ሞዛንቢክና ፀረ- ፈንጂ ትግሏ
የተቀበሩ ፈንጂዎችን ምርት እና ዝውውርን የሚከለክለው የኦታዋ ውል የሚፈተሽበት ሦስተኛው ዓለማቀፍ ጉባዔ ትናንት በሞዛምቢክ ተጠናቀቀ። ውሉን የተፈራረሙት ሀገራት የመጀመሪያውን ጉባዔ ያካሄዱት ከ15 ዓመታት በፊት ነበር ። ደቡባዊትዋ አፍሪቃ ሀገር ሞዛምቢክ ያኔ በዓለም እጅግ ብዙ ፈንጂዎች ከተቀበሩባቸው ሀገራት መካከል አንዷ ነበረች።
የተቀበሩ ፈንጂዎችን ምርት እና ዝውውርን የሚከለክለው የኦታዋ ውል የሚፈተሽበት ሦስተኛው ዓለማቀፍ ጉባዔ ትናንት በሞዛምቢክ ተጠናቀቀ። ውሉን የተፈራረሙት ሀገራት የመጀመሪያውን ጉባዔ ያካሄዱት ከ15 ዓመታት በፊት ነበር ። ደቡባዊትዋ አፍሪቃ ሀገር ሞዛምቢክ ያኔ በዓለም እጅግ ብዙ ፈንጂዎች ከተቀበሩባቸው ሀገራት መካከል አንዷ ነበረች።
ብራዚል ላይ እየተካሄደ ባለዉ የዓለም የእግር ኳስ ጨዋታ፤ ዛሬ የደቡብ አሜሪካ አራት ሀገራት ብሄራዊ የእግር ኳስ ቡድኖች በሚያደርጉት ግጥምያ የጥሎ ማለፍ ዉድድሩ ይጀምራል። ብራዚል ከቺሊ፤ ኮሎምቢያ ከዑሯጓይ። በደቡብ አሜሪካ የሚገኙት ሀገራት በዘንድሮዉ የእግር ኳስ ግጥምያ፤
ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች
የዛሬው የወጣቶች ዓለም እንግዶቻችን በአሁን ሰዓት በመካሄድ ላይ ያለውን የዓለም የእግር ኳስ ዋንጫ ውድድር የበለጠ አጓጊ ለማድረግ የወሰኑ ይመስላል።
በአስተናጋጅ ሀገር ብራዚል ፣ ባለፉት 2 ሳምንታት ከዓለም ዙሪያ በተወከሉ ባጠቃላይ የ 32 ሃገራት ብሔራዊ ቡድኖች መካከል ሲካሄድ የሰነበተው የመጀመሪያ ዙር ውድድር፣ ትንንት ማምሻውን ተደምድሟል። የዓለም የእግር ኳስ ፌደሬሽን
ከ 9 ዓመት በፊት የካርቱምና የጁባ ባለሥልጣናትና ተወካዮች ፣ ጦርነት አቁመው ውል ሲፈራረሙ በአካባቢው ዘለቄታ የሚኖረው ሰላም ይሠፍናል የሚል ብሩሕ ተስፋ ነበረ ያኔ ያሳደረው። ግን አልሆነም። ይባስ ብሎ በዚያው በደቡብ ሱዳን ሁለት የሥልጣንና
የአውሮፓው ሕብረት መሪዎች ትናንት ከብራሰልስ 150 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው፣ ከአንድ መቶ ዓመት በፊት፣ በአንደኛው የዓለም ጦርነት አውድማነት በምትታወቀው ከግማሽ ሚሊዮን የማያንስ ሠራዊት ባለቀባትና ለመጀመሪያ ጊዜ መርዘኛ የሰናፍጭ ጋዝ ሰለባ
የዛሬው የወጣቶች ዓለም እንግዶቻችን በአሁን ሰዓት በመካሄድ ላይ ያለውን የዓለም የእግር ኳስ ዋንጫ ውድድር የበለጠ አጓጊ ለማድረግ የወሰኑ ይመስላል።
ሰኔ ፳(ሃያ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያ የሰላማዊ ተቃውሞ ታሪክ ውስጥ ረጅም ጊዜ በማስቆጠር ክብረወሰን የሰበረው የሙስሊም ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ፣ በረመዳን ጾም መግቢያም ” በአንድነታችን እንጸናለን” በሚል መፈክር ተካሂዷል። እንደወትሮው ሁሉ እጅግ በርካታ ኢትዮጵያውያን በተገኙበት በአንዋር መስጊድ በተካሄደው የጸሎት ስነስርአት፣ ሙስሊሙ “በአንድነታችን እንጸናለን” የሚሉ በወረቀት ላይ የተጻፉ መፈክሮችን ከፍ አድርጎ በማሳየትና እጅ ለእጅ በመያያዝ መልእከቱን አስተላልፏል። …
የዓለም ዜና
ህወሓቶች የመቐለ ህዝብ ዓፈናውን በሰለማዊ ሰልፍ እንዳያሰማ ለማፈን ያህል የነገው የመቐለ የተቃውሞ ሰለማዊ ሰልፍ ከልክሏል። በደብዳቤ እንዲያሳውቁን በጠየቅነው መሰረት የደብዳቤው ይዘት ምን መሆን እንዳለበት ለስድስት ሰዓት ያህል ከተወያዩ በኋላ እነሆ ቀኑና ይዘቱ አዛብተው ሰጥተውናል። ስህተት አለው ስንላቸው፤ ዝም ብላቹ ያዙ እሱም በስንት መከራ ነው ብለውናል። ባጭሩ የተቀመጠው ምክንያት ክልላዊና ከተማዊ ዝግጅት ስላለን አይመችም፤ በቂ የፀጥታ […]
የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሠራዊት ሰኔ 16/2006 ዓ/ም በወልቃይት አድነጣ በተሰኘ ስፍራ ድል ተቀዳጀ!
አምባገነኑ የወያኔ አገዛዝ የይስሙላውን ምርጫ በመጪው ዓመት እንደተለመደው ግልጽና ፍትሃዊ ባልሆነ መልኩ ለማከናወን ሲል ገና ከአሁኑ ለለውጥ የተነሳሱ ዜጎችን በማሰርና በማሳደድ ብሎም ደብዛቸውን እያጠፋ በሚገኝበት በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሠራዊትየወገን ደራሽ ጥቃቱን በጎጠኛው ቡድን ታጣቂዎች ላይ መውሰዱን ቀጥሏል።
በሰኔ 16/2006 ዓ/ም በወልቃይት አድነጣ በተሰኘ ስፍራ በስርዓቱ የሚሊሻ ታጣቂ ላይ በወሰደው ወታደራዊ እርምጃ አስራ ስምንት(18) ገድሎ ሁለት(2) ማርኳል የምርኮኞቹ ስም1ኛ- ቻለው ሲሳይ 2ኛ- ተጫነ ንጉሱ ሲሆኑ ሠራዊቱ ለሁለቱም ምርኮኞች ስለወቅቱ የኢትዮጵያ ሁኔታና ስለ ድርጅቱ አላማና ግብ በማስተማር ለቋቸዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በሰኔ 18/2006 ዓ/ም ነበልባሉ የኢትዮጵያ ሕዝበ አርበኞች ግንባር ሠራዊት ከወያኔው የልዩ ሃይል ታጣቂ ጋር በወልቃይት አወርቂ በተባለ ቦታ ከጠዋቱ 1 ሰዓት እስከ 5 ሰዓት ለአራት ሰዓት ያህል ባካሄደው እልህ አስጨራሽ ውጊያ ሰላሳ ስድስት(36) ገድሎ አርባ ስምንት(48) በማቁሰልና የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን ከነመሰል ጥይቶቻቸውና ትጥቃቸው ጋር ማርኳል።
ውጊያው በተካሄደበት አከባቢ የሚገኙ ነዋሪዎችና በ2007 ዓ/ም ይደረጋል ተብሎ በሚጠበቀው የምርጫ ድራማ ሳቢያ ከፍተኛ እንግልትና ስቃይ እየደረሰባቸው የሚገኙ ወገኖች የተሰማቸውን ደስታ ከመግለጻቸውም ባሻገር የወያኔን ቡድን በጥይት አረር ለመፋለም ግንባሩን እየተቀላቀሉ ይገኛሉ።
source — http://www.arbegnochginbar.org/index.ph … &Itemid=50
Malibo, Equatorial Guinea, AU leaders’ summit
ሽብርተኛነት በመላው ዓለም ላይ የጋረጠውን አደጋ በኅብረት መመከት ግዴታ እንደሆነ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ በናይጀሪያ ጉብኝታቸው ወቅት አስታውቀዋል።
ሃያ ሦስተኛው የአፍሪካ ኅብረት መሪዎች መደበኛ ጉባዔ ዛሬ በኢኳቶርያል ጊኒ ሪፐብሊክ ማላቦ ተጀምሯል።
የጉባዔው መሪ ቃል “የግብርናና የምግብ ዋስትና ዓመት” የሚል ነው።
በጉባዔው ላይ ከአፍሪካ መንግሥታትና ሃገር መሪዎች ሌላ የተለያዩ ሀገሮችና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች መሪዎች ተገኝተዋል።
መለስካቸው አመሀ ከአዲስ አበባ የላከው ዘገባ ዝርዝሩን ይዟል፤ ያዳምጡት፡፡
ከምኒልክ ሳልሳዊ
በወያኔ መኮንኖች እና በኢትዮጵያ የመከላከያ ስራዊት መኮንኖች መካከል በፖለቲካ እና በጥቅማ ጥቅም ጉዳዮች ዙሪያ ውስጥ ውስጡን እየተካረረ የመጣው አተካራ ከባድ ውጥረት መፍጠሩን በእዙ የሚገኙ መኮንኖች የተገኘው መረጃ ጠቁሟል። ሕገመንግስታዊ ጥያቀዎችንእና ወታደራዊ ጥቅማ ጥቅሞችን የሚተይቁ መክንኖች ከየክምፑ ተለቅመው ወደ ሰሜን እዝ እና ወደ ሶማሊያ ከሄደው ጦር ጋር እንዲቀላቀሉ ከተደረገ በኋላ ውጥረቱ እየሰፋ መምጣቱ ታውቋል።
ከዚህ ቀደም የተነሱ ሕገመንግስታዊ ጥያቄዎችን የሕወሓት ከፍተኛ መኮንኖች የጥያቄው ባለመብቶችን ወደ ሌላ አከባቢ በመቀየር የቀሩትንም በጥቅም ለመያዝ ቢሞክሩም ያላዋጣቸው ሲሆን ክመሃል ሃገር ሰልጥነው የተመደቡትም ወታደራዊ ደህንነቶች የአንድ ብሄር አባላት ስለሆኑ የመከላከያ ሰራዊቱ የበታች መኮንኖች በጥርጣሬ ስለሚመለከቷቸው የተላኩበትን ግዳጅ በብቃት መፈጸም ባለመቻላቸው ምንም አይነት ውጤት አለማምታታቸው ችግሩ ዳግም እንዲያገርሽ ሆኗል።
በወታደራዊ ደህንነቶች አማካኝነት እንቆጣጠረዋለን ብለው የምስራቅ እዝ ከፍተኛ የሕወሓት መኮንኖች ያሰቡት ጉዳይ ዳግም ውጥረት መፍጠሩ በድንበሩ አከባቢ ስጋት ስለፈጠረ ወደ አከባቢው አዲስ የመከላከያ ሰራዊት አንድ ሻለቃ ጦር እንዲመደብላቸው ጠይቀዋል።
የምስራቅ እዝ ምኮንኖች አብዛኛው ስራቸው የኮንትሮባድ ተግባራትን መፈጸም መዝረፍ እና ሴቶችን መድፈር መሆኑ ይታወቃል። የሕወሓት መኮንኖች ሌላውን አስፈላጊውን ሕግ የሚፈቅደውን ጥቅማ ጥቅም በመከልከል ከፍተኛ በድል እያደረሱ ሲሆን በሶማሊያ ክልል ውስጥ በዘረጉት ከፍተኛ የቢዝነስ ስራ ውስጥ ማንም ሌላ ሰው እንቅስቃሴ ማድረግ የማይችል ሲሆን እነሱ በሚሰሩ ቢዝነስ ውስጥ የሚገባ ንብረቱ እንደሚወረስ ታውቋል፡፤ የሞባይል ቀፎዎችን እና የኢሌክትሮኒስ ዕቃዎችን በሕገወጥ መንገድ ጭነው ካለፍተሻ ወደ መሃል ህገር በማምጣት በይርጋ ሃይሌ ሕንጻ ካሉ ወኪሎቻቸው ጋር በመተባበር በመላው ሃገሪቱ እንደሚያከፋፍሉ ታውቋል።
ኢትዮጵያን የሚገዛው ጉጅሌ ሀገራችንን እየወሰደበት ያለው አደገኛ አቅጣጫ አሳሳቢ ከመሆን አልፎ የአደጋውን መራራ ፍሬ ማየት ከጀመርን ሰነበትን። የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች ወሳኝ ከሆነው የወደፊቱ የጋራ ጥቅማቸውና ህልውናቸው በበለጠ ልዩነታቸውና ያለፈ ታሪካቸው እንደዋናው ነገር እየተቆጠረ ለሚሰበከው ስብከት የኢትዮጵያ ህዝብ አስተዋይ ባይሆን ኖሮ እስካሁን ብዙ ጥፋት በደረሰ ነበር።
ህወሃት በህዝቡ ውስጥ የኖረውን ልዩነት የጠብ፣ የግጭትና የመፈራራት መሰረት በማድረግ በሥልጣን ላይ ለመቆየት ካለው ምኞት የተነሳ በመደዴ ካድሬዎቹ አማካኝነት ለዘመናት አብሮ የኖረውን ህዝብ በማቃቃር እኩይ ተግባር ላይ ተጠምዶ ይገኛል።
ህወሃት ይህን የማጋጨት ስራ በተለይ በስልጣን የመቆየት ፍርሃት ባባነነው ቁጥር የሚጠቀምበት መሳሪያ አድርጎታል። በባህርዳር ላይ የብሄረሰቦች ኳስ ጭዋታ ውድድር ምክንያት አድርጎ፣ መደዴ ካድሬዎቹን አሰማርቶ ስታዲዮም ውስጥ ኦሮሞዎች እንዲሰደቡ ካደረገ በኋላ ነገሩን ከማረጋጋት ይልቅ በኦሮሞኛ የቴሌቪዥንና ሬድዮ፣ ኦሮሞዎች በአማራዎች ተሰደቡ ብሎ ያስነገረው ለምንድን ነው? ከዚያ በኋላ በኦሮሚያ የተለያዩ አካባቢዎች ቁጣና ጠብ ለመቀስቀስ ብሎም በዚህ ጠብ ውስጥ ገላጋይ በመምሰል የአንዱ ብሄር ጠባቂ መስሎ ለመታየት ጉዳዩን ባልተረዱ የዋሆች ውስጥ ለመግባት ይፈልጋል። በአማራ ተወላጆች አካባቢ እኛ ከሌለን ኦሮሞ ይፈጇቹኋል፤ በኦሮምያም በሶማሊያም እንዲሁ በተዘጋ በር ውስጥ በተቃራኒው ዘረኝነትንና መከፋፈልን በመስበክ ንጹሃኑ ህዝብ ከፍርሃት ተነስቶ ተገዥ ደጋፊዎቹ እንዲሆኑ በማድረግ ላይ መሆኑንም ያልገባቸው የዋሆች ይኖራሉ። ህወሃትንና ባህርዩን በቅጡ ለምናውቀው ወገኖች ግን ይህ ተንኮሉ ትልቅ ሚስጥር አይደለም።
የጉጅሌው ቡድን የራሱን ስልጣንና የዝርፊያ ኢኮኖሚ ኮርቻ ለማደላደል እስከረዳው ወይም የሚረዳው መስሎ እስከታየው ድረስ ደሃ ገበሬዎችን ማፋጀትን፣ ህዝብን እርስበርስ ማናከስን፣ የቂም መርዝ መዝራትን የሚያየው እንደ ፖለቲካ ጥበብ ነው።
ጉጅሌው ብልጠት መስሎት የጎሰኝነትንና የማንነትን ደመነፍስ የሚነካ ፕሮፖጋንዳ በህዝቡ ውስጥ በመንዛት ሊያደርስ የፈለገው ጥፋት በአብዛኛው ህዝብ ዘንድ ስላልሰራለት የራሱን ሎሌዎችና ተካፋይ መደዴ ካድሬዎችን በማሰማራት የጭካኔ ስራዎችን በማካሄድ ላይ መሆኑን በብዙ መረጃዎች አረገጋግጠናል። በአሁኑ ወቅት በየቦታው የሚካሄደውን የህዝብ ማፈናቀልና ግጭት የሚመራው ራሱ ህወሃት ያሰማራቸው ካድሬዎች እንጂ በራሱ በህዝቡ ተነሳሽነት እንዳልሆነ ሁላችንም ልናውቅ ይገባል። በዚህ ሳይጣናዊ አካሄድ ለምትደርሰው ለያንዳንዷ ጉዳት ሀላፊነት የሚወስደውም ራሱ ህወሃት መሆኑን ግንቦት 7 አጥብቆ ያምናል።
ህወሃት መቃብር አፋፍ ላይ ሆኖ የሚደግስልንን የጥፋት ድግስ ለማምከን የየብሄረሰቡ ልሂቃን ሁሉ አንድ ላይ ሆነን ህዝባችንን እንድንታደግ ግንቦት 7 ለሁሉም የነጻነት ሃይሎች ጥሪውን ያቀርባል።
ግንቦት 7 በዚህ የህወሃት የጨለማ መንገድ ላይ የሚያበራውን የብርሃን ችቦ ይበልጥ በማብራት ላይ ይገኛል። ሁላችንም በምናገኘው የብርሃን ሃይል ጨለማው ላይ እያበራን ከማሳየት አልፈን ወደ መቃብሩ ልንገፋው ይገባል።
ግንቦት 7 በኢትዮጵያ የማንነትና የብሄር ብሄረሰብ ጉዳዮች በሰለጠነ መንገድ እና በመደማመጥ ሁሉንም ተጠቃሚ በሚያደረግ መንገድ መፍታት እንደሚቻል ያምናል። ይልቁንም የወደፊቱ የህዝባችንና የሀገራችን ጥቅም ይበልጥ የሚከበረው በስብጥርነታችን ላይ በምንገነባው አንድነት መሆኑን ያምናል።
የተከበራችሁ የአገራችን ዜጎች የነጻነታችን ጊዜ ቅርብ ነው። ህወሃት መቃብር አፋፍ ላይ ሆኖ ያዘጋጀልንን የጥፋት ድግስ፣ ሀገራችን የጋራ ጠላት በመጣባት ጊዜ ሁሉ እንደምታደርገው በአንድ ላይ ታግለን የጋራ ታሪክ እንሰራ ዘንድ የዘወትር ጥሪያችን እናቀርባለን።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!
በአማራ ክልል ለሚገኙ አመራሮችና አባላት የተደረገውን ስልጠና አስመልክቶ ከብአዴን ጽህፈት ቤት በቁጥር ብአዴን 145/10/ኢህ/06 ለኢህአዴግ ጽ/ቤት አዲስ አበባ በሚል የተጻፈው ደብዳቤ “አብዛኛው ህዝብ አሁንም ለመንግስት ከፍተኛ ጥላቻ” ማሳየቱን ገልጿል።
የብአዴን አመራር እና አባላቱ ከሰላም የዘለለ የልማት ለውጥ አለመምጣቱን፣ ኢህአዴግ ቢቀጥል ባይቀጥል ግድ እንደሌላቸው፣ እንዲሁም መንግስትን በትክክለኛ ዋጋው ሳይሆን በፍርሃት እንደሚያመሰግኑ በሰነዱ ላይ ተዘርዝሮ ቀርቧል።
“የኢትዮጵያ ህዝቦችና አገራዊ ህዳሴያችን” በሚለው የማጠቃለያ ግምገማ ሰልጣኞቹ ” ስለአገራቸው ታሪክ ብዙ ትምህርት መቅሰማቸውን፣ የህዳሴውን ጉዞ ለማሳካት ድርጅቱ እየከፈለ ያለውን መስዋትነት፣ የኢትዮጵያ ገናና ስልጣኔ ለምን እንደወደቀ፣ የህዳሴ ጉዞውን ሊያሳካ የሚችል መንግስት ያለ መሆኑን፣ የብዝህነትና እኩልነት ሀገራዊ ጠቀሜታ ፣ የአማራ ገዢ መደብ ሌሎች ብሄሮችና ብሄረሰቦችን ብቻ ሳይሆን አማራውን ጭምር እንደጨቆነ” የሚያሳይ ትምህርት መውሰዳቸውን ሰነዱ ያመለክታል።
በስልጠናው የብአዴን ታሪክ አብሮ መቅረቡንና ሰልጣኞችም የብአዴንን ታሪክ በማወቃቸው መርካታቸውን ሰነዱ አክሎ ይዘረዝራል።
“ግልጽነት ያልተያዘባቸውና በተግባራዊ እንቅስቃሴ ተከታታይ ውይይትና ስራ የሚጠይቁ ጉዳዮች ምንድን ናቸው?” በሚለው ንጹስ ርእስ ስር ደግሞ ” አሁንም ድረስ ብአዴንን የማይቀበሉ እና ከ97 ጋር በተያያዘ በመንግስት ላይ ተቃውሞ የሚያሰሙ ድምጾች አሉ፣ ነገር ግን የመንግስትን የሃይል እርምጃ ተከትሎ በፍራቻ እንዲኖሩ ማድረግ ተችሎአል።” ሲል አስቀምጧል።
“በውይይቱ ወቅት የታዩ የአመለካከት ችግሮች ምንድን ናቸው?” በሚለው ንዑስ ርዕስ ስር በርካታ ችግሮች ተዘርዝረው ቀርበዋል። ” በ1989 ዓም የነበረው የመሬት ክፍፍል ለቢሮክራቶች ለምን 4 ቃዳ መሬት ተሰጠ? በአማራ ክልል ብቻ የአርሶ አደር መሳሪያ ለምን ተነጠቀ? ልማቱ ወደ ትግራይ ይሄዳል፣ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት አስመራንና አሰብን መያዝ ነበረብን” የሚሉት ጥያቄዎችና አስተያየቶች በሰልጣኞች መቅረቡን ያወሳል።
ሰነዱ በስልጠናው የታዩ ደካማና ጠንካራ ጎኖችንም ይዘረዝራል። ሰልጣኙ እርስ በርስ በመተጋገዝ፣ በመማማር ተሞክሮውን በማካፈልና በመተራረም የነበረው ሁኔታ በሚለው ንጹስ ርእስ ስር ደግሞ ” አሁንም ለመንግስት ህዝቡ በአብዛኛው ጥላቻ ማሳየቱ” የሚል ሰፍሮአል።
የብአዴን አመራርና አባላት ” በአብዛኛው ከሰላም የዘለለ የልማት ለውጥ የለም ” ብለው እንደሚያምኑ፣ “ኢህአዴግ ቢቀጥል ባይቀጥል ደንታ እንደማይሰጣቸው”፣ እንዲሁም “መንግስትን በትክክል ዋጋ ሳይሆን በፍርሃት እንደሚያመሰግኑ” በሰነዱ ማብቂያ ላይ ተገልጿል።
ሰነዱን ለኢሳት የላኩትን የኢህአዴግን ከፍተኛ አመራሮች እንደወትሮው ሁሉ በህዝብ ስም ለማመስገን እንወዳለን።
ሰኔ ፲፯(አስራ ስምንት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና
ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች
ዛሬ ማምሻዉን በጉጉት ከሚጠበቁት ዉድድሮች አንዱ በጀርመን እና በዩናይትድ ስቴትስ ብሄራዊ ቡድኖች መካከል የሚካሄደዉ የእግር ኳስ ግጥሚያ ነዉ። የብዙዎችን ዐይን ወደ ሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ እንዲያተኩር የሚያደርገዉ ደግሞ በምናባዊ ትንታኔ በሁለት የጀርመን ቡድኖች መካከል የሚደረግ ፉክክር መምሰሉ ነዉ።
በናይጀሪያ ሰዓት አቆጣጠር ትናንት አመሻሹ ላይ በዋና ከተማ አቡጃ ህዝብ በሚያዘወትረዉ የገበያ ማዕከል የደረሰ ፍንዳታ ለ21 ሰዎች ህይወት መጥፋት ምክንያት ሆኗል። ከ50 በላይ ሰዎችም መጎዳታቸዉ ተነግሯል።
የኬንያ ተቃዋሚ ፖለቲከኞች መንግሥት ጥያቄአቸውን እንዲቀበል ያቀረቡት ጥሪ በጎ ምላሽ ካላገኘ በሃገሪቱ የሰፈነው ውጥረት ሊባባስ እንደሚችል አንድ የፖለቲካ ተንታኝ አስታወቁ ።
ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስ እና የባህል ድርጅት በ«UNESCO» ዘጠኝ መካነ ቅርሶችን እና አንድ የማይዳሰስ ቅርስን፤ በአጠቃላይ አስር ታሪካዊ ቅርሶችን አስመዝግባለች። ጀርመን ደግሞ ከስፔን እና ከጣልያን ለጥቃ 39 ቅርሶችን በዓለም ቅርስነት በማስመዝገብ ሶስተኛዋ የዓለም ሀገር ናት።
የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የአዲስ አበባ ምክር ቤት ባደረገው መደበኛ ስብሰባ በቀረበው ሪፖርት ላይ በመወያየት የ3 ወር ሪፖርት አጽድቋል፤ የተጓደሉ የሥራ አመራር አባላትን በምርጫ አሟልቶ አዲስ የስራ ድልድል አድርጓል በዚህም መሰረት፡ – 1. አቶ ዘካርያስ የማነብርሃን ………….. ሊቀመንበር 2. አቶ ደምሴ መንግስቱ ………………… ም/ሊቀመንበር 3. አቶ እንግዳወርቅ ማሞ……………… ፀሐፊ 4. አቶ ነብዩ ባዘዘው …………………….. […]
ፕሮፌሰር አለማየሁ ገ/ማርያም
ትርጉም – ነጻነት ገብሬ
በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ወንጀል
ፍፃሜ መሪ ተዋንያን ሆነው ከቆዩ በኋላ በመሰደድ በአሜሪካ እራሳቸውን
ደብቀው በተቀመጡ የሰብአዊ መብት ደፍጣጮች ላይ የዩናይትድ
ስቴትስ አሜሪካ የፍትህ መምሪያ ጥቆማእንዲቀርብለት
ኢትዮጵያውያንን/ትን በማበረታታት ላይ ይገኛል፡፡
ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ (ከቃሊቲ እስር ቤት)
በጋዜጠኛ ኤሊያስ ገብሩ
ቅዳሜ ሰኔ 14 ቀን 2006 ዓ.ም ከታች በፎቶግራፍ የምንታይ [ፎቶግራፉን ያነሳው አብነት ረጋሳን ጨምሮ] fጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በዓለም የጋዜጠኞች እና የዜና አታሚዎች ማኅበር የዓመቱ የወርቅ ብዕር የ “pen Golden of freedom 2014″ ተሻላሚ በመሆኑ ‹‹እንኳን ደስ ያለህ›› ለማለት ኬክ አስጋግረን ወደቃሊቲ አምርተን ነበር፡፡
ቁጥራችን መብዛቱ በቃሊቲ ያሉ ፖሊሶችን ግር ማሰኘቱ አልቀረም ነበር።
ሰኔ ቅዳሜ 21 ቀን ፣ በመቀሌ ከተማ የተቃዉሞ ሰላማዊ ሰልፍ እንደተጠራ፣ የአረና አመራር አባል አቶ አብርሃ ደስታ ገለጹ። ሰልፉ በከተማዋ አስተዳደር እውቅና እንዳገኘ የገለጹት አቶ አብርሃ፣ በባህር ዳር፣ በደሴ፣ በአዲስ አበባ እንዲሁም በሌሎች በርካታ ከተሞች እንደታየው የመቀሌ ሕዝብ የሕወሃት ደጋፊ እንዳልሆነ የሚያሳይበት አጋጣሚ እንደሚሆን አስረድተዋል። «የትግራይ ህዝብ እስካሁን ድረስ ሰለማዊ ሰልፍ የማድረግ መብቱ ተነፍጎ ይገኛል። […]
ደረጃውን የጠበቀ የሕክምና አገልግሎት የሚሰጥ ሆስፒታል በመቶ ሚሊየን ዶላር ወይም ወደ ሁለት ቢሊየን ብር በሚጠጋ ወጭ አዲስ አበባ ላይ ለመገንባት በዝግጅት ላይ መሆኑን የኢትዮ-አሜሪካዊያን ሃኪሞች ቡድን አስታውቋል፡፡
የቡድኑ መሪዎች በሰጡት መግለጫ የሚገነባው ሆስፒታል ውጥን የኢትዮጵያንና የአካባቢዋን፣ አልፎም የመላ አፍሪካን የጤና አገልግሎት ደረጃ ትርጉም ባለው መልኩ የሚቀይር ማዕከል ማቋቋም መሆኑን ገልፀዋል፡፡
የላቀ ሙያና አገልግሎት ማዕከልም እንደሚመሠረት አመልክተዋል፡፡
ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
በደቡብ ሱዳን ዋና አደራዳሪ አቶ ስዩም መስፍን የተመራ የምሥራቅ አፍሪካ ሃገሮች የጋራ ልማት ባለሥልጣን – ኢጋድ ልዑካን ቡድን ወደ ወደ ዓለሙ የፀጥታ ጥበቃ ምክር ቤት ሄዷል፡፡
ቡድኑ ከአዲስ አበባ ወደ ኒው ዮርክ የተነሣው ትናንት ሲሆን አባላቱ ሰሞኑን ከፀጥታ ጥበቃ ምክር ቤቱ ጋር ሲገናኙ የደቡብ ሱዳን ባላንጦችን ለማገናኘት እና ለማወያየት ሲያደርግ በቆየው ጥረት ላይ ማብራሪያ ለመስጠንና ለመወያየት መሆኑን ለባለሥልጣኑ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ገልፀዋል፡፡
ኢጋድ የያዘው ሽምግልና አካል የሆነው ብዙ ወገኖችን ያሳትፋል ተብሎ ተጠብቆ የነበረው የአዲስ አበባ ድርድር የጠረጴዛ ዙሪያ ውይይቱ ውክልና ጉዳይ አላስደሰተንም በሚል ተቃዋሚዎቹ ተደራዳሪዎች ለከትናንት በስተያ ሰኞ ተይዞ በነበረው የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ ሳይገኙ መቅረታቸው…
USAID, Maternal and Child health
Meriam Yehya Ibrahim
Ethio-American doctors to build a hospital in Ethiopia
እንደሚታወቀው የኢትዮ – ኤርትራ ጦርነት በሁለቱም አገሮች ከባድ የሚባል መስዋእትነት ተከፍሎበታል። ይህ ጦርነት ሲጀመር ምክንያቱ ምን ነበር? ለመንስ ተደረገ? መቸና ለመን እንዲቆም ተደረገ? በግዜው ጦርነቱ ሲጀመር አንዳንድ የፖለቲካ ተንታኞችና ኢህአዴግ እንዳሉት ከሆነ የኤርትራ መንግስት ኢኮኖሚያዊ ችግር ነው ይላሉ። እውነቱ ይሀ ከሆነ ሆድ ይፍጀው። ለማነኛው ዛሬ ድረስ የእነዛን ጥያቄዎች መልስ ሳይፈታ ይሀው 16 ዓመታት አልፎ ቋጠሮውን […]
ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች
የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በሀዋሳ ከተማ ሰኔ 15 ቀን 2006 ዓ.ም ሊያካሂደው የነበረውን ህዝባዊ ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ተከትሎ በእስር ላይ የሚገኙት የአንድነት ፓርቲ አባላት ባለፈው ሰኞ ሰኔ 16 ቀን 2006 ዓ.ም በሃዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበው የዋስትና መብታቸው ተነፍጎ በግዜ ቀጠሮ ለአርብ ሰኔ 20 ቀን 2006 ዓ.ም የተቀጠሩ ቢሆንም በዛሬው እለት ሰኔ 18 ቀን […]
የኢጣልያ ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን፣ ፣ኮስታ ሪካ፤ ዑሩጓይና ኢንግላንድ ከሚገኙበት መ ምድብ፣ ትናንት ከዑሩጓይ ጋር ባደረገው ግጥሚያ እኩል ለኩል መለያየት ብቻ ለቀጣዩ ዙር ግጥሚያ ከኮስታሪካ ጋር በሁለተኛነት ለማለፍ የነበረው ዕድል በ 1-0
ጫት ወደ ብሪታንያ እንዳይገባና እንዳይሸጥ ብሎም፤ ጫት ሲቅምም ሆነ ሲሸጥ የሚገኝ ሰው በገንዘብ እንደሚቀጣና ለእሥር እንደሚዳረግ የወጣው ድንጋጌ ከትናንት አንስቶ ተግባራዊ መደረጉ ተነገረ። ሕጉ ሥራ ላይ መዋሉ ፤
በዓለም ዙሪያ የውጭ ባለሃብቶች ውረታ እጎአ በ2013 አፍሪቃን ጨምሮ አድጓል ። ግን በአፍሪቃ የእድገቱ መጠን ከሌላው የዓለም ክፍል ጋር ሲነፃጸር ዝቅ ያለ ነው ። የተባበሩት መንግሥታት የንግድና የልማት ጉባኤ በምህፃሩ UNCTAD ትናንት ባወጣው ዘገባ መሠረት በዓለም ዙሪያ የመሰረተ ልማት ግንባታና የኩባንያዎች እንቅስቃሴ በ9 በመቶ አድጓል ።
በመላ ኢትዮጵያ የሚታየው የጨው እጥረትና ውድነት፣ በአንጻሩ ደግሞ አፋር ውስጥ ፣ በአፍዴራ፣ ዶቢና ካዳባ በተሰኙት ቦታዎች ያለው የጨው ክምችት፣ ጤናማ የግብይት ሥርዓት አለመኖሩን ያመለክታል ይላል አካባቢውን ጎብኝቶ የተመለሰው ዘጋቢአችን ፣ ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር ።
ኢትዮጵያ፤ ከባሕር ልክ በታች 120 ሜትር ዝቅ ካለው ቦታ አንስቶ 4,620 ሜትር ከፍታ እስካለው ሥፍራ ፣ የሚያቃጥል የቀን ሐሩር ፣ የሚያኮማትር የሌሊት ቁር ፣ እንዲሁም ለዘብ ያለ የአየር ጠባይ ያላት ሀገር በመሆኗ ፤ ላገር ጎብኝዎች መስሕብነት
![]() |
| Poster Credit Mahilet Solomon |
Ethiopia, Anti-Corruption Commission, report
በሱዳን ሻሪዓ መሠረት ሃይማኖቷን ወደ እሥልምና እንድትቀይር ታዛ እምቢ በማለቷ እንድትሰቀል ተፈርዶባት የነበረችው የክርስትና ዕምነት ተከታይ ሴት ከእሥር ከተፈታች በኋላ እንደገና በቁጥጥር ሥር ውላ እንደገና ተለቅቃለች፡፡
ደምወዝ ጭማሪ ..የምርጫ ጉቦ …. በደምወዝ ጭማሪ የመንግስት ሰራተኛውን የፖለቲካ ባሪያ ማድረግ አይቻልም።ደምወዝ ተጨምሮልሃል የተባለው ከመጋረጃ ጀርባ አንገቱን እንዲሰብር እየተደረገ ያለው የመንግስት ሰራተኛ ማንን እንደሚመርጥ እና ድምጹንም እንደማያባክን ጠንቅቆ ያውቃል። የደሞዝ ጭማሪው የወያኔን አጣብቂን ውስጥ መዘፈቅን ያሳያል። ውሻ ጆሮውን ቆርጠው ቢሰጡት ስጋ የሸለሙት ይመስለዋል .በሚል ወያኔያዊ የፖለቲካ ብሂል ተነስቶ ለመንግስት ሰራተኛው የደሞዝ ጭማሪ ለማድረግ እንደሚፈልግ […]
ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች