግ የተረፉትን ለመታደግ፣ የረገፉትንም ቤተሰቦች ለማፅናናት ዛሬ! አሁን! ቃል ብቻ ሳይሆን ከትግሉም መሃል መግባት ይኖርብናል።

መፈራረሳችን፣ ስድባችን፣ መዋረድና መታረዳችን ዓላማቸው ብቻ ሳይሆን አለማቸውም ለሆነው ጎጠኞች፡ የሃዘን ሲቃችን ብሔራዊም ባይሆን ጎሳዊ መዝሙራቸው ነው። የድረሱልን ለቅሶና ጩኸታችን፡ “አከርካሪውን ሰበርነው – ጥርሱን አወለቅነው” ብለው ለተሳለቁብን ዘረኞች፡ የዓላማቸውን መሳካት የሚያበስር ደወል፣ የግባቸውን ቀጣይነት የሚያረጋግጥ ቃጭል ከመሆን ባሻገር ፋይዳ እንደሌለው ተረድተን፤ ራሰን፣ ወገንን እና ሃገርን የማዳን ዘመቻውን ከራሳችን በራሳችን መጀመር ብልህነት ነው። የዓባይን ውሃ ለኣባዮቹ ትተን፡ የወገናችንን፣ የአዛውንት እናትና አባቶቻችንን የኣይን ፍሳሽ- ዕንባ – ለመገደብ፡ የትግል ቦንድ (ውህደት) መፍጠሩ ከመቼውም በላይ አስፈላጊ የሆነበት ወቅት ላይ ደርሰናልና ወንድ – ሴት፣ እስላም – ክርስቲያን ሳንል በተግባር በስነ-ምግባር እንተባበር።

ኤግል-ዊንግስ-ሶሳይቲ በደቡብ ኣፍሪካ፣ በየመን፡ አንዲሁም በሊቢያ ህይወታቸው ለጠፋው ዜጎቻችን የተሰማንን ከፈተኛ ሃዘን ስንገልፅ፡ ለቤተሰቦቻቸውም አምላካዊ መፅናናትን እየተመኘን ነው። ችግሩ ከመሠረቱ አልተወገደምና፤ በኣሁኑ ወቅትም በአደጋ ወስጥ ላሉት ወንድሞችና እህቶቻችን፡ ከበረከታችን ሳንሰስት በጉልበት፣ በዕውቀትና በገንዘብ የምንችለውን ሁሉ ከማደረግ ባሻገር ትግሉ ለመከራው ዘለቄታዊ መፍትሔ እስኪያመጣ ድረስ፡ የአምላክ ሰፊ መዳፍ የመጠለያ ድንኳን እንዲሆናቸሁ ምኞትና ፀሎታችን ነው።


የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ባወጣው መግለጫ ከነገ ሚያዝያ 14 ቀን ጀምሮ ለሰባት ቀናት ጸሎተ ምሕላ ዐወጀ፡፡

ቅዱስ ሲኖዶስ በአሸባሪዎች የተፈጸመውን ድርጊት አውግዞ ባወጣው ባለ ዘጠኝ ዐንቀጽ መግለጫ ለሰማዕታቱ ተገቢውን ቀኖናዊ ክብር እንደሚሰጥ ገልጧል፡፡ ለዚህም የሰማዕታቱን ቤተሰቦች የመረጃ ትብብር ጠይቋል፡፡ ‹‹የጀግና እናት አታለቅስም›› ያለው መግለጫው የሰማዕታቱ ቤተሰቦች የልጆቻቸው ሰማዕትነት በእግዚአብሔር ዘንድ ዋጋ ስላለው በዚህ እንዲጽናኑ አደራ ብሏል፡፡ ለወደፊቱ ተመሳሳይ ችግር እንዳይከሰት ከመንግሥት ጋር አብሮ የሚሠራ ዐቢይ ኮሚቴ እንደሚያቋቁምም ገልጧል፡፡
መግለጫውን ቀጥሎ ያንብቡት
በተያያዘ ዜና ዛሬ ከሰዓት ዐሥር ሰዓት ላይ በቅዱስ ፓትርያርኩ መሪነት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ወደ ሰማዕታቱ ቤተሰቦች በመሄድ ጸሎት እንደሚያደርጉና እንደሚያጽናኑ ተነግሯል፡፡  
ቅዱስ ሲኖዶስ እንዲህ ሲሠራ ‹ሲኖዶስ ሲኖዶስ› ይላል፡፡

click here for pdf

ዛሬ እኩለ ቀን ላይ ከፖኤቲክ ጃዝ አባላትና ከሌሎች የኪነ ጥበብ ሰዎች ጋር ወደ ቂርቆስ ሄጄ ነበር፡፡ ያቺ ሳቂታዋና ተጫዋቿ ቂርቆስ ኀዘን ወርሯታል፡፡ የቂርቆስን ልጆች አውቃቸዋለሁ፡፡ ማልታ፣ ግሪክ፣ ጣልያን፣ ጀርመን፣ ፈረንሳይ፣ ስዊዘርላንድ አግኝቻቸዋለሁ፡፡ መሳቅ ነው፣ መጨዋት ነው፡፡ መቀለድ ነው፡፡ ችግር እነርሱ ጋር የለም፡፡ ካገኙ ተካፍለው ካጡ ተሳስቀው ያልፉታል፡፡ መተዛዘን፣ መረዳዳት፣ ነገር ማቅለል ማን ይችላቸዋል፡፡ እንግሊዝ ሀገር የደረሱት በመንገድ ያለቁትን የሚያስቡበት ዓመታዊ የመታሰቢያ ቀን አላቸው፡፡
ከቂርቆስ ልጅ ጋራ አብረው ቢሰደዱ
ቢያገኝም ያበላል ቢያጣም ያዝናል ሆዱ
ይላሉ የማልታ ልጆች፡፡

ዛሬ ያ ሁሉ ሳቅና ጨዋታ በኀዘን ተቀይሯል፡፡ የልጆቻቸውን መሞት በቪዲዮ በተመለከቱ ወላጆች፣ ማንነታቸውን ከቪዲዮው ለመለየት አቅቷቸው በሰቀቀን ውስጥ በሚገኙ ወላጆች፣ የልጆቻቸውን መረጃ ፈልገው መልስ ባጡ ወላጆች ቂርቆስ ተሞልታለች፡፡ ትጠይቃለች፤ መልስ ግን አላገኘችም፡፡ እንዴት ያለው ትምህርት፣ እንዴት ያለው ጥበብ፣ እንዴት ያለው ብልሃት እንደሚያጽናናት እንጃ፡፡  
እኔ በልቅሶ ቤት ሄጄ ብዙም አላለቅስም፡፡ ዛሬ ግን አለቀስኩ፡፡ በተለይ የባልቻ እናት ‹ፍቅር እስከ መቃብር› እያሉ ሲያለቅሱ ስሰማ ዕንባዬን መቆጣጠር አቃተኝ፡፡ ኢያሱና ባልቻ ሲበሉም፣ ሲጠጡም፣ ሲሄዱም፣ ሲቀመጡም የማይለያዩ አብሮ አደጎች ናቸው፡፡ ሲሰደዱም አብረው ነው የተሰደዱት፤ መሥዋዕት የሆኑትም አብረው ነው፡፡ ለዚህ ነው ‹ፍቅር እስከ መቃብር› የሚሉት የባልቻ እናት፡፡ እናቱን ሊረዳ እንደሄደ፣ ድሮም በእምነቱ ቀልድ እንደማያውቅ፣ ብዙ ተስፋ ሰጥቷቸው እንደነበረ እያነሡ ያለቅሳሉ፡፡ ‹‹እኔ ሲሞት እንዳላየው ብሎ አንገቱን ዘንበል አደረገ››  ይላሉ፡፡
 አያሌ የከተማው ሕዝብ ለእግር መቆሚያ እስኪጠብ ድረስ ሠፈሩን አጨናንቆታል፡፡ ኡኡታ፣ እሪታ፣ ሰቆቃ፣ ቁጭት፣ ሰቀቀን፣ ይነበባል፡፡ የባልቻ እናት ከልጃቸው ሞት በላይ አሁንም በሊቢያ የሚገኙ ሌሎች ወገኖቻችን ያሳስቧቸዋል፡፡ ስለ እነርሱም ያለቅሳሉ፣ ይወዘወዛሉ፡፡ አይ ኢትዮጵያዊት እናት፡፡  

ሰሞኑን በደቡብ አፍሪካ እንዲሁም በተለያዮ ሀገራት በሚገኙ ኢትዮጵያዉያን ወገኖቻችን ላይ እና የሌላ ሀገር ተወላጅነት ባላቸዉ ንፁሀን ዜጉች ላይ በተፈፀመዉ አሰቃቄ የግድያ ወንጀል አዝነን ሳናበቃ ፦ ዛሬ ደግሞ በሊቢያ በሚገኙ ኢትዮጵያዉያን ወገኖቻችን ላይ የተፈፀመዉን እጅግ አሳዛኝ ፤ አረመኔያዊ ተግባር ስይና ስንሰማ የተሰማኝን ሐዘን ለመግለፅ ቃላትም ሆነ ቋንቋ ያጥረኛል። እንኳን የኔ በሚሉት የራስ ወገን ይቅርና ክቡር በሆነዉ […]

ሰበር ዜና አሁን የደረሰን ዜና እንደሚያመለክተው ከተማ ውስጥ ማን እንደበተነው ያልታወቀ ነገ የስራ ማቆም አድማ እና ሰላማዊ ሰልፍ እንዲደረግ የሚጠይቅ ወረቀት ተበትኗል! በየታክሲውና ከተማ ውስጥም መነጋገሪያ እንደሆነ ታውቋል። ፖሊስ ሰልፈኛው ወደ ሜክሲኮ እንዳይሄድ ለማገት ቢጥርም ህዝቡ ግን አንቆምም ብሎዋል ሰልፉ አዲስ አበባን ሲዞር ሊውል ነው! አሁን ሰልፈኛው ወደ ከቄራ ወደ ሜክሲኮ እየዞረ ነው! ፖሊስ ምንም […]

በዚያን ጊዜ ሰዎች ለመከራ አሳልፈው ይሰጧችኋል፤ ይገድሏችኋል፤ በስሜም ምክንያት በሕዝቦች ሁሉ ዘንድ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ፡፡ በዚያን ጊዜ ብዙዎች ሃይማኖታቸውን በመካድ ይሰናከላሉ፤ አንዱ ሌላውን አሳልፎ ይሰጣል፤ ሰዎችም እርስ በርሳቸው ይጣላሉ፡፡ ብዙ ሃሰተኞች ነቢያት ይነሣሉ፤ ብዙዎችንም ያሳስታሉ፤ ከክፋት ብዛት የተነሣ የብዙ ሰዎች ፍቅር ትቀዘቅዛለች፡፡ እስከ መጨረሻ በትዕግስት የሚጸና ግን ይድናል፡፡ ለሕዝቦች ሁሉ ምሥክር እንዲሆን ይህ የእግዚአብሔር መንግሥት ወንጌል […]

ቅዱስ ሲኖዶስ በሊቢያ በግፍ የተሠው ክርስቲያኖች፣ ሃይማኖታችንን አንክድም በማለት የሃይማኖት ሰማዕትነትን የተቀበሉ የሃይማኖት መስተጋድላን መኾናቸውን አረጋገጠ፤ ‹‹የልጆቻችን ሰማዕትነት በእግዚአብሔር መንግሥት ታላቅ ዋጋ ስላላቸው በዚኽ ከሐዘናችኹ እንድትጽናኑ ቤተ ክርስቲያን ታሳስባለች፡፡›› ነገ ወቅዱስ ፓትርያርኩ እና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ መላው የአዲስ አበባ ገዳማት እና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ሊቃውንት፣ ካህናት የሰንበት ት/ቤቶች ወጣቶች እንዲኹም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመምሪያው …

በሊቢያ፣ በየመን እና በሌሎችም ክርስቲያኖች ለጥቃት በተጋለጡባቸውና የድረሱልን ጥሪ እያሰሙ በሚገኙባቸው አገሮች ከተጨማሪ ጉዳት ለመታደግ የሚሠራ ኮሚቴ ተቋቁሟል በአዲስ አበባ እና በአህጉረ ስብከት የሰማዕታት ቤተ ሰዎችን እያፈላለጉ የማጽናናት እና የመደገፍ መርሐ ግብር ይካሔዳል ከሊቢያው የግፍ ተግባር ጋራ በተያያዘ ባሉ ኹኔታዎች ላይ በየዕለቱ እየተሰበሰበ በመምከር መልእክት ለማስተላለፍ የወሰነው ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬም መግለጫ ይሰጣል

ሊቢያ ላይ በአይ ኤስ አይ ኤስ በተገደሉት ኢትዮጵያውያን መንግስት ትኩረት አለመስጠቱን ተከትሎ በርካታ ህዝብ በተቃውሞ ወደ ቤተ መንግስት እያቀና ነው፡፡ ሰላማዊ ሰልፉ ከሟቾቼ ቤተሰቦች ተነስቶ በመስቀል አደባባይ አልፎ አሁን ውጭ ጉዳይ ላይ ደርሷል:: የነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር በቦታው ተገኝቶ እየዘገበ ይገኛል፡፡Filed under: NEWS Tagged: Addis Ababa, Addis Ababa University, Africa, African Commission on Human and Peoples’ […]

ደጋግመን መፈክር ስላሰገርንና፣ ደጋግመን በቃል ቃል ስለገባን ግባችንን በተግባር እንመታለን ማለት አይደለም፡፡ የምንጓዘው ዓላማችንን አንጥረንና አነጣጥረን መሆን አለበት፡፡ ተግባሩን እንጂ ተደጋጋሚ ወሬውን እንተው፡፡ቃል ስንገባ በስሜታዊነት አይሁን! ቃል ስንገባ በአድር-ባይነት አይሁን! ቃል ስንገባ ለይስሙላ አይሁን! ቃል ስንገባ በእርግጥ አደርገዋለሁ ወይ? ብለን ከልባችን ጠይቀን፣ በአዎንታዊነት እራሳችንን አሳምነን፣ በቁርጠኝነታችን ተማምነን እንጂ እንደው በሞቅ ሞቅና በሰሞነኛ መንገኝነት ተገፋፍተን እንዳይሆን […]

(ይሄን መልእክት እና ሌሎች ተመሳሳይ መልእክቶችን ያሰራጩ። ሕዝቡ መረጃ እንዲደርሰውና የእንቅስቃሴው አካል እንዲሆን የድርሻዎትን ይወጡ) ሐሙስ በመላው አገሪቷ፣ በአዲስ አበባ፣ አዳማ፣ ባህር ዳር፣ ጎንደር፣ አምቦ፣ ወለጋ፣ ደብር ብርሃን፣ ደሴ አርባ ምንጭ አዋሳ …የሥራ ማቆም አድማዎችን ያካተቱ ሰላማዊ እንቅስቃሴዎች ይኖራሉ። ታክሲዎች አይንቀሳቀሱም። ሰራተኞች፣ ተማሪዎች ፣ አስተማሪዎች ሐሙስ ቀን ወደ ስራችሁ እና ወደ ትምህርት ቤታችሁ እንዳትሄዱ። ሐሙስ […]

በሊቢያ ምድር እምነታቸው ወንጀል ሆኖባቸው በአይሲስ የተሠዉትን ሰማዕታተ ሊቢያ በተመለከተ መንግሥታዊና የሃይማኖት ተቋማት ሊያደርጉ ስለሚገባው ነገር ስንለው ስንለው ቆየን፡፡ እስኪ አሁን ደግሞ ወደ ባሕላችንና እምነታችን እንመለስ፡፡
እነዚህ ወገኖቻችን ስማቸውንና ቤተሰቦቻቸው ያሉበትን የምታውቁ ንገሩን፡፡ በባሕላችን መሠረት ልቅሶ እንድረሳቸው፡፡ ኀዘናቸው እነርሱ ብቻ አለመሆኑን እንንገራቸው፤ መከራቸውን እንካፈላቸው፡፡ እንደ ባሕሉ ማድረግ ያለብንን እናድርግ፡፡ ይኼ ከዘወትሩ ኀዘን ይለያል፡፡ የተሠዉበት ምክንያት፣ የተሠዉበት ሁኔታ፣ ለመሥዋዕትነት ያቀረቧቸው አሸባሪዎች ማንነት ከዘወትሩ ይለያቸዋል፡፡ ኀዘኑ የወላጅ፣ የዘመድ የመንደር፣ የዕድር ብቻ አይደለም፡፡ ከፕሬዚዳንቱ እስከ እኔ ላለነው ሁሉ ኀዘን ነው፡፡ ስለዚህም እንደየአመቺነቱ ከፕሬዚዳንቱ ጀምሮ በየደረጃው ያለን እንደ ኢትዮጵያዊነታችን ልቅሶ እንድረስ፤ ሰውነታችንን፣ ለዜጎቻችን ያለብንን ኃላፊነት፣ ለቤተሰቦቹ ያለንን የመጽናናት ምኞት በመግለጫ ብቻ ሳይሆን በባሕሉ መሠረት እንግለጠው፡፡ ፖለቲካዊ ዲስኩሩን፣ ነጥብ ለማስቆጠር መጨቃጨቁን፣ የተለመደ ቢሮክራሲያዊ አሠራሩን ትተን ወደ ባሕላችንና እምነታችን እንመለስ፡፡ ባሕል የሌለን እምነት የሌለን አንምሰል፡፡ ለእንደዚህ ያለ ወቅት የሚሆን ወግና ሥርዓት አለን፡፡  ያለ ወግ የመየጣውን ዕዳ በወግ እንክፈለው፡፡

ታዋቂ ሰዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የእምነት መሪዎች፣ የኪነ ጥበብ ባለሞያዎች፣ የሞያ ማኅበራት መሪዎች፣ ባለ ሀብቶች፣ በባሕሉ መሠረት ወደ ቤተሰቦቹ ሄደን ኀዘናችንን እንግለጥ፤ እንደ ኢትዮጵያዊ ኀዘናችንን እንካፈለው፡፡ ልዩነታችንን ኀዘን አንድ ሊያደርገው ካልቻለ ከእንግዲህ ምን አንድ ያደርገዋል፡፡
እንደ እምነታችን ለሰማዕታቱ ተገቢውን ሥፍራ እንስጥ፤ የጸሎት ሥነ ሥርዓት በየአጥቢያው ይዘጋጅ፤ ፎቶዎቻቸው በየአጥቢያው ይለጠፉ፤ የተሠዉበት ክቡር ዓላማ ይነገር፤ በየአጥቢያው የሚዘመረው መዝሙር፣ የሚሰበከው ስብከት፣ የሚሰጠው ምዕዳን ነገሩን ያገናዘበ ይሁን፤ ቢቻል በየ ቤተ እምነቱ ልዩ መርሐ ግብር ይዘጋጅ፡፡ ስለ ሰማዕታቱ የሚያወሳ፣ሽብርና ሽብርተኛነትን የሚያወግዝ፣ ኢትዮጵያዊነትን የሚያጠነክር፤ በሐሳብ፣ በርእዮተ ዓለም፣ በአካሄድ ብንለያይም በሀገራዊ ጉዳይ አንድ መሆናችንን የሚያበሥር፣ የሰማዕታቱን ሰማያዊ ዋጋ የሚዘክር፤ ነገ ተመሳሳይ ነገር እንዳይደገም  መንገድ የሚቀይስ፣ ጉባኤ ይዘጋጅ፡፡
ይሄንን ነገር ያደረጉት አሸባሪዎች ናቸው፡፡ ይህንን ነገር ያደረጉት ኢሰብአውያን በመሆናቸው እንጂ ሙስሊም በመሆናቸው አይደለም፡፡ አንዱም ፍላጎታቸው እንዲህ ስሜት በሚነኩ ድርጊቶች ልዩነታችንን ማስፋት ነው፡፡ እኔ የብዙ ሙስሊም ወገኖቼን ስልክ ዛሬ ስቀበል ነበር፡፡ እጅግ ያዘኑ፣ የተነኩ፣ በእስልምና ስም በተፈጸመው ድርጊት ልባቸው የበገነ ሙስሊሞች፤ አማኞች እንጂ አሸባሪዎች ያልሆኑ፡፡ ሰው በእምነቱ የተነሣ መገደሉን በምንም መልኩ የማይቀበሉ ሙስሊሞች ኀዘናቸውን ሲገልጡ ነበር፡፡
ይኼንን ሰማዕታቱ የሰጡንን ዕድል ለአንድ ዓላማ ለመቆም እንጠቀምበት፤ የሰማዕታት ዓላማ ማስታረቅ ነው፤ ማግባባት ነው፡፡ ይኼንን የኢትዮጵያዊ መተዛዘንና መረዳዳት ጉዳይ ሙስሊም ወገኖቼ በእምነታቸውና በባሕላቸው አጉልተው ያሳዩናል ብዬ አምናለሁ፡፡ አንዳችን በሌላችን የኀዘን ሥነ ሥርዓት ላይ ተገኝተን ከእኩዩ ተግባር በተቃራኒ በጋራ መቆማችንን እናሳይ፡፡  
ያ ከሆነ የደሙ ልቦች ይድናሉ፣ የተጎዱ ቤተሰቦች ከልብ ይጽናናሉ፤ አራጆቻችንም የፈለጉትን ማግኘት እንዳልቻሉ ያያሉ፡፡ አሸባሪዎቹ በሰማዕትነት እንዳከበሩን ሁሉ እኛ ደግሞ የሰማዕታቱን ዓላማ በማጽናት እናዋርዳቸዋለን፡፡ ማን ያውቃል፣ የሰማዕታቱ ደም አልግባባ ላለው ልዩነታችን ሥርየት ይሆነን ይሆናል፡፡

ሚያዝያ ፲፩(አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢትዮጵያውያን ሳምንቱን በሀዘን ተውጠው አሳልፈዋል። በየመን የተጀመረው የኢትዮጵያውያን የድረሱልኝ ጩኸት በደቡብ አፍሪካ እና በሊቢያ ተሰምቷል። 30 ክርስቲያን ኢትዮጵያውያን በአሰቃቂ ሁኔታ በአይ ኤስ ወታደሮች የተገደሉበት ዜና መላውን አለም እያነጋገረ ነው። ኢትዮጵያውያን ሀዘናቸውን ከመግለጽ በተጨማሪ ምን እናድርግ እያሉ በመጠየቅ ላይ ናቸው። በፌስቡክ እና በማህበራዊ ድረገጾች የፖለቲካ እምነታቸውም ሆነ ሃይማኖታዊ …

ሚያዝያ ፲፩(አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዛሬ ሚያዚያ 12 ፣ 2007ዓም ኡራኤል አካባቢ አንድ ኢትዮጵያዊ ቤንዚን በራሱ ላይ አርከፍክፎ የተወሰነ የሰውነት ክፍሉ ከተቃጠለ በሁዋላ በህዝብና በፖሊስ እርዳታ ሊተርፍ ችሎአል። የአይን እማኞች ግለሰቡ ሙሉ ልብስ የለበሰ እና ጥሩ የሰውነት ቁመና  ያለው መሆኑን ተናግረዋል።  ፖሊሶችም ግለሰቡን ወደ ስድሰተኛ ፖሊስ ጣቢያ ወስደውታል ዘግይቶ በመጣው መረጃ ደግሞ …

(ይሄን መልእክት እና ሌሎች ተመሳሳይ መልእክቶችን ያሰራጩ። ሕዝቡ መረጃ እንዲደርሰውና የእንቅስቃሴው አካል እንዲሆን የድርሻዎትን ይወጡ) ሐሙስ በመላው አገሪቷ፣ በአዲስ አበባ፣ አዳማ፣ ባህር ዳር፣ ጎንደር፣ አምቦ፣ ወለጋ፣ ደብር ብርሃን፣ ደሴ አርባ ምንጭ አዋሳ …የሥራ ማቆም አድማዎችን ያካተቱ ሰላማዊ እንቅስቃሴዎች ይኖራሉ። ታክሲዎች …

ሀሙስ ሚያዝያ 15 ቀን ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ በርካታ የፖለቲካ፥ የሲቪክ፥ የሙያ፥ የሃይማኖትና ሌሎችም ድርጅቶች በአንድ ላይ በመላው ኢትዮጵያና ዓለም ዙሪያ የሀዘን ቀን አውጀዋል Read more »

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

በሊቢያ እስላማዊ መንግሥት የተሰኘው አክራሪ ድርጅት 30 ኢትዮጵያውያንን በጥይትና በመቀላት የገደለበት የጭካኔ ተግባር ፣ እንዲሁም፣ በደቡብ አፍሪቃ በውጭ ዜጎች አንፃር በቀጠለው ሁከት በኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሰ ያለው የኃይል ተግባር በኢትዮጵያ ተወገዘ።

በሜድትሬንየን ባህር ከሊቢያ የባህር ዳርቻ ወደ ኢጣልያ በመጓዝ ላይ የነበረች መርከብ ከትናንት ወዲያ ባጋጠማት የመስመጥ አደጋ 950 ያህል ስደተኞች ሳይሞቱ እንዳልቀረ ተነገረ።

ከሊቢያ ወደብ ተነስታ የሜድትራኒያንን ባህር በማቋረጥ ወደ ጣሊያን በማምራት ላይ የነበረች መርከብ በመስጠሟ ከ900 ሰዎች በላይ ሳይሞቱ አልቀረም። በመርከቧ ከተሳፈሩ ሰዎች መካከል 28 ስደተኞች ብቻ ተርፈዋል።

በሊቢያ የአይሲስ ታጣቂ ቡድን የተገደሉት 30 ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን የኢትዮጵያ መንግስት ማረጋገጡን አስታወቀ። ግድያው በኢትዮጵያውያን ዘንድ ቁጣን ቀስቅሷል። የአውሮጳ ህብረት፤የአፍሪቃ ህብረትና ዩ.ኤስ አሜሪካ የታጣቂ ቡድኑን ድርጊት በጽኑ ኮንነዋል።