ኢትዮጵያ ውስጥ ፤ ከአዲስ አበባና አካባቢዋ ጋር የተጣመረውን የልማት መሪ አቅድ፤ የገጠር አርሶ አደሮችን ከርስት ጉልታቸው አፈናቅሎ ለችግር ይዳርጋል በማለት፣ በኦሮሚያ ፌደራል መስተዳድር የተለያዩ ከተሞች የሚኖሩ የዩንበርስቲ ተማሪዎች የተቃውሞ ሰልፍ

ከጀኔቭ የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብት ኮሚሽን እንደዘገበው፣ መንግሥት በሚወስደው ብርቱ የጭቆና ርምጃና ዜጎችንም በመላ ለዐሠርተ ዓመታት ለብሔራዊ ወታደራዊ አገልግሎት ስለሚያሠማራ በየወሩ ከሞላ ጎደል 4,000 ኤርትራውያን አገራቸውን እየለቀቁ ይሰደዳሉ ።

ወቅቱ የአለም የእግር ኳስ ዋንጫ የሚተላለፍበት፣ ከልጅ እስከ አዋቂው ወንድ ሴት ሳይል ከቴሌቪዥን ፊት ለፊት ተቀምጦ ከብራዚል የሚተላለፉትን የእግር ኳስ ግጥሚያዎች የሚመለከትበት ነው።

“እስሩ ቅስቀሳውን አያስተጓጉለውም” አንድነት ፓርቲ በአዋሳ ከተማ የጠራውን ሰላማዊ ሰልፍ ተከትሎ የፓርቲው ብሄራዊ ምክር ቤት አባልና በአንድነት ፓርቲ የሴቶች ጉዳይ ስራ አስፈፃሚ የሆኑትን ወ/ሪት እልፍነሽ ከበደን የተሳፈሩበትን ሚኒባስ በማስገደድ ወደ ምስራቅ ክ/ከተማ ፖሊስ ጣቢያ ተወስደዋል ፡፡ ሀላፊዋ ከጠዋቱ 4፡00 ጀምሮ በጣቢያው ታስረው የሚገኙ ሲሆን በምን ምክንያት ቁጥጥር ስር እንደዋሉና እስከመቼ በእስር እንደሚቆዩ ለማወቅ እንዳልቻሉ ገልፀዋል […]

በሰሜን ጎንደር ምዕ/አርማጨሆ ወረዳ አብርሃጅራ ከተማ የአንድነት ፓርቲ የወረዳ የፋይናንስና የምርጫ ጉዳይ ኃላፊ የሆነው አቶ ደስታው ተገኝ ከአ.አ ዩኒቨርስቲ በ2000 ዓ.ም በቢዝነስ ኢዱኬሽን የመጀመሪያ ዲግሪ ካገኘ በኋላ በሐረር፣ በጎንደር ያስተማረ ሲሆን በም/አርማጨሆ ትምህርት ቢሮ ጽ/ቤት የመማር ማስተማር ጉዳይ ፈፃሚ ሆኖ ከ4 ዓመት በላይ አገልግሏል፡፡ በት/ቢሮው ለማስትሬት ትምህርት ዕድል ብቸኛ ተወዳዳሪ የነበረ ቢሆንም ለ3 ዓመታት ተከልክሏል፡፡ […]

የደቡብ ክልል ዋና ከተማ ናት። በርካታ ብሄረሰቦች በፍቅር የሚኖሩባት ዉብ ከተማ። ሰኔ 15 ቀን 2006 ዓ.ም ደሴን፣ ባህር ዳርን፣ አዳማን፣ ጊዶሌን አዲስ አበባ እና ደብረ ማርቆስን በመቀላቀል ድምጿን ታሰማለች። አዋሳ !!!! የሚሊዮኖች ድምጽ ለፍትሕና ለመሬት ባላቤትነት በሚል መርህ በሐዋሳ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ተጠርቷል። ለሰልፉ የከተማዋ ባለስልጣናት እውቅና የሰጡ ሲሆን፣ የአንድነት አባላትን ደጋፊዎች ቅስቀሳ ጀምረዋል። የሰላማዊ […]

ያቋረጥነውን የሰላም ድርድር ለመቀጠል የፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪርን መመሪያ እየጠበቁ መሆናቸውን የደቡብ ሱዳን ማስታወቂያ ሚኒስትርና የመንግሥት ተደራዳሪዎች ቃል አቀባይ አመልክተዋል፡፡

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የአፍሪቃ ሕብረት ፣ የግብፅ ጦር ኃይል በወታደራዊ መፈንቀለ መንግሥት፤ የቀድሞውን በዴሞክራሲ የተመረጡትን ፕሬዚዳንት ከሥልጣን እንዲወገዱ አድርጓል በማለት ፣ የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት መሥራች የሆነችውን ሀገር አንድ ዓመት ያህል ከአባልነት አግዶአት

በመስጊዶች እና ቤተክርስትያን ዉስጥ የሚገኙ ጥንታዊ የሥነ-ጽሑፎች አብያተ-መጻሕፍት፤ የአንድ ሀገር፤ አህጉር ብሎም የሰዉን ልጅ የእድገት ታሪክ ያዘሉ በመሆናቸዉ እንክብካቤ እና ልዩ ጥበቃ ሊደረግላቸዉ ይገባል።

ኢራቅ ዉስጥ የሱኒ ሚሊሺያዎች የሀገሪቱን ሁለተኛ ታላቅ ከተማ ሞሱልን ከያዙና በባግዳድ አካባቢም ጥቃታቸዉን ካጠናከሩ ወዲህ የፕሬዝደንት ኑሪ አልማሊኪ ሺአቶች የሚበዙበት መንግስት ህልዉና አደጋ ላይ መዉደቁ እየተነገረ ነዉ።

የዓለም የስደተኞች ቀን በነገዉ ዕለት ይታሰባል። በያዝነዉ በተለይም ጦርነት እና ግጭት ከሚካሄድባቸዉ ሃገራትና አካባቢዎች የሚሰደዱት ሰዎች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል የተመ የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን UNHCR ባለፈዉ ወር ነዉ የጠቆመዉ።

በቅርቡ የታጠቁ ግለሰቦች ከዶላር ጋር በተያያዘ በመሃል አዲስ አበባ በጠራራ ጸሃይ ሁለት ሚሊዮን ብር በመዝረፍ መሰወራቸውን ተከትሎ የተገኙ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ዘረፋውን የፈጸሙት ግለሰቦች በአቶ ጌታቸው እና በአቶ ኢሳያስ የሚመራው የደህንነት የማፊያ ቡድን አባላት መሆናቸው ታውቋል። እስካሁን በምርመራ ላይ ተብሎ ሌሎችን በመያዝ ካለወንጀላቸው ያሰረው ፖሊስ ከሳሾች የተባሉትን በመክሰስ እንዲሁም ከሳሾች ዘራፊ ግለሰቦቹ እነዚህ አይደሉም ቢሎም ፖሊስ ለመስማት ፈቃደኛ አልሆነም።

በመከላከያ ሰራዊት የሕወሓት መኮንኖች ስር የሰደደው የሙስና እና የዘረፋ አድራጎት በደህንነት መስሪያ ቤት ውስጥም ከሹሙ ከአቶ ጌታቸው እና ከባለስልጣኖቻቸው ጀምሮ እስከ ገራፊዎች ድረስ መንሰራፋቱን ውስጥ አዋቂ ምንጮች ገልጸዋል:: እንደውስጥ አዋቂ ምንጮቹ መረጃ ከሆነ የደህንነት ባለስልጣኖቹ የተዘፈቁበት የሙስና ተግባር በተጨማሪ ዘረፋን እና ሴት መድፈርን እንዲሁም የቡድን ወንጀሎችን ያካተተ መሆኑ ተጠቁሟል::በተለያዩ ከተሞች የሚገኙ ባለሃብቶችን በማስፈራራት ከፍርድ ቤት ትእዛዝ ውጪ በማሰር እንዲሁም የሙስና ወንጀል ተገኝቶብሃል ይህን ያህል ገንዘብ አምጣ ካላመጣህ እንገድልሃለን እስከማለት በከመድረሳቸውም በተጨማሪ ይህንን ጉዳይ ለፖሊስ የጠቆመ ባለሃብት በማፈን ንብረቱ ባማገድ እና በተለያዩ ስልቶች የተጠየቀውን ገንዘብ እንዲሰጥ በማስገደድ ላይ መሆናቸውን ምንጮቹ ጠቁመዋል::

ከዚህ ቀደም በሙስና የተከሰሱ የስርኣቱ ባለስልጣናትን ተገን በማደርግ በአዲስ አበባ ውስጥ የሚገኙ ባለሃብቶችን በመከታተል እና ደህንነት ቢሮ ድረስ በመውሰድ በሙስና ከታሰረው ስም እየተጠቀሰ … ከሚባል ባለስልጣን ጋር ግንኙነት አለህ ማስረጃ ተገኝቶብሃል በማለት በፈጠራ ወንጀል ባለሃብቱን በመዝረፍ ስራ ላይ ተሰማርተው የነበረ እና እንዲሁም የአዲስ አበባን ቆነጃጅት ቢሯቸው ድረስ በግብረአበሮቻቸው አፋኝነት እና አስገዳጅነት በመውሰድ ካለፍላጎታቸው አስገድደው በመድፈር ላይ ናቸው ያሉት ምንጮቹ ተራ የደህንነት አባላት ለዚሁ ተልእኮ ተሰማርተው የሚሰሩት ምንም አይነት ወንጀል በቡድን ሲፈጽሙ የሚጠይቃቸው አለመኖሩን የሕዝቡን በደል የከፋ አድርጎታል::

ኢትዮጵያውያን በሕወሓቱ የደህንነት መዋቅር የሚመራ የሽብር ተግባራትን አጥብቆ ስለሚፈራ እና በየጊዜው በሕወሓት ደህንነቶች መሪነት የሚወሰዱ እርምጃዎች በሃገሪቱ ውስጥ ከፍተኛ ስጋትን በመፍጠራቸው በየእስር ቤቱ የሚካሄዱ ሕገወጥ ጸረ ፍትህ ተግባራት እና የሰብኣዊ መብት ጥሰቶች የኢትዮጵያውያን የቀን ተቀን አጀንዳ ሆነው መምጣታቸው ገዢው ፓርቲ ሕዝቡን ምን ያህል እንዳሸበረ ይጠቁማል ሲሉ ምንጮቹ አክለው ገልጸዋል::
#ምንሊክሳልሳዊ

‹‹መመሪያው በኦርቶዶክሳውያን ተማሪዎች ላይ በማተኮር በአድሏዊነት ይፈጸማል›› /ተማሪዎቹ/ ‹‹መንግሥት ለሙስሊም ኾነ ለክርስቲያን ተማሪዎች በልዩ ኹኔታ ምግብ እንዲዘጋጅ ፈቅዷል›› /የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የሚያዝያ ፳፻፮ ዓ.ም. የመመሪያው አጸፋዊ ማብራሪያ/ ‹‹ዩኒቨርስቲው ያወጣው መመሪያ ላይ እንዲህ የሚል የለም፤ ሴኩላሪዝም ባለበት ዩኒቨርስቲና በዩኒቨርስቲው የሴኔት ሕግ መሠረት የሰኔን ጾም ይኹን ሌላውን ጾም የማጾም ግዴታ የለብንም፤ ዩኒቨርስቲው የራሱ ፕሪንስፕልና መመሪያ አለው፡፡›› /በአድሏዊነት …

 

የምሥራቅ አፍሪካ ሃገሮች የጋራ ልማት ትብብር ተቋሙ ኢጋድ አንድ ባለሥልጣን በደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር እና በተቃዋሚው መሪ ሪያክ ማሻር ላይ የዘለፋ ቃል ሠንዝረዋል በሚል በሁለቱ ወገኖች መካከል ይካሄድ የነበረው ውይይት ተቋርጧል፡፡

ውይይቱ የተስተጓጎለው ተቃዋሚዎቹ በሰዓቱ ባለመገኘታቸው ጭምር ነው ሲሉ አንድ የመንግሥቱ ቃል አቀባይ የተናገሩ ሲሆን ተቃዋሚዎቹ ደግሞ የተሟላ ውክልና ስለመኖሩ ሥጋት አለን ብለዋል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ ተቃዋሚዎቹ ባለፈው ዕሁድና በማግስቱም ሰኞ በናስር ከተማ ላይ ጥቃት አድርሰዋል ሲሉ የአፐር ናይል ግዛት ባለሥልጣናት ክስ አሰምተዋል፡፡

ጥቃቱ በደረሰ ወቅት በመረጋጋቱ የተበረታቱ ሰላማዊ ነዋሪዎች ወደ ከተማይቱ እየተመለሱ እንደነበረ ባለሥልጣናቱ አመልክተዋል፡፡

የተቃዋሚዎቹ ቃል አቀባይ ግን…

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

Image

ዜጎችን መታደግ የማይችሉ በአስቸኳይ ቆባቸውን አውልቀው ከተራው ሕዝብ የመቀላቀል ግዴታ አለባቸው።
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

ቤተክርስቲያን እና መንግስት በኢትዮጵያ ውስጥ እጅና ጓንት ሆነው በኢትዮጵያውያን ላይ የማያባራ ጭቆና ማካሄድ ከጀመሩ ረዥም ዘመናት ተቆጥረዋል። ይብልጡኑ የመንግስቶች ጎህ ከቀደደ ጀምሮ በተለይ የተዋህዶ ሃይማኖት መሪዎች አስፈሪ እና አስደንጋጭ እንዲሁም አሳዛኝ ደግሞም አሳፋሪ ቃላቶችን በመጠቀም ስጋዊ እና ምድራዊ ስልጣኖችን ለገዢዎች ለማደላደል ይህ ነው የማይባል ግፍ በምእመናኖቻቸው እን በሌሎች አማኞች ላይ ፈጽመዋል አስፈጽመዋል፤ እየፈጸሙ ነው፤ እያስፈጸሙ ነው። ይህ የማይዋጥለት አሊያም የሚክድ ካለ እውነት የማይደላው ብቻ ነው።

የኢትዮጵያ ጨቋኝ መንግስታት የሆኑ ከጥንት እስከ ዛሬ የተንሰራፉ በህዝብ ላይ የሚያደርጉት ጭቆና እና በደል ታሪክ የማይሽረው ጠባሳ በሰው ልጆች የትውልድ ሂደት ላይ መፍጠሩ እንደተጠበቀ ሆኖ የሃይማኖቶች ሚና ግን እጅግ በሚያሳዝን መልኩ ዜጎች በግፍ በጨቋኝ መንግስቶች ሲታረዱ በመባረክ የመንግስታቱን እድሜ አስረዝመዋል አሁንም እያስረዘሙ ነው። የመንግስት እና የሃይማኖት ቁርኝት የሚፈለገው ስልጣንን አደላድሎ ለመያዝ እና ህዝብን ረግጦ ለመግዛት ካለ ምኞት እንጅ ለዜጎች ከመቆርቆር የመነጨ አይደለም። የሃይማኖት አባቶች በሃይማኖታዊ የመንፈስ ጥኡም ሰበካና ዜማ ጋር በማጣፈጥ የጨቋኞችን የበላይነት በመስበክ ማስፈራራት እና ማሸማቀቅ የጳጳሳት እና የሼህዎች አብይ ተግባር ነው።
በኢትዮጵያ ውስጥ ተገዝተው አሊያም አድርባይ ሆነው በመስራት ላይ ያሉ የሁሉም ሃይማኖት መሪዎች እጅግ ጥንቃቄ በጎደለው ሁኔታ በዜጎች ላይ የሚደርሱ ግድያዎች ድብደባዎች እስሮች እና መንገላታቶችን እንደ አንድ መንፈሳዊ የሃይማኖት መሪ እንደ ሰብአዊ ተፈጥሮ አሊያም መጽሃፋቸው እንደሚያዛቸው ለዚጎች ሲደራደሩ ሲከራከሩ ሲዋያዩ ሲሆንም አንተም ተው አንተም ተው ሲሉ አልታዩም ከዚህ በከፋ መልኩ በልማታዊ ዲሞክራሲ የፖለቲካ ፉጨት ስር ተደብቀው በለው በሚል አብዮታዊ ዜማ ዜጎችን እያስፈጁ ይገኛሉ።

አንድ የሃይማኖት አባት የታመመ ሲጠይቅ፤ የሞተ ሲቀብር ፤የተቸገር ሲረዳ ፤የታሰረ ዞሮ በመጎብኘት ሲያጽናና እንጂ ሲፖተልክ አሊያም ሲወሸክት ማየት ያማል። በሃገራችን ምእመናንን እንምራለን የሚሉ ሕዝብን መንፈስ እንመግባለን የሚሉ የለሊት ወፍ የሆኑ የክርስትና እና እስልምና የሃይማኖት መሪዎች ዜጎችን መታደግ የማይችሉ ከሆነ በአስቸኳይ ቆባቸውን አውልቀው ከተራው ሕዝብ መቀላቀል ግዴታ አለባቸው። ይህ ጉዳይ የብዙሃኑ የዜጎች ጉዳይ ስለሆነ ክርስቲያን እስላም የሚባልበት ሳይሆን የኢትዮጵያውያን የጋራ ጉዳይ ነው።

Image

በሃገሪቱ ዜጎች በአለም ላይ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በነጻነት በመጻፋቸው የእኩልነት እና የነጻነት ጥይቄ በማንሳታቸው ብቻ አሸባሪ ተብለው እስር ቤት በታጎሩባት ኢትዮጵያ ጉዳዩን እስኪ ላስጠናው ላጥናው ያለ የሃይማኖት መሪም ይሁን የሃይማኖት ሃራጥቃ የለም። እንዲሁም በታሰሩ ሰዎች እና በአሳሪዎች መካከል እርቀ ሰላም እንዲወርድ ለወደፊቱ ስህተቶች ካሉ እንዳይደገሙ ነገሮችን ለማግባባት እና ለማቻቻል የፈቀደ አንድም የሃይማኖት መሪ የለም። ይብስኑ የሃይማኖት መሪዎቹ በየስብሰባው እና በየጭብጨባው ዜጎች የመንግስታዊ ሽብር ዱላ ሰለባ እንዲሆኑ እያበረታቱ ይገኛሉ ።

የዜጎች ሁኔታ ያሳሰባቸው የሃይማኖት መሪዎች በከፍተኛ ዛቻ እና ማስፈራራት እንዲሁም በጥቅም በማሰር እንዳይንቀሳቀሱ አሊያም በተዘዋዋሪ ባልሰሩት ወንጀል ለማጥመድ ሴራ በመጎንጎን እያስፈራሩ የህዝቦችን የሰብ አዊ መብት ጥያቄዎች እንዳያነሱ በማስደንገጥ እንዲሁም በጥቅማ ጥቅም እና በገንዘብ በመደለል አባትነታቸውን ለስጋዊ ባለስልጣናት እንዲሸጡ እና የፖለቲካ ምንዝር እንዲፍጽሙ እየተደረገ ሲገኝ ይህንን የምንዝር ጌጥ ከመለማመዳቸው የመጣ የሃይማኖት አባቶች ከጨቋኞች ብሰው በሕዝብ ላይ ከፍተኛ በደል እንዲፈስም ከባዱን ሚና እየተቻውቱ ይገኛሉ ።

የሃይማኖት አባቶች ሰጥ ለጥ ብለው ስለልማት ብቻ እንዲሰብኩ የእስላሙንም ሆነ የክርስቲያኑን ጥያቄዎች በተገኙበት እንድያስተጋቡ ማስጠንቀቂያ ከተሰጣቸው አባቶች መካከል አቡነ ማትያስ አቡነ ሉቃስ እና ሌሎችም ተጠቃሾች ናቸው እንዲሁም የወያኔ መንግስት በቅርቡ ለሾማቸው የእስልምና ምክር ቢት ሼሆችን ከፍተኛ የሆነ ምክር አዘል ማስጠንቀቂያ አስተላልፏል። እኔ ስጨፈጭፍ እናንተ አጨብጭቡ የሚለው አሸባሪው የወያኒ መንግስት ሃይማኖቶችን በራሱ አይዲኦሎጂ በመቀጽ ቀሚሳቸውን ያንዥረገጉ ሰላዮችን እና የሃይማኖት ነቅእዞችን በመመደብ ዜጎችን በተመለከተ የሚደርሱ በደሎች እና ገፈፋዎች ጠያቂ እንዳያገኙ አስታራቂ እንዳይሹ አድርጓል። ፓትርያርኩ ተንገላተው ከተለቀቁ በኋላ በማህበራዊ ድህረገጾች ላይ ብዕራቸው ለምን ታቀበ? ከፋሲካ ክብረ በአል በኋላ በትዊተር ላይ እንዳልተገኙ የሚነገርላቸው ፓትርያርኩ ራሳቸውን ከማንኛውም አንደፋዳፊ ንግግር በመቆጠብ በተረጋጋ መልኩ አንገታቸውን እንዲሰብሩ እና በቅርባቸው ለተመደቡላቸው የመንግስት ደህንነቶች /አማካሪዎች ተገዢ እንዲሆኑ ተደርጓል።

ዜጎቹን የማይታደግ የሃይማኖት መሪ ቆቡን አውልቆ ከፖለቲካው ጎላ ልኢቀላቀል አሊያም ገለልተኛ ሰው ሆኖ እንዲቀመጥ ለመምከር እንፈልጋለን ። በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ሃይምኖቶች ለመንግስታዊ ሽብር ተገዢ እና ታዛዥ እንዲሁም የሽብር ሰባኪ ሆነው ዜጎችን በአደባባይ እያስግደሉ ዜጎች ከሞቱ በኋላ በሃይማኖታቸው ስር አት እና ደንብ እንዳይቀበሩ ተጽእኖ በማድረግ ለምድራዊው የጨቋኝ ምደብ ተባባሪ እና አስተባባሪ በመሆን ከባድ ወንጀል እየፈጸሙ ይገኛሉ። ስለዚህ በዜጎች ላይ የሚደርሱ በደሎች የማይቆረቁራቸው የሃይማኖት አባቶች ሊወገዱ ይገባል።
http://minilik-salsawi.blogspot.com/201 … st_18.html
ማሳሰቢያ ፦ በዛሬው እለት በኦርቶዶክስ በእስልምና በካቶሊክ እና ከመካነ እየሱስ ቤተክርስቲያን የተዘዋወረው የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ቡድን ያሰባሰበውን ጉድ የያዘ መረጃ በቅርቡ በይፋ እናወጣዋለን ይጠብቁን።

ዋና ጽ/ ቤቱ በሙዑንሸን፤ ደቡብ ጀርመን የሚገኘው፣ የአውሮፓ የአዲዲስ ግኝቶች የባለቤትነት መብት መዝጋቢና ዕውቅና ሰጪው መ/ቤት ከተለያዩ የአውሮፓ ሃገራት በአንድ ዓመት ውስጥ፤ የፈጠራ ውጤት ባለቤትነት መብት ለማግኘት፣ 265,690 ማመልከቻዎች ናቸው የደረሱት።

ከማራኪ ጨዋታ ጋር በሰፊ ብልጫ ተጋጣሚዎቻቸውን ፤ ሆላንድ እስፓኝን፣ 5-1 ፣ ጀርመን ፖርቱጋልን 4-0 ያሸነፉበት ሁኔታ በኳስ ጨዋታ ተመልካቾችና ሐያስያን በሰፊው ሲወሳ ፣ የሌሎቹ ያን ያህል አድናቆት አልተቸረውም።

ዋና ጽ/ ቤቱ በሙዑንሸን፤ ደቡብ ጀርመን የሚገኘው፣ የአውሮፓ የአዲዲስ ግኝቶች የባለቤትነት መብት መዝጋቢና ዕውቅና ሰጪው መ/ቤት ( በጀርመንኛው Europäsche Patentamt)ከተለያዩ የአውሮፓ ሃገራት በአንድ ዓመት ውስጥ፤ የፈጠራ ውጤት ባለቤትነት መብት ለማግኘት፣ 265,690 ማመልከቻዎች ናቸው የደረሱት።

የእሥራኤል ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አቪግዶር ሊበርማን በኢትዮጵያ ይፋ ጉብኝት አደረጉ። አቪግዶር ሊበርማን እና እሳቸው የመሩት የልዑካን ቡድን ከሀገሪቱ ባለሥልጣናት እና ከንግዱ ማህበረሰብ ጋ ተገናኝተው ሀሳብ ተለዋውጠዋል።

የኬንያ መንግሥትም ፦ ምክትል ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በተደጋጋሚ እንዳሉት ለአሸባሪዎች ዛቻ ተንበርክኮ ጦሩን አያስወጣም።እና ለኬንያ-ሶማሊያ ዉስጥ የመዋጋት፤ኬንያ ዉስጥ የመጠቃት መወዛገቡ አዙሪት-ይቀጥላል።

አዲስ-አበባ ምርጥ ሆቴሎች እየዋሉ-እያደሩ እንዲደራደሩ አሥራ-ሰባት ሚሊዮን ዶላር የፈሰሰላቸዉ ሹማምንት ግን የዚያን ሕዝብ-እልቂት-ስደት ፤ ችግርና ችጋር ለማቆም ተነጋገሩ-ሲባሉ እንቢኝ ይላሉ።«እሺ» እንዲሉ ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ «ቆንጠጥ»-ሊያደርጋቸዉ ይገባል።

በምስራቅ ጎጃም በነማይ ወረዳ ደንጎሊማ ቀበሌ አቶ ሞሳ አዳነ የተባሉ የመኢአድ አባል ቅዳሜ ሰኔ 7 ቀን ከቤታቸው ወደ እስር ቤት መሄድ አለብህ በሚሉ የብአዴን ካድሬዎች ድብደባ ሕይወታቸው አልፏል፡፡ ይህን ድርጊት የፈጸሙት ሁለት የብአዴን ካድሬዎች አቶ አዲሱ ጫኔና አቶ ብርሃኑ ታመነ ወደ መኖሪያቸው በመሄድ ወደ እስር ቤት ትሄዳህ በማለት ለማስገደድ ሲሞክሩ በተፈጠረ እሰጣገባ አቶ ሞሳ አዳነ […]

ቤተክርስቲያን እና መንግስት በኢትዮጵያ ውስጥ እጅና ጓንት ሆነው በኢትዮጵያውያን ላይ የማያባራ ጭቆና ማካሄድ ከጀመሩ ረዥም ዘመናት ተቆጥረዋል። ይብልጡኑ የመንግስቶች ጎህ ከቀደደ ጀምሮ በተለይ የተዋህዶ ሃይማኖት መሪዎች አስፈሪ እና አስደንጋጭ እንዲሁም አሳዛኝ ደግሞም አሳፋሪ ቃላቶችን በመጠቀም ስጋዊ እና ምድራዊ ስልጣኖችን ለገዢዎች ለማደላደል ይህ ነው የማይባል ግፍ በምእመናኖቻቸው እን በሌሎች አማኞች ላይ ፈጽመዋል አስፈጽመዋል፤ እየፈጸሙ ነው፤ እያስፈጸሙ […]

ሁለት ፈረሶች እንደነበሩ ተነገረ፡፡ አንደኛው እጅግ ለምለም በሆነ ሰፊ ሜዳ ላይ ተሠማርቶ፣ ሲያሻው ደግሞ በግራ በቀኝ ገብስ ፈስሶለት፣ ሲጠማው የሚጠጣው ውኃ በሜዳው መካከል ኩልል ብሎ እየወረደለት፣ አውሬ እንዳይተናኮለው ዙሪያውን በውሻ እየተጠበቀ ይኖር ነበር፡፡ ሁለተኛው ደግሞ የሣር ዘር ለአመል ያህል ብቻ እዚህም እዚያም በበቀለበት፣ ጭው ባለ ደረቅ ሜዳ ላይ ተሠማርቶ ያገኛትን እየነጨ፣ ከዕለታት በአንድ ቀን ከደጋ የዘነበ ዝናብ በአካባቢው ሲያልፍ የሚያገኘውን ጥፍጣፊ ውኃ እየተጎነጨ፣ ሌትና ቀን ምን ዓይነት አውሬ መጥቶ ይዘነጥለኝ ይሆን? እያለ በሥጋት ይኖር ነበር፡፡

ምንም እንኳን ሁለቱም ፈረሶች በኑሮ በማይቀራረብ ሜዳ ላይ በመከራና በቅንጦት ተለያይተው ቢኖሩም የኑሮ ጥያቄ ግን አገናኝቷቸው ኖሯል፡፡ ያ እንዲያ በለመለመ መስክ ተሠማርቶ እምብርቱ እስኪነፋ ሆዱ እስኪቆዘር እየበላ ሲተኛ ሲነሣ የሚውለው ፈረስ ‹‹ይኼ ሣር ያለቀ ዕለት፣ ይኼም ውኃ የነጠፈ ጊዜ፣ እነዚህም ውሾች እኔን መጠበቅ ትተው የሄዱ ጊዜ፣ ይኼስ ገብስ የጠፋ ቀን ምን ይውጠኝ ይሆን? ያስ ቀን መቼ ይሆን? ይል ነበር፡፡ ይኼ ጥያቄ ምንጊዜም ይረብሸው ነበር፡፡

ያ በደረቅ ሜዳ ላይ እዚህም እዚያም የበቀለች ሣር እየነጨ ከርሱን ሲደልል የሚውለው ፈረስ ደግሞ ‹‹መቼ ይሆን አልፎልኝ ለምለም መስክ ላይ ውዬ፣ ከፈሰሰ ውኃ እንደ ልቤ ተጎንጭቼ፣ ያለ ሥጋት አድሬ የሚነጋልኝ? ያ ቀን መቼ ይሆን?ይል ነበር፡፡

እዚህ ሀገር ያለን ሰዎች በሁለቱ ፈረሶች ጥያቄ ውስጥ ወድቀናል፡፡ አንደኛው መስኩ ለምልሞለት፣ ውኃው መንጭቶለት፣ ሥጋቱ ጠፍቶለት፣ ሕይወቱ ቀንቶለት የሚኖረው ሰው ጥያቄ ነው፡፡ እንዴት ሜዳው ላይ እንደደረሰ አያውቀውም፤ ብቻ አንድ ቀን ተቀለጣጥፎም፣ ተጣጥፎም፣ ተለጣጥፎም፣ ራሱን ሜዳ ላይ አግኝቶታል፡፡ ለስንትና ስንት ፈረስ የሚበቃውን መስክ ብቻውን ተሠማርቶበታል፡፡ አገር የሚያጠጣውን ወንዝ ብቻውን ይንቦራችበታል፡፡ ጥጋብን ከልኩ በላይ፣ ምቾትንም ከመጠን አልፎ ቀምሶታል፡፡ ድህነትን ረስቶ የት መጣውን ዘንግቶታል፡፡ ግን ሥጋት አልለቀቀውም፡፡

ይኼ መሥመር የተበጠሰ ዕለት፣ ይኼ ሥርዓት ያለፈ ቀን፣ ከእገሌ ጋር የተጣላሁ ጊዜ፣ ቀን የዞረችበኝ ሰዓት፣ የተነቃ ለታ፣ ዕቁቡ የተበላ ጊዜ፣ ካርታው ያለቀ ቀን፣ መንገዱ የታወቀ እንደሆን፣ ሕግ የተቀየረ ቀን፣ ምን ይውጠኝ ይሆን? ያችስ ቀን መቼ ትሆን? እያለ ይጠይቃል፡፡ እየበላ ይሠጋል፣ እየጠጣም ይጨነቃል፤ አይቷል፣ ሰምቷል፡፡ ድንገት ለምለሙ  ሜዳ ላይ ተገኝተው ድንገት ከሜዳው የጠፉ አሉና፡፡

አሁን ሆዱ ተቀይሯል፤ አንገቱ ተቀይሯል፤ እጁ ተቀይሯል፤ መቀመጫው ተቀይሯል፤ ማረፊያና መዋያው ተቀይሯል፡፡ ይህንን ያጣ ዕለት ምን ይውጠዋል?

ያኛውም ፈረስ አለ፡፡ እንደ ዐርባ ቀን ዕድል ሆኖ የደረቀ መስክ ላይ ውሎ እንዲያደር የተፈረደበት፤ ቢሄድ ቢመጣ፣ ቢወርድ ቢወጣ ከዚያ መስክ መላቀቅ ያቃተው፡፡ መቼ ይሆን የእኔስ ሜዳ በሣር ተሞልቶ እንደነዚያ ሣር የምጠግበው እያለ ምኞት የገደለው፡፡ የእኔስ ወንዝ መቼ ይሆን ውኃ ሞልቶት ሳልጨነቅ የምጠጣው? እያለ ሃሳብ ያናወዘው፡፡ የእርሱ ቤት እየፈረሰች ከጎረቤቱ ዘጠኝ ፎቅ ሲበቅል አይቷል፡፡ ስትተከል፣ ውኃ ስትጠጣ፣ አላያትም፡፡ እንዲሁ ብቻ ፎቋ በቀለች፡፡ ስትገዛ ያላያት፣ ፍንጥር ያልጠጣባት መኪና እንዲሁ ሽው እልም ስትል አያት፤ እናም ምን ዓይነት ፈረሶች ይሆኑ ለዚህ የሚበቁት እያለ ይጠይቃል፡፡ ዝርያቸው ምን ቢሆን ነው? መልካቸውስ ምን ቢሆን ነው? የፈረስ ጉልበታቸውስ ምን ያህል ቢሆነ ነው? ፍጥነታቸውና ቅልጥፍናቸውስ እንዴት ያለ ቢሆን ነው? ጌቶቻቸውንስ እንዴት አድርገው ቢያገለግሏቸው ነው? እንዲህ ለምለም መስክ ላይ የለቀቋቸው? እኛም ስናገለግል ኖረናል፤ ጋሪ ስንጎትት፣ እህል ስንሸከም፣ ዕቃ ስናጓጉዝ ኖረናል፤ ጌቶቻችን ሲጋልቡን ኖረናል፤ ግን እነርሱ ምን ያህል ቢያስደስቷቸው ነው ይህንን ዕድል የሰጧቸው? እያለ ይጠይቃል፡፡

ለመሆኑ እነርሱ ናቸው ወደ እኛ የሚመጡት ወይስ እኛ ነን ወደ እነርሱ የምንሄደው? ለመሆኑ የኛን ድህነት ነው ወይስ የእነርሱን ሀብት ነው የምንካፈለው? በርግጥ ከኛም የሄዱ አሉ፤ ከእነርሱም የሚመጡ አሉ? ይላል፡፡ አንዱ ሜዳ ላይ ተሠማርተን እንደ አቅማችንና እንደ ችሎታችን መጋጥ ሲገባን ለምን ሁለት ዓይነት ሜዳ ሆነ፡፡ አሁን እኛና እነርሱ እኩል ‹‹ፈረስ›› ተብለን እንጠራለን? እኛ ‹‹ሌጣ ፈረስ›› ነን፣ እነርሱ ደግሞ ‹‹ባለ ወግ ፈረስ›› ናቸው፡፡

ግን ይሁን፤ እሺ መቼ ይሆን እኛስ እንደነርሱ የምንሆነው? መቼ ይሆን ያለ ሥጋት ውለን የምናድረው? ለምለሙን መስክ ማን ይነካዋል፤ ላለው ነው ድሮም የሚጨመርለት፤ የኛ የድኾቹን መስክ ነው ለሀብታሞቹ የሚሰጡት፤ የድኾቹን ደረቅ መስክ ሀብታሞቹ የሚቀኑበትን ያህል እኛ በእነርሱ ለምለም መስክ አንቀናም፡፡ ደግሞ አንድ ቀን ይመጣሉ፡፡ ‹‹ይህንን መስክ ለምለም ማድረግ እንፈልጋለን›› ይላሉ፡፡ እኛም ደስ ይለናል፡፡ የዘመናት ምኞታችን አይደል? መንገዱ ጠፍቶን እንጂ እኛም ለምለም ማድረግ እንፈልግ ነበርኮ? መንገዱን ያወቀው ሰው ሲመጣ ለምን እንቃወመዋለን፡፡

ግን ይቀጥሉና ሌላ ነገር ይሉናል፡፡ ‹‹መስኩን ግን ለምለም የምናደርገው ለእኛ እንጂ ለእናንተ አይደለም›› ይሉናል፡፡ ለምን? ለምን? እኛ ለምለም ሣር አይወድልንም? እኛ ለምለም የምናደርግበትን መንገድ ለምን አያሳዩንም? ባያሳዩንስ ለምን አይፈቅዱልንም? ባይፈቅዱልንስ ለምን አይተውንም? እንላለን፡፡ ይህ ግን ጥያቄ ነው እንጂ መልስ የለውም፡፡ እኛም ጥያቄውን የምናውቀውን ያህል መልሱን አናውቀውም፡፡ ስንጠይቅም ‹‹ምላሽ›› እንጂ ‹‹መልስ›› የሚሰጥ አናገኝም፡፡

እኛም ከዚያ መስክ እንወጣለን፣ ወደሌላ መስክም እንዛወራለን፤ አሁንም ቅንጥብጣቢ ሣር እንፈልጋለን፤ ጥፍጣፊ ውኃ እናስሳለን፡፡ ያ እኛ የነበርንበት መስክ ግን በአንድ ጊዜ ይለመልማል፡፡ ውኅው ጅረት ሆኖ ይፈስበታል፡፡ ይገርመናል፡፡ እኛ እዚያ ሳለን፡፡ ውኃ አልነበረም፡፡ እንደ ወር በዓል ቀን ቆጥረን ነበር የምናገኘው፡፡ አሁን ግን ይንፎለፎላል? ለመሆኑ እኛ ምን ብለን መጠየቅ ነበረብን? ይኼ ራሱ ሌላ ጥያቄ ይሆንብናል፡፡ መቼ ይሆን እኛስ እንዲህ ባለው መስክ ላይ የምንሠማረው? እንላለን፡፡ የማይሳካ ምኞት እንመኛለን፤ የማይመለስ ጥያቄ እንጠይቃለን፡፡

እዚያም ቤት ሌላ ጥያቄ አለ፡፡ ፀሐይዋ እንደወጣች ትቀጥል ይሆን? ወንዙ እንደፈሰሰ ይቀጥል ይሆን? ነፋሱ እንደነፈሰ ይቀጥል ይሆን? ሣሩ እንደለመለመ ይዘልቅ ይሆን? እኔስ እንደተወደድኩና ሞገስ እንዳገኘሁ እኖር ይሆን?

ሰውየው ስለ አውሮፕላን አነዳድ የሚገልጥ ማኑዋል አገኘና አውሮፕላኑን አስነሥቶ አበረረ፡፡ ገጹን ይገልጣል፤ የተጻፈውን ይፈጽማል፤ አውሮፕላኑም ይበራል፡፡ በቀጣዩ ገጽ ላይ ምን እንዳለ የሚያውቀው ነገር አልነበረም፡፡ ገጹ ተገንጥሎ ቢገኝ ምን ማድረግ እንዳለበትም የሚያውቀው ነገር አልነበረም፡፡ ብቻ ይገልጣል፣ ያነባል፣ ይነካካል፣ ይበራል፡፡ አውሮፕላኑ ተነሥቶ በሃያ አምስት ሺ ጫማ ከፍታ ላይ ሲደርስ የመጨረሻው ገጽ ላይ ደረሰ፡፡ ‹‹ክፍል ሁለትን በክፍል ሁለት መጽሐፍ ይመልከቱ›› ይላል፡፡ ክፍል ሁለት መጽሐፍ ግን የለውም፤ የት እንዳለም አያውቅም፡፡ ምን ማድረግ እንዳለበትም አልተዘጋጀም፡፡ ስለዚህም እንደወጣ መውረድ ጀመረ፡፡ ያውም በዝግታ ሳይሆን እየተምዘገዘገ፡፡

እናም እኛ በለምለም መስክ ላይ ያለን ፈረሶች፣ አንድ ክፉ ቀን መጥቶ ‹‹ክፍል ሁለትን በሌላ መጽሐፍ›› ቢለንስ? ምን ይውጠናል? ለመሆኑ ክፍል ሁለት የት ነው ያለው? እስካሁን ያሳየን የለም፡፡ እኛ የምናውቀው የየዕለቱን ምዕራፍ ብቻ ነው፡፡ ያንን እናነባለን፣ በእርሱ እንኖራለን፣ ቀጣዩን ምዕራፍ አናውቀውም? ስለዚህም እኛም እንጠይቃለን? እንዲሁ እንዘልቅ ይሆን? ብለን፡፡

© ይህ ጽሑፍ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት ላይ የወጣ ነው

 

የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ – ሰመጉ ከአውሮፓ ኅብረት የሁለት መቶ ሺህ ዩሮ እርዳታ አግኝቷል፡፡

ድርጅቱ ባገኘው ድጋፍ ኢትዮጵያ ውስጥ ተዘግተው የቆዩ ቢሮዎቹን እንደሚከፍት አስታውቋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የመለስካቸው አምሃን ዘገባ ያዳምጡ፡፡

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የእስራኤል ጦር ኃይል በምዕራባዊ ዮርዳኖስ ወንዝ አካባቢ የታገቱ ሶስት ወጣት እስራኤላዉያንን ለማስለቀቅ ናቡስ የተባለችዉን ከተማና አካባቢዉን ወርሮ የተጠናከረ ፍተሻ ማካሄዱን ዘገባዎች ያመለክታሉ።

እንደኦክስጅን ሁሉ ለፍጥረታት እጅግ አስፈላጊ ከሆኑ ነገሮች አንዱ ዉሃ መሆኑ ይታወቃል። የፍጥረታት መሠረት የሆነዉ ዉሃ ለምግብ የሚሆኑ ተክሎችን በማብቀል ነፍስ ለማቆየት ሲፈለግ እሱ ራሱ በልዩ ልዩ ነገሮች ተበክሎ የበሽታ መንስኤ ሲሆን አሳሳቢነቱ ያኔ ነዉ።