እነዚህ ወገኖቻችን ሰማዕታት ናቸው፡፡ ሃይማኖታቸውን አንለውጥም ብለው የተሠዉ፡፡ ‹ስደተኛ ኢትዮጵያውያን› የሚለውን አገላለጽ ነፍሴ ትጸየፈዋለች፡፡ ከአኩሪው የሰማዕትነት ተግባራቸው በላይ ስደተኛነታቸው ለማጉላት ስለሚያኮበኩብ፡፡ ሰው በሀገሩ ቢኖር፣ ቢሠራና ቢከብር የመጀመሪያ ምርጫው ነው፡፡ በተለይ ኢትዮጵያውያን፡፡ ነገር ግን ‹እልፍ ሲሉ እልፍ ይገኛል› ይባላልና የቸገረው ቢሰደድ ምን ይፈረድበታል? በርግጥ ስደቱ በሰላም፣ በሕግና በጤና ቢሆን የማይወድ የለም፡፡ ግን ሁል ጊዜ ይቻላል ወይ? […]

የኦሮሞ ብሄር ኣክራሪ ድርጅት መሪ የሆነውና የኦሮሞ ሚዲያ ኔትወርክ ፕሬዝዳንት አንዲሁም ኦሮሞ ፈርስት መሪ የሆነው ጃዋር የሊቢያው እልቂት በኢትዮጵያ አንዲደገም የኦሮሞ ሚድያን (OMN) በመጠቀም ሲሰራ አንደነበር ሁሉም ኢትዮጵያዊ ከገዜ ወደ ጊዜ ግልጽ አየሆነለት መጥትዋል:: ኣንገታቸውን በሜንጫ ነው የምንለው የሚለው ኣነጋገሩ በተለይ ኣሁን ሊቢያ ውስጥ ከተፈጠረው ሁኔታ ጋር ብዙ ሰዎች ስጋታቸውን ንዴታቸውን ና ፍርሀታቸውን በመሀበራው ድህረ […]

ሚያዝያ ፲፭(አስራ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሊቢያ በረሃና  በደቡብ አፍሪካ በ አሰቃቂ ሁኔታ  የተገደሉትን ኢትዮጵያዊያንን ለማሰብ ረቡዕ ሚያዚያ 15 ቀን 2007 ዓም መንግስት የጠራው ሰልፍ ወደ  ሕዝባዊ ተቃውሞ በመለወጡ በብዙ መቶወች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በፖሊሶች ተደብድበው ሆስፒታል ከገቡ በሁዋላ፣ በቦታው ላይ የተያዙ፣ ማሽት ላይ በየቤቱ እየተለቀሙ የተያዙ እንዲሁም ዛሬ ሃሙስ ጧት የተያዙ በየክፍለ ከተማው …

ሚያዝያ ፲፭(አስራ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ህብረቱ የተለያዩ የፖለቲካ እና ሲቪክ ማህበራት መሪዎችን በመጋበዝ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ከ4 ሰአት በላይ ውይይት አድርጓል። የአውሮፓ ህብረት የእንግሊዝ ተወካይ፣ ወ/ሮ ጁሊ ዋርድ፣ በህብረቱ የፖርቱጋል ተወካይ ወ/ሮ አና ጎሜዝ፣ የስዊድኖቹ፣ ሶራያ ፖስትና ቦዲል ሲቢሎስ እንዲሁም የስፔን ተወካይ ሚ/ር ጆርዲ ሴባሲቲያ  እና ሌሎችም የህብረቱ ባለስልጣናት በውይይቱ ላይ …

ሚያዝያ ፲፭(አስራ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ማንነታቸው ያልታወቁት ሟቾች አስከሬን ማልታ ውስጥ በክብር እንዲያርፍ ተደርጓል። የኢትዮጵያ፣ የሶማሊ፣ የኤርትራና ሌሎችም አፍሪካውያን በቀብር ስነስርአቱ ላይ ተገኝተው ሀዘናቸውን ገልጸዋል። የሟቾቹ ዜግነት በውል ባይታወቅም፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባወጣው መረጃ ኤርትራውያን፣ ኢትዮጵያውያን፣ ሶማሊያውያንና ሌሎች አፍሪካውያን ይገኙበታል።

እነዚህ ወገኖቻችን ሰማዕታት ናቸው፡፡ ሃይማኖታቸውን አንለውጥም ብለው የተሠዉ፡፡ ‹ስደተኛ ኢትዮጵያውያን› የሚለውን አገላለጽ ነፍሴ ትጸየፈዋለች፡፡ ከአኩሪው የሰማዕትነት ተግባራቸው በላይ ስደተኛነታቸው ለማጉላት ስለሚያኮበኩብ፡፡ ሰው በሀገሩ ቢኖር፣ ቢሠራና ቢከብር የመጀመሪያ ምርጫው ነው፡፡ በተለይ ኢትዮጵያውያን፡፡ ነገር ግን ‹እልፍ ሲሉ እልፍ ይገኛል› ይባላልና የቸገረው ቢሰደድ ምን ይፈረድበታል? በርግጥ ስደቱ በሰላም፣ በሕግና በጤና ቢሆን የማይወድ የለም፡፡ ግን ሁል ጊዜ ይቻላል ወይ? ምቹ ሁኔታስ አለ ወይ? ዛሬ ከአውሮፓ፣ አሜሪካና አውስትራልያ፣ ከአፍሪካና እስያ ገንዘባቸውን እየላኩ አንዳንዴ ከቡና በላይ አንዳንዴም ከቡና ቀጥሎ የውጭ ምንዛሬውን የሚያስገኙልን ወገኖች አብዛኞቹ ዛሬ ‹ሕገ ወጥ› በምንለው መልኩ የሄዱ አይደለም ወይ? እንዲያ እንዲሆኑ ያደረጋቸውን መሠረታዊ ምክንያት መፍታት እንጂ የሆኑበትን መንገድ ማውገዝ ምን ይጠቅማል? 

 

በሀገራችን ኢትዮጵያ እየኖሩ በአክራሪዎችና አሸባሪዎች ሕይወታቸው የተሠዉ ክርስቲያኖች አልነበሩም ወይ? በ1980ዎቹ መግቢያ በአሰቦት ገዳም የታረዱት መነኮሳት፣ በአርሲ ኮፈሌ የተገደሉትን ምእመናንና በ1998 ዓ.ም. በጅማ በሻሻ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ የተሠዉት ምእመናንና ካህናት ስደተኞች ሆነው አልነበረምኮ? ክርስቲያን ስለሆኑ እንጂ፡፡ በአይሲስ እጅ ወደቀው ከነበሩት መካከልኮ እነርሱ የእስልምና እምነት ይከተላሉ ብለው ያሰቧቸውን ሱዳናውያንና ሶማልያውያንን ያለ ምንም እንግልት ይለቋቸዋል፡፡ የቁርዐን ጥያቄ የሚጠየቁት ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ናቸው፡፡ ከእነርሱም መካከል ሙስሊም አይደለም ብለው ያሰቡትን ነው በኮንቴይነር አስገብተው ወደ አልታወቀ ሥፍራ የሚወስዱት፡፡ እነዚህም ቢሆኑ ምርጫ ይቀርብላቸዋል፡፡ ‹እስልምናን ወይንም ሞትን መቀበል› እምነታችንን አንለውጥም ሲሉ ይገደላሉ፡፡ አይሲስ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ክርስቲያኖችን ሲያርድ በግድ እንዲመለከት የተደረገው ኤርትራዊው የ16 ዓመት አዳጊ ወጣት ናኤል ጎይቶም ከእጃቸው አምልጦ ከወጣ በኋላ ለኢንተርናሽል ቢዝነስ ታይምስ የነገረውም ይሄንኑ ነው፡፡ ለቪኦኤ ቃሉን የሰጠው ከሞት ያመለጠ ወጣት ይህንኑ ያረጋገጠ ነበር፡፡ አይሲስም በአድራሻ ‹ጠላታችን ለሆነቺው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን› ብሎ ተናግሯል፡፡ አይሲስ ራሱ ሀገራዊ ብሔርተኝነትን ሳይሆን ሃይማኖታዊ ብሔርተኝነትን ማስፈን ነው  ዓላማው፡፡ ሊመሠርትም የተነሣው ‹የእስልምናን መንግሥት› ነው፡፡
ይኼ ሁሉ የሚያሳየው እነዚህ ወንድሞቻችን የተሠዉት ክርስቲያን በመሆናቸው እንደሆነ ነው፡፡ በንግግራችንም ሆነ በመግለጫችን ልንናገረው የሚገባን እውነትም ይኼው ነው፡፡ ሕገ ወጥ ስደትን እንኳን እኛ ስደተኛው ራሱም አይፈልገውም፡፡ የሞታቸው ዋና ምክንያት ግን ስደት አይደለም፡፡ ያ ቢሆን አብረዋቸው የተሰደዱት ሶማልያውያንና ሱዳናውያንም ይገደሉ ነበር፡፡ ምክንያቱ ክርስትናቸው ነው፡፡ እነርሱን ‹ባይሄዱ ኖሮ አይገደሉም ነበር› በሚል ዓይነት ጥፋተኞች ለማድረግ ለምን እንደክማለን፡፡ እነርሱ የአቋም ሰዎች ናቸው፡፡ ዘላቂውን አቋም ለጊዜያዊ ጥቅም መቀየር ያልፈቀዱ፡፡
ስለ እነዚህ ወንድሞች ክርስትና መናገር ሌሎች አማኞችን ያስቀይማል ወይም ያገላል ብለን ከሆነ ስሕተት ነው፡፡ ሙስሊሞችና ሌሎችም ወገኖቻችን ‹ማንም በእምነቱ ምክንያት መገደሉን እናወግዛለን› እያሉኮ ነው፡፡ የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ርእሰ መንበር ‹በዲናችን አስተምሮና አሳምኖ እንጂ አስገድዶና ገድሎ እምነት ማስቀየርን አንቀበልም› ነው ያሉት፡፡ ይኼ ነገር እነዚህ ወገኖቻችን በግድ እምነታችሁን ቀይሩ ተብለው በአረመኔዎች መገደላቸውን እየነገሩን ነው፡፡
ከአይሲስ እጅ በእግዚአብሔር ቸርነት ለወሬ ነጋሪነት ያመለጡ ወገኖች እንደሚናገሩት አይሲስ ትልቁ ትኩረቱ በኢትዮጵያና ኤርትራ ስደተኞች ላይ ነው፡፡ ሱዳናውያንንና ሶማልያውያን ወዲያው ነው የሚለቀው፡፡ በተለይ ደግሞ የመስቀል ምልክት በሰውነታቸው ላይ የተነቀሱና ሌሎች ሃይማኖታዊ ምልክቶችን ያደረጉትን ወዲያው ያለምንም ጥያቄ ክርስቲያን መሆናቸው አረጋግጦ ለብቻ በኮንቴይነር ያስቀምጣቸዋል፡፡ ከአይሲስ ጋር የሚደረግ ውይይት፣ ድርድር፣ ክርክር የለም፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ የለበሱት የሊቢያ ወታደሮችን ልብስ ስለሆነ እነማን እንደሆኑ የሚታወቀው በኋላ ነው፡፡ የሰዎችን ጥያቄና ልመና ለማስተናገድ ዕድል የሚሰጡ አይደሉም፡፡
ከዚህ አንጻር ከኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች ጋር ጀማል የተባለ ሶማልያዊ ሙስሊም ‹ክርስቲያኖችን እረዳለሁ ብሎ› አብሮ ተሠውቷል የሚለውን መረጃ ለመቀበል ይቸግራል፡፡ በመጀመሪያ ሶማልያውያንን ለጥያቄ አያቀርቧቸውም፡፡ በሁለተኛ ደረጃ ጓደኞቼን ትቼ አልሄድም ስላለ አይሲስ ‹ና አብረሃቸው ሂድ› ብሎ አስተያየት የሚያደርግ ቡድን አይደለም፡፡ በሌላ በኩል ተጓዦቹ ሲያዙ የሊቢያ ወታደሮች እንደያዟቸው እንጂ አይሲስ መሆናቸውን የሚያውቁበት ዕድል የለም፡፡ የለበሱት የወታደር ልብስ ነው፡፡ የመጀመሪያው መለያየት የሚፈጠረው ደግሞ እምነትን ሳይሆን ዜግነትን መሠረት አድርጎ ነው፡፡ ሶማልያውያንና ሱዳናውያን ወዲያው ያስኬዳሉ ኤርትራውያንና ኢትዮጵያውያን ይይዛሉ፡፡ ሶማልያውያንና ሱዳናውያን የሚይዙት የተለየ እምነታቸውን የሚጠራጥር ነገር ካገኙባቸው ብቻ ነው፡፡ እንደ ማተብ፣ የመስቀል ንቅሳት፣ የአለባበስ ለውጥ ወዘተ፡፡ ክርስትና ጥያቄ ሆኖ የሚመጣው ከዚያ በኋላ ነው፡፡ በኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ዘንድ፡፡
በዚህ ሁሉ ነገር ጀማል ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖችን ለመርዳት ዕድል የሚያገኝበት መንገድ የለም፡፡ ቢፈልግ እንኳን፡፡ እርሱ ከሶማልያውያን ጋር መጀመሪያ ተለይቶ ወይ ሄዷል፤ ወይ ሌላ ቦታ ተቀምጧል፡፡ እስካሁን ለማምለጥ ዕድል ያገኙ ወገኖችም ይህንን ታሪክ አያውቁትም፡፡ መረጃውን ሰጡ የተባሉት የሶማልያ ምንጮች ናቸው፡፡ ተርፈው የወጡ ወገኖች የሚጠራጠሩት ሁለት ነገር ነው፡፡ አንድ ጀማል እምነቱን ቀይሮ ክርስቲያን ከሆነና ይህንንም ከመሰከረ፤ ሁለት በሰውነቱ ላይ የመስቀል ንቅሳት አሠርቶ ከሆነ፡፡ ከዚያ ውጭ ግን ሶማልያዊ ሙስሊም ሆኖ ከኢትዮጵያውያን ጋር የሚታረድበት በቂ ምክንያት ሊኖር አይችልም፡፡ እንኳን ለመታረድ አብሮ ለመቆየት ዕድል የለውም፡፡  
ይኼ ማለት ሙስሊሞች ክርስቲያኖችን አይወዱም ወይም አይረዱም ማለት አይደለም፡፡ በሊቢያ ተደብቀው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን መረዳዳቱን በሚገባ መስክረዋል፡፡ ይኼ የማይታበል ሐቅ ነው፡፡ ይኼ ነገር በራሱ ቆሞ ሊናገር የሚችል ስለሆነ ሌላ ነገር መፍጠር የሚያስፈልገው አይመስለኝም፡፡
ጀማልን በተመለከተ የተሠራጨውን ዜና መቶ በመቶ አይሆንም ማለት አይቻልም፡፡ በቦታው የለንምና፡፡ ከዓይን ምስክሮችና በሊቢያ ምድር ከሚገኙ ምንጮች፣ ተርፈውም ለመገናኛ ብዙኃን ምስክርነት ከሰጡ ሰዎች ተነሥተን ስናየው ግን ‹ተረጋግጦ ያለቀ እውነት ነው› ብሎ ለመቀበል የበለጠ መረጃ የሚያስፈልግ ይመስለኛል፡፡   
እነዚህን ወገኖች ለማሰብ፣ ቤተሰቡን ለማጽናናት በቀጣይም ተመሳሳይ ነገር እንዳይከሰት ለመሥራት ቤተ መንግሥት፣ ቤተ ክህነት፣ ሚዲያዎች፣ ታዋቂ ሰዎች፣ የንግድ ተቋማትና ሌሎችም እያደረጉ ያለው ነገር ነገሩን በኢትዮጵያዊ ባሕልና ወግ መሠረት ለማከናወን የሚደረገውን ጥረት ያሳያል፡፡ በየእምነት ተቋማቱ ጸሎት እየተደረገ ነው፡፡ በየ አጥቢያው ምሕላ እየተከናወነ ነው፡፡ በኀዘንተኞቹ ቤት ሕዝቡ በነቂስ እየተገኘ ኀዘኑን እየተካፈለ ነው፡፡ ኀዘንተኞቹም በሕዝቡ አጋርነት እየተጽናኑ ነው፡፡ ፓርላማው ያወጀው የሦስት ቀን ብሔራዊ ኀዘን እየተተገበረ ነው፡፡ የሚስመሰግን ነው፡፡
የምናደርጋቸው ነገሮች ግን እምነቱንና ትውፊቱን፣ ወጉንና ባሕሉን፣ ኅሊናንና ሰብእናን የጠበቁ ቢሆኑ መልካም ይሆናሉ፡፡ ርዳታችን፣ ኀዘናችን፣ ማጽናናታችን፣ ችግሩን ለመፍታት መሯሯጣችን እምነት፣ ኅሊና፣ ባሕልና ወግ አስገድዶን እንጂ ለተወዳጅነትና ለገጽታ ግንባታ ባይሆን ይመረጣል፡፡ የወገኖቻችንን መሥዋዕትነት ለፖለቲካ ጥቅም፣ ለሚዲያ ፍጆታ፣ ሩኅሩኅነታችንን ለማሳያ፣ ለጋስነታችንን ለማስመስከሪያ እንድንጠቀምበት ኢትዮጵያዊ ባሕልና ወግ አይፈቅድልንም፡፡ የምንሰጠው ገንዘብ፣ የምንወስደው የእዝን እንጀራ፣ የምንደርሰው ልቅሶ ሁሉ እየተቀረጸ፣ በፎቶ እየተነሣ፣ በሬዲዮ እየተላለፈ የሚደረግ ከሆነ ለራሳችን ገጽታ ስንል እንጂ አዝነን ያደረግነው መሆኑን ያጠራጥራል፡፡ ሌሎች ስለ እኛ ይናገሩ እንጂ እንዴት ‹ይህን አድርገናል፣ ይህን ሰጥተናል› እያልን ራሳችንን ራሳችን እንቀርጻለን፣ ራሳችንንስ እንዴት ራሳችን እናስተዋውቃለን? ነውር ቀረ ማለት ነው? የንግድ ድርጅቶችና ‹ታላላቅ ሰዎች› ይህንን ለራስ መክበሪያነት ሲያውሉት ማየት ግን ያማል፡፡
አንዳንድ ሰዎችን አይተናል ረድተዋል፣ ልቅሶ ደርሰዋል፣ አጽናንተዋል፣ የሚችሉትን ሁሉ አድርገዋል፡፡ ነገር ግን ነጋሪት እየጎሰሙ አይደለም፡፡ በርግጥ በተራራ ላይ ያለች መብራት ልትሠወር ስለማይቻላት ሌሎች አይተዋቸው ስለ እነርሱ ዘግበዋል፡፡ እነርሱ ግን ‹እዩልን ስሙልን› አላሉም፡፡ ‹አምስት ሺ ብር ሰጠሁ፣ ዐሥር ሺ ብር ሰጠሁ› ሲሉ አልተሰሙም፡፡ ድርጊቱን የተደረገለትና ዋጋ ቆጣሪው አምላክ ያውቀዋል፡፡ በሚዲያ ገብተውም ‹እገሌ ይህንን ያህል ሺ ብር ስለሰጠዎት አመስግኑት› ብለው የኀዘንተኛ ምስጋና አልሰበሰቡም፡፡
ጎበዝ እየተስተዋለ እንጂ፤ አንገቱን ለሰጠ ገንዘብ ሰጥን ብለን ይሄ ሁሉ ነጋሪት?
  

የሃዘኑ ድባብ ከመብራቱ መቆራረጥ ጋር ተዳምሮ ጨለማውን አብሶታል። የአሁኑ መብራት መቋረጥ ግን ከወትሮ ፈረቃ ለየት ያለ ነው። ሆን ተብሎ የተደረገ ይመስላል። ከጥቂት ስፍራ በስተቀር ሁሉም ቦታ በአንዴ እንዲጠፋ ነው የተደረገው። ከሬድዋን ሁሴን እና ከሃይለማርያም የቴሌቭሽን ዲስኩር በኋላ ሃገሩ ሁሉ ጨለማ እንዲሆን አደረጉ። ይህንን ለማድረግም በቂ ምክንያት ነበራቸው። ሃዘን ያልወጣለት ህዝብ አደባባይ ወጥቶ በአረመኔ ወታደሮች ሲቀጠቀት […]

የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ ከብዙ ሚሊዮን የኢትዮጵያ ሕዝብ፣እንዲሁም ነጻ ከሆኑት የሰብአዊ መብት ድርጅቶች፣ ከፍሪደም ሃውስ፣ከሂውማን ራይትስ ዋች፣ከአምነስቲ ኢንተርናሽናል፣ከኢንተርናሽናል ሪቨርስና ከሌሎቹ ጋር በማበር የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ የፖለቲካ ቢሮ ም/ሃላፊ የሆኑት ዊንዲ ሸርማን በቅርቡ ባደረጉት የአዲስ አበባ ኦፊሴላዊ ጉብኝት ወቅት በ16-04-2015 የሰጡት አስተያየት እውነትን የማያንቀባርቅ በመሆኑ ከማዘናችንም በላይ የአሜሪካንንም ሆነ የኢትዮጵያን መሰረታዊ ጥቅም ሊያሰከብር የሚችል እንዳልሆነ […]

‹‹Leadership is Falling in Love with the People You Lead or Serve›› (ቀድሞዋ የማላዊ ሴት ፕሬዝዳት ጆሴ ባንዳ) ለዚህ ጽሑፍ መነሻ የሆነኝ ከትናንትና በስቲያ ከሥራ ወጥቼ ወደ ቤቴ ለመሄድ በተሳፈርኩበት ሃይገር ባስ ውስጥ ያጋጠመኝ እጅጉን ያሰዛነኝ ክስተት ነው፡፡ በተሳፈርኩበት ሃይገር ባስ ውስጥ ወጣቱ ሹፌር የይሁኔ በላይን የአገር ባህል፣ ሞቅ ያለ የበዓል ዘፈን እስከ ጣራው ለቆታል፡፡ […]

ፓስተር አርቲስት ጥበቡ ወርቅዬ የቤተክርስቲያኒቱን ተልኮ ለመፈፀም ትላንት ማምሻውን ከመካኒሳ ሙሉ ወንጌል ቤ/ክ ከሌሎች አገልጋዮች ጋር በመሆን ነበር ወደ ሻሸመኔ የተንቀሳቀሱት ሆኖሞ ዝዋይ ላይ ባጋጠማቸው የመገልበጥ አደጋ ጥበቡን ጨምሮ ፓስተር ይሳቅ አለማየው (የሻሸመኔ ሙሉ ወንጌል አስተዳደር) እና አሽከርካሪው ህይወታቸው ሊያልፍ ችሏል:: ቀሪ ጉዳት የደረሰባቸው አገልጋዮች በዝዋይ ሪፈራል ሆስፒታል እርዳታ እየተደረገላቸው ነው ሲል ኤልሻዳይ ቲቪ ዘግቧል::ለቤተሰብ […]

ላለፉት ሁለት ሳምንታት የኢሕአዴግ መንግስት ላይ ወርደንበታል !!!! ጥሩ ነው ያደረግነው። በተለይም ትላንትና ህዝቡ ተቃዉሞዉን ማሰማቱ በጣም አስደስቶኛል። አርክቶኛል። ሕዝብ ሲናገር መስማት የመሰለ ትልቅ ነገር የለም። ምርጫ 2007 ትላንት የተደረገ ነው የመሰለኝ። በተለየም መሪዎቹ እዚያ ቆመው፣ የሕዝቡን ፉጨትና ጩኸት መስማታቸው ጥሩ ነው። ያለዉን የሕዝቡን ስሜት በአካል መረዳታቸው፣ ምናልባት አይምሯቸው ላይ የሚጭረው ነገር ሊኖር ይችላል። አፉን […]

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

በቦስተን የመካነ ሕይወት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን በሊቢያ እና በተለያየ ቦታዎች በግፍ ለተጨፈጨፉት ወገኖች በትናንትናው ምሽት የጸሎት እና የሻማ ማብራት ስነ ስርአት በርካታ ኢትዮጵያውያኖች በተገኙበት፤ በደማቅ ስነ ስርዓት ተካሄደ!! የመካነ ሕይወት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን በጠራው የሻማ እና የጸሉት ስነ ስርዓት ላይ በቦስተን እና አካባቢዋ የሚገኙ ኢትዮጵያውያኖች፤ የመካነ ሕይወት ቤተ ከርስቲያን እና የመካነ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን […]

ኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት የላትም። የገዥውን ፓርቲ የስልጣን ዕድሜ ለማስረዘም የሚንቀሳቀስ የጉጅሌ ስብስብ ነው “መከላከያ ሰራዊት” ተብዬው። ለማንኛውም ከዚህ በታች ያለውን የወያኔ “ወታደራዊ ባለሙያዎች” አስተያየት ማንበቡ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በምን አይነት ጭንጋፍ መንግስት እንደምትተዳደር በይበልጥ ግልጽ ያደርጋል።  አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 15፣ 2007 (ኤፍ.ቢ.ሲ) …

የ”ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት” በአይሲስ ላይ ወታደራዊ እርምጃ የመውሰድ አቅም እንደሌለው የገዥው ፓርቲ የደህንነትና ወታደራዊ ሳይንስ ጠበብቶች ለፋና ብሮድካስቲንግ አስረዱ Read more »

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤ አሜን ‹‹ርትዕት ሃይማኖቶሙ ለቅዱሳን አበዊነ = የአባቶቻችን ሃይማኖት የቀናች ናት›› ራሱን እስላማዊ መንግሥት (አይ ኤስ አይ ኤስ) እያለ የሚጠራው የጨካኝ አረመኔዎች ስብስብ፣ በግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ላይ ያካሔደው ዘግናኝ ግድያ ሳይበቃው ይህን እኩይ ድርጊቱን በልዩ ልዩ ምክንያት ከአገር ተሰድደው በሊቢያ በነበሩ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምእመናን …

በሶሻል ሚዲያ (ፌስ ቡክ) Ahamab muhamad oromo የሚባል ሰው ከብሄር ጋር የተያያዙ ጠንከር ያሉ መልእክቶችን በአማርኛና በኦሮምኛ ሲያስተላልፍ ቆይቷል፡፡የኢትዮጵያን ባንዲራ ሲረግጥ የሚያሳይ የራሱን ምስልም በመለጠፍ ጥላቻውን ማሳየቱን ብዙዎች ያስታውሱታል፡፡ ግለሰቡ የፕሮፋይል ምስሉ የአሜሪካ መንትያ ህንጻዎች ሲጋዩ የሚያሰይ ፎቶ ግራፍ ካደረገም ረዘም ያሉ ግዜያት ተቆጥረው ነበር፡፡ ወንድሞቻችን በሜድትራንያን ባህር አካባቢ በአይ ኤስ አይ ኤሶች ግድያ ከተፈጸመባቸው […]

  ማምሻውን ፖሊሶችና ፌድራል ፖሊሶች ጨርቆስ ቤተክርስቲያን ውስጥ በመግባት በምእምናን ላይ ድብደባ መፈጸማቸውን ጉዳት የደረሰባቸው  ገለጹ ህወሃት መራሹ ኢህአዴግ የእምነት ቦታዎችን በማርከስ ከዚህ ቀደም በገዳማት በመስጅዶች ውስጥ በመግባት በምእምናን ላይ ድብደባ ሲፈጸም መቆየቱ የሚታወስ ሲሆን በዛሬው እለት በጨርቆስ ቤተክርስቲያን ውስጥ ድረስ በመዝለቅ ከፍተኛ ድብደባ መፈጸማቸውን በቦታው ላይ ድብደባ የተፈጸመባቸው  ገልጸዋል፡፡… በቤተክርስቲያኑ ውስጥ ከሚስቱ ጋር እንደነበር […]

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤ አሜን፡፡ ‹‹ኢትዮጵያዊ መልኩን ነብር ዝንጉርጉርነቱን ሊለውጥ ይችላልን? ልጆቻችን የምንኮራባቸው መጻሕፍቶቻችን፣ የምንማርባቸው ዩኒቨርስቲዎቻችን ናቸው፤ አስተምረውናል፤ አኩርተውናል፤ አስከብረውናል›› (ብፁዕ አቡነ ሉቃስ፤ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፤ የሰቲት ሑመራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ) የልጆቻን የኃይለ ሚካኤል(ኢያሱ ይኵኖ አምላክ) እና የኃይለ ኢየሱስን(ባልቻ በለጠ) ነፍስ ይማርልን፡፡ እግዚአብሔር አምላካችን የሐዘን ዳርቻ ያድርግልን፡፡ እግዚአብሔር አምላካችን የቤተሰቡን …

ሚያዝያ 14 ቀን 2007 ዓ.ም. ‹‹እስመ በእንቲኣሁ ይቀትሉነ ኲሎ አሚረ፡፡ ወኮነ ከመ አባግዕ ዘይጠብሑ = ስለ አንተ ቀኑን ኹሉ እንገደላለን፤ እንደሚታረዱ በጎች ተቆጠርን::›› (መዝ.43÷22) *       *       * ራሱን እስላማዊ መንግሥት (IS) እያለ በሚጠራው ዓለም አቀፋዊው አሸባሪ ድርጅት በይፋ በኢንተርኔት ባሰራጨው የቪዲዮ መረጃ፣ በኹለት የተለያዩ ቦታዎች በአሠቃቂ ኹኔታ የገደላቸው ወንድሞቻችን የተገኘባቸው አበሳ ወይም ወንጀል ክርስቲያን ኹነው …

የቀድሞው የግብፅ ፕሬዚዳንት መሐመድ ሙርሲ የሃያ ዓመታት እስራት ፍርድ

ለግብፅ አምስተኛው ፕሬዚዳንት ናቸው፡፡ በግብፅ ታሪክም የመጀመርያው በዴሞክራሲያዊ ምርጫ የፕሬዚዳንትነቱን መንበር የጨበጡ ሲቪል መሪ ነበሩ፡፡

ግብፅን ለሦስት አሥርት ያህል የገዟትን ፕሬዚዳንት ሆስኒ ሙባረክ ከገረሰሰው የግብፅ አብዮት በኋላ፣ እ.ኤ.አ. በሰኔ 2012 ሥልጣን የያዙት የቀድሞ የግብፅ…

Abune Elias. ብፁዕ አቡነ ኤልያስ

Ethiopia Zare (ረቡዕ ሚያዝያ 14 ቀን 2007 ዓ.ም. April 22, 2015)፡- ዛሬ ማምሻውን ከ12 ሰዓት (18፡00) ጀምሮ ለሁለት ሰዓታት በስቶክሆልም በደብረሰላም መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን በሊቢያ ለተገደሉት ወገኖቻችን በብፁዕ አቡነ ኤልያስ የምስራቅ አፍሪካና የአውሮጳ ሊቀጳጳስ የተመራ ሥርዓተ ጸሎት ተደረገ። በርካቶች ሲያለቅሱ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ …

በአይሲሲ እና በደቡብ አፍሪካ ለተገደሉት ኢትዮጵያዊያን በኖርዌይ ስታቫንገር የመድሐኒያለም ቤተክርስቲያን የፀሎት ስነ ስርዓት ተደረገ በአይሲሲ እና በደቡብ አፍሪካ ለተገደሉት ኢትዮጵያዊያን በኖርዌይ ስታቫንገር መድሐኒያለም ቤተክርስቲያን የፀሎት ስነስርዓት ተደረገ። የማጽናኛ ትምህርት በቤተክርስቲያን አባቶች ተሰጠ  እንዲሁም የማች ቤተሰቦች የመጽናኛ ፀሎት እና የጣፍ ማብራት  ስነስርዓት የተደረገ ሲሆን ከዛም በመቀጠል አይሲሲ እና ደቡብ አፍሪካን በመቃወም በስታስታቫንገር ሴንትሩም የተቃውሞ ሰልፍ ተካሄደ። ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ […]

ከምሺቱ ፫ ሰሃት ጀምሮ በድፍን አዲስ አበባ አሸባሪው የወያኔ መንግስት መብራት በማጥፋት በ  በተገደሉት ወገኖቻችንና ለህዝቡ ግድ የሌለው የወያኔን ጉጂሌ በመቃወማቸው በዚህም የተበሳጨው የወያኔ መንግስት በለሊት ህዝቡን ከየቤቱ እያፈሰና በመኪና እያጋዘ ይገኛል ብዙ ወገኖቻችን ኣሁን ባደረሱኝ መረጃ መሰረት የከተማዋ መብራት በማጥፋት ልባቸው በሃዘን የተቃጠሉትን ወገኖቻችንን በጂምላ እያፈሰ ነው የትም እንዳደረሳቸው አልታወቀም ተብላል። posted by Aseged […]

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ኢስላሚክ ስቴት ወይም ISIS/ISIL በመባል የሚታወቀው አሸባሪ ድርጅት በሊቢያ በኢትዮጲያውያንን ክርስቲያኖች ላይ የፈፀመውን ግድያ ቪድዮ ባለፈው እሁድ ማሰራጨቱን ተከትሎ፤ ድርጊቱን ለማውገዝ ዛሬ ሰልፎች ተካሂደዋል፡፡ ያንን አስመልክቶ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊ ሚኒስተር ሬድዋን ሁሴን ዛሬ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ ከጽ/ቤቱ ያገኘነውን የመግለጫው ጭማቂ ጽሑፍ ከዚህ በታች አትመነዋል፡፡ 1) የተሳካ ሰልፍ ተካሂዷል፣ * ህዝቡ ከጫፍ ጫፍ ወጥቷል፣ * በሰላማዊ መንገድ በጋራ ሀዘኑ ዙሪያ፣ በቀጣይ የጋራ ጥረቶች ዙሪያ ያጠነጠነ መልዕክቱን አስተጋብቷል፣ * አንድነቱን በማጉላት ሽብርተኞች ለመፍጠር የፈለጉትን የመከፋፈል ሴራ ሙስሊም ክረስቲያን ሳይል በጋራ ተሰልፎ በመምጣት አክሽፏል፣ * ሽብርተኝነት ሃይማኖታዊ መሰረት እንደሌለው በማንኛውም ሃይማኖት ጀርባ መሸሸሸግ እንደማይገባ አረጋግጧል፣ * ISIS ማንኛውንም ሃይማኖት እንደማይወክል ፅንፈኝነትና አክራሪነትን እንዲሁም የሽብር ተግባርን ብቻ እንደሚወክል ስለዚህም የጋራ ጠላት መሆኑን በአንድ ድምፅ አስረግጧል፡፡ * የፀረ ሽብርና አክራሪነት ትግሉን ከመንግስት ጎን ቆሞ ለማጧጧፍ ያለውን ፅኑ አቋም አስተጋብቷል፡፡ * ህገ ወጥ ስደትን በመላ ህዝቡ ተሳትፎ ማስወገድ እንደሚገባ በቁጭት ገልጿል፣ * በሀገራችን ሰርቶ መለወጥ የሚቻልበት ዕድል እየተፈጠረ በመሆኑ ከነክብራችን በሀገራችን ሰርተን እንለወጥ የሚል ፅኑ አቋም አስተጋብቷል፣ * የሃይማኖት አባቶችንና የመንግስትን መልዕክት በጥሞናና በትእግስት አዳምጦ የቀጣይ ትግል ባለቤትነቱን አረጋግጧል፣ * በመሆኑም መንግስት የከበረ ምስጋና ያቀርባል፣ * ከህዝቡ በተጨማሪም የሀገራችን ተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ ከአንዳንዶች በስተቀር የደረሰው አደጋ በሰው ልጆች ላይ የተቃጣ ኢሰብአዊ ድርጊት መሆኑንና የኢትዮጵያውያን የጋራ ሀዘን መሆኑን፣ ሽብርተኝነትን ለመዋጋት በሚደረገው ጥረትም የበኩላቸወን ድርሻ የሚወጡ መሆኑን በፓርቲዎች […]

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 14፣ 2007(ኤፍ.ቢ.ሲ) ባሳለፍነው እሁድ በሊቢያ ውስጥ በአሸባሪው አይ ኤስ በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉ ኢተዮጵያውያን ማንነት በመለየት ላይ ይገኛል።

በዚህም መሰረት በርካታ የሟች ቤተሰቦች የልጆቻቸውን ሞት ተረድተው ሀዝን በመቀመጥ ላይ ይገኛሉ።

ቀደም ብሎ ኢያሱ ይኩኖአምላክ እና…

ከቴዎድሮስ ሓይሌ ሰሞኑን በየመን በደቡብ አፍሪካ በወገኖቻችን ላይ የደረሰው የሞት አደጋ የፈጠረው ህዝባዊ ቁጭትና ሃዘን ሳይበርድ ይባስ ብሎ በሊብያ በዚህ ዘመን ይፈጸማል ብሎ ለማሰብ የሚከብድ አረመኔያዊ በሆነ መልኩ በግፍ የተሰየፉትን ወንድሞቻችን የተቀላ አንገት ተመልክተናል ። ይህ የሽብር ድርጊት ለእኛ ለባለቤቶቹ …

ወያኔና ISIS – የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች! Read more »

መንግስት ራሱ በጠራው ሰልፍ ላይ በተገኙት ነዋሪዎች ላይ ከፍተኛ ድብደባ ፈጸመ:: ፎቶች ይዘናል ይመልከቱ፤ የBBN ድምጽ ዘገባ እዚህ በመጫን ያዳምጡ ህዝቡ ካለማንም ነጋሪነት ካለማንም ተቃዋሚ ጣልቃ ገብነት ራሱ በራሱ የሚከተሉትን መፈክሮⶭ አስምቷል። * የፈሰሰው ደም የውሻ አይደለም * መከላከያ ስራህ ምንድነው * የወያኔ ጉልበት እኛ ላይ ብቻ * ና ና መንግስቱ ናና * አባረዋቸው አሳረድዋቸው […]

IS ወይም ISIS/ISIL በመባል የሚታወቀው አለም-ዓቀፍ አሸባር ቡድን አል ፉርቃን በተባለ ሚዲያ በኩል “የኢትዮጵያ ቤተ ክርስትያን አባላት የሆኑ የመስቀሉ ተከታዮችን” በአረመኔያዊ አኳኋን የገደለበትን ቪዲዮ መልቀቁ ይታወሳል፡፡ ቪዲዮውን መሰረት በማድረግ እንደሚከተለው ለመዳሰስ ተሞክሯል፡፡ ዋና ዋና ነጥቦች፡- * ነሳራ (Christians/The people of the book) * ኢብን ቴይሚያ (Ibn Teymiyyah) * ጂዝያ (ያላመኑ ላይ የሚጣል ግብር) * የኢትዮጵያ ቤተ ክርስትያን አባላት የሆኑ የመስቀሉ ተከታዮች (The Oriental Orthodox Church (Ethiopia & Egypt)) ይሀ ቪዲዮ የ29 ደቂቃ ርዝመት ያለው ሲሆን በጥቅሉ በነሳራ/በክርስትያኖች (The people of the book) ላይ ያተኮረ ነው፡፡ በዚህም ነሳራን በአራት ክፍሎች ያስቀምጣል፡፡ 1/Western Catholic Church (Europe & other Eastern countries). 2/ The Oriental Orthodox Church (Ethiopia & Egypt). 3/ The Eastern Orthodox Church (Russia, Greece, Many Mediterranean states). 4/ The Protestant Church (Germany, America, Scotland, Norway and Holland) ከዚህ ቪዲዮ አላማ አንፃር ሲታይ ይህ ቪዲዮ ያነጣጣረው የኢትዮጵያና ግብጽ የጋራ መለያ በሆነው ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ላይ መሆኑን መገንዘብ ይቻላል፡፡ ለዚህም ነው የግድያውን ምክንያት “ጠላት የሆነችው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስትያን መስቀል ተከታዮች” በማለት የገለፀው፡፡ ከ22፡30 – 23፡40 ባሉት ደቂቃዎች ለኢትዮጵያ ቤተ ክርስትያን አባላት የሆኑ የመስቀሉ ተከታዮች ሁለት (2) መሰረታዊ መልዕክት ያላቸውን ለማስተላለፍ የሞከረው፡፡ እነኝህም፡ 1/የኢስላሚክ ኢስቴት (IS) አገዛዝ ስርዓትን እስልምናን በመቀበል እንዲቀላቀሉ ጥሪ ማቅረቡ 2/ ከባርነት ወደ ነጻነት እንዲሸጋገሩ – አንድ ግዛትና አንድ መሪን በመቀበል ከ24፡00 […]

በሳውዲ፣ የመን፣ ደቡብ ኣፍሪካና ሊብያ በኢትዮጵያውያን ላይ ችግር ባጋጠመ ጊዜ በቦታው የሌሉ ብዙ ኢትዮጵያውያን የኢትዮጵያ መንግስት በነዛ ኣገራትና ቡድኖች ላይ እንዲወስደው የሚጠብቁት እርምጃ ኣርበኛዊ እርምጃ ነው፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት ደግሞ ጥሎበት (በባህሪው) ኣርበኛዊ ዲፕሎማሲ ኣያራምድም፡፡ ቢያንስ መንግስት በኣንዳንድ ወገኖች የሚነሳበትን የ”ወኔ-ቢስነት” ክስ ለመከላከልና ለዜጎቹ እንደሚቆረቆር ለማሳየት ያክል እንኳን (ባያደርገዉም) በቴሊቪዥን ብቅ ብሎ ዘራፍና ያዙኝ ልቀቁኝ ማለት ኣይሆንለትም ወይም ኣያምንበትም፡፡ ይሄ ማለት ግን መንግስት ምንም ኣይነት እርምጃ ኣይወስድም ማለት ኣይመስለኝም ፡፡ በኢትዮጵያውያን ላይ ችግርና ጥቃት በደረሰ ቁጥር እኛ ዜጎች እንደምናሳየው ኣይነት ቁጣ የመንግስት ፊት (ግንባር) ላይ ባናየዉም በጊዜው እንደየሁኔታው የተሻለ የሚለው እርምጃ ይወስዳል የሚል ግምት ኣለኝ፡፡ ይሄንን ባህሪው ተቃዋሚዎቹ የፖለቲካ ነጥብ ለማስቆጠር ኣንዳንድ ደጋፊዎቹ ደግሞ የሚደግፉትን ፓርቲ/መንግስት ባህርይ በደንብ ካለመረዳት ኣሊያም በስሜትና ሃዘኑና ጥቃቱ በሚፈጥርባቸው ተፅእኖ ምክንያት መንግስትን ይወቅሳሉ፡፡ ለነገሩስ የኛን ስሜትና ምክር እየተከተለ እርምጃ የሚወስድ መንግስት ቢሆን ኖሮ ይሄኔ ከሱዳንና ግብፅ (በኣባይ ምክንያት)፣ ከሳውዲ ኣረቢያ (በዜጎች ምክንያት)፣ ከኤርትራ (በሄሊኮፕተር ምክንያት) እንዲሁም ከሌሎች ኣገሮች ጋር ጦርነት ውስጥ እንገባ ኣልነበር ? የሰሞኑ የ ISIL ጉዳይ ግን ትንሽ ስሜትን ይፈታተናል፡፡ ድህነት ኣንገሽግሽዋቸውና የቤተሰቦቻቸውን ኑሮ ለመቀየር የሰሃራ በረሃን ኣቋርጠው የመሞትና የመትረፍ ኣጋጣሚው እኩል የሆነበትን የሜዲትራኒያን ባህር የጀልባ ጉዞ ለማድረግ የተዘጋጁትን ወጣት ወገኖች በኣደባባይ ኣንገታቸው ሲቀላና ሰረሸኑ ማየትን የሚያክል ዘግናኝ ነገር የለም፡፡ ህዝባችን በሃዘንም በቁጭትም ኣደባባይ ወጥቶ ሆ ቢል፣ እስቸኳይ የኣጸፋ እርምጃ እንዲወሰድ ቢጠይቅ ኣይገርምም፡፡ ጥያቄው […]

ምነዋ መንግሰተ ሰማይ! የምህረትሽ ቀን ራቀ? ምነው ትንግርትሽ ረቀቀ ? ምነው ኪዳንሽ ታጠፈ … ወዝሽ ወዘናሽ ነጠፈ? እንደ ዳጉሳ ድፍድፍ … ላቦትሽ ተንጠፈጠፈ አሳርሽ ጠሎ አሰፈፈ ምነው እርሾው ተማጠጠ …. ጎታው ጎተራው ታጠጠ ረሀብ ላንቃው ፈጠጠ….ያዳም ልጅ አፅሙ ገጠጠ ምነው ጭር አለ ቀየው! ሀሩር ነዲዱ በረታ ኮርማው ጥማዱ ተረታ ምነው ነበልባሉ አየለ … ማሳው ተንቀለቀለ […]

በተለያዩ የባለ ሥልጣናትና የእምነትመሪዎች መግለጫዎች ላይ በሊቢያ ምድር የተሠዉትን ሰማዕታት በኢትዮጵያዊነታቸው ወይም በስደተኛነታቸው ብቻ አደጋ እንደደረሰባቸውተድርጎ እየተነገረ ነው፡፡ እነዚህ ክቡራን ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች ናቸው፡፡ የተሠዉትም እምነታቸውን አንለውጥም ስላሉ ነው፡፡አይሲስ የሠዋቸው በኢትዮጵያዊነታቸው አይደለም፡፡ አይሲስኮ ዜግነት የለውም፡፡ ዐረቦች፣ አውሮፓውያን፣ አፍሪካውያን እስያውያን የተቀላቀሉትአሸባሪና አሰቃቂ ድርጅትና አስተሳሰብ ነው፡፡ እንዲያውም ባለፈው ሰሞን ትውልደ ኢትዮጵያውያን ከእንግሊዝ ወደ አይሲስ ለመግባትያደረጉትን ጥረት በመገናኛ ብዙኃን […]

ወጣቱ የቪኦኤ ጋዜጠኛ ስሙን እንዲደብቅለት ከተማፀነ በኃላ እንዲህ አለ – ”….እኔ ያለሁት ትሪፖሊ ውስጥ ነው።አሁን ከግማሽ ሰዓት በፊት ፊታቸውን የተሸፈኑ ሰዎች እኔ ወደምኖርበት ግቢ ገቡ እና ወደ 40 የሚሆኑ ኢትዮጵያውያንን ይዘው በመኪና ሄዱ።ከተወሰዱት ውስጥ በቅርቡ ኦፕራሲዮን የሆነች እና ነፍሰ ጡር አለችበት። እነማን እንድሆኑ ማወቅ አልቻልኩም።እኔ ተደብቄ ነው ያመለጥኩት። እዚህ እስላም እና ክርስቲያን ኢትዮጵያውያንን ሊለያዩን ሞክረው […]

አሁን ከማልታ ባገኘሁት መረጃ በቀደም ከተሠዉት ወንድሞቻችን ጋር የነበረ ፣በእግዚአብሔር ቸርነት አምልጦ ትሪፖሊ የገባ ወንድም አግኝቼ ነበር፡፡
 

እርሱ እንደነገረኝ በአጅዛቢያና ቤንጋዚ መንገድ ላይ የአይሲስ አራጆች የሊቢያ መንግሥት ወታደሮችን ዩኒፎርም  ለብሰው በዚያ የሚያልፉትን ለመያዝ ይጠብቃሉ፡፡ በአካባቢው ወደ ትሪፖሊ የሚጓዙ መንገደኞችን ሲያገኙ ይይዛሉ፡፡ ሱዳኖችንና ሶማልያውያንን ሙስሊሞች ናቸው ብለው ስለሚያስቡ ወዲያው እንዲሄዱ ይለቋቸዋል፡፡ ኤርትራውያንና ኢትዮጵያውያንን ግን ለብቻ ይይዛሉ፡፡ ከዚያም ሙስሊሞችን ለብቻ ክርስቲኖችን ለብቻ ያሰልፏቸዋል፡፡ በመቀጠልም ክርስቲያኖችን በኮንቴይነር ውስጥ ከትተው ወዳልታወቀ ሥፍራ ይወስዷቸዋል፡፡ ሙስሊሞችን ደግሞ ይለቋቸዋል፡፡

በቀደም ዕለት አይሲስ በባሕር ዳርቻ የሠዋቸው ክርስቲያኖች በሰውነታቸው ላይ የመስቀል ምልክት የነበረባቸውን መርጦ ነው፡፡ እነርሱን በተለየ ኮንቴይነር አስቀምጧቸው ነበር፡፡ ይኼንን መረጃ የነገረኝ ሰው ሊገደሉ ተመርጠው ከተለዩት ወገን ነበረ፡፡ ሌሎች በኮንቴይነር ያስቀመጣቸው ክርስቲያኖችም አሉ፡፡ ምናልባት ከዚህ የከፋ ዜና እንሰማ ይሆናል፡፡ አምላክ ይጠብቀን፡፡ አሁንም የአይሲስ አራጆች የመንግሥት ወታደሮችን ልብስ ለብሰው ሌሎች ስደተኞችን እየያዙ ነው፡፡

ይኼ መረጃንውን ያደረሰኝ ሰው ሊያመልጥ የቻለው ሌሎች ክርስቲያኖችን በጨለማ ወደ ኮንቴይነሩ ለማስገባት ኮንቴይነሩን በከፈቱበት ጊዜ ነው፡፡ የተወሰኑ ተያዦች አምልጠው ነበር፡፡ አንዳንዶች ተያዙ፡፡ ሦስቱ ግን አመለጡ፡፡ ሁለቱ የት እንደደረሱ አያውቅም፤ እርሱ ግን በእግዚአብሔር ቸርነት አምልጦ ትሪፖሊ ገብቷል፡፡
እባካችሁ ባገኛችሁት አጋጣሚ ሁሉ ሰሞኑን ለመጓዝ የተነሡት ቢያንስ ለጊዜው ይታገሡ፡፡ ሱዳን ያሉትም ከሱዳን አይውጡ፡፡ መንገዱ በአይሲስ አራጆች ተይዟል፡፡ ለማታለልም የመንግሥት ወታደሮችን ልብስ ለብሰው ድንበር ጠባቂ ይመስላሉ፡፡
እግዚአብሔር በእጃቸው የተያዙትን እንዲታደግ እንጸልይ፡፡

Ethiopian martyrs in Libyaበተለያዩ የባለ ሥልጣናትና የእምነት መሪዎች መግለጫዎች ላይ በሊቢያ ምድር የተሠዉትን ሰማዕታት በኢትዮጵያዊነታቸው ወይም በስደተኛነታቸው ብቻ አደጋ እንደደረሰባቸው ተድርጎ እየተነገረ ነው፡፡ እነዚህ ክቡራን ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች ናቸው፡፡ የተሠዉትም እምነታቸውን አንለውጥም ስላሉ ነው፡፡ አይሲስ የሠዋቸው በኢትዮጵያዊነታቸው አይደለም፡፡ አይሲስኮ ዜግነት የለውም፡፡ ዐረቦች፣ አውሮፓውያን፣ አፍሪካውያን እስያውያን የተቀላቀሉት አሸባሪና አሰቃቂ ድርጅትና አስተሳሰብ ነው፡፡ እንዲያውም ባለፈው ሰሞን ትውልደ ኢትዮጵያውያን ከእንግሊዝ ወደ አይሲስ ለመግባት ያደረጉትን ጥረት በመገናኛ ብዙኃን ሰምተን ነበር፡፡ አይሲስ አገር የለውም፡፡

እነዚህ ወንድሞቻችንማ ማተብ የሚያደርጉበትን አንገት ለእምነታቸው ሲሉ የሰጡ ቅዱሳን ሰማዕታት ናቸው፡፡ እኛ በቃል ብቻ የምንናገረውን ሰማዕትነት በ21ኛው ክፍለ ዘመን በተግባር ያሳዩ የተግባር ክርስቲያኖች ናቸው፡፡ ምናልባት ባለ ሥልጣናቱና ሚዲያዎቹ ይህንን ለመናገር የከበዳቸው ሌሎች አማኞችን እናስከፋለን ብለው አስበው ይሆናል፡፡ እውነት ለመናገር ግን በግድ ሃይማኖታቸውን ወደ እስልምና (ያውም አይሲስ ወዳጣመመው የእስልምና አመለካከት) መቀየር ነበረባቸው ብሎ የሚከራከር ኢትዮጵያዊ ሙስሊም ይኖራል ብዬ አላምንም፡፡ ቢኖርም አመለካከቱን እንዲፈትሽ ማድረግ እንጂ እርሱን ላለማስቀየም እውነቱን መካድ አያስፈልግም፡፡ የአይሲስን ሐሳብ ተቀብለው፣ እምነቱን አራምደው፣ ከእርሱ ጋር ተቀላቅለው ለተወሰነም ጊዜ ቢሆን እድሜ ለማራዘም ቢፈልጉ መንገዱ ነበረ፡፡ ወላዋዮች፣ ለእምነት ግድ የለሾ፣ እምነታቸው እንደ ሸሚዝ ለመቀያየር የሚፈልጉ አቋም የለሾች ቢሆኑ ኖሮ ሞት ሩቅ ነበረ፡፡ እነ ኢያሱ፣ እነ ባልቻ፣ እነ ተስፋየና እነ ዳንኤል ግን እንደዚያ አልነበሩም፡፡ በእምነታቸው ጸኑ፤ በክርስቲያንነታቸው ታረዱ፣ ሰማዕትነትንም ተቀበሉ፡፡ይኼንን እውነታ መካድ ሰማዕታቱን ሁለት ጊዜ መግደል ነው፡፡ ከሞታቸው በላይ የሞቱበትን ክቡርና ቅዱስ ዓላማ መካድ አብልጦ ይገድላቸዋል፡፡ደግሞም ስደተኛነታቸው ለአደጋው ምክንያት ሆነ እንጂ የተሠዉት በስደተኛነታቸው አይደለም፡፡ ስደተኞችም ሆነው እምነታቸውን ለመለወጥ ቢፈልጉ ኖሮ ይችሉ ነበር፡፡ የተሠዉት በክርስትናቸው ነው፡፡ ክርስቲያን ኢትዮጵያውያን ናቸው፡፡ አንገታቸውን የሰጡት ለክርስቶስ ነው፡፡ እንደ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ አነጋገር ‹እንደ ንጹሕ መገበሪያ ስንዴ ሆነው› ለአምላካቸው ነው በመሥዋዕትነት የቀረቡት፡፡ እነርሱ አንገት የሰጡለትን ክርስትና እኛ ለመናገር ለምን ፈራነው?

(Click here for PDF)