የካቶሊክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳትና የጸረ ማፍያ አስተያየት
ጣሊያን ዉስጥ በሶስት ክፍላተ ሃገራት በካላብሪያ እንድራንጌታ፣ በሲሲሊ ማፊያ፣ እንዲሁም በካምፓኛ ኔፕልና አካባቢዉ ደግሞ ካሞራ የተባሉ የተደራጁ የአመፅ ቡድኖች መኖራቸዉ የአደባባይ ምስጢር ነዉ።
ጣሊያን ዉስጥ በሶስት ክፍላተ ሃገራት በካላብሪያ እንድራንጌታ፣ በሲሲሊ ማፊያ፣ እንዲሁም በካምፓኛ ኔፕልና አካባቢዉ ደግሞ ካሞራ የተባሉ የተደራጁ የአመፅ ቡድኖች መኖራቸዉ የአደባባይ ምስጢር ነዉ።
በተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች በመንግስት መሥሪያ ቤቶች የሚሰጡ አገልግሎቶች የተወሰነ መሻሻል ቢያሳዩም አሁንም መጉላላቶች እንደሚስተዋሉ አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች ገለጹ።
ሳይንቲስቶች ሳይቤሪያ በቅርቡት አደገኛ ጎርፍና ሌሎች የተፈጥሮ አደጋዎች በተደጋጋሚ ሊገጥማት እንደሚችል አመለከቱ። ባለሙያዎቹ እንደሚሉት እያደገ የመጣዉ የዓለም የሙቀት መጠን ያስከተለዉ ጎርፍም በተጠቀሰዉ አካባቢ ባለፈዉ እና በያዝነዉ ወር ከ50 ሺህ የሚበልጡ ሰዎችን ኑሮ አናግቷል።
የኢራቁ ውጊያ ዜጎችን ብቻ ሳይሆን በሃገሪቱ የተሰማሩ የውጭ ኩባንያዎችንም ከሃገር እያስወጣ ነው ። በጦርነቱ ሃገር ለቀው እንዲወጡ ከተገደዱት ውስጥ የጀርመን ኩባንያዎች ይገኙበታል ።
A ban comes into force in the UK on Tuesday on the drug, khat, that is traditionally used by Ethiopian, Kenyan, Somali and Yemeni communities.
The British government says outlawing khat brings the UK into line with other European countries where it is a controlled substance.
However in Kenya’s khat-growing region, there is concern about the economic impact of the ban.
The BBC’s Anne Soy reports.
Read more http://betinews.com/?p=1354

ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ(አንድነት)ባሳለፍነው ሳምንት ሰኔ 15 ቀን 2006ዓ.ም በሃዋሳ ከተማ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ተከትሎ በእስር ላይ የሚገኙት የአንድነት ፓርቲ አባላት ‹‹ፍትህን ተነፍገን ትግላችን አይቆምም ››በማለት ዛሬም ለ4ኛ ቀን በርሀብ አድማ ላይ ናቸው፡፡አባላቱ በቁጥጥር ስር ከዋሉበት ቅዳሜ እለት ጀምሮ በረሀብ አድማ ላይ ሲሆኑ በትላንትናው እለት ሰኞ ሰኔ 16 ቀን 2006 ዓ.ም በሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ […]
World Cup, Monday, 06/23/14
South Sudan’s peace talks suspended, 06/23/14
ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች
በብራዚል ካለፉት 12 ቀናት ወዲህ እየተካሄደ ባለው የ2014 ዓም የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ግጥሚያ ላይ በፍፁም ያልተጠበቁት ስጳኝ እና እንግሊዝ ግን ገና በጊዜ ከውድድሩ ተሰናብተዋል፣
የጋዜጠኝነትን ሙያ የሚያስከብሩ ነፃ ጋዜጠኞች የሚመሩት ማህበር መቋቋም ለሙያው እድገትም ሆነ ለጋዜጠኞች ደህንነት ወሳኝ መሆኑን ተናግሯል ።
እገታውና በተከታታይ የቀጠለው እስር ሃማስና የፍልስጤማውያን ፕሬዝዳንት ማህሙድ አባስ በተፈራረሙት የአንድነት ስምምነት ላይ ተፅእኖ በማድረግ ላይ መሆኑ ተዘግቧል ።
የዛሬዎቹ አሸባሪዎች እስላማዊ መንግሥት የመመስረት ቅዠታቸዉ ነቅተዉ ከድሮዎቹ አሸባሪዎች ከኩርዶች ተምረዉ ማዕከላዊና ምዕራባዊ ኢራቅ ላይ «ሱኒስታን» ወይም ሌላ መንግሥት ቢያቆሙስ?
ኢህአዴግ የግንቦት 3 ቀን 2006 ዓ.ም የጐፋ ሳውላ ሰላማዊ ሰልፍን እቅድ ከሰማበት ጊዜ አንስቶና ከሰልፍ በኋላም እጅግ አስከፊ የሰብአዊ መብት ረገጣ እየፈጸመ ይገኛል፡፡ ይህም የሰላማዊ ትግሉን ሂደት ከምርጫ 2007 የቅድመ ዝግጅት የዕለት ተዕለት ሥራው አንዱ ዲሞከራሲን የማጥፋት ተግባር በመሆኑ ለጐፋ አካባቢ ከተማ ፍ/ቤት ጀምሮ እስከ ወረዳ ፍ/ቤቶች ከፓሊስ ኃይል ጋር በመተባበር እያጠቁ ናቸው፡፡ ተግባሩን በምንከታተልበት […]
በብራዚል ካለፉት 12 ቀናት ወዲህ እየተካሄደ ባለው የ2014 ዓም የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ግጥሚያ ላይ በፍፁም ያልተጠበቁት ስጳኝ እና እንግሊዝ ግን ገና በጊዜ ከውድድሩ ተሰናብተዋል፣
ሰዎች ለሰዎች በኢትዮጵያ የሚያከናውናቸውን ሥራዎች በሙያዊ ተጠያቂነትና በግልፅነት እንዲሁም በመረጃ ቴክኖሎጂ በመታገዝ ለመሥራት አቅዷል።
አዋሳ ሆይ እስከመቼ የዳንስ ከተማ ብቻ እንድትሆኝ ይፈረድብሻል? የፖለቲካ ከተማም ሁኝ እንጅ!!! የህዝቡ የለውጥ ፍላጎት ገፍቶ በወጣ ቁጥር የአምባገነኖች መደናበር ያይላል፡፡ ሲደናበሩም ህግ ይጥሳሉ፣ ህዝብ ያሰቃያሉ፣ ሀገር ይበድላሉ፡፡ ግን እድሜ ልክ ዕየተጨቆኑ መኖር አይቻልም፡፡ ‹‹ተቀምጦ ከመኖር ቆሞ መሞት ይሻላል›› እንዲሉ፡፡ ቆሜ መሞት ይሻለኛል የሚሉ ዴሞክራሲ ናፋቂዎች እየበረከቱ ነው፤ እምቢ ከፈለግህ ይሄው እሰረኝ! የሚሉ ትንታግ ወጣቶች […]
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ) ባለፉት 23 ዓመታት የኢትዮጵያ ሕዝብ ስርዓቱ አምጦ የወለዳቸው ሀገራዊ አፈና፣ ማዋከብ፣ የመኖር ዋስትናን መንፈግ፤ ዜጎችን ማሰደድና ማሰር የተለመዱ ድርጊቶ ሆነው ኖረዋል፡፡ አሁንም በዚህ አስከፊ የአፈና መንገድ ጉዞውን ቀጥሏል፡፡ የስርዓቱ መንግስታዊ አፈናና ፀረ-ሕዝብ አቋም በመላ ኢትዮጵያ የተዘረጋ ቢሆንም ፓርቲያችን በእንቅስቃሴዎቹ ውስጥ እንደታዘበው በደቡብ ክልል […]
ከአምስት ወር በፊት በአስታራ ሆቴል የተመሰረተው የኢትዮጵያ የጋዜጠኞች መድረክ(ኢ.ጋ.መ) ትላንት ሰኔ 15 ቀን 2006 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00-6፡00 ሰዓት “የፕሬስ ነፃነት፣የጋዜጠኞች ደህንነት እና ልማት” በሚል ርዕስ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበተት የፓናል ውይይት በአዲስ ቪው ሆቴል አከናውኗል፡፡ የእለቱን መርሀ ግብር በንግግር የከፈተው የኢ.ጋ.መ ም/ፕሬዝዳንት ጋዜጠኛ ስለሺ ሃጎስ ሲሆን በመቀጠልም ሁለት ምሁራን የውይትት መነሻ ሀሳብ አቅርበው በተሳታፊዎች ሰፊ ውይይት […]
ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ ያዘጋጀው የፓናል ውይይት እየተካሄደ ነው፡፡ በመሀል ፖሊሶች አስተባባሪውን እንፈልጋለን ብለው በሆቴሉ ሰዎች መልዕክት ላኩ ከነብዩ ሀይሉ ጋር ሪሴብሽን ሄጄ አገኘናቸው፡፡ እነሱም ፕሮግራሙን አቋርጣችሁ ንገራቸውና አሁኑኑ ተበተኑ የሚል ቀጭን ትእዛዝ አስተላለፉ፡፡ ለምን ብንል? መልሱ- ትእዛዝ ነው!! የሚል ሆነ ነብዩ ፈጠን ብሎ “እሺ ለተሳታፊዎቹ እንንገራቸውና እንበተናለን” ብሎ ወደ አዳራሹ ተመለስን፡፡ አሁን ፕሮግራሙ ቀጥሏል፡፡ ፖሊሶቹም […]
በነገረ-ኢትዮጵያ ጋዜጣ የተስተናደ
ይስጥልኝ!! እንደምን ሰነበቱልኝ፡፡ ዛሬ ከካሳንቺስ ስድስት ኪሎ በቤተ-መንግስቱ አጥር ስር እያለፍን እናወራለን፡፡ እንቀጥል፡፡ ከካዛንቺስ ስድስት ኪሎ ለመሄድ የታክሲ ሰለፍ ይዣለሁ፡፡ እንደ በረሃ ዘንዶ የተጥመለመለው ሰልፍ የቤተ-መንግስቱን አጥር ታኮ ፊት በር ሊደርስ የጥቂት ምስኪን ተሰላፊዎችን ከኋላ መሆን ብቻ ይጠባበቃል፡፡ ትንሽ ክብዶ(ማካበድ) ስንጨምርበት ደግሞ ከኋላ በተሰለፈውና በቤተ-መንግስቱ ጠባቂ መካከል ያለው ርቀት አንድ መትረየስ አያሥጠምድም፡፡ አንድ ሰዓት ላይ የማልቀርበት ብርቱ ቀጠሮ 6 ኪሎ አካባቢ ይጠብቀኛል፡፡ ሳላረፍድ ለመድረስ 11 ሰዓት ካዛንቺስ ታክሲ መያዣ ደርሸ የመሰለፍ ግዴታየን መወጣት ይኖርብኛል፤ ወይም ይህን ሰልፍ ትቸ የአንድ ሰዓት የእግር ጉዞ በቤተ መንግስት አጥር ስር አንገቴን ደፍቸ ማለፍ ይጠበቅብኛል፡፡በዚህ ቤተ-መንግስት ለሚያልፍ ሰው አንገቱን ደፍቶ ማለፍ ግድ ይለዋል፡፡ ይህን ማድረግ ያልቻለን አስገድደው አንገት የሚያስደፉ ስልጡን ጠባቂዎች እንደ ግሪሳ ወፍ ወረውታል ቤተ-መንግስቱን፡፡ የሆነ ነገር ፈልገው ወይም የሚያሳክክ ነገር ቢገጥምዎት እንኳን ቀና ማለት ውጉዝ ነው፡፡ ይህን ካደረጉ ደግሞ ቁጭ በል ተነስ፤ቁም ሂድ የሚል ግልምጫ ሊከተልዎት ይችላል፡፡ አለፍ ካለና ጥበቃዎቹ እጅና እግራቸውን ማፍታታት ካስፈለጋቸው ደግሞ ጡጫ ነገርም ሊቀምሱ ይችላሉ፡፡ ለምን ብሎ ጥያቄ የለም፡፡ ምክንያቱም ይህ ቤተ-መንግስት ነው፡፡ በመሆኑም በዚህ ሽር ማለት የሚችል መንግስት እንጅ እንደ እኔ አይነት አመዳም ድሃ አይደለምና፡፡ እድለ ጠማማ ከሆንክ ደግሞ አንዱ የአፍሪካ ነፍሰ ገዳይ አምባገነን መሪ ከቦሌ አየር ማረፊያ እየመጣ ስለሆነ ጀርባህን ሰጥተህ ቁም ልትባል ትችላለህ፡፡ በደርግ ጊዜ ነው አሉ እንዲህ እንዳሁኑ ሊቀመንበሩ ሲያልፉ ፊትህን አዙረህ ቁም ይባል ነበር፡፡ ይህ ድርጊታቸው ስልችት ያላቸው ሴትዮ ‹‹ሰውየውን የሚጠብቁት ከአይን ነው ወይስ ከጥይት›› አሉ ይባላል፡፡ ስለዚህ ይህን አካባቢ ፈጥን ብሎ በታክሲ ላፍ ማለት ይበጃል፡፡
በዚህ ደዲቃዎችን ሳይሆን ሰዓታትን በሚጠይቀው ሰልፍ ላይ የተደረደሩት ምስኪን የሀገሬ ዜጎች ሰማያዊ ታክሲ ላይ ትኩረት አድርገው አይናቸውን ላይ ታች ያቅበዘብዛሉ፡፡ በዚህ ሰልፍ ላይ የሌለ የሰው አይነት የለም፡፡ ከወፍራም እስከ የኔ ቢጤ ሲንብሮ፡ከሰማይ ቅርቡ ሞጋጋ እስከ እንቅፋት የመሰለ ድንክ፡ከምሁራን እስከ መሰረተ-ትምህርት ምሩቅ ብቻ ሁሉንም ሊያስማማ ከሚችለው መመዘኛ ከድህነት ውጭ ሰልፉ የሰው ማህበራዊ ነው ማለት ይቻላል፡፡ በነገራችን ላይ እንዲህ ታክሲዎች የመስቀል ወፍ በሚሆኑበት አጋጣሚ እንደ እኔ አይነት ቀጫጫዎች ተወዳጅነታቸው ይጨምራል፡፡ ቀጫጫዎችን በአንድ ወንበር እስከ ሶስትና አራት ሰው ለመጫን ስለሚመች፡፡ በመሆኑም እርስዎ ታክሲ ይሳፈራሉ እርስዎን ሌላ ሰው ተሳፍሮዎት ይጓዛሉ፡፡ ለምን ብሎ ጥያቄ የለም ምክንያቱም ይህ ጽሀዩ መንግስታችን ያመጣው ልማት ውጤት ነውና፡፡ በፈረንጅ ሀገር ወፍራም ሰዎች ተጨማሪ ክፍያ ይጠየቃሉ ሲባል ብሰማ መንግስቴን አጥብቄ አመሰገንኩት፡፡ እንዴት ብለው ከጠየቁኝ፤እንዲህ እመልሳለሁ፡፡ ሀገሬ ፍትሀዊነት የሰፈነባት በመሆኗ ወፍራሙም ቀጫጫውም እኩል የታክሲ ታሪፍ ስለሚከፍል፡፡ ደግሞ ኢቲቪ እንዳይማኝ፡፡ ኢቲቪ ከሰማ ግን እንዲህ ነው የሚዘግበው፡፡ ሀገራችን በታክሲ ታሪፍ ፍትሃዊነት በምስራቅ አፍሪካ አንደኛ ናት፤ አክሎም የታክሲ ሰልፈኛው ፈዛዛነት ለጎረቤት ሀገራት ምርጥ ተሞክሮ ሊቀመር የሚችል ነው ሲሉ አንዳንድ የታክሲ አሽከርካሪዎች ተናግረዋል!! ማለቱ አይቀርም ኢቲቪ ነፍሴ፤ ነፍሱ ይጥፋና፡፡ ጎበዝ በስንቱ አንደኛ ሆንን ተብሎ ይዘለቃል፡፡ ሌሎቹ ሀገራ ስራ አቆሙ እንዴ?!! በአንድ ወቅት አቶ መለስ ስለ ፍትሀዊ የገቢ ክፍፍል ሲናገሩ ሀገራችን ኢትዮጵያ ከኖርዌይ ቀጥላ ሁለተኛ ናት ሲሉ ሙድ ይዘው ነበር፡፡ ከደረጃ ጋር በተያያዘ የሆነ ወቅት ላይ ሚስተር ኦባማ የአለም መሪዎችን ሰብስበው ተወያዩ ሲባል የሰማ ካድሬ መሪዎቹ በጉብዝናቸው ነው የተመረጡት ሲል አወራለት፡፡ ጓደኛየ ካድሬውን እንዲህ ጠየቀው ‹‹የመረጣው መስፈርት አንድ ከላይ አንድ ከታች ነው እንዴ››ብሎ ነበር፡፡ በታችኛው መመዘኛ የገባው ማን እንደሆነ መቸም ገምታችኋል፡፡ የእኔ ነገር የተነሳውበትን ነገር ስቸ ወዴት ተሰነቀርኩ፡፡ ወደ ቀደመ ነገሬ ልመለስና ስለ ታክሲ ሰልፌ ላውራ፤ ሰልፍ ሰልፍ ሰልፍ………….ኡፍፍፍፍፍፍ……….
ለምንና እስከ መቸ እንዲህ እንደምንሰለፍ ባይገባኝም፡የወገኔ ድካም ግን እጅጉን ያመኛል፡፡ ተሰላፊው የሰውነቱን ክብደት መሸከም አቅቶት እግሩ የዛለው ወገቡን ይዞ፤የባሰበት እየተቀመጠ፤የቀናው ደግሞ ከጎኑ የተሰለፈችን ኮረዳ እያሽኮረመመ ሰማያዊ ታክሲ ይጠባበቃል፡፡ ኮረዳ አሽኮርማሚው እንኳ ታክሲው ባይመጣም ግድ አይሰጠውም፡፡ በስንት ደቂቃ ልዩነት ብቅ የምትለው ታክሲ ከአስራ አምስት ሰው በላይ ጭና ላፍ ትላለች፡፡ ቀሪዎቹ ሰዎች ሰማያዊ ታክሲ መጠበቃችን እንደቀጠለ ነው፡፡ ፍቅረኛው ‹‹ሰማያዊ ልብስ ለብሸ እመጣለው ያለችው ጎረምሳ በታክሲ ይደነብራል›› እንደሚባው ሰማያዊ ነገር ባየን ቁጥር እናንጋጥጣለን፡፡ እንዲህ ወደ ታክሲው ያንጋጠጥነውን ያክል ወደ ቤተ-መንግስቱ ብናጋጥጥ መና ይወርድልን ነበር አልላችሁም መቸም፡፡ ታዲያ ቤተ-መንግስት ምን የሚወርድ ነገር አለ እንዳላችሁ ገብቶኛል፡፡ ‹‹ሆድ ይፍጀው›› አለ ሰውየው ብየ አልፈዋለው፡፡ በአሁኑ ጊዜ እኮ ስለ ቤተ-መንግስቱ የማይሆን ነገር ማሰብ አሸባሪነት ነው፡፡ ቀድማ የሄደችው ታክሲ የምትመለሰው ሾፌሩና ረዳቱ መቶ ግራም ገለምሶ ካኘኩ በኋላ ነው፡፡ ከስንት ሰዓት በኋላ እንደምንም እየተንፋቀቅን በሀይለ ስላሴ ጊዜ የተገዛች ከርካሳ ታክሲ ላይ ተጭነናል፡፡ መኪናዋ በጣም ከማርጀቷ የተነሳ ግጭት ቢደርስባት ቲታነስ ሊገድለዎት ይችላል፡፡ የብሄራዊ ሙዚየም ድክመት ነው እንጅ ታክሲዋ መገኛዋ እዛ ነበር፡፡ ለማንኛውም ጠጋ በል ከሚል የወያላ ንዝንዝ ለመዳን ስል ጋቢና መሳፈር እወዳለሁ፡፡ በእዛውም ቶሎ ለመድረስ ጋቢና መቀመጥ መፍትሄ ነው፡፡ ይህ ደግሞ በታክሲ ፈልፍ ያባከንኩትን ጊዜ ያካክስልኛል ብል በአለም የመጀመሪያው ውሸታም አልሆንም፡፡
ሰው እንደ ቲማቲም ግጥግጥ ብሎ ተጭኗል…….ተሳፋሪዎች ጥቅጥቅ ብለው እንደገቡ ሴታ ሴት መሳዩ ሾፌር ገብቶ የመኪናውን ሞተር ቆሰቆሰው፡፡ ሞተሩ ተረክ ብሎ ተነሳ፡፡ በመቀጠል የተወዳጇ አስቴር አወቀ ተስረቅራቂ ድምጽ ከእስፒከሩ ወደ ጆሯችን ፈሰሰ፡፡ ‹‹ወይ ኑሮ ወይ ኑሮ›› ትላለች አስቱ የዛን ዘመን ኑሮ ዳገት ለመተረክ፡፡ የተዘፈነበትን ዘመን ሳይሆን ዛሬን የሚሰብከው የአስቴር ዘፈን ኑሮ እንዴት ከባድ እንደሆነ ለማስረዳ ያጣጥራል፡፡ ዘፈኑ በዚህ ዘመን ተዘፍኖ ቢሆን ምን ሊባል ኑሯል፡፡ ይህ ዘፈን ሲዘፈን የአንድ ኩንታል ጤፍ ዋጋ በአሁኑ የአንድ ምግብ ዋጋ ጋር እኩል ነበር፡፡ አስቱ አሁን ሪሚክስ አድርጋ ብትዘፍነው እንደ ብሄራዊ መዝሙር ሁሉም ሰው ተቀባብሎ ይጫወተው ነበር፡፡በዚህ በሀል አንዱ ተሰፋሪ በኑሮ ይማረር በምን እሱ ያውቃል፤ከሙዚቃው ድምጽ በላይ 11.2% ጮክ ብሎ ሙዚቃውን ቀንሰው ሲል ደነፋ፡፡ እንደ ተንቤን ኮረዳ ሹርባ የተሰራው ሴታሴት ሾፌር ድንገት ወንዳወንድ ሆኖ አልቀንሰውም ሲል መለሰለት፡፡ ቀጠል አድርጎም ተሳፋሪው ላይ የትችት ማዕበል አወረደበት፡፡‹‹ታክሲ ውስጥ ብቻ ነው መብትህ ትዝ የሚልህ?››ከሁለት ሰዓት በላይ ተሰልፈህ ስትቆይ ለምን ብለህ አልጠየቅክም? ወይስ አሁን ነው ሰው መሆንህ የገባህ? በሚሉ ሞጋች ጥያቄዎች ያፋጥጠው ጀመር፡፡ ሁሉም ተሳፋሪ በሾፌሩ መልስ በመገረም ጸጥ አለ፡፡ አሁንም ሾፌሩ መናገሩን ቀጥሎ ‹‹እኛ ላይ የምትጮኸው ጠብ-መንጃ ስለሌለን ነው›› ሲለው የኮረኮሩኝ ያክል አሳቀኝ፡፡ ሌላው ተሳፋሪም አብሮ ሳቀ፡፡ ሰውየውም ሂሱን ውጦ ዝም አለ፡፡ ‹‹ጠብ መንጃ ስለሌለን›› ድንቅ አባባል፡፡ ተናጋሪው ሰውየ ድንገት የተቃዋሚዎች ስብሰባ እንደታደመ ካድሬ ቅስሙ ተሰብሮ ጸጥ አለ፡፡ ወደ ውስጤ አሰብኩ የሹፌሩ ነገር ትክክል ነበር፡፡ ከሁለት ሰዓታት በላይ ታግሶ መሰለፍ የቻለ ሰው እንዴት የሙዚቃ ድምጽ በዛ ብሎ ለመቃወም ወኔ አገኘ፡፡ ያውም ለስለስ ብሎ የተከፈተን ሙዚቃ ካቀነስክ በሚል ጥያቄ፡፡ በነገራችን ላይ ከመጠን በላይ የሚለቀቁ ሙዚቃዎች አግባብ ናቸው የሚል መከራከሪያ የለኝም፡፡
ታክሲዋን ቀና ብየ አየኋት፡ጥቅሶች ተንጠልጥለዋ፡፡ ዙሪያ ገባዋ በአብዮተኛ ጥቅሶች ተሞልታለች ያች ከርካሳ ታክሲ፡፡ ትኩረቴን የሳበችኝ ግን ‹‹መብትህን ከታክሲ ስትወርድም ጠይቅ!!›› የምትለዋ ነች፡፡ ለሁለተኛ ጊዜ ሾፌሩን አደነቅኩት፡፡ ሳትፈራ ጠይቅ ነው ያለው ሾፌሩ፡፡ የጥበብ መጀመሪያው መጠየቅ ነው!! እንዲል የእኔ ፍልስፍና የመጨረሻው ምዕራፍ፡፡ ትክክል መስሎ ያልተሰማንን ነገር መጠየቅ፤ያላመንበትን ላለማድረግ እንቢ ማለትን መለማመድ ይጠበቅብናል፡፡ እኛ ኢትዮጵያዊያን ስንባል ትልቁ ችግራችን ክፉ ቀንን ታግሎ ከማሸነፍ ይልቅ ችግሩን መለማመድ ይቀለናል፡፡ ልመደው ሆዴ የዘወት እንጉርጎሯችን ነው፡፡ ‹‹ክፉ ቀንን እና ቅዝምዝምን ጎንበስ ብሎ ማሳለፍ ነው›› ስንል እንተርታለን፡፡ ‹‹ቀን ሲያልፍ ተናገር ወንዝ ሲጎድል ተሻገር›› እንላለን፡፡ በአባቶቻችን ተረት የምንኖር በተረት እንኳን እራሳችንን ያልቻልን ምስኪኖች፡፡ ‹‹ቻለው ሆዴ ልመደው በዘዴ››ን በአደባባይ የምዘፍን………
የተንዘላዘለውን ሰልፍ ለማስቀረት ከምንዘይደው ይልቅ የምንለምድበትን ዘዴ እንፈጥራለን፡፡ ኑሮ ማለት ሰልፍ እስኪመስለን ድረስ ለዳቦ እንሰለፋለን፡ለታክሲ ሰልፍ፡ሲያስለቅሰን ለኖረ ሰው የሀዘን ሰልፍ፡ለሰልፋችን መንስኤ የሆነን አምባገነን ለመቅበር ሰልፍ፡በአጠቃላይ ኑኗችን ሰልፍ የሆንን ድንጉጦች….!! በኢትዮጵያ ሰማይ ስር ከእድገት በህብረት ዘመቻው ሰልፍ ቀጥሎ ረጅሙ ሰልፍ የታክሲ ሰልፍ ሳይሆን አይቀርም፡፡ የዚህ ሁሉ ሰልፋችን መንስዔ የሆነውን መንግስት እንፈረዋለን፡፡ ከፍርሀታችን የተነሳም መንግስትን ለማማረር እንኳ በራችን በደንብ መዘጋቱን እርግጠኛ የምንሆን ስንቶቻቻን ነን?፡፡ እንዚህን ሰልፎች አንድ ቀን አንዱ ወፈፌ መፎክር ያስያዛቸው እለት ምን ሊሆን እንደሚችል መገመቱ ከባድ አይሆንም፡፡ ‹‹መንግስት ባቡሩ ሲያልቅ ችግሩ ይቀረፋል እስከዚያው ድረስ ባቡሩን መስላችሁ ተሰለፉ›› እያለ ጥሩምባውን ይነፋል፡፡ ድሃ በህልሙ ቅቤ ባይበላ ኖሮ እከክ ይበጣጥሰው ነበር እንዳሉት አይነት ነው፡፡እኔ የምጠቀመው የስድስት ኪሎ ታክሲ ስለሆነ ችግሬ አይቀረፍምና ዝም አልልም፡፡ ወይም እንደተባለው ተስፋ ማድረግ ይቻላል፡፡ ለነገሩ ዝም ባንልስ ምን እናመጣለን፡፡ እኛ ጠብ-ምጃ የለን ማን ይፈራናል፡፡ ከታክሲው በሰላም ወርጃለው፤የቀጠርኩት ወዳጀም ከፊት ለፊቴ ይታየኛል፡፡ የሾፌሩ ድምጽ ግን አሁንም ይከተለኛል፡፡ ‹‹እኛ ጠብ-መንጃ ስለሌለን ነው የምትጮኸው››?!! ትልቅ አባባል!!
ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል!!
አዲስ አበባ እና መቀሌ ላይ በተከታታይ እየተካሂዱ ያሉ ስብሰባዎች ውጥረቱ ያመለክታሉ። እያንዳንዱን እንቅስቃሴያችንን የሚከታተሉ እና የሚያጨልሙን ሰላዮች ተመድበውብናል ሲል መቀሌ ያለው የሕወሓት አንጃ አኩርፏል። ከመሃል አገር የፌዴራል መንግስቱን በመቆጣጠር እያሾረው ያለው የሕወሓት አመራሮች ቡድን መቀሌ በሚገነው አንጃ ላይ ሰላዮችን አሰማርቷል ሲሉ በትግራይ ክልል ያሉ የሕወሓት ባለስልጣናት እየከሰሱ ነው፡፤ ይህንን ተከትሎ የተነሳው ኩርፊያ እና አለመግባባት ሕወሓቶችን ዳግም ወደ ቀድሞው ሽኩቻ እና ቅራኔ ውስጥ እንዳይከታቸው ያሰጋል ሲሉ ቅርብ የሆኑ ምንጮች ጠቁመዋል።
በግንቦት ሃያ በአል ምክንያት ወደ አውስትራሊያ ተጉዘው የነበሩት አለቃ ፀጋይ በርኸ እና ወይዘሮ ቅዱሳን ነጋ ብምካከላቸው በተነሳ አለምግባባት በተለያየ በረራ ወደ አገር ቤት መመለሳቸው የሚታወስ ሲሆን አለቃ ጸጋይ አብረውን በተጓዙ ጭፍሮቹ ያሰልለናል ሲሉ የቡድኑ አባላት ሲናገሩ ተደምጧል። አለቃ ጸጋይ ሰክረው የሰው ሚስት ሊያሽኮርምሙ ሲዳዳቸው በቡጢ መዘረራችው ይታወቃል።
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
የአሜሪካን ድምጽ ራዲዮ አማርኛዉ ክፍል ባቀረበው ዘገባ በሺሆች የሚቆጠሩ ሰላማዊ ኢትዮጵያዉያን ከቅያቸው እንደተፈናቀሉ ታወቀ። ከምዕራብ ወለጋ ጊምቢና ቀለም የተፈናቀሉ ወገኖች፣ ሲሆን፣ «ተባረርን ቤት ንብረታችን ወደመ፣ ተቃጠለ» ሲሉ የደረሰባቸውን ሰቆቃ ለአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ በዝርዝር ገልጸዋል። በጉዳዩ ላይ አስተያየት እንዲሰጡ የተጠየቁት የክልሉ ባለስልጣናት ዜጎች መፈናቀላቸውን ያመኑ ሲሆን፣ «ተገደው ሳይሆን ፈርተው ነው የሄዱት» የሚል ምላሽ ሰጥተዋል። ሕወሃት/ኢሕአዴግ በኢትዮጵያ […]
ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች
ስምምነቱ በዋነኛነት የጅቡቲ ወደብ አገልግሎት ተጠቃሚ ለሆነችው ለኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን መንግሥት ይናገራል።በዚህ የሚስማሙ ወገኖች እንዳሉ ሁሉ የዜጎች የመጠጥ ውኃ አቅርቦት ችግር ሳይሟላ ለሌላ አገር ውኃ ለማቅረብ መስማማት ተገቢ አይደለም የሚሉም አልጠፉም ።
የኢራቅ እና የሌቫንት እሥልማዊ መንግሥት የተሠኘዉ አክራሪ ቡድን፤ በኢራቅ እና በሶርያ ሥልታዊ ቦታዎችን መቆጣጠሩ፤ የዩኤስ አሜሪካዉ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ በመካከለኛዉ ምሥራቅ እና አዉሮጳ ዉይይት እንዲያደርጉ አስገድዶአቸዋል። ሚንስትሩ በቅድምያ ጉዞአቸዉን ወደ ግብፅ ያደረጉ ሲሆን፤ በግብፅ የዉስጥ የፖለቲካ ጉዳይም ይነጋገራሉ።
በዛሬው ዕለት በአዋሳ ከተማ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) በሀዋሳ ከተማ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ አስመልክቶ በቅስቀሳ ላይ የነበሩ የፓርቲው አባላት ከሐሙስ ዕለት ጀምሮ እስከ ትላንት ድረስ ከ30 በላይ በፖሊስ የታሰሩ ሲሆን የሲአን የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ለገሰ ላንቃሞ ለምን ይታሰራሉ ብለው በመጠየቃቸው እሳቸውንም አስረው ከምሽቱ 3፡30 ለቀዋቸዋል፡፡ በቅስቀሳው ወቅት ወረቀቶች የተበተኑ በመሆኑ ህዝብ በነቂስ […]
ሐሳብን የመግለጽ ነጻነትና ኢህአዴግ አለማችን ለጋዜጠኞች፣ለብሎገሮችና ሐሳባቸውን በመግለጽ ተፈጥሯዊ መብታቸውን ለሚጠቀሙ ሰዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ ገሃነማዊ መልክ እየተላበሰች ትገኛለች፡፡በሶሪያ፣ሶማሊያ፣ኢራቅ፣አፍጋኒስታን፣ሊቢያ ፣ግብጽና ዮክሬይን የተፈጠሩ ሰብኣዊ ቀውሶች የጋዜጠኞችና ጦማሪያን ህይወትን በልተዋል፡፡ የቀውሱ ሃይሎች ጋዜጠኞቹንና ጦማሪያኑን የመጀመሪያ ኢላማቸው በማድረጋቸውም ዛሬ በእነዚህ አገራት በሚገኙ ማጎሪያዎች ስቃይ እየደረሰባቸው ይገኛል፡፡በዚህ ዓመት ብቻ በእነዚህ አካባቢዎች የ27 ጋዜጠኞች ህይወት ተቀጥፏል፡፡ በግብጽ እስር ቤት የአልጀዚራ […]
አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) በነገው እለት ሰኔ 15/2006ዓ.ም የሚያካሂደውን ሰላማዊ ሰልፍ አስመልክቶ በቅስቀሳ ላይ የነበሩ ከ30 በላይ የፓርቲው አባላት በፖሊስ መታሰራቸውን ተከትሎ የሀዋሳ ከተማ ባለስልጣናትና የከተማው ፍትህ መምሪያ ሐላፊ በተገኙበት የተካሄው ስብሰባ መታሰር አልነበረባቸውም፤አሁንም ያለምንም ቅድመ ሁኔታ መፈታት አለባቸው በሚሉና ማሰራችን ትክክል ነው ከተለቀቁ ነገ ሰልፉን ከማድረግ ወደኋላ አይሉም በሚል ለሁለት ተከፍለው ሲሟገቱ ማምሸታቸውንና […]
ሰኔ 15 የሰማእታት ቀን ነው። ሰኔ 15, 1980 ዓም በሐውዜን ከ2500 በላይ ንፁሃን ዜጎች በአንድ ፀሓይ የተጨፈጨፉበት ቀን ነው። ጭፍጨፋው የህወሓት እጅ እንደነበረበት ይነገራል። ይህ ማለት ቦምቡ የጣሉት ጀቶች የህወሓት ነበሩ ማለት አይደለም። ህወሓት በግዜው በሓውዜን ከተማ ጉባኤ እንደሚያደርግ ሆን ብሎ (የህዝብ ድጋፍ ለማግኘት) ለደርግ የሐሰት መረጃ አስተላልፏል። ብዙዎቹ የደርግ ጀነራሎችና መርማሪዎች የህወሓት “ስርዒት” ነበሩ። […]
የመንበረ ፕትርክናው ነጻነት በተገኘበትና ብሔራዊ ቅዱስ ሲኖዶስ በተቋቋመበት ባለፈው ግማሽ ምእት በተነሡ ቅዱሳን ጥናትና አሠያየም ላይ ትኩረት ይሰጣል፡፡ ቀኖናው ተደጋጋሚ ራእይና ተኣምራት በማሳየት የተመሠረተውን የቤተ ክርስቲያናችንን የቅዱሳን አሠያየም ትውፊት ሲኖዶሳዊ በማድረግ የሚያጠናክር ነው ተብሏል፡፡ የኮፕት ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ብፁዕ ወቅዱስ ፖፕ አቡነ ቄርሎስ ስድሰተኛንና ሊቀ ዲያቆን ሐቢብ ጊዮርጊስን በቅድስና ለመሠየም በምታደርገው ዝግጅት ቅድስናቸውን ዐውቃላቸዋለች፡፡ ኹለተኛው …![]()
ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች
ትናንት ታስቦ የዋለውን የዓለም ስደተኞች ቀን ምክንያት በማድረግ የተመድ የስደተኞች ጉዳይ ተመልካች መስሪያ ቤት፣ በምሕፃሩ « ዩ ኤን ኤች ሲአር» ባወጣው ዘገባ ከሁለተኛ ዓለም ጦርነት ወዲህ ትውልድ ሀገሩን ለቆ መሰደድ የተገደደው ሰው ቁጥር እንዲህ እንዳሁኑ በዝቶ እንደማያውቅ አመልክቶዋል።
ምንም እንኳን ሩስያ ወታደሮቿ በተጠንቀቅ ብታቆምም፤ የምዕራቡ ሀገራት ማዕቀባቸውን ቢያጠናክሩም፤ ዮክሬይን በመንግሥትም የአንድ ወገን የተኩስ አቁም ዉሳኔ ቢደርስም፤ የመፍቀሬ ሩሲያ አማፂያን ጦራቸዉን አላስቀመጡም።
ግብፅ ወደ ናይል ተፋሰስ ትብብር እንደማትመለስ አስታወቀች፡፡
ግብፅ ይህንን አቋሟን በድጋሚ የገለፀችው ሱዳን ዋና ከተማ ኻርቱም ላይ ትናንት በተካሄደው የትብብር ተቋሙ የሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ የውኃና የመስኖ ሚኒስትሯ በተወካያቸው ባስተላለፉት መልዕክት መሆኑን የኢትዮጵያ የውኃ፣ የመስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር አለማየሁ ተገኑ ለቪኦኤ በሰጡት ማብራሪያ ገልፀዋል፡፡
ግብፅን ጨምሮ አሥር አባላት ያሉትና ኤርትራ በራሷ ፍላጎት በታዛቢነት የሚገኙበት የናይል ወይም የአባይ ተፋሰስ ትብብር ጅማሮ ትናንት ባካሄደው 22ኛው መደበኛ የሚኒስትሮች ስብሰባው ላይ ከግብፅ ጋር ከትብብሩ እራሷን አግልላ የቆየችውንና ባለፈው ዓመት መመለሷን ያሳወቀችውን የሱዳንን የውኃና መስኖ ሚኒስትር ሙታዝ ሙሳ አብደላ ሳሊምን የመጭው ዓመት የትብብሩ ፕሬዚዳንት…
World Refugee Day
Egypt is not returning to Nile Basin Initiative
Corruption charges, Ethiopia
ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች
ከሁለተኛዉ የዓለም ጦርነት ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ በጦርነትና ቀዉስ ምክንያት ከቤት ንብረታቸዉ የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር 50 ሚሊዮን መድረሱን የተመ የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽን UNHCR አስታወቀ።
ኀሙስ ሰኔ 5 ቀን በብራዚል በደመቀ ሥነ ሥርዓት የተጀመረው የዓለም የእግር ኳስ ዋንጫ ውድድር ፤ ሁለተኛ ሳምንቱን ጀምሯል። የሰሞኑን ውድድሮች ፤ በተለይም አፍሪቃን ወክለው የሚገኙት 5 ቡድኖች ያሳዩትን ጨዋታ ጥንካሬና ድክመት በተመለከተ ፣