ሲኖዶስ፡- ሟቾቹ ጀግኖች እንጂ ተጎጂዎች አይደሉም፣ የሰማዕትነት ክብር ይሰጣቸዋል

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስትያን ሲኖዶስ ዛሬ ሚያዝያ 13/2007 ባወጣው ባለ9 ነጥብ መግለጫ፡- በሊቢያ ውስጥ በተደረገው አሰቃቂ ድርጊት ቤተ ክርስቲያንኒቱ እጅግ ያዘነች መሆኗን ገልጾ በዚህ ግድያ ውስጥ ግን ሟቾቹ ሰማዕት በመሆን የተጠቀሙ ጀግኖች እንጂ ተጐጂዎች እንዳልሆኑም ጭምር ማሰብ እንደሚገባ ገልጿል፡፡ በነገው ዕለት በአዲስ አበባ የሚገኙ ገዳማት እና አድባራት በአጠቃላይ ከጠዋቱ 2 ሰዓት ጀምሮ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በመገኘት ጸሎተ ፍትሐት እንዲያደርሱ ጥሪ አስተላለፏል፡፡ በመላው ዓለም የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናትም ሁሉ ከሚያዚያ 14 ጀምሮ ለ7 ተከታታይ ቀናት በሁሉም አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ምህላ እንዲያረግ ቅዱስ ሲኖዶስ አያይዞ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ አክሎም ለሟቾቹ የሰማዕትነት ክብርን በቀኖናው መሠረት መስጠት እንዲቻል ቤተሰቦቻቸውን የሚያውቁ ምዕመናን ፎቶአቸውንና ስማቸውን አሰባስባው ለቅዱስ ሲኖዶስ እንዲያቀርቡ አዝዟል፡፡ ሙሉ የሲኖዶስን ሙሉ መግለጫ ለማንበብ ከሥር ካለው ምስል ያንብቡ ወይም እዚህ ጋር በመጫን (link) ዳውንሎድ ያድርጉ፡፡ *********** — More from Horn Affairs AmharicSendek | የጁነዲን ሳዶ ባለቤትን ጨምሮ 29 ሰዎች በሽበርተኝነት ተከሰሱETV | የግንቦት 7ቱ አንዳርጋቸው ፅጌ በየመን ተይዞ ለኢትዮጵያ ተላልፎ ተሰጥቷልማዕተብም መስቀልም በግለሰቦች ነፃነት ውስጥ የሚካተት ነው – ዶ/ር ሺፈራው ተክለማርያምየዩኒቨርስቲዎች ሃይማኖታዊ ስነስርአትና አለባበስ ደንብን በመቃወም በሽብር የተሳተፉ ግለሰቦች ጥፋተኛ ተባሉሕገ-መንግስት እንዲያከብሩ ሲመከሩ – በሃይማኖታችን ጣልቃ ተገባ ይላሉ (ሚ/ር እውነቱ ብላታ)ማዕተብ ከሂጃብ